Debre Markos city administration health office

Debre Markos city administration health office በዚህ ገፅ ዓለም አቀፋዊ፣ አገራዊ፣ ክልላዊ፣ የከተማውንና የአካባቢውን ወቅታዊ የጤና ጉዳይ መረጃዎችን እናጋራለን።

18/10/2025

የኮሌራ በሽታ መከላከያ መንገዶች:-

ሁልጊዜ ውሃን አፍልቶ እና አቀዝቅዞ መጠጣት ወይም በውሃ ማከሚያ ኬሚካል የታከመ ውሃ መጠቀም፤ ምግብን በሚገባ አብስሎ በትኩስነቱ መመገብ፤የምግብ እቃዎችን በንጹህ ወይም በኬሚካል በታከመ ውሃ ማጠብ እና መጠቀም ፣ መጸዳጃ ቤትን አዘጋጅቶ በአግባቡ መጠቀም፤ እጅን በሚከተሉት ወሳኝ ጊዜያት በንጹህ ውሃና በሳሙና ሳሙና ከሌለ በአመድ በሚገባ መታጠብ

• ከመጸዳጃ ቤት መልስ፣
• ምግብ ከማዘጋጀት በፊት
• ምግብ ከማቅረብ በፊት፣
• ምግብ ከመመገብ በፊት፣
• ሕጻናትን ካጸዳዱ በኃላ፣
• ሕጻናትን ጡት ከማጥባት በፊት ፣
• በበሽታው ለተያዙ ሰዎች እንክብካቤ ካደረጉ በኃላ፣
• በበሽታው የሞቱ ሰዎችን አስክሬን በድንገት ከነኩ፤

• ማንኛውንም ከቤት የሚወጣ ደረቅ ወይም ፈሳሽ ቆሻሻን ውሃንና አካባቢን እንዳይበክል በአግባቡ በተመደበለት ስፍራ ማስወገድ፣
• በኮሌራ በሽታ የታመመን ሰው ልብስ በፈላ ውሃ መቀቀል ወይም በበረኪናና በልብስ ማጽጃ ሳሙና ዘፍዝፎ ማጠብ፣
• በበሽታው የተያዘን ሰው በፍጥነት ወደ ሕክምና ተቋም በመዉሰድ የህክምና እርዳታ እንዲያገኝ ማድረግ ናቸው።

የግልና የአካባቢን ንጽህና በመጠበቅ ዝንቦች እንዳይራቡ ያድርጉ፣ፈሳሽና ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ በተመደበለት ስፍራ ያስወግዱ፤ ሽንት ቤት በመገንባት በአግባቡ ይጠቀሙ እንዲሁም በንጽህና ይያዙ፣ በተቅማጥና ተውከት የተነካካ እቃን፣ ወለልና መሬትን ከማጽዳትዎ በፊት በረኪና በማፍሰስ ብክለትን ይከላከሉ።

የበሽታ ምልክት ሲታይ መከናወን ያለባቸው ተግባራት:-

- በሽታው የሰውነትን ፈሣሽና ጠቃሚ ንጥረ ነገሮችን በብዛት ከሰውነት የሚያስወጣ ስለሆነ የሚከተሉትን እርምጃዎች በፍጥነት በመውሰድ እንዲተኩ ያድርጉ።

- በመጀመሪያ ቤት ውስጥ የሚገኘውን ማንኛውም ንጽህናው የተጠበቀ ፈሣሽ የሚችሉትን ያህል ይጠጡ።

-ህይወት አድን ንጥረ ነገር ወይም ኦ.አር.ኤስ በቤት ውስጥ ካለ አንድ ፓኬት ተፈልቶ በቀዘቀዘ አንድ ሊትር ውሃ በመበጥበጥ ይጠጡ ፤ የተበጠበጠ ኦ.አር.ኤስን መጠቀም የሚቻለው በተበጠበጠ በ24 ሰዓት ውስጥ ነው።

- ኦ.አር.ኤስ በቤት ውስጥ ከሌለ 8 የሻይ ማንኪያ ስኳር እና ግማሽ የሻይ ማንኪያ ጨው በአንድ ሊትር ንጹህ ውሃ በመበጥበጥ ባስቀመጥዎ ቁጥር ይጠጡ።

#አብክመጤናቢሮ

18/10/2025

በኢትዮጵያ ብሎም በክልላችን የክረምት ወቅት ማለፋን ተከትሎ የወባ ወረርሽኝ በስፋት ሊከሰት ይችላል

‎የወባ በሽታ በትንኝ አማካኝነት ከታመመ ሰው ወደ ጤነኛው የሚተላለፍ በዋነኛነት በትኩሳት የሚገለጥ ተወሳስቦ ለከፍተኛ አደጋ ሊዳርግ የሚችል በሽታ ነው፡፡

‎በሽታው በዓለም ላይ የበርካቶችን ህይወት የቀጠፈና በትንኝ አማካኝትት የሚከሰት ተላላፊ በሽታ እንደሆነም ይነገራል፡፡

‎ በተለይ በኢትዮጵያ ፕላዝሞዴም ፋሲፋረም በተለምዶ ቢጫ ወባ የሚባለውን እና አንድ ሶስተኛው ደግሞ ቫይቫክስ በተባለ ተህዋስ ዝርያ የሚከሰት ነው።

‎ወንድ እና ሴቴ ተህዋስ በወባ ውስጥ አንድ ሳምንት ያድግና ትንኟ ለመራባት የሰው ደም የሚያስፈልጋት በመሆኑ በዚህ ሁኔታ ሰውን በምትነክስበት ጊዜ በሽታውን ታስተላልፋለች፡፡

‎ትንኟ ለመራባት ቆላማ አካባቢ በመምረጥ ከባህር ጠለል በላይ ከ1ሺህ 400 ሜትር በታች በሆኑ አካባቢዎች ላይ እንደምትገኝና ከዛ በላይ ባለ ከፍታ የመራባት ምጣኔዋ እንደሚቀንስ ይገለፃል፡፡

‎በሽታው ከዚህ በፊት ለተያዘ ሰው እንዲሁም በተለይ በነፍሰ ጡር እናቶች እና ህፃናት ላይ የመከላከል አቅማቸው አናሳ በመሆኑ የከፋ ጉዳት ያደርሳል፡፡

‎በአብዛኛው የክረምት ወቅት አልፎ የበጋ ወቅት ሲጀምር ውሀዎች ሙሉ ለሙሉ ስለማይደርቁ እና የታቆሩ ውሀዎች ስለሚኖሩ እንዲሁም በትንንሽም ውሀዎች የመራባት እድል ስለሚኖር ለትንኞች መራባት አመቺ ይሆናል፡፡

‎የወባን በሽታን ለመከላከል ትንኟ የምትራባባቸውን ቦታዎች ማጽዳት ያስፈልጋል ያቆሩ ውሀዎችና የቆሸሹ ነገሮችን ማስወገድም ይገባል፡፡

‎ጸረ-ትንኝ ኬሚካሎች በሚረጩበት ጊዜ ቀለም መቀባት፣ ማጠብ እንደማይገባ እንዲሁም በጸረ ትንኝ የተነከረ አጎበር መጠቀም እንደሚገባ የህክምና ባለሙያዎች ይመክራሉ፡፡


‎ #አብክመጤናቢሮ

የአምቡላንስ ሹፌሩ አስቸጋሪ ገጠመኝ
18/10/2025

የአምቡላንስ ሹፌሩ አስቸጋሪ ገጠመኝ

18/10/2025
የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ እድሳት እስከ ጥቅምት 30, 2018ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን የጤና ሚኒስተር አሳውቋል። የአማራ ክልል እና ሌሎች የክልል ጤና ቢሮዎችም በተዋረድ ለአንድ ወር ማራዘ...
09/10/2025

የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ እድሳት እስከ ጥቅምት 30, 2018ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን የጤና ሚኒስተር አሳውቋል። የአማራ ክልል እና ሌሎች የክልል ጤና ቢሮዎችም በተዋረድ ለአንድ ወር ማራዘማቸውን አሳውቀዋል።

የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በ2018 በጀት አመት ለ1350 ዲፕሎማ የጤና ባለሙያዎች ዲግሪያቸውን እንዲማሩ መፍቀዱን ለጤና ቢሮው በፃፈው ደበዳቤ አሳውቋል!
09/10/2025

የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በ2018 በጀት አመት ለ1350 ዲፕሎማ የጤና ባለሙያዎች ዲግሪያቸውን እንዲማሩ መፍቀዱን ለጤና ቢሮው በፃፈው ደበዳቤ አሳውቋል!

08/10/2025

“ህጻናትን የፖሊዮ ክትባት በማስከተብ ከልጅነት ልምሻ በሽታ እንከላከል!”

የልጅነት ልምሻ (ፖሊዮ) በሽታ ሕፃናትን ለሕመምና ለዘላቂ የአካል ጉዳት ከሚዳርጉ በሽታዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ በሽታው የህፃናትን አካል በተለይም የእጅና የእግርን ጡንቻ የሚያዳክምና የሚያልፈሰፍስ ብሎም ለሞት የሚዳርግ ተላላፊ በሽታ ነው፡፡

አብዛኛውን ጊዜ በሽታው መለያ ምልክቶችን የማያሳይ በመሆኑ በቀላሉ ለመረዳት አዳጋች ያደርገዋል፣ በሽታው በማንኛውም የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝን ሰው የሚያጠቃ ቢሆንም አብዛኛውን ጊዜ ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናት ተጋላጭ ናቸው፡፡ በሽታውን መከላከል የሚቻለውም ሕፃናት ከተወለዱበት ጊዜ ጀምሮ መደበኛና ተጨማሪ ክትባቶችን በዘመቻ መልክ በመስጠት ነው፡፡

በአማራ ክልል በዚህ ዓመት በጎንደር ከተማ እና በደቡብ ጎንደር ዞን አስተዳደር ሁለት ሰዎች ላይ በሽታው ተከስቷል፡፡ በመሆኑም የበሽታውን ስርጭት ለመግታት ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በሰሜን ጎጃም፣ ምስራቅ ጎጃም፣ ደቡብ ጎንደር እና ማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደሮች፣ በጎንደር፣ ደብረ ታቦር፣ ደብረ ማርቆስ እና ባሕር ዳር ከተማ አስተዳደሮች ክትባቱ ይሰጣል፡፡ በዘመቻው ከ3 ነጥብ አምስት ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ህፃናት ይከተባሉ፡፡ ክትባቱ ቤት ለቤት፣ በመጠለያ ጣቢያና በትምህርት ቤቶች ይሰጣል፡፡

በመሆኑም እድሜአቸው ከ1ዐ ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት ከዚህ በፊት የፖሊዮ ክትባት ቢከተቡም ባይከተቡም ወላጆችና አሳዳጊዎች ልጆቻችሁን እንድታስከትቡ እያሳሰብን፤ የሐይማትኖ አባቶች፣ መምህራኖች እና በየደረጃው የሚገኙ የህብረተሰቡ ክፍሎች ለዘመቻው ውጤታማነት የበኩላችሁን አስተዋፅዖ እንድታበረክቱ እናሳስባለን፡፡

“ህጻናትን የፖሊዮ ክትባት በማስከተብ የልጅነት ልምሻ በሽታን እንከላከል!”

08/10/2025
04/10/2025

Malaria is resurging — and Africa is bearing the brunt.

In 2023, there were an estimated 263 million new malaria cases globally and nearly 597,000 deaths, with Africa accounting for the vast majority of that burden.

We are also witnessing new outbreaks in parts of Southern Africa.

Africa CDC calls for urgent action to:
✅Strengthen surveillance and genomic research
✅Ensure equitable rollout of malaria vaccines
✅Invest in proven prevention tools
✅Secure sustainable, Africa-led financing.

In our BMJ piece, we outline a critical roadmap: Africa must reclaim the fight against malaria by reinforcing surveillance, advancing vaccine equity, scaling prevention, and boosting domestic investment.

Read more: https://ow.ly/8rwR50WWEH9

04/10/2025
02/10/2025

Address

Ethiopia, Amhara Region
Debra Markos

Telephone

+251587711940

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Markos city administration health office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Debre Markos city administration health office:

Share