Habesha Daily/ ሀበሻ

የኦቻ ዋና ዳይሬክተር በደብረብርሀን የሚገኙ ተፈናቃዮችን ጎብኝተው በሀዘን አለቀሱ፡፡ የተመድ የሰብአዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ ወይንም ኦቻ የኦፐሬሽን ዳይሬክተር ኤደም ዎሶርኑ በደብረብርሀን...
03/09/2025

የኦቻ ዋና ዳይሬክተር በደብረብርሀን የሚገኙ ተፈናቃዮችን ጎብኝተው በሀዘን አለቀሱ፡፡ የተመድ የሰብአዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ ወይንም ኦቻ የኦፐሬሽን ዳይሬክተር ኤደም ዎሶርኑ በደብረብርሀን ተገኝተው ተፈናቃዮችን መጎብኘታቸውን ገለፁ፡፡

ከ22 ሺ በላይ ተፈናቃዮች በሚገኙበት በዚህ የተፈናቃዮች መንደር ውስጥ ያለውን ችግር መመልከታቸውንም አስታውቀዋል፡፡ የተፈናቃዮቹ መኖሪያ ድንኳን በውሀ መጥለቅለቁንና መጨቅየቱን መታዘባቸውን የገለፁት ዳይሬክተሯ ‹‹ጭቃው ወደውስጥ ለመግባት እንኳ አስቸግሮኝ ነበር›› ብለዋል፡፡

እነዚህ በግጭትና በጦርነት የተነሳ የተፈናቀሉ ሰዎች ግን በዚህ ሁኔታ ውስጥ ያለፉትን አራት አመታት መቆየታቸውን ገልፀዋል፡፡ በአንድ መጋዘን ውስጥ 1900 ሰዎች እርስ በእርስ ተደራርበው እንደሚኖሩ ያስታወቁት ዳይሬክተሯ በሲሚንቶው ወለል ላይ ያለምንም ብርድ ልብስ ሲተኙ ማየታቸውንም አስረድተዋል፡፡ የተፈናቃዮቹ ኑሮ እንዳሳዘናቸውና እንዳስለቀሳቸውም አስታውቀዋል፡፡

የሚመለከታቸው አካላት በትብብር እነዚህን ሰዎች ከዚህ ስቃይ ማውጣትና ህይወታቸውን መቀየር እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡ ዘሀበሻ በተደጋጋሚ የደብረ ብርሀን ተፈናቃዮችን ስቃይ ሲዘግብና መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጥሪ ሲያቀርብ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡

ዘ ሀበሻ

ናኦሚ ፒሉላ  በዛምቢያ ውስጥ በሚገኝ አንድ ትልቅ ቢሮ በጥብቅና ሙያ የምታገለግል የ36 አመት ሴት ናት  ። እና ከጥቂት ሳምንታት በፊት የሳምንቱን የስራ ቀናት በትጋት ለመጀመር ወደስራ ከመ...
03/09/2025

ናኦሚ ፒሉላ በዛምቢያ ውስጥ በሚገኝ አንድ ትልቅ ቢሮ በጥብቅና ሙያ የምታገለግል የ36 አመት ሴት ናት ።

እና ከጥቂት ሳምንታት በፊት የሳምንቱን የስራ ቀናት በትጋት ለመጀመር ወደስራ ከመሄዷ በፊት አንድ ሰልፊ ፎቶ ተነስታ መልካም ሰኞ ፡ መልካም የስራ ሳምንት ከሚል ጥቂት ፅሁፍ ጋር አንድ ሺህ ፎሎወር ብቻ ባለው የኢንስታግራም አካውንቷ ፖስት አድርጋ ወደስራ ቦታዋ ሄደች .....
ከጥቂት ሰአታት በኋላ አረፍ ብላ ስልኳን ስትከፍት ግን ያየችው ነገር እንግዳ ሆነባት ።
ናኢሚ ከዚህ በፊት አይታቸው የማታውቅ በተለያዩ ሀገራት ያሉ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰወች በኢንስታግራም አካውንቷ ስር እየተጠራሩ አካውንቷን ገበያ አስመስለውታል ።....
ፈጽሞ ይከሰታል ብላ ባላሰበችው መልኩ የትልቁ አፍንጫዋ ጉዳይ መነጋገሪያ ሆኖ ፖስት ያደረገችውን ሼር እያደረጉ ከፎቶዋ ስር እየተሳለቁባት ፡ እየቀለዱ እያሾፉና እየተሳደቡ ነው ። አንዳንዶቹ የፕላስቲክ ቀዶ ህክምና እንድታደርግ የሚመክሯትም አሉ ። ..
በመቶሺ የሚቆጠሩ ሰወች በመልኳ ለመሳለቅ ቪዲዮውን ሼር አድርገውት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች መልሰው አጋሩት ፡ በዚህ አይነት ቫይራል የሆነው የናኦሚ ፖስት አጠቃላይ የኮመንትና የሼር መጠኑ ከግማሽ ሚሊየን በላይ ደረሰ ።........
ይህ ያልታሰበ አጋጣሚ ናኦሚን የረበሸ ነበር ።
ነገሮች በዚህ መልኩ አልፈው ከተረጋጋች በኋላ ግን ሰሞኑን ይህን መልእክት አስተላለፈች....
" ሰዎች እግዚአብሔርን በእኔ ውስጥ እንዲያዩት እፈልጋለሁ ። ሰወች በእኔ ውስጥ በራስ መተማመንን እንዲያዩ እፈልጋለሁ ። እርግጥ ነው እኔ በሰወች መስፈርት ቆንጆ ሴት እንዳልሆንኩ አውቃለሁ፣ እና ግን ያ .. ምንም ማለት አይደለም ። .......

አንዳንዶች አፍንጫዬን በፕላስቲክ ሰርጀሪ እንዳስተካክለው ሁሉ ነግረውኛል ፡ ይህን ለማድረግ የገንዘብ አቅሙም አለኝ ፡ ግን ለምን ? ከቤታችን በተለይ የአባቴን መልክ ይዤ የተወለድኩት እኔ ነኝ ፡ ይህ አፍንጫ የአባቴ ነው ።
እና ይህንን ከአባቴ ጋር የሚያመሳስለኝን ነገር ነው የማስወግደው ? ፈጽሞ አላደርገውም ።

እኔ አሁን ያለሁበትን መልክም ሆነ ሁኔታ እወደዋለሁ ፡ራሴን ለመውደድ የሰው ማረጋገጫ አያስፈልገኝም ።

ሰወች ራሳቸውን መውደድ ተፈጥሯቸውን መቀበል መቻል አለባቸው ። ሰወች በተፈጥሯቸው መደሰት አለባቸው ይህ በራስ መተማመን ይባላል ።
በማለት ምላሽ ሰጥታለች ።

በዋሲሁን ተስፋዬ

የሼህ አል-አሙዲ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከ74 ሺህ ለሚልቁ ሰራተኞቹ በየወሩ ከ500 - 600 ሚሊዮን ብር ደሞዝ እንደሚከፍል ምን ያህሎቻችን እናውቃለን?ኢትዮጵያም የእናታቸው አደራ ሆና...
03/09/2025

የሼህ አል-አሙዲ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከ74 ሺህ ለሚልቁ ሰራተኞቹ በየወሩ ከ500 - 600 ሚሊዮን ብር ደሞዝ እንደሚከፍል ምን ያህሎቻችን እናውቃለን?

ኢትዮጵያም የእናታቸው አደራ ሆናባቸው አል-አሙዲ ሀገርን በኢንቨስትመንት ረገድ ለመሳተፍ በኢትዮጵያ ከተሰማሩበት ጊዜ አንስቶ በሶስት ምዕራፍ የፖለቲካ ትርጓሜ እየተሰጠባቸው ብዙ ውጣ ውረድ ገጥሟዋል፤ ሸራተን ሆቴል እስኪዘጋ ድረስ፡፡

አል - አሙዲን ከሳኡዲ ስለመጡ “ወሀቢያን ወደ ኢትዮጵያ ሊያስፋፋ ነው፤ የእስልምና አክራሪነትን ሊያመጣ ነው” በሚለው ጥርጣሬ ሼራተን ለጊዜው እንዲዘጋ ተወስኖ እና ሆቴል ሳይሆን መስጊድ ነው የሚል ወሬም ተናፍሶ ሆቴሉ ተዘግቶ ከተፈተሸ በኋላ ተረጋግጦ እንደገና ተፈቅዶ መከፈቱንስ እናውቅ ነበር?

ያኔ የኢህአዲግ መንግስትን ይቃወሙና ተችተው ይጽፉ የነበሩ እንደ እነ ጋሽ ጻውሎስ ኞኞ ያሉትን ሼሁ ጀርመን ልከው ማሳከማቸው፤ ቀጥሎም አርቲስቶቹን እነ ታማኝ በየነና ፀሀዬ ዮሀንስ ላይ ከመንግስት ሹሞች ጫና ሲበዛባቸው አላሙዲን አሜሪካ ወስደው መደገፋቸውን ተከትሎ በመንግስት በኩል ጥርጣሬው መባሱን፤ በዚህ ሳያበቃም - አፍቃሬ ደርግ ተብለው እንደነበርም በሚድሮክ በጣም መረጃ ሰጪ ዶክመንተሪ ላይ ተጠቅሷል፡፡

“አፍሪካ ከልቤ ብትሆንም - ኢትዮጵያ ግን የእናቴ አደራ ናት አሉ” - ቢሊየነሩ ሼህ መሀመድ አላሙዲን፡፡

ለኢህአዲግ መንግስት ሼህ አላሙዲን በ1997 ምርጫ ድጋፍ ሁነት ላይ መገኘታቸውን ተከትሎ ብዙ ሰው ሚድሮክ የህወሀት ነው፣ የወያኔና የአዜብ መስፍን ነው እስከሚለው ድምዳሜ ድረስ የዘለቀው ነቆራ ሚድሮክን ከፖለቲካ ፓርቲ ጋር አላጥፎ በባለሀብቱና በድርጅቶቹ ላይ ከፍተኛ ፈተና ደቅኖም ማለፉን ዶክመንተሪው ከትቦታል፡፡

በሚድሮክ ዶክመንተሪ ላይ እንደ ወግ በጣም ቀልብን በሚገዛ ሁነት ማብራሪያውን የሚሰጡት አቶ ጀማል አህመድ እንዲህ ሲሉ በአጽንኦት ያነሳሉ - “አላሙዲ ለኢትዮጵያ ስላላቸው በጎ ሕልም በህዝቡ ዘንድ በቂ ግንዛቤ አልተያዘውም፤ እናም አሁንም ድረስ ፈተና ሆኖ የቀጠለው አብዛኛው የሼሁን የሀገር ወዳድነት ውስጠታቸውን አልተረዳውም”

መንግስት በደንብ ያመናቸው በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ነው ይሉና የሚድሮኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሲያብራሩ - “በዚህ ወቅት ሀገሪቱ ከባድ የፋይናንስ ማጥ ውስጥ ነበረችና አልአሙዲ የተጠየቁትን ድጋፍ ሁሉ በደስታ በማድረግ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጎን በቁርጠኝነት ቆመዋል”፡፡

የሚያደርጉት ድጋፍ ሼህ አላሙዲን የማህበራዊ ግዴታቸውን ለመወጣት የሀገር ውለታ የዋሉ ሰዎችን መደገፍ መውደዳቸው ግን በአንዳንድ ፖለቲከኞች በበጎ ጎን አለመታየቱ ፈተና አመጣባቸው በማለት በቁጭት የሚያነሱት ስራ አስፈጻሚው አቶ ጀማል ለካ ደግነትም ፈተና መሆኑን ያወቅሁት በእሳቸው ነው በማለት በአግራሞት በምልሰት ሄደው ያወሱታል፡፡

ሌላው በሚድሮክ የውስጥ ድርጅት የአስተዳደራዊ ልቅ አሰራር ችግርና ሙስና ብሎም የገንዘብ ብክነትና ስርቆትን ተከትሎ ኩባንያዎቹ የመውደቂያ ቀናቸውን የሚቆጥሩ ነበሩና ከግራ አጋቢ ሁኔታ የገባው ሚድሮክ የራሱን customized መዋቅር አበጅቶ በስሩ ያሉ 45 ድርጅቶች በ6 ዘርፎች ተጣምረው በ2012 ዓ.ም መጨረሻ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ መፈጠሩ ይነገራል፡፡

ከወሎዋ ወልዲያ ትውልዳቸውን አድርገው ደሴ ወ/ሮ ስህን ት/ቤት ተከታትለው - የስራን ልምድ ከአንድ ስዊድን ካለ ትልቅ ኩባንያ ተቀጥረው ስለቢዝነስ ተሞክሮ ጨብጠዋል፡፡
አውሮፓ ላይ ነው ሀብት ቢያፈሩም ወደ ኢትዮጵያ ግን መጥተው አያውቁም ነበር፡፡ ይሁንና አንድ ቀን ግን እናታቸው የጤና አያያዛቸው አላምር አላቸው፤ እንግሊዝ ሀገር ለህክምና ከመሄዳቸው በፊት ግን ኢትዮጵያ ውሰዱኝ አሉ፡፡
ኢትዮጵያ መጥተው መርካቶን ጭምር ጎበኙ እና “ልጄ አደራህን!” አሉ ለሼህ አላሙዲን - “አደራ ሀገርህን ኢትዮጵያን አግዝ!” የሚል አደራ ተቀበሉ - ይህ የእናቲቱ አደራ አላሙዲንን ከበዳቸው፡፡
ለምን መንግስት ብቻ - የግል ባንክ ለምን አይኖርም ኢኮኖሚው እንዲያድግ መደገፍ አለበት መንግስት የሚለው ሌላ የተሳሳተ የፖለቲካ ስሌት አስነስቶባቸው - ስማቸውንም የጠለሸበት አጋጣሚ ተፈጥሮ ነበር - ከበጎ ምክር ይልቅ ጥርስ አስነከሰባቸው - በዚህ መዘዝ የስራቸው ቀዳሚ የነበረው የመጀመሪያውን ሼራተን ሆቴል ታሽጎባቸው ነበር፤ የተሳሳተ ስሌቱመ ስማቸውን አጠለሸባቸው፡፡

እኔ የተሸለምኩት መንግስት ኢትዮጵያ ሀገርህ ናት - ናና አልማ ስባል ነው - ለነገሩ የተወለድኩባትን እናት ሀገሬን እንዴት ነው የምረሳው ብለው ነበር በአንድ ሽልማት ስነ ስርአት ላይ ባደረጉት ንግግር፡፡

ለበርካታ ወገኖች ስራ እድል በመፍጠር ኢትየጵያን ከድህነት መንጋጋ ፈልቅቆ ማውጣት ቅድሚያ ግዴታዬ ነው ይላሉ ዛሬም ድረስ ሼህ አል-አሙዲን፡፡

የሻይና ቡና ተክል ልማት ላይ በመሰማራት ኢትዮጵያን በዚህ ዘርፍ በአለም ቀዳሚ ረድፍ ላይ ማሰለፍ ህልማቸው ነበር፡፡

ሁሌም በተስፋ ይስተካከላል የጊዜ ጉዳይ ነው ይሉኝ ነበር በማለት አቶ ጀማል የሼሁን ጨለምተኛ አለመሆን ይገልፁና አሁን ያለው ፈተና ደግሞ ሳኡዲ ውስጥ ካለ ችግር ጋር የተያያዘ እና ከዛ ሀገር እንዳይወጡ በመደረጉ ድርጅቶቻቸውን ተከታትለው እንዳይመሩ እንደሆነ በቅሬታ ያነሳሉ፡፡ ይሁንና አሉ አቶ ጀማል - “አልአሙዲን ሁሌም ይፈተናሉ፤ አላህምዱሊላሂ ሁሌም ግን ፈተናውን ያልፉታል”፡፡

መንግስት ትኩረት የሰጣቸው የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ መዋቅር (home grown economic reform pillars) ከሚባሉት ከአይቲ በስተቀር በአራቱ ስለምንሳተፍ ትኩረቱ ለእኛ ጠቃሚ ነው ባይ ናቸው ከፍተኛው አመራር፡፡

ለ22 አመታት በኪሳራ የኖረው ኤልፎራ በዶሮ ዝርያ ከምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚውን ስፍራ ስለመያዙ ተጠቅሷል፡፡ ጫጩትን ከውጭ ለምታስመጣው ኢትዮጵያ መድህን ሊሆን ጥረት ላይም ይገኛል፡፡ የሻይ ቅጠል ምርትን ከኬንያ እያስመጣች የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን በሚድሮክ ፍላጎቷን የሚሞላ አቅርቦትና የውጭ ምንዛሪ ገቢም እየተገኘበት ነው፡፡

የአፍሪካ ቢዝነስ ሊደርሺፕ ኦርጋናይዜሽን የአመቱ ምርጥ ዋና ስራ አስፈጻሚ በሚል “CEO of the Year” በሚል ሚድሮክ የእውቅና ሽልማት እና በቅርቡም እንዲሁም የአፍሪካ መሪዎች በተገኙበት ሌላ የእውቅና ሽልማት አንስቷል፡፡

ፋብሪካዎቹ ጋ ሲኬድ - እኛ የዚህ ድርጅት ባለቤቶች ነን - የዚህ ድርጅት እድገት በእኛ ይወሰናል - የሚል አባባል አለ - ሆራይዘን ጋ የነበሩ ሰራተኞች የፈጠሩት መሪ ቃል ነው - ሌሎቹም ተጋሩትና ቀጠሉ - ጀማል አዝዞት የሆነ አይደለም፡፡

ሚድሮክ ባለፉት አስር አመታት ሰርቶ አምርቶ ካመጣው የሽያጭ ገቢ በላይ የዘንድሮ አንድ አመቱ ውጤት እጅግ ያስከነዳልም ተብሏል፡፡

በውጭ አልሚነት የተመዘገቡት ሼህ አላሙዲን ብዙ ሚሊዮን ዶላር ወደ ኢትዮጵያ ይዘው መጥተው ድርጅቶች ከፍተው አምርተው በውጭ ምንዛሪም ሸጠው ከፍተኛ ገቢም አግኝተዋል፤ ግን አንድ ዶላር ከሀገር አውጥተው አያውቁም ተብሎላቸዋል፡፡

የዚህን እውነትነት ለማረጋገጥ አሉ አቶ ጀማል በዶክመንተሪው - “የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክም ጋ ሄዶ ማረጋገጥ ይቻላል፤ ከእኛ ብር ይወስዱ ስላልነበር፤ ማበረታቻ ቲፕ የሚሰጡት እንኳ በዩሮ ነበር፡፡

ጋዜጠኛ እሸቱ ገለቱ

ቴሌ ብር ሳኡዲ አረቢያ ሊገባ ነው ተባለ፡፡ በኢትዮ ቴሌኮም ስር የሚተዳደረው ቴሌ ብር የሳኡዲን ገበያ ሊቀላቀል መሆኑ ተሰማ፡፡ ይህ የተሰማው ኢትየ ቴሌኮምና የሳኡዲ ቴሌኮም ይህንን በተመለከ...
30/08/2025

ቴሌ ብር ሳኡዲ አረቢያ ሊገባ ነው ተባለ፡፡ በኢትዮ ቴሌኮም ስር የሚተዳደረው ቴሌ ብር የሳኡዲን ገበያ ሊቀላቀል መሆኑ ተሰማ፡፡ ይህ የተሰማው ኢትየ ቴሌኮምና የሳኡዲ ቴሌኮም ይህንን በተመለከተ የውል ስምምነት ማሰራቸውን ተከትሎ ነው፡፡

በውል ስምምነቱ ላይ ከሳኡዲ ቴሌ ኮም ምክትል የሽያጭ ፕሬዝደንቱ ኢንጂነር ዛይድ ሀማድና የሽያጭ ዳይሬክተሩ ባንደር አልኮዴይር በአዲስ አበባ ተገኝተው ከኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩና ሌሎችም አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡

በዚህ ውይይት ወቅት ኢትዮ ቴሌኮም ሁለቱንም ተቋማት በጋራ ተጠቃሚ የሚያደርግ ሀሳብ ያቀረበ ሲሆን ይህም አገሪቱ ከያዘችው ዲጂታል ኢኮኖሚ መገንባት ጋር የተያያዘ መሆኑን ወይዘሪት ፍሬህይወት አስረድተዋል፡፡ በመሆኑም የዲጂታል ገንዘብ ማስተላለፊያ ስርአት የሆነውን ቴሌ ብር በሳኡዲ ውስጥ ማስጀመር ድንበር ተሻጋሪ የገንዘብ ዝውውርን ለማሻሻልና ለተጠቃሚዎች የተሻለ ጠቀሜታ ለማስገኘት አስፈላጊ መሆኑን ሁለቱም አካላት ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡

የሳኡዲ ቴሌኮም ባለስልጣናትም የቴሌ ብርን ያለፉት ስድስት አመታት የስራ አፈፃፀም ተመልክተው በጋራ ለመስራት የሚያስችል አቅም እንዳለው መገንዘባቸውን የተናገሩ ሲሆን ይህንን በተመለከተ ሁለቱ አካላት በቅርቡ ይፋዊ ስምምነት እንደሚያደርጉና ስራ እንደሚያስጀምሩ ይጠበቃል፡፡ ኢትዮ ቴሌኮም ለሚቀጥሉት 3 አመታት በነደፈው ስትራቴጂ ከአገር ውጭ በተለያዩ ስራዎች ላይ እንደሚሰማራ መግለፁን መዘገባችን ይታወሳል::

የሰሜን ኮሪያው መሪ ወደ ቻይና በሚስጥራዊዉ ባቡር ይጓዛሉ !‎‎በቀጣይ ቀናት ወደ ቻይና የሚጓዙት የሰሜን ኮርያዉ መሪ ኪም ጆንግ_ኡን ወደ ቤጂንግ ለሚያደርጉት ጉዞ ሚስጥራዊውን ባቡር እንደሚ...
30/08/2025

የሰሜን ኮሪያው መሪ ወደ ቻይና በሚስጥራዊዉ ባቡር ይጓዛሉ !

‎በቀጣይ ቀናት ወደ ቻይና የሚጓዙት የሰሜን ኮርያዉ መሪ ኪም ጆንግ_ኡን ወደ ቤጂንግ ለሚያደርጉት ጉዞ ሚስጥራዊውን ባቡር እንደሚጠቀሙና ድንገት ጥቃት ቢከፈትባቸዉ ወዲያዉኑ የ ኒኩሊየር መሳርያዎች ለማስወንጨፍ ምላሽ ለመስጠት ዋና ማዘዣውን ይዘው እንደሚጓዙ ተነገረ ።

‎የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ-ኡን በሚቀጥለው ሳምንት በቻይና ሰፊ ወታደራዊ ትርኢት ላይ ለመገኘት ወደ ቤጂንግ ሲጓዙ ለእይታ አስቸጋሪውን ጥይት የማይበሳዉ ልዩ ባቡሩን ሊጠቀሙ እንደሚችሉ አርብ እለት የዉስጥ ምንጮችን ጠቅሰዉ በርካቶች እየዘገቡት ይገኛል ።

‎እንደ ኢንዲያን ታይምስ ዢንዋ ያሉ የዜና ወኪሎች ‎ ቻይና እ.ኤ.አ. በ1945 ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ያበቃበትን 80ኛ አመት በጃፓን ላይ ያሸነፈበትን ቀን ለማክበር ረቡዕ መከበሩን ተከትሎ በቤጂንግ ቲያናንመን አደባባይ በሚካሄደው ከፍተኛ ወታደራዊ ትርኢት ላይ ለመገኘት ቀጠሮ የያዙት ኪም መቼ እና እንዴት ፒዮንግያንግ ወደ ቤጂንግ እንደሚሄድ እስካሁን ድረስ ምንም አይነት መረጃ ባይገለፅም በምን አይነት የትራንስፖርት እና መንገድ እንደሚጓዝ ለማወቅ መረጃ ያነፈነፉ ሚዲያዎች ከዉስጥ አዋቂ አገኘነው በሚል ባሰራጩት ዘገባ ከአሜሪካና ጎረቤት ሀገራት ጋር አይንና ናጫ የሆኑት ኪም ከአዉሮፕላን ይልቅ ልዩ ባቡሩን የመጠቀም እድላቸው ሰፊ ነው ሲሉ ዘግበዋል ።

‎ኪም በስልጣን ዘመናቸው በቻይና ላደረገው አራት ጉብኝት ሁለት ጊዜ በባቡር እና ሁለት ጊዜ በአውሮፕላን
‎ጉዞ እንዳደረጉ የገለፀው ዘገባው ሰሜን ኮሪያ ቻማኢ-1ን የሚተካ አዲስ አውሮፕላን ማግኘት ባለመቻሏ ለመጪው ቻይና ለሚደረገው ጉዞ ኪም የግል ባቡር የመጓጓዣ ዘዴው ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
‎በባቡር የሚደረገዉ ጉዞም ለአራት ቀናት ያስፈልጋቸዋል ብለዋል ።

‎ትንበያውን ሊደግፍ በሚችል ምልክት በሰሜን ኮሪያ ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው የቻይና ከተማ ዳንዶንግ የሚገኘው ዞንግሊያን ሆቴል ከሰልፉ በፊት እና በኋላ ባሉት ጊዜያት ለውጭ ቱሪስቶች የሚሰጠውን ቦታ ማቆሙ ገልፀዋል ።

‎ከሰሜን ኮሪያ ወደ ቻይና በባቡር መስመር ላይ የሚገኘው ሆቴሉ ኪም ወደ ቻይና ሲሄድ ለውጭ ሀገር ቱሪስቶች ምዝገባን በማቆም ሪከርድ እንዳለው ዮንሃፕ የዜና አገልግሎት ዘግቧል።

‎የኪም ልዩ ባቡር ለደህንነት ሲባል ጥይት የማይበገሩ ሽፋን እና ሞርታርን ጨምሮ ከባድና ቀላል መሳርያዎች የታጠቀ እንዲሁም የመገናኛ መስመሮችን፣ የአለም አቀማመጥ መሳሪያዎችን እና ሌሎች መገልገያዎችን ታጥቋል ተብሏል።

‎የሰሜን ኮርያው ሁለንተናዊ መሪ ኪምም የኒኩሊየር ቦንቦችን ትዕዛዝ መስጫ ቁልፍ በአንገታቸው ላይ አንጠልጥለው እንደሚጓዙ ማንኛውም ትንኮሳ ካጋጠመ ወዲያውኑ እንዲወነጨፉ ትዕዛዝ እንደሚሰጡ ተገልጿል ።

‎ ባቡሩ እጂግ ዘመናዊ ሲሆን በአንድ ወቅት እድሉን በማግኘት በባቡሩ የገባ አንድ የሩሲያ ባለስልጣን “ፍፁም የሚንቀሳቀስ ምሽግ” ሲል ገልጿል ሲል ዮንሃፕ የዜና ወኪል አስነብቧል ።


‎የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ

ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት የምትገኘው አሊ ዶሮ እና አካባቢዋ ለምን የእገታ ማዕከል ሆኑ?የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ አሽከርካሪ የሆኑት አቶ ታረቀኝ* ብዙ ጊዜ ይመላለሱበት በነበረው የአዲስ ...
24/08/2025

ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት የምትገኘው አሊ ዶሮ እና አካባቢዋ ለምን የእገታ ማዕከል ሆኑ?

የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ አሽከርካሪ የሆኑት አቶ ታረቀኝ* ብዙ ጊዜ ይመላለሱበት በነበረው የአዲስ አበባ ወደ ጎጃም መስመር፣ ከፍቼ እስከ ጎሃ ጽዮን ያሉት አካባቢዎች 'የሞት ቀጠና' ነው የሚመስሏቸው።
በዚያ መስመር ሲመደቡ ወደ አእምሯቸው የሚመጣው ሞት አሊያም ቤተሰቦቻቸው ከእገታ ማስለቀቂያ ምፅዋት ሲጠይቁ ነው።
'እንጀራ ስለሆነባቸው' እንጂ በተደጋጋሚ በባልደረቦቻቸው ላይ ደርሶ የሰሙት እገታ እና ግድያ አንድ ቀን በእርሳቸውም ላይ ሊከሰት እንደሚችል ስጋት ነበራቸው፤ የሰጉትም አልቀረ።
ከሁለት ወር ገደማ በፊት በጠዋት ሥራ ቦታቸው ተገኝተው ከ50 በላይ መንገደኞችን አሳፍረው ወደ ደብረ ማርቆስ ለማቅናት ጉዞ ጀመሩ።
እንደ ወትሮው ሁሉ ለጉዞ ከተነሱ በኋላ የመንገድ ቅኝት እስከሚደረግ ድረስ ከአዲስ አበባ መውጫ ላይ ባሉ ኬላዎች ቆመው ጠብቀዋል።

እርሳቸው እንደሚሉት ተሽከርካሪዎች አዲስ አበባ መውጫ ላይ በጫንጮ እና በፍቼ ከተሞች በሚገኙ ኬላዎች ላይ ለረዥም ሰዓታት እንዲቆሙ ተደርጎ የመንገዱ ደኅንነት ይጣራል።
ቅኝቱን የሚያካሂዱት በየአካባቢዎቹ የሚገኙ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ናቸው።

አቶ ታረቀኝ እና ሌሎች አሽከርካሪዎች ከኬላዎቹ የተነሱት የመንገዱ ደኅንነት ከተረጋገጠ እና እንዲያልፉ ከተፈቀደላቸው በኋላ ነበር።
ሆኖም መንገዳቸውን ሳያገባድዱ ነበር ድንገት የተኩስ ሩምታ የተከፈተባቸው።
ጥቃቱ የተከፈተባቸው ከእገታ ጋር ተያይዞ ስሟ ከሚነሳው አሊ ዶሮ ቀበሌ ሳይደርሱ ባለች ትንሽ መንደር ላይ ነበር።
"ታጣቂዎቹ ወደ 30 ገደማ ይሆናሉ" የሚሉት አቶ ታረቀኝ፤ ከእርሳቸው በፊት ይጓዝ የነበረ አውቶብስ ካመለጣቸው በኋላ እርሳቸው ሲደርሱ ተኩሱ ድንገት እንደተከፈተባቸው ይናገራሉ።
"እንድንቆም ቢጠይቁን እነርሱ መሆናቸውን ስለምናውቅ እንቆም ነበር። ግን ተኩስ ነበር የከፈቱት። እኔም ለማምለጥ ስል ነዳሁት" ይላሉ።
መቆም የቻሉትም በዘነበባቸው ጥይት የተሽከርካሪው ጎማ ከተመታ በኋላ ነው። ድንጋጤ ውስጥ ስለነበሩ አንድ እግራቸው ላይ ከባድ ጉዳት እንደደረሰ ያወቁት ከመኪናው ለመውጣት ሲሞክሩ እንደነበር ይናገራሉ።
"እንደምንም ወርጄ፣ በደረቴ እየተሳብኩ ከመኪናው መንገድ ከወጣሁ በኋላ በአንድ እግሬ እየዘለልኩ ስሮጥ ደረሱብኝ። እቆማለሁ ስል ወደቅኩ። ሌሎቹ ወደ መኪናው እየተኮሱ ተሳፋሪው እንዲወርድ አደረጉ" በማለት ሁኔታውን ያስታውሳሉ።
"እያገላበጡ ሲፈትሹኝ እንደ ሞተ ሰው ዝም አልኳቸው። ኪሴ ውስጥ የነበረ ገንዘብ እና ስልክ ወስደው ሞቷል ብለው ጥለውኝ ሄዱ።"
ታጣቂዎቹ ትተዋቸው ከሄዱ በኋላ ግን [በግምት ከ30 ደቂቃ በኋላ] ሌላ ተኩስ መሰማት ተጀመረ። ይህ የሕይወታቸው የመጨረሻ ሰዓት ነበር የመሰላቸው።
"ታጣቂዎቹ ሊጨርሱኝ ድጋሚ የመጡ ነበር የመሰለኝ። ነገር ግን የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ናቸው። 'አይዟችሁ! ደርሰንላችኋል!' ብለው ከወደቅኩበት አነሱኝ።"
አቶ ታረቀኝ እና ያሳፈሯቸው መንገደኞች ላይ የተፈፀመውን ጥቃት እንደማሳያነት ጨለፍነው እንጂ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ይህ በርካቶች የሚያልፉበት ተደጋጋሚ ክስተት ነው።
ከፍቼ - ጎሃ ጽዮን
ሲራክ* በአውራ ጎዳናው በሳምንት ውስጥ ቢያንስ አራት ጊዜ ይመላለሳል።
የጭነት መኪና በማሽከርከር በሚያገኘው ገቢ ራሱን እና ቤተሰቡን የሚያስተዳድረው ሲራክ፣ አካባቢውን የሚያልፈው በጭንቀት እንደሆነ ይናገራል።
ከፍቼ እስከ ጎሃ ጽዮን ድረስ ያሉት የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች እጅጉን አስጊ ቦታዎች መሆናቸውንም ይጠቅሳል።
ሲራክ እንደሚለው ከፍቼ እስከ ሙከጡሪ፤ ከገርበ ጉራቻ እስከ ጎሃ ጽዮን ባሉት አካባቢዎች በመንገደኞች እና በአሽከርካሪዎች ላይ በርካታ ወንጀሎች ተፈፅመዋል።
ከእነዚህ ልዩ ቦታዎች መካከልም አሊ ዶሮ፣ ገርበ ጉራቻ፣ ሙከጡሪ፣ ቱሉ ሚልኪ፣ ጎርፉ ገብርኤል እና ዱበር የተባሉ አካባቢዎች እንደሚገኙበት አሽከርካሪው ይጠቅሳል።
በተደጋጋሚ የአውቶብስ ተሳፋሪዎች በታጣቂዎች ታግተው የመወሰዳቸው ዜና እየተለመደ እንደመጣ የሚናገረው አሽከርካሪው፣ "እኛም ተራችንን ነው የምንጠብቀው" ይላል።
ሲራክ እንደሚለው በዚህም ስጋት ምክንያት አሽከርካሪዎች እነዚህን አካባቢዎች በአንድ ላይ እጅብ ብለው ማለፍ ግድ ይላቸዋል።
"እነዚህን አካባቢዎች በቶሎ ለማለፍ ለቁርስም ሆነ ለምሳ፣ አንዳንዴ ለውሃ ሽንትም ቢሆን አንቆምም" ይላል።
በአውራ ጎዳናው ከሚሄዱ ሌሎች መኪኖች ጋር በጋራ አብሮ ለማለፍና ርቀትን ለመጠበቅ በፍጥነት ማሽከርከርን ስለሚጠይቅ አደጋ ሲከሰትም ተመልክቷል።
አለበል* የተባለ ሌላ አሽከርካሪም ከሲራክ የተለየ ሃሳብ የለውም። ለእርሱም ከፍቼ ጀምሮ እስከ ጎሃ ጽዮን ያለው አካባቢ የስጋት ቀጠና ነው።
መንግሥት ከታጣቂ ቡድን ጋር ግጭት ውስጥ በገባበት እና ከአዲስ አበባ ጋር በሁሉም አቅጣጫዎች በሚዋሰነው ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ያለው የፀጥታ ሁኔታ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተሻሻለ መምጣቱ ቢነገርም፣ እገታዎች ግን አልቆሙም።
ከዚህ ቀደም በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የሚፈፀመው የሰላማዊ ሰዎች እገታ በክልሉ፣ ሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ በሚገኙ አካባቢዎች በተደጋጋሚ ሲከሰት ተዘግቧል።
ከእነዚህ አካባቢዎች መካከል ኩዩ፣ ወረ ጃርሶ፣ ደገም፣ ሂደቡ አቦቴ፣ ያያ ጉለሌ የተሰኙ ወረዳዎች በተለየ ይጠቀሳሉ።
በደገም ወረዳ ሥር የምትገኘው አሊ ዶሮ ቀበሌ እና የወረ ጃርሶዋ ከተማ ቱሉ ሚልኪ እንዲሁም የኩዩ ወረዳ ከተማ - ገርበ ጉራቻ የእገታ ወንጀል ከሚፈፀምባቸው አካባቢዎች ስማቸው በዋናነት ይነሳል።
'አሊ ዶሮ' ግን ዋነኛ ማዕከል ናት። አሊ ዶሮ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ መንገደኞች ብቻ ሳይሆን፣ የጭነት መኪና አሽከርካሪዎችም በስጋት የሚያልፉባት አነስተኛ ቦታ ነች። ማለፍ የሚችሉትም ዕድል የቀናቸው ናቸው።

በሌላ በኩልም መንግሥት በክልሉ በሚገኙ ሌሎች አካባቢዎች አጠናክሮ የወሰደው እርምጃ ታጣቂዎቹን ወደ ማዕከል እንዳስጠጋቸው የሚነገር ሲሆን፣ ታጣቂዎቹ ግን ለዚህ የእንቅስቃሴ አድማሳቸው እየሰፋ መምጣቱን ይገልጻሉ።
ቢቢሲ ይህንን ማረጋገጥ ባይችልም ታጣቂ ቡድኑ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት በሚገኙ አካባቢዎች እንደሚንቀሳቀስ ይነገራል።
ለዚህም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልሉ ሰሜን ሸዋ ዞን በሚገኙ የመንግሥት አመራሮች ላይ በታጣቂዎች የሚሰነዘረው ጥቃት አንዱ ማሳያ ነው።
ከታኅሣሥ እስከ የካቲት 2017 ዓ.ም. ባሉት ሦስት ወራት ብቻ በርካታ የዞኑ አመራሮች መንግሥት ሸኔ በሚለው ታጣቂ ቡድን በተፈፀመባቸው ጥቃቶች መገደላቸው ይታወሳል።
የኦሮሚያ የፀጥታ ኃይሎች፣ የፌደራል ፖሊስ እና የመከላከያ ሠራዊት ካምፖች ከአካባቢው በቅርብ ርቀት ላይ ይገኛሉ።

ተመሳሳይ ወንጀሎች በተለያዩ ቦታዎች እንዲፈፀሙ በር እንደከፈተ ቢቢሲ ያነጋገራቸው አንድ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ይናገራሉ።
የተማሪዎቹ እገታ የሚከታተል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሚመራ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ የነበረ ሲሆን ባለሥልጣናትም የተጎጂ ቤተሰቦችን አግኝተው አነጋግረዋል።
ሆኖም ግብረ ኃይሉ የደረሰበትን ሳያሳውቅ ተማሪዎቹም የደረሱበት ሳይታወቅ ዓመታት ተቆጥረዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ያሬድ ኃይለማሪያም እንደሚሉት አጋች የሚባሉት አካላት አንድም ጊዜ ለፍርድ አለመቅረባቸው፣ መደበኛ ስልክ እየተጠቀሙ ታጋቾችን ለመልቀቅ በገንዘብ ሲደራደሩ እንዲሁም በባንክ ገንዘብ ሲተላለፍ ትኩረት ተሰጥቶ ክትትል አለመደረጉ ወንጀሉን አባብሶታል።
"በአሊ ዶሮ አካባቢ ተደጋጋሚ እገታ መፈፀሙም አንድም አካባቢው ላይ ያሉ የፀጥታ አካላት ኃላፊነታቸውን እየተወጡ አለመሆኑን፣ አሊያም ይህን ድርጊት ከሚፈፅሙ ወንጀለኞች ጋር ግንኙነት አላቸው ብሎ መጠርጠር ይቻላል" ይላሉ።
ይህም የሕግ መላላት መኖሩንና መንግሥት የሕግ የበላይነትን እያስከበረ አለመሆኑን የሚያመለክት እንደሆነም የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ይናገራሉ።
"ዜጎች የሚደርስባቸውን ችግር እራሳቸው ጠይቀው ራሳቸው መልስ መስጠት ከጀመሩ ቆዩ" የሚሉ አንድ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራር በበኩላቸው መንግሥት እየተንሰራፉ ያሉ ወንጀሎችን ጆሮ ዳባ ልበስ እንዳለ ይገልጻሉ።
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ታጠቅ አሰፋ በእገታ እና ጥቃት ስጋት ምክንያት አሁን ላይ ከወከሏቸው የፓርቲ አባላት ጋር ያላቸው ግንኙነት በአየር ጉዞ እና በስልክ ተወስኗል ይላሉ።
መጋቢት ወር 2017 ዓ.ም. ውስጥ ሁለት ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በአንድ ቦታ ላይ [አሊ ዶሮ አካባቢ] ተመሳሳይ ወንጀል እንደተፈፀመ የሚጠቅሱት አቶ ታጠቅ፣ አካባቢው በአሰቃቂ ድርጊት ሲወረር የሚወሰድ እርምጃ የለም ሲሉም ይወቅሳሉ።
"ከሦስት ዓመት በፊት ለማደራጀት ሥራ ወደ ባሕር ዳር ሄጄ ነበር። ወደ አዲስ አበባ እየተመለስኩ ሳለ የአባይ በረሃን ሳንሻገር በርካታ ተሽከርካሪዎች ተደርድረው ቆመዋል። ተሽከርካሪዎቹ የቆሙት በአንድ የጭነት ተሽከርካሪ ላይ ጥቃት ተፈፅሞ መኪናው በመገልበጡ ነው። ሹፌሩ እና ረዳቱም በጥይት ተመትተዋል" ሲሉ እማኝነታቸውን የሚናገሩት አቶ ታጠቅ፣ አካባቢው በመከላከያ ቁጥጥር ሥር መዋል የቻለው ከ15 ደቂቃ ገደማ በኋላ እንደነበር ያስታውሳሉ።
እንዲህ ዓይነት ወንጀሎች የሚፈፀሙት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ከሥፍራው ከተነሱ በኋላ መሆኑም ጥያቄ እንደፈጠረባቸው ያስረዳሉ።
የአካባቢው ነዋሪዎችም በተለያዩ ጊዜያት አደባባይ በመውጣት ሰላም እንዲመጣ ተማፅኗቸውን በተደጋጋሚ አሰምተዋል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲም በኢትዮጵያ ውስጥ ገንዘብ ለማግኘት እየተፈፀሙ ያሉ ሰላማዊ ሰዎች እና የተማሪዎች እገታዎች እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል።
ሰኔ ወር መጨረሻ ላይ የተፈፀመውን የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እገታን ተከትሎ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች በተደጋጋሚ የሚፈፀሙት እገታዎች እየተካሄዱ ያሉት ግጭቶች ምን ያህል ወንጀለኞችን እንዳደፋፈሩ እና የሕግ የበላይነትን እንዳዳከሙ ያሳያሉ ብለዋል።
መንግሥት በተለያዩ ጊዜያት በታጣቂ ቡድኑ ላይ እርምጃ እየወሰደ እንደሆነ ሲገልጽ ቢቆይም በተለያዩ አካባቢዎች በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን እና እገታዎችን ማስቆም ግን አልቻለም።

BBC Amharic

የገደብ ወንዝ ድልድይ ከነ ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናልነሐሴ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ሌሊት ጮቄ ተራራ ላይ የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ በደረሰበት ጉዳት ምክንያት በተገጣጣሚ ብረት...
23/08/2025

የገደብ ወንዝ ድልድይ ከነ ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል

ነሐሴ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ሌሊት ጮቄ ተራራ ላይ የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ በደረሰበት ጉዳት ምክንያት በተገጣጣሚ ብረት የመገንባቱ ሥራ ሲከናወንለት የቆየው የገደብ ወንዝ ድልድይ በዛሬው ዕለት ሥራው ሙሉ በሙሉ በመጠናቀቁ ከነገ ነገ ነሐሴ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል፡፡

በጎርፍ ምክንያት ድልድዩ ጉዳት ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ ግንባታው እስኪጠናቀቅ በትዕግስት ሲጠባበቁ ለቆዩ መንገደኞችና አሽከርካሪዎች የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምስጋና እያቀረበ ድልድዩ ሁለት መኪና በአንዴ ማስተላለፍ ስለማይችል በመጠባበቅ እንዲተላለፉ፣ ድልድዩ የሚገኝበት ቦታ ኩርባ ላይ ስለሆነ ፍጥነት በመቀነስ እና ቅድሚያ በመስጠት በትዕግስት እንዲተላልፉ ያሳስባል፡፡

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን

በ13/ 12/ 2017 ማስታወቂያው የተለጠፈው እስከ መስከረም 2 / 1 / 2018 ድረስ ገቢ መሆን አለበት
21/08/2025

በ13/ 12/ 2017 ማስታወቂያው የተለጠፈው እስከ መስከረም 2 / 1 / 2018 ድረስ ገቢ መሆን አለበት

በህገወጥ መንገድ የሚሰበስበውን ገንዘብ ተቃውመውኛል በሚል በበቀል የአንድ ቤተሰብ አባል የሆኑ ሶስት ሰዎችን የገደለው  የፀጥታ አካል በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበትበምዕራብ ወለጋ ዞን ሰኞ ኖሌ ...
20/08/2025

በህገወጥ መንገድ የሚሰበስበውን ገንዘብ ተቃውመውኛል በሚል በበቀል የአንድ ቤተሰብ አባል የሆኑ ሶስት ሰዎችን የገደለው የፀጥታ አካል በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበት

በምዕራብ ወለጋ ዞን ሰኞ ኖሌ ቀበሌ ኮኮሪ በተባለ አካባቢ የአንድ ቤተሠብ አባል የሆኑ ሶስት ልጆች የገደለ የፀጥታ አካል በሞት እንዲቀጣ ተወስኖበታል።

የምዕራብ ወለጋ ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የኮምንኬሽን ፅፈት ቤት ሐላፊ ኢንስፔክተር ቹቹ ኢቱ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ተከሣሽ ሸዋ ቀና የተባለው የፀጥታ አካል በተመደበበት ሰኞ ኖሌ ቀበሌ ኮኮሪ የተባለ ስፍራ ከ2016 ጀምሮ በስራ ተመድቦ እያለ በአካባቢው ያለውን የፀጥታ ሑኔታ ተጠቅሞ ያለምንም ሕጋዊ ደረሠኝ ከተለያዪ ግለሠቦች ላይ ብር ሲሰበስብ እንደነበረ በክስ ዝርዝሩ ላይ ተገልፅዋል።

የተከሳሹን ሕገወጥ ተግባር የተቃወሙትን ለመበቀል አስቦ የአካባቢ ሰዎች መካከል የአንድ ቤተሰብ አባል የሆኑ አንደኛ ዳንሱሬ በቀለ እድሜዋ 13፣ሁለተኛ አያንቱ በቀለ የተባለችዉንና እድሜ 15 የሆነች እና ሶስተኛ ሶሬ በቀለ እድሜዋ 17 ዓመት የሆነ ታዳጊን ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓም ከምሽቱ አራት ሰዓት ቤተሠቦቻቸው በሌሉበት ከፍቶ በመግባት ሶስቱንም ሴት ታዳጊዎች ወደ አንድ የተዘጋ ቤት ይዝዋቸው ይሄዳል፡፡

ሶስተኛዋ ሶሬ በቀለ ሮጣ በማምለጥ ወደ አካባቢዋ ተመልሣ በእሕቶቻቸው ላይ የተፈፀመውን የእገታ ተግባር ምስጋናው በቀለ ለተባለዉ ወንድሟ እንደተናገረች ታዉቋል።

ምስጋናው በቀለም ከእሕቱ የደረሠውን ጥሪ ተቀብሎ ወደተባለው ስፍራ ሲደርስ ተከሣሹ ተበርከክ ብሎ ካንበረከከው በሗላ በያዘው መሣርያ ተኩሶ እንደገደለው ና ተመልሶ ወደቤት በመግባት ሑለቱን ሴት ልጆችም እንደገደላቸው ተረጋግጧል።

ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን ሲፈፅም ሁለተኛ ተከሣሽ የሆነው ግብረ አበሩ ጐበና ገቢሣ የወንጀል ድርጊቱ ሲፈፀም መከላከል ና ለሕግ አካል ማሣወቅ ሲገባው ድርጊቱ ሲፈፀም ዝም ብሎ በማየቱ በሕግ ሊከሰስ ችሏል።

ተከሣሹ የአንድ ቤተሠብ ሶስት ልጆችን ሕይወት ካጠፋ በሗላ ለግዜው ቢሠወርም ፖሊስ ባደረገው ጥብቅ ክትትል ከተሸሸገበት በቁጥጥር ስር ዉሏል፡ ፖሊስም የወንጀል ድርጊቱን በበቂ ማስረጃ ና በሆስፒታል የአስክሬን ምርመራ ውጤት የምርመራ መዝገቡን በማጠናቀቅ እንዲሁም ያለማንም እውቅና ከነዋሪዎች ገንዘብ መሰብሰቡን በበቂ ማስረጃ በማጠናከር የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለአቃቢ ሕግ ይልካል።

አቃቢ ሕግም ከፖሊስ የቀረበውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በወንጀል ሕግ 539- ንኡስ አንቀፅ ፣1--2--3 ፣ በከባድ የሰው መግደል ወንጀልና በሕገወጥ መንገድ ገንዘብ መሠብሠብ ክስ እንደ መሰረተበትም ገልፀዋል።

በአቃቢ ሕግ የተመሰረተው ክስ ሲከታተል የቆየው የምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነሐሴ፣13 ቀን 2017ዓም ባስቻለው ችሎት ተከሳሽ ሸዋ ቀና ሞገስ እጅግ ነውረኛ በሆነ አኳኃን ሰውን ለመግደል አስቦ፣ተዘጋጅቶና አቅዶ የአንድ ቤተሠብ ሶስት ልጆች መግደሉ በበቂ ማስረጃ በመረጋገጡ እንዲሑም ያለማንም እውቅና ገንዘብ በሕገወጥ መንገድ ሲሰበስብ እንደነበረ በመረጋገጡ ተከሣሹ በተለየ መልኩ ጨካኝነቱን ፣ነውረኛነቱንና አደገኛነቱ የሚያሣይ በመሆኑ በመጨረሻው የቅጣት እርከን በሞት እንዲቀጣ የወሠነበት ሲሆን ይሕ ድርጊት ሲፈፀም ዝምብሎ የተመለከተው ሑለተኛ ተከሣሽ ጐበና ገቢሣ በሑለት ዓመት እስራት እንዲቀጣ ውሣኔ ማስተላለፉን ኢንስፔክተር ቹቹ ኢቱ ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል፡፡

Via በኤደን ሽመልስ
©️ዳጉ_ጆርናል

በመቀሌ የአንድነት ጥሪ ቀረበ !‎ከመቀሌ  የደረሰን እንደወረደ እነሆ‎እነዚህ ሰልፈኞችም የሰሜን ህዝብ አንዱ ከሌላዉ መነጠል የማይችል ለዘመናት አብሮ የኖረ የሚኖር በጋብቻ በጡት አባትነት በ...
17/08/2025

በመቀሌ የአንድነት ጥሪ ቀረበ !

ከመቀሌ የደረሰን እንደወረደ እነሆ

‎እነዚህ ሰልፈኞችም የሰሜን ህዝብ አንዱ ከሌላዉ መነጠል የማይችል ለዘመናት አብሮ የኖረ የሚኖር በጋብቻ በጡት አባትነት በክርስትና ልጅነት እና በሌሎች ማህበራዊ መስተጋብሮች የተዋሃደ የጋራ ታሪክ ባህል እምነት ባለቤት የሆነ ህዝብ ነዉ ።

‎ክፍለዘመናትን ባሳለፈው አብሮነታችን ዉስጥ በተወሰኑ የስልጣን ፈላጊዎች ለመነጣጠል በሞከሩበት ወቅትም እንደህዝብ እርጥብ ቅጠል ይዘዉ ይቅር በመባባል ግጭቶቻቸዉን በጋራ ማለፍ መገለጫችን ነዉ ።

‎ባለፉት ሀምሳ አመታት በሃገራችን በነበሩ ፖለቲከኞች ምክንያት በተፈጠረ የጎጥና የመንደር እሳቤ በተወሰኑ ግለሰቦች ፍላጎትና ድርጊት የህዝብ ግኑኝነቱን በማሻከር አብረዉ የኖሩ አብረዉ ያደጉ ወጣቶች እርስ በእርስ ተቃቅረዉ በሽዎች በለጋነታቸዉ ተቀጥፈዋል አባት ያለ ጧሪ እናት ያለ ልጅ ቀርተዋል ።

‎ባለፉት አመታት ብቻ አንተም ተዉ አንተም ተዉ !! የሚል ሽማግሌ ጠፍቶ ወንድሞቻችን በስሜት ወደእሳት ዘለዉ ገብተዉ ደም ፈሷል ኢትዮጵያ ጠብቀዉ ከትዉልድ ትዉልድ ያስተላለፉ ህዝቦች ላዬ ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ስነልቦናዊ ቀዉስ ተፈጥሯል ።
‎በዚህ ሂደት ውስጥም ማንም አሸናፊ ማንም ተሸናፊ እንዳልሆነ እያየን ነዉ ።

‎ፖለቲከኞች ለስልጣን ሽኩቻ ከሚዘሩት ጥላቻ ይለቅ በትዳር የተሳሰረዉ በፍቅር የኖረዉ ይበልጣል ።
‎እምነታችን ስነልቦናችን አስተዳደጋችን ባህላችን ታሪካችን አንድ ነዉ ።

‎ስለዚህም ያለፈ ዉሃ አይታፈስምና ያለፈዉን እንዳለፈ ትተን ከትላንት ተምረን የፍቅሩን የአንድነቱን መንገድ መርጠናል ።

‎ጦርነት በቃን ጥላቻ በቃን መበታተን በቃን !!
‎ከዚህ በኋላ ዉዱ የሰዉ ልጅ ወደጦርነት አይማገድም ‎ሲሉ ተደምጠዋል::

13ኛው ማዕዶት ለኢትዮጵያ   በሚሊኒየም አዳራሽ
17/08/2025

13ኛው ማዕዶት ለኢትዮጵያ በሚሊኒየም አዳራሽ

የቆቃ ግድብ በመሙላቱ ውሃ ይለቀቃል የቆቃ ግድብ ውሀ ይለቀቃል የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በክረምት እየጣለ ባለው ዝናብ የቆቃ ግድብ ከመጠን በላይ በመሙላቱ ከነገ ጀምሮ ከግድቡ ውሃ ይለቀቃል ...
13/08/2025

የቆቃ ግድብ በመሙላቱ ውሃ ይለቀቃል

የቆቃ ግድብ ውሀ ይለቀቃል

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በክረምት እየጣለ ባለው ዝናብ የቆቃ ግድብ ከመጠን በላይ በመሙላቱ ከነገ ጀምሮ ከግድቡ ውሃ ይለቀቃል አለ።

ግድቡን ለማስተንፈስ የሚለቀቀው ውሃ ከፍተኛ መጠን ያለው በመሆኑ በግድቡ ዙሪያ ያሉ ማህበረሰቦች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

በሚኒስቴሩ የገጸ ምድር ውሃ ዴስክ ኃላፊ ሚካኤል ብርሃኔ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት፤ ውሃ የመያዝ አቅሙ 110 ነጥብ 3 ሜትር ከፍታ የሆነው የቆቃ ግድብ እስካሁን 109 ነጥብ 1 ሜትር ከፍታ ድረስ ውሃ ይዟል።

ስለሆነም ግድቡ ከአቅም በላይ በመሙላት ጉዳት ከማድረሱ በፊት ማስተንፈስ አስፈላጊ በመሆኑ ከነገ ጀምሮ ውሃ ይለቀቃል ብለዋል፡፡

በመሆኑም ወንጂ ስኳር፣ መልካስ የምርምር ማዕከል፣ አፍሪካ ጁስ፣ የላይኛው አዋሽ አግሮ ኢንዱስትሪ፣ አዋሽ ወይነሪ እና መተሃራ ስኳር ፋብሪካ አካባቢዎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም የአዋሽ ወንዝን የሚጋሩት አዳማ፣ መልካሳ፣ ቦሰት፣ ጀጁ እና መርቲ ወረዳዎች እንዲሁም የመካከለኛው አዋሽ አምቤራ እርሻ ልማት እና አሚባራ ወረዳ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ሚኒስቴሩ መልዕክቱን አስተላልፏል።

ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር

Address

Debra Markos

Telephone

+251948916040

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Habesha Daily/ ሀበሻ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Habesha Daily/ ሀበሻ:

Share