Debre Markos city administration health office

Debre Markos city administration health office በዚህ ገፅ ዓለም አቀፋዊ፣ አገራዊ፣ ክልላዊ፣ የከተማውንና የአካባቢውን ወቅታዊ የጤና ጉዳይ መረጃዎችን እናጋራለን።

Amhara Region State University Calls an Educational Announcement!
10/12/2025

Amhara Region State University Calls an Educational Announcement!

10/12/2025

🔹 Right to life 🔹 Freedom 🔹 Justice

Human rights belong to all of us. They are non-negotiable.

We all have a role to play in upholding them for every human being.

Wednesday is Human Rights Day.

– via United Nations Human Rights

የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል የሚያስችል የሙከራ ክትባት መስጠት መጀመሩ ተገለፀ::የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ለመከላከል የሚያስችል ክትባት በደቡብ ኢትዮጵያ እና ሲዳማ ክልል በተመረጡ ...
09/12/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል የሚያስችል የሙከራ ክትባት መስጠት መጀመሩ ተገለፀ::

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ለመከላከል የሚያስችል ክትባት በደቡብ ኢትዮጵያ እና ሲዳማ ክልል በተመረጡ አከባቢዎች ለፈቃደኛ ተሳታፊዎች መስጠት ተጀምሯል።

ክትባቱ በዓለም ዙሪያ በተደረጉ ቅድመ ጥናቶች ደህንነቱ የተረጋገጠ ሲሆን፣ ከአንድ አመት በፊትም በሩዋንዳ በተከሰተው ተመሳሳይ የማርበርግ በሽታ ጥቅም ላይ ዉሎ በሽታውን ለመከላከል ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን አሳይቷል፡፡

ክትባቱ በቅድሚያ ተጋላጭ ለሆኑ ጤና ባለሙያዎች እንዲሁም በቫይረሱ ተይዘው ከነበሩ ሰዎች ጋር ግንኙነት ለነበራቸው በፈቃደኝነት የሚሰጥ ሲሆን ሂደቱም በዓለም ጤና ድርጅት እና በኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት ባለስልጣን መመሪያዎች መሰረት ደረጃውን ጠብቆ ይከናወናል፡፡
ምንጭ ፡- ጤና ሚኒስቴር

ዓለም አቀፍ ከመውለጃ ቀናቸው ቀድመው ለሚወለዱ ህጻናት እና የሳንባ ምች በሽታ መታሰቢያ ወር ህዳር 2018 ዓ.ምAmhara Health Bureau - አብክመ ጤና ቢሮ  የተወሰደ
08/12/2025

ዓለም አቀፍ ከመውለጃ ቀናቸው ቀድመው ለሚወለዱ ህጻናት እና የሳንባ ምች በሽታ መታሰቢያ ወር ህዳር 2018 ዓ.ም
Amhara Health Bureau - አብክመ ጤና ቢሮ የተወሰደ

አራተኛው ዙር የፖሊዮ ክትባት በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በዘመቻ ከታህሳስ 3 - 6/2018ዓ.ም ሊሰጥ ስለመሆኑ ተገለፀ።*********************************ህዳር 27/...
06/12/2025

አራተኛው ዙር የፖሊዮ ክትባት በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በዘመቻ ከታህሳስ 3 - 6/2018ዓ.ም ሊሰጥ ስለመሆኑ ተገለፀ።
*********************************

ህዳር 27/2018ዓ.ም (ደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ):

በሀገር አቀፍ ደረጃ በተመረጡ ክልሎችና ዞኖች ለሚሰጠው የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የንቅናቄ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ፈፃሚ አካላት በተገኙበት በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳድር እየተካሄደ ነው።

ለፈፃሚ አካላት የጤና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን በዩኒሴፍ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳድር የክትባት አስተባባሪ አምሳያ ጥላሁን እየሰጡ ነው።

በሶስተኛው ዙር ክትባት የወሰዱ ሁሉም ከ10 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት nOPV2 እና bOPV ክትባትን ይወስዳሉ ሲሉ አቶ አምሳያ ገልፀዋል።

በዘመቻውም ከሶስተኛው ዙር በኋላ የተወለዱ ህፃናት እንዲከተቡ ይደረጋል ብለዋል።

አራተኛው ዙር የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተመረጡ ክልሎች፣ ዞኖችና ከተማ አስተዳድሮች የሚሰጥ ሲሆን ክትባቱ የሚሰጠው የፖሊዮ በሽታን ለመከላከልና እንደ ሀገር የታቀደውን በሽታውን የማጥፋት እቅድ ለማሳካት ስለመሆኑ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳድር ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሀብቴ ወርቁ ገልፀዋል።

በክትባት ዘመቻው እስከ 10 ዓመት ያሉ 66,555 ህፃናትን ተደራሽ ለማድረግ ከታህሳስ 3 - 6/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 4 ቀናት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የባለፈውን አደረጃጀትና አሰራርን ተከትሎ ስራውን በውጤታማነት መፈፀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የክትባት ዘመቻው በዋናነት የሚሰጠው ቤት ለቤት ስለሆነ ሁሉንም ቤቶች ተደራሽ ማድረግና ሌሎች ቤት ለቤት የሚሰሩ የጤና ስራዎችን አብረው የሚፈፀሙ ስለሆነ ማህበረሰቡ ልጆቹን ከማስከተብ ጀምሮ ተባባሪ እንዲሆን አቶ ሀብቴ አሳስበዋል።

በንቅናቄ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ጤና ኤክስቴንሽ፣ የጤና ጣቢያ ፣ የጤና መምሪያ ባለሙያዎችና ሃላፊዎች እንዲሁም በጤናው ዘርፍ የሚሰሩ ድርጅቶች የስራ ሃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ ።

ከደብረ ማርቆስ ከቸማ ኮሙኒኬሽን ፌስቡክ ገፅ የተወሰደ

አሜሪካ ለማርበርግ ቫይረስ የሙከራ ክትባት ድጋፍ ማድረጓን ጤና ሚኒስተር አሳወቀ።*************************የማርበርግ ቫይረስ ምላሽ ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፍ 2 ሺ ...
05/12/2025

አሜሪካ ለማርበርግ ቫይረስ የሙከራ ክትባት ድጋፍ ማድረጓን ጤና ሚኒስተር አሳወቀ።
*************************

የማርበርግ ቫይረስ ምላሽ ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፍ 2 ሺ 500 የማርበርግ ቫይረስ የሙከራ ክትባት ከአሜሪካ መንግስት በድጋፍ የተገኘ ሲሆን፤ ክትባቱን ለኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት የአሜሪካ በኢትዮጵያ አምባሳደር አርቪን ማሲንጋ አስረክበዋል።

ክትባቱ በአርማወር ሃንሰን የምርምር ተቋም በሚመራ ፈጣን የደረጃ 2 ክሊኒካዊ ሙከራ ተደርጎለት ጥቅም ላይ እንደሚውል የገለጹት ክትባቱን የተረከቡት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሲሆኑ፣ የምርመራ ተቋሙ ከኢትዮጵያ የምግብ እና የመድኃኒት ባለስልጣን ጋር በመተባበር ቁጥጥር እንደሚያደርግም አክለዋል። ክትባቱን ከህዳር 29 ቀን ጀምሮ መስጠት የሚጀመር ሲሆን የጤና ባለሙያዎችን እና ከፍተኛ ተጋላጭ ለሆኑ ቡድኖች ቅድሚያ ይሰጣል ብለዋል።

ዩናይትድ ስቴትስ በባርዳ እና በሳቢን የክትባት ተቋም በኩል ክትባቱን ተደራሽ ማድረጉን የገለጹት አምባሳደር ማሲንጋ፤ የማርበርግ ወረርሽኝ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ ጠንካራ አጋር መሆኗን ማረጋገጧን ተናግረዋል።

ጤና ሚኒስቴር ወርሽኙን ለመግታት ከሚመለከታችዉ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሚላሽ አሰጣጡን አጠናክረዉ የቀጠሉ ሲሆን የቅኝትና ቁጥጥር ስራዉን ማጠናከር፣ የጤና ባለሙያዉንና ጤና ሰራተኞች ጨምሮ ተጋላጭ የሆኑትን በመጠበቅ ላይ ትኩረት በማድረግ የመከላከል ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ዶ/ር መቅደስ ተናግረዋል።

(ጤና ሚኒስቴር)

04/12/2025
04/12/2025
"ተግዳሮቶችን በመቋቋም የኤች አይ ቪ /ኤድስ  ምላሽን በዘላቂነት እናረጋግጥ"!! በሚል መሪ ሀሳብ  በደብረ ማርቆስ  ከተማ አስተዳደር የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን በፓናል ውይይት ተከበረ።***...
03/12/2025

"ተግዳሮቶችን በመቋቋም የኤች አይ ቪ /ኤድስ ምላሽን በዘላቂነት እናረጋግጥ"!! በሚል መሪ ሀሳብ በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን በፓናል ውይይት ተከበረ።
*****************
ህዳር 24/2018ዓ.ም (የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ):

በአለም ለ38ኛ በሀገራችን ደግምለ37ኛ ጊዜ የሚከበረው የአለም የኤድስ ቀን ከልዩ ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር በተለያዩ ዝግጅቶች በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳድር ተከብሯል።

በእለቱ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደረ ምክትል ከንቲባ ስለሽ ተመስገን የዛሬውን እለት ስናስብ በኤች አይቪ ከኤድስ ህይወታቸውን በሞት ያጡትን የምናስታውስበት ቫይረሱ በደማቸው ያለባቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች የምንረዲበት ሊሆን ይገባል ብለዋል።
በአለማች ከ40 ሚልዮን በላይ ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ መሆኑን ያነሱት ምክትል ከንቲባው በዚህም አምራች የሆነው ወጣቱ ክፍል እና ሴቶች የበለጠ ተጋላጭ ሁነዋል ብለዋል። እንደ ሀገር መንግስት የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራቱ የቫይረሱ ስርጭት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መጧል። ይሁን እንጅ በክልላችን የተከሰተው የርስ በርስ ግጭቱ ችግሩን የበለጠ እንዲስፋፋ እድል የሚፈጥር ስለሆነ በልዩ ትኩረት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በሽታውን ለመቆጣጠር የህክምና አገልግሎትን ማዘመን ፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተግባራትን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ሲሉም ምክትል ከንቲባው አስገንዝበዋል።

በውይይቱ የመነሻ ሀሳብ ጽሁፍ ያቀረቡት የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳድር ጤና መምሪያ የኤች አይቪ ኤድስ ዘርፈ ብዙዎች ምላሽ እቅድ ክትትል ባለሙያ አቶ ደርበዉ አውደውም እየተዘነጋ የመጣው የኤች አይቪ ኤድስ ስርጭት በከፍተኛ ደረጃ አሁንም የሚያዙና የሚሞቱ የማህበረሰብ ክፍሎች በርካታ መሆናቸውን ገልፀዋል።

አሁንም ማግልና መድሎ መኖር እንዲሁም የተለያዩ የውጭ ድርጅቶች ከሀገር መውጣታቸውና የግንዛቤ ፈጠራ አናሳ መሆኑ በሽታው እየተዘነጋ መሆኑን የበዓሉ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

ኤች አይቪ ኤድስ ዘርፈ ብዙ ምላሽ ያስፈልገዋል ያሉት የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የኤች አይ ቪ ኤድስ ዘርፈ ብዙ ምላሽ ብድን መሪ አቶ ሃይለሚካኤል ፀጋዬ ስርጭቱን ለመቀነስ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።

ስርጭቱን ለመቀነስ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ሊሰራ ይገባል ሲሉም አቶ ሃይለሚካኤል አሳስበዋል።

መረጃዉ የደብረ ማርቆስ ኮሚኒኬሽን ነዉ

03/12/2025

Early HIV diagnosis and testing are important to:
✅start treatment and care if needed
✅reduce infections
✅reduce AIDS-related deaths

በአማራ ክልል ህፃናት እንደ ተወለዱ የሚሰጥ የጉበት (ሄፓታይተስ - ቢ ) በሽታ መከለከያ ክትባት መስጠት መጀመሩን ጤና ቢሮው አሳወቀ::===========================‎‎የአብክመ...
03/12/2025

በአማራ ክልል ህፃናት እንደ ተወለዱ የሚሰጥ የጉበት (ሄፓታይተስ - ቢ ) በሽታ መከለከያ ክትባት መስጠት መጀመሩን ጤና ቢሮው አሳወቀ::
===========================

‎የአብክመ ጤና ቢሮ ህጻናት እንደተወለዱ የሚሰጠውን የጉበት በሽታ (ሄፓታይተስ - ቢ ) መከላከያ ክትባት ክልላዊ የማስጀመሪያ መርሀ- ግብር በባህር ዳር ጤና ጣቢያ አስጀመረ ።

‎በማስጀመሪያ መርሀ -ግብሩ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአብክመ ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ አበበ ተምትሜ እንደ ሀገር ብሎም እንደ ክልል የጉበት ቫይረስ በሽታ ስርጭትን ለመቀነስ እንዲሁም ለማጥፋት እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል ያሉ ሲሆን ለዚህም የጉበት በሽታ መከላከያ ክትባት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

‎ሀላፊው አክለውም ሁሉም ጤና ተቋማት በመደበኛ የክትባት ፕሮግራም የሚሰጠውን የጉበት በሽታ ክትባት አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበው የተወለዱ ህፃናት በ24 ሠአት ውስጥ እንዲከተቡ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

‎በክትባት ላይ የሚደረግ ርብርብ ውጤታማ እንደሆነ ያነሱት ሀላፊው በጤና ተቋሞቻችን የጉበት በሽታ የስርጭት ደረጃው ከፍተኛ የታማሚ ሽፋን የያዘ መሆኑን ጠቁመው ታክሞ መዳንም ፈተና ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በክትባት መከላከሉ አማራጭ የሌለው አጋጣሚ ነው ብለዋል።

‎በዚህ ላይ ተሳትፎ ያደረጉ አጋር አካላትንና ክትባትን ባህል ያደረጉ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማመስገን ተሳትፏቸው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀው ለህፃናት ከሚሰጡ 15 የክትባት አይነቶች ይሄ አንዱ እንደሆነና በክልሉ ከ 7 መቶ ሺህ በላይ ህፃናት የዚህ ክትባት ተቋዳሽ እንደሚሆኑ ገልፀዋል።

‎ኢትዮጵያ የጉበት በሽታ መከላከያ ክትባት ማስጀመሯ ትልቅ ስኬት ነው ያሉት አቶ አበበ በሽታውን ለመከላከል ብቻ ሳይሆን ለመጪው ትውልድ ማሻገር የሚያስችል ጤና መሠረት ለመጣል በቅንጅት መስራት ይገባል ብለዋል።

‎በተጨማሪም ህጻናት እንደተወለዱ ወዲያውኑ የጉበት በሽታ መከላከያ ክትባቱን ቢከተቡና በተከታታይ መደበኛ ክትባቱን ቢወስዱ በከፍተኛ ደረጃ ከበሽታው ስለሚጠበቁ ክትባቱ በአማራ ክልል በሁሉም ጤና ተቋማት በነጻ የሚሰጥ በመሆኑ ወላጆች ተረድተው ልጆቻቸውን እንዲያስከትቡ መልዕክት አስተላልፈው ክትባቱ በይፋ መጀመሩን አብስረዋል።

‎የቢሮው የክትባት ቴክኒካል አማካሪ አቶ ወርቅነህ ማሞ በሀገር ደረጃ በሁሉም ክልሎች የጉበት በሽታ መከላከያ ክትባት ህፃናት እንደተወለዱ የሚሰጠው በሽታው ካለባት እናት ወደ ልጅ በደም ንክኪና በተለያየ መንገድ የመተላለፍ አቅሙ 90 ፐርሰንት አንደሆነና ሀፃናት የዚህ በሽታ ሰለባ እንዳይሆኑ ለማድረግ ነው ብለዋል ።

‎አክለውም እንደሀገር አቀፍ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት ሰባት ፐርሰንቱ የማህበረሰብ ክፍል የጉበት በሽታ ተጋላጭ እንደሆኑና 5 ፐርሰንት የሚሆኑት ነፍሰጡር እናቶች የዚህ በሽታ ተጋላጭ ናቸው ብለዋል።

‎ገና የተወለደ ህፃን ሲያስከትቡ ያገኘናቸው የባህር ዳር ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ አዲሱ ንብረት የአምስት ልጆች አባት እንደሆኑና የጉበት በሽታ ክትባት ገና እንደተወለደ ያገኘው ይሄኛው ልጅ ብቻ ነው በማለት እድለኛ መሆኑን ገልፀው ክትባቱ አዲስ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር ይገባል ብለዋል።

‎ክትባቱ በሁሉም የመንግስት ጤና ተቋማት እና በተወሰኑ የግል ጤና ተቋማት ውስጥ ይሰጣል!

‎የሀይማኖት አባቶች ፣ አጋር አካላት ፣ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የጤና ጣቢያው ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳታፊ ነበሩ።

03/12/2025

An estimated 1.3 billion people live with a significant disability today.

No one understands the needs of persons with disabilities better than they do themselves. To achieve a more inclusive and accessible world, people with disabilities must have a seat at decision-making tables.

Wednesday is the International Day of Persons with Disabilities. https://www.un.org/en/observances/day-of-persons-with-disabilities

Address

Ethiopia, Amhara Region
Debra Markos

Telephone

+251587711940

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Markos city administration health office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Debre Markos city administration health office:

Share