Bahir Dar Tube ባህር ዳር

Bahir Dar Tube ባህር ዳር Bahir Dar
ባህር ዳር
Ethiopia
ኢትዮጲያ

ግልፅ ለማድረግ...ስለ አዲሱ የኢትዮጵያ ፓስፖርት ማወቅ ያለብን ፦የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ትላንት በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም አዲስ ፓስፖርቶችን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ የበርካቶ...
24/02/2025

ግልፅ ለማድረግ...

ስለ አዲሱ የኢትዮጵያ ፓስፖርት ማወቅ ያለብን ፦

የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ትላንት በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም አዲስ ፓስፖርቶችን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ የበርካቶች ጥያቄ የሆነው “የቀደሞ ፓስፖርታችንን በአዲሱ መቀየር አለብን ወይ?” የሚለው ነው፡፡

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ነባሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን የሚቀጥል ሲሆን የዕድሳት ጊዜው ሲደርስ በአዲሱ ኢ-ፓስፖርት እንደሚተካ አሳውቋል፡፡

ማንኛውም ግለሰብ የአገልግሎት ዘመኑ ያላለፈበት ፓስፖርት ካለው መለወጥ ሳይጠበቅበት መጠቀም ይችላል፡፡

ይህ ማለት ግዜው ያላለፈ የቀድሞው ፓስፖርትና አዲሱ መሳ ለመሳ አገልግሎት እየሰጡ በመቆየት የቀድሞው የአገልግሎት ግዜው ሲጠናቀቅና ግለሰቡ እድሳት ሲያደርግ አዲሱን ኢ ፓስፖርት ማግኘት ይችላል ማለት ነው፡፡

አዲሱን ኢ-ፓስፖርት የሚጠይቅ ግለሰብ በሁለት ወር ከ10 ቀን ማግኘት የሚችል ሲሆን የአገልግሎት ዘመኑም ወደ 10 ዓመት ከፍ ተደርጓል፡፡

>> አጫጭር መረጃዎች...

• አዲሱን ኢ-ፓስፖርት በሁለት ወር ከ10 ቀን ማግኘት ይቻላል፣

• 14 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት አገልግሎቱን ለመስጠት ዝግጅት ተጠናቋል፣

• ከአንድ ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ኢ-ፓስፖርት ታትሞ ተዘጋጅቷል፣

• ከፓስፖርት በተጨማሪ ከ10 በላይ የጉዞ ሰነዶችን ማዘመን ተችሏል፣

• አዲሱ ኢ-ፓስፖርት በነበረው ዋጋ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ ይሆናል፤

• ለፓስፖርት ህትመት የሚወጣውን የውጭ ምንዛሬ በማስቀረት የሚኖረው ፋይዳ ጉልህ ነው፣

• ከዚህ በፊት አገልግሎት እየተሰጠ የቆየው 20 ዓመት ባለፈው ቴክኖሎጂ ነው፣

• ይህንን ቴክኖሎጂ በሀገር ውስጥ መገንባት መቻሉ ትልቅ ድል ነው፣

• አዲሱ ቴክኖሎጂ ደንበኞች ባሉበት ፓስፖርታቸውን በፍጥነት ማግኘት እንዲችሉ ያደርጋል፣

• ከዚህ በፊት የሚያጋጥሙ የደህንነት ችግሮችን ሙሉ በሙሉ ይቀርፋል፤

• ነባሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን ይቀጥላል፤

• የዕድሳት ጊዜው ሲደርስ በኢ-ፓስፖርት ይተካል፤

ምንጭ፦ Sheger Times Media

ኢትዮጵያ ኮከብ ተጨዋቿን አጣች!አዲሱ ሙሽራ ማረፉ ተሰምቷል !በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የባህርዳር ከነማው ድንቅ የአማካይ ተጨዋች አለልኝ አዘነ በድንገት ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።በቅርቡ የጋብ...
27/03/2024

ኢትዮጵያ ኮከብ ተጨዋቿን አጣች!

አዲሱ ሙሽራ ማረፉ ተሰምቷል !

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የባህርዳር ከነማው ድንቅ የአማካይ ተጨዋች አለልኝ አዘነ በድንገት ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።

በቅርቡ የጋብቻ ስነ ስርዓቱን በቤተክርስቲያን የፈፀመው አዲሱ ሙሽራ ድንገት ዛሬ ለሊት ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል ።

ለአርባምንጭ ታዳጊ ቡድን እስከ ዋናው፤ ለሀዋሳ ከተማና አሁን ለባህርዳር ከተማ በሊጉ የሚጫወተው አለልኝ አዘነ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም ጥሪ ተደርጎለት አገልግሎት ሰጥቷል።

አመለ ሸጋው ተጨዋች አለልኝ አዘነ ላለፉት ሁለት አመታት በጣና ሞገዶቹ ቤት አስደናቂ ብቃቱን በማሳየት ክለቡንና ሀገሩን እያገለገለ የሚገኝ ወጣት ተጨዋች ነበር።

(ባላገሩ ቴሌቪዥን)

ፌስ ቡክ የፖስወርዳችሁን ጥንካሬ ማወቂያ መንገድ አሣውቋል ። በመሆኑም በኮሜንት መስጫ ዉ  ብላችሁ ስትጽፉ ብላሩን ወደ ሰማያዊ ከቀየረው ጠንካራ ፓስወርድ አላችሁ ማለት ነው ሞክሩት !
26/03/2024

ፌስ ቡክ የፖስወርዳችሁን ጥንካሬ ማወቂያ መንገድ አሣውቋል ። በመሆኑም በኮሜንት መስጫ ዉ ብላችሁ ስትጽፉ ብላሩን ወደ ሰማያዊ ከቀየረው ጠንካራ ፓስወርድ አላችሁ ማለት ነው ሞክሩት !

05/02/2024
ችኮላን ቀንሱ!ስለቸኮላችሁ በፍጥነት ያሰባችሁበት የምትደርሱ ሊመስላችሁ ይችላል ነገር ግን ስለመድረሳችሁ ምንም አይነት ዋስትና የላችሁም፣ ስለተንገበገባችሁ የምትፈልጉትን ሁሉ ቶሎ በእጃችሁ የ...
03/02/2024

ችኮላን ቀንሱ!
ስለቸኮላችሁ በፍጥነት ያሰባችሁበት የምትደርሱ ሊመስላችሁ ይችላል ነገር ግን ስለመድረሳችሁ ምንም አይነት ዋስትና የላችሁም፣ ስለተንገበገባችሁ የምትፈልጉትን ሁሉ ቶሎ በእጃችሁ የምታስገቡ ሊመስላችሁ ይችላል ነገር ግን የመሰላችሁ ሁሉ እውን የማይሆንበት መንገድ ይኖራል። ነገሮችን ለማበላሸት የፈጠኑ እድሜ ዘመናቸውን በፀፀት ውስጥ ይኖራሉ፣ ሰከን ማለትን ያልመረጡ ዘወተር ውስጣቸውን እያሸበሩ ይኖራሉ። የማትቸኩሉት ለራሳችሁ ጥቅም እንጂ ለሌላ ለማንም ብላችሁ አይደለም። የተረጋጋ ህይወት ቁብነገር ይኖረዋል፣ በማስተዋል የተቃኘ ውሳኔ ማንነትን ይገራል፣ ስብዕናን ያስተካክላል። መድረሳችሁ ላይቀር አትጣደፉ፣ ማግኘታችሁ ላይቀር ዛሬ ካልሆነ ብላችሁ እራሳችሁንም ሆነ የሚሰጣችሁን አታስጨንቁ። ነገር ሁሉ ውብ ይሆን ዘንድ ጊዜውን መጠበቅ ይኖርበታል።

አዎ! ችኮላን ቀንሱ፤ እራሳችሁን ገታ ያዝ አድርጉት። ሁሌም በስሜታችሁ መንገድ እየተጓዛችሁ እራሳችሁን አጣብቂኝ ውስጥ አትክተቱ። ጥቂት የማይባል ሰው እንደሚጎዳው የሚያውቀውን ውሳኔ በቶሎ ይወስናል፣ ያሰበበት ለመድረስ ይዋከባል፣ ምኞቱን ከእጁ ለማስገባት በጭንቀት ይዋጣል፣ የፈለገው ነገር በሙሉ በፈለገው ቅፅበት እንዲሆንለት ይመኛል። ነገር ግን ህይወት በዚህ መንገድ ለሚጓዙ ሰዎች የምታድለው ትሩፋትን ሳይሆን ጥፋትን ነው፣ ደስታን ሳይሆን ሃዘንን ነው፣ ውስጣዊ ሰላምን ሳይሆን ጭንቀትን ነው፣ መረጋጋትን ሳይሆን ብክነትን ነው። እንደ ነገ እግዚአብሔር ሊመጣ ብዙ ሰዎች ዛሬ ላይ ሆነው ለመጥፎ ውሳኔ በመቸኮላቸው እራሳቸውን አጥፍተዋል፣ እንደ ነገ ለአመታት የለፉበትን ውጤት ሊያገኙ ብዙዎች ዛሬ አመሻሽ ላይ ተስፋ ቆርጠው ቆመዋል።

አዎ! ጀግናዬ..! በችኮላህ ምክንያት እራስህን ለአደጋ አታጋልጥ፤ ስትጣደፍ የሚገባህን ህይወት አትጣ፤ በስሜታዊነት ለጥፋት አትቸኩል። ህይወትን በእርጋት ውስጥ መኖርን ተለማመድ። አብዝቶ በመጨነቅና በመጣደፍ የሚገኝ ነገር ቢኖር መንገድን መሳትና ለከፋ አደጋ መጋለጥ ብቻ ነው። አንድ ነገር አስተውል፦ ህይወት በጥድፊያ ውስጥ የለችም፣ መኖር ከችኮላ ጋር ምንም ህብረት የለውም። ህይወትን የምትኖረው እያንዳንዱን ቀናት በማጣጣም፣ በእያንዳንዱ ቅፅበት ውስጥም እራስን በማሳለፍ ነው። ማለፍ የሚገባህን የህይወት ምዕራፍ ሳታልፍ የምትደርስበት አስደሳች ውጤት አይኖርም። ከባዱን ጊዜ መቻል ለመልካሙ ጊዜ ስንቅ ነው፤ ነገሮችን ተረጋግቶ ማሳለፍም እንዲሁ የተሻለ ስፍራ ያደርሳል። እራስህን ግዛ፣ ለሁሉም ነገር ትክክለኛውን ጊዜ ጠብቅ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ

በቲክቶክ የማህበራዊ ሚዲያ የሚታወቀው ናፒ አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴን ይቅርታ ጠየቀ********************በቲክቶክ የማህበራዊ ሚዲያ የሚታወቀው ናፒ ሀዋሳ የሚገኘው ኃይሌ ሪዞርትን በ...
03/02/2024

በቲክቶክ የማህበራዊ ሚዲያ የሚታወቀው ናፒ አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴን ይቅርታ ጠየቀ
********************

በቲክቶክ የማህበራዊ ሚዲያ የሚታወቀው ናፒ ሀዋሳ የሚገኘው ኃይሌ ሪዞርትን በተመለከተ ለለቀቀው ቪዲዮ ይቅርታ ጠይቋል።

በቲክቶክ የማህበራዊ ሚዲያ የሚታወቀው ናፒ፤ ሀዋሳ በሚገኘው ኃይሌ ሪዞርት ቀረጻ እንዳያካሂድ መከልከሉን ተከትሎ በለቀቀው ቪዲዮ ብዙዎች ድርጊቱን ተቃውመውታል።

ሀዋሳ የሚገኘው ኃይሌ ሪዞርት ባወጣው መግለጫ፤ የሆቴሉን ደንብ የሚጥስ እና የደንበኞቹን ምቾት የሚነሳ በመሆኑ ቀረጻው እንዳይካሄድ መከልከሉን መግለጹ ይታወሳል።

ቲክቶከሩ ከኢቲቪ ጋር ባደረገው ቆይታ "ታላቁ ኃይሌ ገብረሥላሴ የኢትዮጵያውያን ኩራት ነው" ያለ ሲሆን "በሰራሁት ስራ ክብሩን ዝቅ ካደረኩ ከልቤ ይቅርታ ማለት እፈልጋለሁ" ብሏል።

"ታላቁ ኃይሌን በተግባሬ እና በለቀቅኩት ቪዲዮ ካስከፋሁ፤ ቅር ካሰኘሁ፤ የወንድሜን ክብር ካጎደልኩ፤በጣም ይቅርታ ማለት እፈልጋለሁ" ሲል ገልጿል።

ኃይሌን እንደ አፍሪካዊ ወንድሜ በጣም አከብረዋለሁ ያለው ቲክቶከሩ፤ ትክክለኛው ነገር መደረግ አለበት ብዬ ስለማምን ነው ይቅርታ የምጠይቀው ብሏል።

በኢትዮጵያ ጥሩ ቆይታ እያደረገ እንደሆነ የገለጸው ናፒ፤ በተቻለው አቅም ኢትዮጵያን ከፍ አድርጎ ለማሳየት እንደሚጥርም ተናግሯል።

የታላቋ ንግስት የእቴጌ_ጣይቱ ብርሀን መታሰቢያ ሃውልት በዛሬው ዕለት በደብረ ታቦር ከተማ ተመርቋል!!!
03/02/2024

የታላቋ ንግስት የእቴጌ_ጣይቱ ብርሀን መታሰቢያ ሃውልት በዛሬው ዕለት በደብረ ታቦር ከተማ ተመርቋል!!!

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተራዘመ።የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አንደኛ ልዩ ስብሰባው በአማራ ክልል የታወጀውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት  አራዝሞታል።የአስቸኳይ ጊዜ...
02/02/2024

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተራዘመ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አንደኛ ልዩ ስብሰባው በአማራ ክልል የታወጀውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት አራዝሞታል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በሁለት ተቃውሞ በሶሰት ድምፅ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ነው ለአራት ወራት የተራዘመው።

Address

Debra Markos

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bahir Dar Tube ባህር ዳር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share