Otona Times

Otona Times Otan love

02/02/2024
 ከ3 ሚሊዮን በላይ መራጮች ሰኔ 12 በሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ለመምረጥ በጉጉት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ተሰማሰኔ 12 በሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ከ3 ሚሊዮን በላይ መራጮች ለመምረጥ በጉጉት እየተ...
31/05/2023



ከ3 ሚሊዮን በላይ መራጮች ሰኔ 12 በሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ለመምረጥ በጉጉት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ተሰማ

ሰኔ 12 በሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ከ3 ሚሊዮን በላይ መራጮች ለመምረጥ በጉጉት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ተሰምቷል፡፡

ምርጫ ቦርዱ መራጭ ህዝቡ በወላይታ ዞን አንድ ሚሊዮን የሚደርስ መራጭ ህዝብ የለም ያለውን ስምተው ቁጭትና በወኔ ተላብሶ ሰኔ 12 ቀን በጉጉት እየጠበቁ ይገኛል፡፡

ሰኔ 12 የሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ለወላይታ ህዝብ የማንነትና የህልውና ጉዳይ መሆኑን በማገንዘብ በነቂስ ወጥተው ነጭ ርግብን እንደሚመረጡ ታማኝ መንጮች አረጋገጡ፡፡

ልዩነታችንን አክብረን፤ ለወላይታ ህዝብ ጥቅም ለማስከበር በጋራ መቆም እንደሚያፈልግም ጥሪ ቀርቧል፡፡

በማህበራዊ ሚዲያ የሚጦዙ ሀሰተኛና የተቀነባበሩ መረጃዎችን ህዝቡ ወደ ጎን በማለት ለወላይታ የሚበጀውን በነቂስ ወጥተው ነጭ ርግብን ይመርጣል፡፡ በዚህም መላው የወላይታ ህዝብ ታላቅ ድል እንደሚጎናጽፍም ይጠበቃል፡፡

06/01/2023

ከወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ዮሐንስ በየነ የተላለፈ የገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት!

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል (ገና) በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

በሰማይና በምድር ለሚገኙ ነገዶች የእልልታና የምስጋና ምንጭ የሆነው ነቢያት የተመኙት መላእክት ያወደሱት እረኞች ያወሩለት ሰብዓሰገል የሰገዱለት ኃጢያተኞች የዳኑበት ግዞተኞች የተፈተኑበት ለሰዎችና ለመላእክት ታላቅ ደስታ የሆነው የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን!

ገና የሰው ልጆች ከገቡበት የጥፋት መንገድ ሊያወጣቸው መዳን ሊሆኒልን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማሪያም የተወለደበትን ዕለት የምንዘክርበት በዓል ነው። የሰው ልጆች ከነበሩበት ዝቅታ የመውጣታቸው ተስፋ የተበሰረበት ከጨለማ ወደ ብርሃን የመምጣታቸው ምዕራፍ የተጀመረበት ታላቅ በዓል ነው - የገና በዓል።

የክርስቶስን መወለድ ሲጠብቁ የኖሩት የተወለደውን ሕፃን በማየታቸው የተገባላቸው ቃል ፍፃሜ አግኝቷል። በክርስቶስ መወለድ የሰው ልጆች ለዘመናት አብሯቸው የዘለቀው የውድቀት ጉዞ ተገትቶ አዲስ የከፍታ ጉዞ ብስራትም ታውጇል። በመወለድ፣ መውደቅ በመነሳት፥ ዝቅታም በከፍታ እንዲተካ የግድ ሆኗል።

በዓሉን ስናከብር አንድነታችንን ይበልጥ በማጠናከርና በማጎልበት ሊሆን ይገባል። የጀመርነው ጎልቶ የመውጣት ጉዞ ይበልጥ እንዲሰምር ኅብረታችንን አጠናክረን አንድ መሆንም ይኖርብናል።

በፈተናዎቻችን ትምህርት፣ በችግሮቻችን ጥንካሬ፣ በእንቅፋቶቻችን ብርታት እያገኘን፣ ከእያንዳንዱ ጨለማ ወዲያ ንጋት መኖሩን እያመንን፣ ዐይናችንን ወደ ወጋጋኑ አቅንተን በተራመድን ቁጥር ችግሮቻችን ወደኋላ ይሸሻሉ፤ እኛ ይበልጥ በበረታን ቁጥር የሚንመኘውን ብልጽግናን እናረጋግጣለን፡፡

ብርሃን ጨለማን፤ ሰላም ጦርነትን፣ ፍቅር ጥላቻን፣ አንድነት መለያየትን፣ ብልጽግና ድህነትን ማሸነፋቸው እንዳማይቀር ሁላችንም በቁጭት ከሰራን እና አንድነታችንን ካጠናከርን ሩቅ የመሰለን ህልም በእጃችን መዳፍ ስር እንደሚሆን መጠራጠር የለብንም፡፡

የዞናችን የለውጥ ጉዞ ፍጥነቱ ከምንም በላይ የሚወሰነው መላው የዞናችን ሕዝብ ጥንካሬና አንድነት በመላበስ ሁላችንም በተሰማረነው ስራ መስክ መረባረብ እንደሚያስፈልግም ላሳስባችሁ እወዳለሁ።

በዚህ ወሳኝ ወቅት ሁላችንም ዐቅማችን የፈቀደውን መሥራት ከቻልን፣ ያለ ጥርጥር ነገ ብሩህ ይሆናል፤ የመከራ ዘመንም እስከ ወዲያኛው ይሸኛል። ኢትዮጵያም የማትደፈር፣ የምትታፈር ሀገር ሆና በዐለት ላይ ትቆማለች።

ውድ የፓርቲያችን አባላትና ደጋፊዎች በየጊዜው ለውጡን ለሚፈልገው ማህበረሰብ ጠንክሬን በመሰራት ብልጽግናን ማማ ላይ ለማስቀመጥ ኃላፊነታችንን በአግባቡ መወጣት ይኖርብናል፡፡

ለሁሉም ነገር መሠረት የሆነውን ሠላማችንን እንደዓይን ብሌናችን መጠበቅ ከሁሉም ህብረተሰብ ክፍል የሚጠበቅ ስለሆን ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን አከባቢያችን መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡

ጥር 29 የሚካሄደው ህዝበ ውሳኔ ፍጹም ሠላማዊና በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለው ሆኖ እንዲጠናቀቅም የበኩላችሁን ድርሻ እንዲትወጡ እያሳሰብኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምርጫ ምልክት የሆነችውን ነጭ ርግብ እንዲትመረጡ በዚህ አጋጣሚ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡

በዓሉን ስናከብር አቅመ ደካሞችን፣ ረዳት የሌላቸውን አረጋዊያን፣ አዛውንቶችንና እንዲሁም ወላጅ አጥ የሆኑ ሕፃናትን እንድንደግፍ እና ካለን እንድናካፍል ቤተሰባዊ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

በድጋሚ ለወላይታ ዞን ሕዝቦች እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል (ገና) በሰላም አደረሳችሁ በማለት በራሴና በፓርቲው ስም መልካም በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!

መልካም የገና በዓል!!
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ታኅሣሥ 28 ቀን 2015 ዓ.ም

23/09/2022

ዮ ዮ ጊፋታ!
የ2015 የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል አስመልክቶ የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ዮሐንስ በየነ ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞት መልዕክት፡፡

የተወደዳችሁ መላው የወላይታ ህዝቦች! እንኳን ለ2015 የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል በሠላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን!!

ጊፋታ በዓሉ የአዲስ ዓመት ብርሃን ማብሰሪያ፣ በተለያየ ምክንያት ከአካባቢው ርቀው የሚኖሩ ወገኖች ከወላጆቻቸው ጋር የሚገናኙበት፣ የተጣላ የሚታረቅበት ታላቅ ክብረ በዓል ነው።

ጊፋታ የወላይታ ብሔር ከጥንት ጀምሮ ሲያከብሩ የነበረ የአሮጌው ዓመት ማብቂያና የአድሱ ዓመት መጀመሪያ የዘመን መለወጫ በዓል ነው፡፡

በወላይታ ህዝብ ዘንድ ጊፋታ ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ አእዋፋትና የቤት እንስሳትም ጭምር በጋራ የሚያከብሩት በዓል እነደሆነ በዚሁ አጋጣሚ ልገልጽላችሁ እፈልጋለሁ፡፡

የጊፋታ በዓል በውስጡ ማህበራዊ፣ ባህልዊ፣ ፖለቲካዊና ስነልቦናዊ ፋይዳዎችን የያዘ ሲሆን በህዝቦች መካከል ያለው የአብሮነት፣ የአንድነትና የመቻቻል እሴቶች በውስጡ የሚገለጹበት ነው፡፡

በዞናችን ውስጥ ባለፉት ዓመታት ውስጥ የተከናውኑ የልማት፣የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን በማጠናከር በቀጣይም ከህዝባችን ጋር በመሆን ለመሥራት ያቀድናቸውን ተግባራት ከህዝባችን ጋር በመወያየት ጠንካራ የለዉጥ እንቅስቃሴ የምንመራበት ወቅት ሊሆን ይገባል፡፡

ጊፋታ የተጣሉ የሚታረቁበት የእርቅና የሠላም በዓል ነው፡፡ በወላይታ ብሔር ማንም የተጣላ ሰው ሳይታረቅ አዲሱን ዓመት መሻገር ነውር ነው፡፡

መላዉ የወላይታ ህዝብ ይሄ ብርቅዬ ባህል ሳይበረዝና ሳይከለስ ከትዉልድ ወደ ትዉልድ እንዲተላለፍና ከነሙሉ ክብሩ ተጠብቆ እንድቆይ የሁል ጊዜ ትጋታችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ እጠይቃለሁ፡፡

የወላይታ ህዝብ ሀብትና ንብረት የሆነውን የጊፋታን በዓል በቀጣይ የኢትየጵያ ህዝብ በዓል በማድረግ በዓለም ከሚገኙ ከማይዳሰሱ የሰው ልጆች ወካይ እንድታበርክቱ ቅርሶች አንድ አድርገን ለማስመዝገብ ለምናደርገው ጥረት ሁላችሁም የበኩላችሁን አስተዋፆኦ እንድበረከቱ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡

ተፈጥሮ ህጓን ጠብቃ፤ ክረምት በጋውን ስታፈራርቅ፣ መሄር በልጉን ስታመጣ፣ ፀሃይ ብርሃኗን፣ ስማይ ዝናቡን፣ መሬት ቡቃያዋን እንዳትከለክል ፈጣሪያችን እንዲረዳን ምኞተም ጸሎቴም ነው፡፡

ሠላም የሁሉም መሠረት ነው። ሠላም ማለት ሰው፣ ሀገር፣ ይቅርታ፣ ፍቅርና አንድነት ነው። ሠላም ካለ ሁሉም አለ። የሀገራችንን ሠላም በጋራ እንጠብቅ። ጥላቻን አርቀን በፍቅር እንኑር።

የኢትዮጵያዊነት የመጨረሻው መዳረሻው ሠላም፣ ፍቅርና አንድነት ነው። እያንዳንዳችን ለሀገራችን ሠላም የየድርሻችንን እንወጣ።

መረዳዳትና መደጋገፍ የብልፅግና አንኳር እሴት ነው!! ስለዚህ በዓሉን ስናከብር የተቸገሩትን በመርዳት፣ በመተሳሰብ፣ በይቅር-ባይነት፣ በመግባባት፣ በወንድማማችነትና በአብሮነት መንፈስ ልናከብር ይገባናል፡፡

በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የአንድነትና የብልጽግና እንዲሆን በራሴና በዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ስም በድጋሚ መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ፡፡

ዮ ዮ ጊፋታ!
ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን እግዚአብሔር ይባርክ!

የደቡብ ክልል መቀመጫው አርባምንጭ ሄዷል ተብሎ እየተሰራጨ ያለ መረጃ ከእውነት የራቀ ነው_______________________ሰሞኑ ለሆዳቸው ብቻ የሚኖሩ ጥቅት አክቲቪስት ባዮች እድሜ ልካቸው...
04/07/2022

የደቡብ ክልል መቀመጫው አርባምንጭ ሄዷል ተብሎ እየተሰራጨ ያለ መረጃ ከእውነት የራቀ ነው
_______________________
ሰሞኑ ለሆዳቸው ብቻ የሚኖሩ ጥቅት አክቲቪስት ባዮች እድሜ ልካቸውን ከውሸት ዜና ያልተቆጠቡ ዛሬም ቀጥለዋል።

ከዚህ በፊት የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ የወላይታ ህዝብን ዘርፎ በኬንያ አድርጉ አሜርካ ኮብልሏ ብለው ሀሰት መረጃ ስያሰራጩ የነበሩ ግለሰቦች ዛሬ ላይ ደግሞ የደቡብ ክልል መቀመጫ አርባምንጭ ሄዷል ብለው የበሬ ወለደ መረጃዎችን እያሰራጩ ይገኛሉ።

እነዚህ ግለሰቦች ለግል ጥቅማቸው ብለው ከዚህ በፊት ሀሰት መረጃዎችን በማሰራጨታቸው ምክንያት በወላይታና አከባቢው ሰላም በማሳጣትና በማወክ የህዝቡን ንብረት ዘርፈዋሉ፣ ንጹሃን ዜጎች እንዲሞቱ አድርገዋል።

አሁንም እንዲህ አይነት ግርግር ለማውጣትና ለመዝረፍ ቀንና ሌሊት እየሰሩ መሆናቸውን ከደህንነት አካላት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

መንግስት የህዝቡን ጥያቄን ተቀብሎ ህዝቡን በሚጠቅም መልኩ ለመመለስ ቁርጠኛ ነው ከዚህ ውጪ የሚሰራጩ መረጃዎችን ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል።

ያልተረጋገጥና ምንጩ ያልታወቀ የውሽት መረጃ እያሰራጩ የሚገኙ ግለሰቦች አደብ ልተገዙ ይገባል። አለበለዚያ ዋጋ ሊያስከፍላችሁ ይችላል።

መታሰርን እንደጀግና ሰው አድርጉ የሚያስቡ ሰዎች የአሁን መጨረሻ ሊሆን ይችላል።

ከመታሰርን በኃላ ከመጮህ ይልቅ ጥንቃቄ እናድርግ። የክልል ጥያቄን ተገን በማድረግ የህዝቡን ሰላም ለማወክ በሚደረጉ አካላት ላይ መንግስት የማያዳግም እርምጃ ለመወሰድ አይታገስም።

ሠላም ለወላይታ!
ሠላም ለሀገራችን!

19/06/2022
ነጻነታችንን በአግባቡ እንጠቀም፤ አለበለዚያ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል!____ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለማስከበር የህግ ጥሰቶች እንዳይኖር የሌሎች ሰዎች መብት ማክበር አለብን። መብትና ግደታው ...
22/05/2022

ነጻነታችንን በአግባቡ እንጠቀም፤ አለበለዚያ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላል!
____
ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለማስከበር የህግ ጥሰቶች እንዳይኖር የሌሎች ሰዎች መብት ማክበር አለብን። መብትና ግደታው ከኃላፊነት ጋር የሚመጣ ጉዳይ ነው። ስንታሰር በግፍ ታስራያለሁ ከማለታችንን ይልቅ ነገሮችን በሴከነ መንግድ የህዝባችንና ሀገራችን ህልውና አደጋ ላይ ከሚጥሉ ጉዳዮች መቆጠብ አለብን።

የኑሮ ውድነት በህዝባችን አናት ላይ በወጣበት ጊዜ፣ የሥራ አጥነት ችግር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሰ በመጣበት ወቅት ችግሮችን ለመቅረፍ መፍትሔ ማበጀትና የህልውና ስጋት የሆነውን በድል ለመውጣት አንድ መሆን ስገባን በአንዳንድ ግለሰቦች በጭፍን ጥላቻ ተሞልተን እስከመቼ እንዘልቃለን፡፡

ከጭፍን ጥላቻ ወጥተን ለህዝባችን የሚጠቀሙና ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር ፍጹም ሰላማዊና ህዝባዊ በሆኑ መንገድ መንቀሳቀስ ያስፈልጋል፡፡

በሀሰተኛ አካውንት ተደብቀህ ስለጻፍክ ከህግ ጥላ ስር ማምለጥ አትችልም። ማህበራዊ ሚዲያ የራሱ የሆኑ ህጎች አሉ፡፡ የጥላቻ ንግግር በአዋጁ ቁጥር 11/85 መሠረት በህግ ተጠያቂ ያስደርጋል፡፡

በየአከባቢው ህብረተሰቡን የሚሸብሩ ግለሰቦችን ህዝቡ ለይተው ያዉቃል፡፡ ስለዚህ ነጻነታችንን በአግባቡ እንጠቀም፤ አለበለዚያ ዋጋ ሊያስከፍለን ይችላልና፡፡ መብትና ግደታችንን ለየትን መጠቅም አለብን፡፡

የህዝቡን ሠላምና ደህንነትን አደጋ ላይ ለመጣል የሚቀሰቅሱ አካላትን መንግስት አይታገስምመንግስት የህዝቡን ሠላምና ደህንነትን ለማስጠበቅና ለማስከበር የተኛውንም እርምጃ እንደሚወሰድ በተደጋጋሚ...
22/05/2022

የህዝቡን ሠላምና ደህንነትን አደጋ ላይ ለመጣል የሚቀሰቅሱ አካላትን መንግስት አይታገስም

መንግስት የህዝቡን ሠላምና ደህንነትን ለማስጠበቅና ለማስከበር የተኛውንም እርምጃ እንደሚወሰድ በተደጋጋሚ ጊዜ መገለጹ ይታወሳል።

ይህንን እየሰሙ ያልሰሙ የሆኑና ከዚህ በፍት በተደጋጋሚ ታስረው መታረም ያልቻሉ ግለሰቦች ላይ መንግስት እርምጃ መውሰድ ጀምሯል።

ከህግ አግባብ ውጭ የታሰሬ አካላት እንደሌለ በዚህ አጋጣሚ ልገልፅላችሁ ወዳለሁ።

ሠላም ለሀገራችን!

01/05/2022

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ዮሐንስ በየነ ለኢድ አል ፈጥር በዓል ያስተላለፉት መልዕክት

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1443ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

እጅግ የተከበረውና ቅዱስ ቁርአን ከሰማይ የወረደበት ወርሃ ረመዳን ሙስሊም ወንድሞቻችን በፆም፣ በፀሎት፣ የተቸገሩትን በመርዳት በማሰብና አላህ ለሃገራችንና ህዝቦቿ መልካም ነገርን ያደርግላቸው ዘንድ ዱዓ የሚያደርጉበት ታላቅ ወር ነው፡፡

ከጠዋት እስከ ማታ በጾም፣ በጸሎት እና በመልካም ምግባር ማሳለፍ ከባድ ፈተና ነው። በጾሙ ወቅት የሚገኘው ስጦታ ደግሞ በረከት ነው። አንድን ወቅት ጥሩ ወቅት ነው የምንለው እየተፈተንን የምናልፍበት፣ አልፈንም የምንሸለምበት ጊዜ ሲሆን ነው።

ጥላቻን ነቅለን ፍቅርን እየተከልን የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ እንድናስቀጥል ብሎም የሕዝባችንን ችግር ደረጃ በደረጃ እየለየን እንድንፈታ ከምንጊዜውም በተለየ መልኩ የለውጥ ሀሳብን በማመንጨትና በመተግበር አጠቃላዩ የዞናችን ማህበረሰብ እንዲንቀሳቀስ፣ ተግቶም እንዲሰራ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

የመጠፋፋት ፖለቲካ ለዚህች አገር እንደማይጠቅም ያለፉትን 27 ዓመታት ጉዞ መመልከት በቂ ነው፡፡ ዛሬ ላይ በአገራችን እዚህም እዚያ የሚታዩ ችግሮች የትላንት የሴራ ፖለቲከኞች እና ለውጡ መጣብን በሚሉ ኃይሎች የተቀበረ ፈንጅ እንደሆነ ሃቅ ነዉ።

ሰላም የሁሉ መሠረት ነውና ሰላማችንን እንጠብቅ፣ ባህላዊ ዕሴቶቻችን የማንነታችን መገለጫዎችና የቀደምት ወገኖቻችን ውድ ስጦታዎች ናቸውና እንከባከባቸው፣ ለትውልድም እናሻግራቸው፤ የቤተሰብ፣ የአካባቢያችንን ብሎም የአገራችንን ሰላምና ደህንነትን ከወጣቶችና ከአባቶቸቻችን ጋር በጋራ እንጠብቅ፣ ያላወቅነውን ለማወቅ፣ ያወቅነውን በጎ ነገር ለሌሎቸ ለማሳወቅ እንትጋ፣ አካባቢያችንን ብሎም አገርን ለማልማትና ወደ ብልፅግና ማማ ለማውጣት ተግተን እንሥራ የሚለው ዋነኛ መልዕክቴ ነው፡፡

የምንጽፋቸው፣ የምንናገራቸውና በሌሎች የተግባቦት ዘዴዎች የምናሰራጫቸው መረጃዎች ከአሉባልታ ይልቅ ጀግንነታችንን፣ ልማታችንን፣ የሐገራችንን ሉአላዊነት፣ የህዝባችንን አንድነትና ብሩህ ተስፋችንን የሚያጎሉ ሊሆኑ ይገባል፡፡

የብሔር፣ የሀይማኖትና የፖለቲካ ጽንፈኝነትን በመቃወም አንዳችን ለአንዳችን ዋልታ እና ማገር፤ ድርና ማግ መሆን ያስፈልጋል። ሀገራችን አንድ ብቻ ናት፥ ለሁላችንም ትበቃለች። ስለዚህ የሠላም ጉዳይ የእኔ፣ ያንተ፣ ያንቺ፣ የሁላችንም ጉዳይ መሆን አለበት፡፡

በረመዳን ወር መላው ህዝበ ሙስሊሙ ያሳየው መደጋገፍ፣ መጠያየቅ፣ ፍቅርና ትህትና በቀጣይ ጊዜያት በመድገም ሀገራችን የጀመረችው የብልፅግና ጉዞ እውን እንዲሆን የበኩላችሁን ሚና በመጫወት አርአያነታችሁን እንድትወጡ በዚህ አጋጣሚ አደራ እላለሁ።

በድጋሚ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ እህት ወንድሞቸ እንኳን አደረሳችሁ፡፡

ኢድ- ሙባረክ!

ዮሐንስ በየነ
የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!!

24/04/2022

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!- አቶ ዮሐንስ በየነ

የተወደዳችሁ መላው የሀገራችን ሕዝቦች!!

የተወደዳችሁ መላው የዞናችን ህዝቦች!

በጾምና በጸሎት ስለራሳችሁና ስለአገራችሁ ብሎም ለዓለም ሰላም ከፈጣሪ ጋር በመገናኘት ካሳልፋችሁ በኃላ እንኳን ለዚህች ለተቀደሰች ቀን በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን!

የትንሳኤ በዓል ጌታችንና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤዛነቱ ለሰው ልጆች ጥልቅ ፍቅሩን የገለጸበት የፍቅር ተምሳሌት በመሆኑ አርያነቱን ተከትለን አንድነታችንንና ህብረታችንን ይበልጥ ልናጎለብት እንደሚገባ በዚህ አጋጣሚ ላሳስባችሁ እፈልጋለሁ።

ኢትዮጵያን ብሎም አከባቢያችን ወደ ብልጽግና ማማ ላይ ማውጣት የምንችለው ሁሉም ኢትዮጵያዊያን በእኩልነት፣ በፍቅር፣ በወንድማማችነት ተከባብረው፣ ተፈቃቅደው እና ተዋድደው መትጋት ሲችሉ ብቻ ነው፡፡

በክርስቶስ የማዳን መንገድ የአዳም ዘር በሙሉ ለደስታ ቢታጭም እንደ ይሁዳ ያሉት በመንገዱ ተሸንፈው ስለወደቁ የድሉ ባለቤት አልሆኑም። ስለዚህ የተስፋ መንገዳችን በስኬት እንዲቋጭ ዛሬም ሆነ ነገ ፈተናውን በድል መወጣት ይኖርብናል። በየመንገዳችን የሚገጥሙን ፈተናዎች ወደ ተስፋ መሻገሪያ በሮቻችን ናቸው፡፡

የፋሲካ በዓል ጌታችንና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጥል ግድግዳን በማፍረስ እርቅ ያወረደበት የእርቅና የሰላም በዓል በመሆኑ ከዚህ በዓል ብዙ የምንማርበት ነው፡፡

የዘንድሮን የፋሲካ በዓል ስናከብር የበደሉህንን ይቅር በማለት አብሮ ማዕድ መጋራት፣ የመንፈስ ጥንካሬን በመገንባት መሆን ይገባል፡፡

ብልጽግና ፓርቲ የያዛቸው አቋሞች ህዝባችንን በማህበራዊ፤ በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ተጠቃሚ ለማድረግና በጥቂት ጊዜ ውስጥ ባስመዘገባቸው ሀገራዊ የለውጥ ድሎችን ማስቀጠልና መተግበር የሁላችንንም ጥንካሬ ይፈልጋል፡፡

የብልጽግና ፓርቲ 1ኛ ጉባኤ አቅጣጫዎችና ውሳኔዎች ዙሪያ ህዝቡ የተለያዩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ማንሳቱ ይታወሳል፡፡

ለዚህም የህዝባችንን መሠረታዊ ጥያቄዎችን ለመመለስ የ90 ቀናት ዕቅድ ታቅደው ምላሽ እንዲያገኙ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ በዚሁ አጋጣሚ ልገልጽላችሁ እወዳለሁ!

ከቃል ባለፈ ሁላችንም እንደ አንድ ልብ መክረን እና እጅ ለእጅ ተያይዘን ለተግባራዊነቱ መትጋት ይኖርብናል።

ህብረ ብሔራዊነት ልዩነቶችንና የሚከፋፍሉ፣ የሚያጣሉ ሁኔታዎችን ከማጉላት ይልቅ የሚያቀራርቡና የሚያስተሳስሩንን እውነታዎች በማጉላት፣ ከትናንትና ይልቅ ዛሬና ነገ ላይ ማተኮርና መጠንከር ያስፈልጋል፡፡

ቀጥ ያለ ብረት ዉሃ ዉስጥ ሆኖ ሲታይ የተጣመመ መስሎ ይገኛል፡፡ የብረቱን መጣመም የሚፈጥረው የሰዎች የእይታ ግድፈት ነው፡፡ ስለዚህ የእይታ አድማሳችንን በማስፋትና አመለካከታችንን በማስተካከል ለአንድ ዓላማ መቆም አለብን፡፡

የተከበራችሁ የዞናችን ህዝቦች፡- በዞኑ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍንና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንዲጠናከር ህብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ በሰላም እንዲገባ ድርሻችሁን እንዲትወጡ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡

መረዳዳትና መደጋገፍ የብልፅግና አንኳር እሴት ነው! ስለዚህ በዓሉን ስናከብር የተቸገሩትንና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ውስጥ ለሚገኙ ወገኖቻችን በመርዳት፣ በመተሳሰብ፣ በይቅር-ባይነት፣ በመግባባት፣ በወንድማማችነትና በአብሮነት መንፈስ ልናከብር ይገባል፡፡

በድጋሚ የዘንድሮ የጌታችን የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል ለሁሉም የክርስትና እምነት ተከታዮች የሰላም፤ የፍቅርና የደስታ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ፡፡

ዮሐንስ በየነ
የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ

Address

Wolaita
Dabat

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Otona Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share