መረጃ ከነምንጩ - ምጥን

መረጃ ከነምንጩ  - ምጥን በአሳማኝ ምንጭ ላይ የተመረኮዙ ወቅታዊ ሁነቶችን በአጭር እና

• የንጸሐን ጭፍጨፋ በብራቃት። "…ዐማራው ወገናቸውን ይወጉ ዘንድ ወደ ዘመቻ የገቡት የዐማራ አድማ ብተናውና በኦሮሙማው መካከል ግጭት ተፈጥሮ ትናንት መጋቢት 22/2017 ዓም ከተዋጉ በኋላ ...
01/04/2025

• የንጸሐን ጭፍጨፋ በብራቃት።

"…ዐማራው ወገናቸውን ይወጉ ዘንድ ወደ ዘመቻ የገቡት የዐማራ አድማ ብተናውና በኦሮሙማው መካከል ግጭት ተፈጥሮ ትናንት መጋቢት 22/2017 ዓም ከተዋጉ በኋላ በንዴት የጦፈው መከላከያ በጎጃም ክፍለ ሀገር ሰሜን ሜጫ ወረዳ ብራቃት ከተማና በዙሪያዋ ወደሚገኙ ቀበሌዎች በመግባት በመንገድም፣ በቤትና በእርሻ ላይ ያገኛቸውን የሃይማኖት አባቶችን፣ ሴቶች እና ሕፃናትን፣ አረጋውያንና ገበሬዎችን ሳይቀር ቤት ለቤት እየዞረ ለጊዜው የታወቁ በስምም የተለዩ 46 ንጹሐን የጎጃም ዐማሮችን መጨፍጨፉ ተሰምቷል።

🎯 የአደጋ ጊዜ ደወል 🎯 🔊"…በእምነት ሰበብ ደም ለማፋሰስ አገዛዙ ዝግጅቱን አጧጡፎ ቀጥሏል። ሰሞኑን ከክልል የመጡ ባለሥልጣናት፣ አንድ ጄነራል ጭምር የተሳተፉበት እስላሞች ብቻ የተጠሩበት ...
27/03/2025

🎯 የአደጋ ጊዜ ደወል 🎯 🔊
"…በእምነት ሰበብ ደም ለማፋሰስ አገዛዙ ዝግጅቱን አጧጡፎ ቀጥሏል። ሰሞኑን ከክልል የመጡ ባለሥልጣናት፣ አንድ ጄነራል ጭምር የተሳተፉበት እስላሞች ብቻ የተጠሩበት ምሥጢራዊ ስብሰባ በአጣዬ፣ በከሚሴ፣ በኮምቦልቻ እና በደሴ ከተሞች ጭምር ተደርጓል። ባለሥልጣናቱ በቀጥታ ለእስላሞቹ ያሏቸው "ከዚህ ዘመን የተሻለ ጊዜ አታገኙም፣ ዘመኑ የተመቸ ነው። ፋኖውም እንደምታዩት ከፋፍለነዋል። በአንድነት መቆም አይችልም። እናም እስከ ኢድ በአል ድረስ የዐማሮቹን፣ የካፊሮቹን ንብረቶቻቸውን ውረሱ፣ ዝረፉ፣ ቀሙ፣ ከብቶቻቸውን ንዱ። በመሬታቸው ላይም ስፈሩ።

"…አትፍዘዙ፣ ፌደራሉንም፣ ክልሉንም መጠየቅ በማይችሉ በራሳችን ሰዎች ተክተን ጨርሰናል። በምንም በምንም ብላችሁ ባለ በሌለ ኃይላችሁ ዝረፉ፣ ፍጠኑ፣ ፍጠኑ ተብለዋል። በስብሰባው መድረክ ላይ እጅ አውጥቶ በድፍረት የተናገረ እስላም ባይኖርም ግን ከስብሰባው ውጪ ሰለምቴዎቹ፣ ነፍስ ያላቸው እስላሞች ይሄ ነገር እንዴት ይሆናል? በማለት ገሚሱ ይሄን ከማይ ብሰደድ እመርጣለሁ በማለት የከሚሴ፣ የአጣዬ እስላሞች ወደ ደሴ፣ ወደ አዲስ አበባ መሸሽ ጀምረዋል። ሕዝቡ እንዲጠነቀቅ ንገር ተብያለሁ። ይኸው ነግሬአለሁ።

"…በአቶ ጋንፉር በኩል የኮንፈል አገውንና የጎንደር ዐማራን ለማፋጀት በጎንደር ቋራ የተዘጋጀውንም የሞት ድግስ ቆይተህ ልቀቅ ብላለች ርግቤ ቆይቼ ወይ ነገ እለቀዋለሁ።
• እየጸለያችሁ፣ እየተጠነቀቃችሁም ይሁን። ይላል ዘመዳችን 🎯

🎯 ከባድ ማስጠንቀቂያ 🎯"…በሁሉም መስክ የከሸፈው፣ በነገሮች ሁሉ የደነበረው፣ የደነቦሸውም አገዛዝ በቅርብ ቀናት ውስጥ አዲስ አበባን ጨምሮ በተመረጡ የኦሮሚያ ከተሞች ውስጥ ከቁጥጥር ውጪ የ...
27/03/2025

🎯 ከባድ ማስጠንቀቂያ 🎯
"…በሁሉም መስክ የከሸፈው፣ በነገሮች ሁሉ የደነበረው፣ የደነቦሸውም አገዛዝ በቅርብ ቀናት ውስጥ አዲስ አበባን ጨምሮ በተመረጡ የኦሮሚያ ከተሞች ውስጥ ከቁጥጥር ውጪ የማይወጣና ኢላማ የተደረጉ ግለሰቦችን እና ተቋማትን ብቻ አጥቅቶና አውድሞ የሚቆም የእርስ በእርስ ግጭት እና ፍጅት ለማስነሣት ሰውየው ለመረጃ ሰዎቹ ትእዛዝ ሰጥቷል። እናም ዘመዴ ኅብረተሰቡ ከወዲሁ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ንገር ነው የምትለው ርግቤ። • ጥንቃቄ አይለያችሁ። ይላል ዘመዳችን 🎯

19/08/2024

በአምስት ግንባሮች ድልን የተቀዳጀው የአማራ ፋኖ በጎንደር እና ጎንደር ዕዝ ዕለታዊ የግንባር ጥቅል መረጃዎች፤

የአማራ ፋኖ በጎንደር ከሀምሌ ወር መገባደጃ ጀምሮ በአብይ አህመድ አራዊት ሰራዊት ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት በመሰንዘር ሰራዊቱን በማፈራረስ ላይ ይገኛል:: ተጋድሎው ዛሬም ቀጥሎ በአምስት ግንባሮች አስደናቂ የጦር ሜዳ ጀብዱ ተፈፅሟል::

በዚህም መሰረት፥

በበለሳ ግንባር:-

በበለሳ የሚገኘው ንስር በለሳ ቅጣው እጅጉ ክፍለጦር፥ ኪንፋዝ በገላ ብርጌድ፥ ኪንፋዝ በለሳ ወረዳ፥ ስላሌ ከተማ የመሸገውን ጦር ለመተካት 5 ኦራል መኪና በመንቀሳቀስ ላይ ሳለ ጭቅቄ ላይ ጠብቀው በአርበኛ ሳለ አምላክ በመመራት ሁለቱን ኦራል ጦር ሙሉ በሙሉ ሲደመስሱት ቀሪውም ተበታትኖ እግሬ አውጭኝ ብሎ ወደመጣበት ፈርጥጧል።

በሐሙሲት ግንባር:-

ሐሙሲት ከተማ ላይ የተወሸቀው የአብይ አህመድ አራዊት ሰራዊት በተሰነዘረበት የተቀናጀ ጥቃት ተሰንዝሮበት ሙት እና ቁስለኛ በመሆን የተረፈው ወደ ኅሀላ ከተማ ፈርጥጦ ሲገባ የአማራ ፋኖ በጎንደር ጀግኖች እግር በእግር ተከታትለው፥ ጎሀላ ከተማ ላይ ለሊቱን ሲቀጠቅጡት አድረው ዛሬ ጎሀላ ከተማን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥረዋታል።

በታች አርማጭሆ ግንባር:-

በታች አርማጭሆ ሳንጃ ወረዳ ድጋው ቀበሌ ላይ የአማራ ፋኖ በጎንደር ሀይሌ ማሞ ብርጌድ እና የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ደጀንና ዋግሹም ብርጌዶች በሰሩት የጋራ ኦፕሬሽን፥ ኮልሎኔል አፍሪካ በሚባል ከፍተኛ የስርአቱ መኮንን የሚመራው ግትልትል ጨፍጫፊና ሌባ ሰራዊት፥ ሙሉ ለሙሉ ተደምስሶ ወታደራዊ አዛዡ ፈርጥጦ አምልጧል። በዚህ አውደ ግንባርም ሶስት ዲሽቃና በርካታ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያወች ተማርከዋል። ምአሰሮ ደንብ ከተማንም ነፃ ማውጣት ተችሏል።

በሶረቃ ግንባር:-

የአማራ ፋኖ በጎንደር ተከዜ ክፍለ ጦር ነፃነት ብርጌድ እንዲሁም፥ የአማራ ፋኖ በጎንደር ዘርአይ ክፍለ ጦር፥ ሳተናው በየነ ተስፉ ብርጌድ እንዲሁም የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ጎቤ ክፍለ ጦር፥ ጠራ ብርግልድ በቅንጅት የስርአቱን ጥምር ጦር አፈራርሰው ጊዜያዊ ካምፑን ጭምር በመቆጣጠር ሶሮቃ ከተማን እጅ ለማስገባት ተችሏል።

06/07/2024

ሰበር..‼️ ሰኔ 29, 2016 ዓ.ም

መሃል ሳይንት📌

የአማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ አትሮንስ ብርጌድ አሁን በዚህ ስዓት ከአገዛዙ አራዊት ሰራዊት ጋር እየተፋለመ ይገኛል። የሚመራው አትሮንስ ብርጌድ የአብይን ስልጣን አስጠባቂ አላማ የለሽ ቡድን እየቀጠቀጠ መሆኑ ተረጋግጧል። የጀግኖችን ክንድ መቋቋም ያልቻለው ሰው በላው አራዊት ወደ ከተማ እግሬ አውጭኝ እያለ ፍርጣጣ ጀምሯል ሲሉ አክለው ገልፀዋል!!

💪

30/06/2024

ቅምሻ ምጥን መረጃ ፦ የሰኔ 23/2016 ዓ.ም

1) ደራ (ሸዋ) በመራቤቴ አጎራባች ቀበሌዎች በሚገኙ ወታደራዊ ጣቢያዎች በተፈፀመ ድንገተኛ ጥቃት ከፍተኛ ሰብዓዊ ጉዳት ደረሰ። ሰኔ 23/2016 ማለዳ በተመሳሳይ ሰዓት በሬሳ፣ራቼ፣ ቱሉ፣ ባቦ በተባሉ ቦታዎች ነው ጥቃት የተፈጸመው ሲሉ ምንጮች ገልፀዋል።

2) በምንጃር ቀጠና በረኸት ወረዳ ማለዳ ጀምሮ ከባድ ውጊያ እየተደረገ ነው የሚሉት የመረጃ ምንጮች ውጊያው የተጀመረው አክርሚት በተባለ ቦታ ወታደራዊ ጣቢያ ላይ የፋኖ ኃይሎች ጥቃት ማድረሳቸውን ተከትሎ ነው። በጥቃቱ በመንግሥት ኃይሎች ላይ በውል ያልታወቀ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ደርሷል ብለዋል።

3) ሊቦ ከምከም(ዐዲስ ዘመን )

የመንግሥት ኃይል ከአዲስዘመን ተነስቶ ወደ እብናት በሚያቀናበት ሰዓት ቅራረኝ ወንዝ ድልድይ ላይ የደፈጣ ጥቃት ተፈጽሞ ሰብዓዊ ጉዳት ደርሷል። በጥቃቱ አምስት የመንግስት ወታደሮች ሲሞቱ ፤ 22 እና አንድ መቶ አለቃ አዛዥ በፋኖ እጅ ይገኛሉ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሣሪያዎች በፋኖ ተወስዷል ተብሏል።

4) በሰሜን እና በደቡብ ወሎ የተለያዩ ቦታዎች የከባድ መሣሪያ ድብደባ እንደቀጠለ ነው ተባለ። በሰሜን ወሎ ውርጌሣ ከተማ አቅራቢያ ጊራና ሸለቆ በከባድ መሣሪያ የታገዘ ውጊያው መደረጉ ሲሰማ ከውጫሌ ከተማ ጀምሮ ወደ ተለያዩ የአምባሰል ተራራማ ስፍራዎች የከባድ መሣሪያ ድብደባ እየተደረገ ነው ተብሏል። በመሣሪያ ድብደባ የደረሰው ጉዳት አልታወቀም።

አሳዛኝ ዜና ፦   የብልጽግናው ወንበር ጠባቂ በንፁሃን አማራወች እና እንስሳት ላይ የጅምላ እርሸና ተግባር ፈፀመ። ሰኔ 20/2016 ዓ/ምበሸዋ ግዛት መርሃቤቴ ወረዳ ከአለም ከተማ በቅርብ እ...
27/06/2024

አሳዛኝ ዜና ፦
የብልጽግናው ወንበር ጠባቂ በንፁሃን አማራወች እና እንስሳት ላይ የጅምላ እርሸና ተግባር ፈፀመ።
ሰኔ 20/2016 ዓ/ም

በሸዋ ግዛት መርሃቤቴ ወረዳ ከአለም ከተማ በቅርብ እርቀት ላይ በሚገኝ ልዩ ስሙ ኩሳይ ጮሬና ቡዩ በሚባል አካባቢ የአማራ ፋኖ ሸዋ እዝ ናደው ክፍለጦርን ታበላላችሁ ታጠጣላችሁ በሚል ቂም የቋጠረ ጥላቻ ሀገር ሰላም ብለው ከቤታቸው በተቀመጡ አዛውንቶች ሴቶች እና ህፃናትን በድንገት ዘልቆ በመገንባት በቤት ውስጥ የነበሩ እንስሳትን ጭምር ሙሉ በሙሉ እረሽኗቸው ወጥቷል።
በዚህ እርሸናው ያረካው እራሱን መከላከያ እያለ የሚጠራው አራዊቱ የብልጽግና ሰራዊት በእርሻ ላይ የነበሩ አርሶ አደሮችን እና በእርሻ ስራ ላይ የነበሩ በሬችን ጭምር እረሽኖ ሄዷል።
እስከ አሁን ባለው መረጃ ከአስር በላይንፁሀን ህፃናት ሴቶችና አርሶ አደሮች የተረሸኑ ሲሆን ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ግለሰቦች መቁሰላቸው ተረጋግጧል።

"ድላችን በክንዳችን"
የአማራ ፋኖ ሸዋ እዝ ህዝብ ግንኘነት ክፍል

ሰበር የድል ዜና ፦ ሰኔ 11/2016 ዓ.ም     💪💪💪ሸዋ 🦅🦅🦅የሚተማመንበትን ከባድ መሳሪያ በመሸከም ከካራ ቆሬ ወደ አጣዬ ተጨማሪ ሀይል ይዞ ወረራ ለመፈፀም  ያቀደው የአብይ አህመድ ወን...
19/06/2024

ሰበር የድል ዜና ፦ ሰኔ 11/2016 ዓ.ም
💪💪💪ሸዋ 🦅🦅🦅
የሚተማመንበትን ከባድ መሳሪያ በመሸከም ከካራ ቆሬ ወደ አጣዬ ተጨማሪ ሀይል ይዞ ወረራ ለመፈፀም ያቀደው የአብይ አህመድ ወንበር ጠባቂ ሰራዊት ካሰበው ቦታ ሳይደርስ የአሞራ ቀለብ ሆኖ ቀርቷል።

አናብስቶቹ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ የአፄ ይኩኖአምላክ ክፍለጦር በአርበኛ ውባንተ ብርጌድ ስር የሚገኘው የአይሻ ሰይድ ሻለቃ የጠላትን እንቅስቃሴ እግር በእግር በመከታተል ከካራ ቆሬ ተጨማሪ ሀይል ይዞ ወደ አጣዬ ለመግባት የሞከረውን የአማራ ጠላት ሀይል ከቀኑ 4:00 ጀምሮ ሆራ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ላይ በወሰዱት ጥቃት የብርሀኑ ጁላ ቀኝ እጆች ሙትና ቁስለኛቸውን ታቅፈው ወደ አቀዱት ቦታ ሳይሆን ወደ ተነሱበት ካራ ቆሬ ሲመለሱ አናብስቶቹ በድጋሜ ከቀኑ 9:30 ላይ ቀርሳ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ በወሰዱት የደፈጣ የማጥቃት ውጊያ በድጋሜ ሌላ ሽንፈትን አስተናግዶ አጣዬን በሩቅ እያዬ ወደ መጣበት ተመልሷል።

በአስነዋሪ ተግባሩ የሚታወቀው ኦሮሙማ መራሹ ቡድን ያሰበው ሳይሳካ ተቀጥቅጦ ሲመለስ የበቀሉ ማሳያ ይሆንለት ዘንድ በእረኝነት ስራ ላይ የነበሩ ንፁሀን ህፃናትን ገድሏል።

በሌላ ዜና የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ በከሰም ክፍለጦር ስር የሚገኘው የሀይለማርያም ማሞ ብርጌድ የወረዳው መዲና በሆነችው ሾላ ገበያ ከተማ መሽጎ በሚገኘው የአገዛዙ ወንበር ጠባቂ ቡድን ላይ በተለያዩ አቅጣጫ የማጥቃት ኦፕሬሽን በመውሰድ የጠላትን ሀይል መውጫ መግቢያ አሳጥተውታል።

ሰኔ 11/2016 ዐ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ በደብረፅጌ ቀበሌ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ፣ወላድ አካባቢ ቁና ተራራ ተብሎ በሚጠራ ልዩ ስፍራ እንዲሁም ጥጎር በር በሚባል ስፍራ የተደራጀ ማጥቃት የፈፀመው የሀይለማርያም ማሞ ብርጌድ ሞርተር እና ዲሽቃ ታቅፎ የሚገኘውን የብልፅግናው ባለሟል ክላሽና ስናይፐር ብቻ በመጠቀም እንደ ቅጠል እያረገፉት የሚገኙ ሲሆን ይህን ዜና እስካጠናቀርንበት ሰዓት ድረስ ውጊያው በሁሉም አቅጣጫዎች እንደቀጠለ ነው።

በተያያዘ ዜና ለዘላለም የሚመኛትን የግሼራቤል ወረዳ ለመውረር ሰኔ 8/2016 ዓም በዙ_23፣ሞርተርና ዲሽቃ ታጅቦ ከመሀል ሜዳ ከተማ በመነሳት ወደ ግሼራቤል ወረዳ ያመራው ወንበዴው የአብይ አህመድ ሰራዊት ወዠድ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ላይ በአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ የአፄ ይኩኑ አምላክ ክፍለጦር የተለያዩ ብርጌዶች በቆረጣ የውጊያ ስልት በደረሰበት የተደራጀ ጥቃት የጠላት ሀይል ተቀጥቅጦ ራቤል ከተማን በልቡ እያሰበ ወደ ኋላ ተመልሷል።

ጀግናው የአማራ ፋኖ የአፄ ይኩኖአምላክ ክፍለጦር የተለያዩ ብርጌዶች ባደረጉት የሶስት ቀናት ውጊያ የብርሀኑ ጁላ ጦር ሙትና ቁስለኛ ሆኖ በሔሊኮፕተር እየተለቀመ በመነሳት ላይ ይገኛል።
ድል ለአማራ ፋኖ
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት ክፍል

💪
💪

10/10/16 ዓ'ምአሳዛኝ ዜና - ከደብረማርቆስ ዮኒቨርስቲ 😭ሰኔ ዐ9/2016 ዓ.ም ምሽት ጀምሮ የጨቅላው አብይ አህመድ ሰራዊት ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በመግባት ከ15 በላይ ሴቶችን...
17/06/2024

10/10/16 ዓ'ም
አሳዛኝ ዜና - ከደብረማርቆስ ዮኒቨርስቲ 😭

ሰኔ ዐ9/2016 ዓ.ም ምሽት ጀምሮ የጨቅላው አብይ አህመድ ሰራዊት ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በመግባት ከ15 በላይ ሴቶችን መድፈራቸው ታውቋል። ከእነዚህ ውስጥ ለጊዜው በስም ማወቅ ያልቻልናት በ7 ወታደሮች የተደፈረች ተማሪ ዛሬ ህይወቷ ማለፉ ተነግሯል። ስሟን እንዳወቅን ተጨማሪ መረጃ የምናደርስ ይሆናል።

ከላይ ከተፈፀመው ኢሰብዓዊ የአገዛዙ ወታደሮች ድርጊት ባሻገር የበርካታ ተማሪዎች ሞባይል ስልክም በእነዚህ ወታደሮች መዘረፉ ታውቋል።

ይህንን መረጃ ማንኛውም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ከዮኒቨርስቲው ተማሪዎች ሊያረጋግጥ የሚችለው ነው።

ድል ለፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ

16/06/2024

ሰኔ 9/2016 ዓ.ም ቅምሻ ፦ጎንደር

1) ሰኔ 8/2016 ዓ.ም የፋኖ ኃይሎች ወደ ጎንደር ከተማ በመግባት ሐምሌ አምስት መዘጋጃ ቤት እና የፀጥታ ተቋማት በማጥቃት ተተኳሾችን በእጃቸው አስገብተዋል። ይህንን ተከትሎ በጎንደር ከተማ ከፍተኛ ስጋት አለ። ጥብቅ ፍተሻ እየተደረገ ነው።

2) ጎንደር ዙሪያ ዓይባ እና ደንቀዝ በተባሉ ቦታዎች ሁለተኛ ቀኑን የያዘ ከባድ ውጊያ እየተደረገ ነው።

3) ጎንደር አዘዞ ክ/ከተማ የአካባቢው የደህንነት አስተባባሪ ተገድሏል። ቁጥራቸው ያልታወቁ ሚሊሺያዎች በፋኖዎች ተይዘው ተወስደዋል።

4) ጎንደር ዙሪያ ምንዝሮ ተክለ ኃይማኖት በሁለት ኦራል ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች ላይ በተፈፀመ የደፈጣ ጥቃት ከባድ ሰብዓዊ ጉዳት ደርሷል። አንደኛው ኦራል ላይ የነበሩ ወታደሮች አልቀዋል ተብሏል። አሁንም በከተማው ዙሪያ ተኩስ ቀጥሏል።

5) በስሜነኛው ወገራ ወረዳ አምባ ጊዎርጊስ ከተማ አቅራቢያ ከማለዳ ጀምሮ ከባድ ውጊያ መደረጉ ታወቀ። ከብርቱ ውጊያ በኋላ የፋኖ ኃይሎች ወደ ከተማው ዘልቀው ገብተዋል። የመንግሥት ኃይሎች ካምፕ ጥለው ወጥተዋል።

በውጊያው ከባድ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ውድመት ደርሷል።

ከበለሳ እስከ አዘዞ ከደንቀዝ እስከ ወገራ ከአምቦ በር እስ ዓይቫ ከምንዝሮ እስከ ቁልቋል በር ድረስ እየተደረገ ባለው ውጊ መንግሥት ሥስት ክ/ጦሮች በርካታ የአድማ ብተናና የሚሊሺያ አባላት ያሰለፈ ሲሆን መካናይዝድ እና ሞተረኛ ኃይልም አሰልፏል ተብሏል።
@በቀለ

15/06/2024

ሰበር ዜና
የጄኔራል አሳምንው ፅጌ ልጆች
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ነውረኛው የአቢይ አመድ አገዛዝ ስመ ጥር የሀገርና የህዝብ ሀብት የሆኑትን የኢትዮጵያ አየር መንገድንና የኢትዮጵያ ቴሌ ኮሙኒኬሽን ለስልጣኑ ማስጠበቂያ በመጠቀም ፋኖ ከህዝቡ በሚያገኘው መረጃ እያጠቃን ነው በሚል ሙሉ ለሙሉ የኔትወርክ ማጥፋት ሥራ በመስራት ፋኖን ከመሸገበት አጠፋዋለሁ በማለት ከሚያዚያ መጨረሻ ጀምሮ በመደበኛ ሠራዊቱ ያልቻለውን ውጊያ ከአስራ አራቱ ክልል ያውጣጣውን ሠራዊት ያዘመተ መሆኑ ይታወቃል። ነገርግን በሁለቱ ኮማንዶዎች በዋና አዛዥ አምሳ አለቃ ወንድሙ ማሩ እና በም/ል አዛዥ አምሳ አለቃ ፍቅሩ ሙሉዬ የሚመራው የዐማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ ላስታ አውራጃ የጄ/ል አሳምነው ፅጌ ክፍለ ጦር ፋኖዎች ጨለማን ለብሠው ጠላት ከመሸገበት ቦታ ድረስ በመሄድ አርብ ለቅዳሜ ዛሬ ግንቦት 8/2016ዓም ከማለዳ ጀምሮ መቄት ወረዳ ፍላቂትና ገረገራ ከተማ ውስጥ የመሸገውን የጠላት ጦር ሙሉ ለሙሉ በመደምሠሥ ከተማውን የተቆጣጠሩ ሲሆን ከአስታጥቄ ብሬንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን መታጠቃቸውን ገልፀዋል። ለጠላት ሽፋን ሊሠጥ በውር ድንብር በሁለት ኦራል ተጭኖ ሲከንፍ የነበረ ተጨማሪ የጠላት ጦር በደፈጣ መሀንዲሶቹ ገረገራ ከተማ አቅራቢያ ላይ እምሽክ ሲደረግ የተወሠኑ ብሬን ከእነ ተተኳሻቸው እና ከአምሳ በላይ ጥቁር እና ቀይ አዲስ ክላሽም መገኘቱን የላስታ አውራጃ የጄ/ል አሳምነው ክፍለ ጦር የሜጄር ጄኔራል ውብአንተ አባተ ብርጌድ አዛዥ ኮማንዶ አማን ተናግሯል።

በከተማው ውስጥ የሚገኙ የህዝብ መገልገያ ባንኮች ምንም እንኳን ለጨካኙ ስርዓት መሳሪያ ከሆኑት ባንኮች መካከል ግንባር ቀደሙ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሆኑ ቢታወቅም መደበኛ የህዝብ አገልግሎታቸውን እንዲቀጥሉ በማሠብ
- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
- የፀደይ ባንክ (አብቁተ)
- ዓባይ ባንክ
- አቢሲኒያ ባንክ
ከውድመትና ከዝርፊያ በፋኖዎቹ ጥበቃ እየተደረገላቸው ይገኛል።

በከፍተኛ የፋኖ አመራሮች የተመራው ልዩ ኦፕሬሽን ጠላት ባላሰበው ስዓትና ጊዜ በመድረስ ድባቅ በመምታቱ በኩል በግዙፉ የላስታ አውራጃ የጄ/ል አሳምነው ፅጌ ክፍለ ጦር ስር ከሚንቀሳቀሱ በርካታ ብርጌዶች መካከል በአምሳ አለቃ ጌታዬ የሚመራው ጄ/ል ተፈራ ማሞ ብርጌድና በኮማንዶ አማን የሚመራው የሜ/ጄ/ል ውብአንተ አባተ ብርጌድ ጣፋጭ ድል ማስገኘታቸውን አምሳ አለቃ ኮማንዶ ወንድሙ ማሩ ገልጿል።

በተመሳሳይ ቀን በተሠጠ ወታደራዊ ግዳጅ እና ተልዕኮ የላስታ አውራጃ የጄ/ል አሳምነው ክፍለ ጦር ኃይሉ ከበደ ብርጌድ በበርካታ ሻለቃዎች ጥምረት ውጊያ እየተደረገ ይገኛል። የማኩሽ ሻለቃ መሪ በፋኖ ዘላለም እየተመራ በሠቆጣ እና በአምደ ወርቅ ከተማ መካከል የምትገኘውን የቀውዝላ ከተማን የተቆጣጠሩ ሲሆን በጠላት ላይ የበላይነቱን በመውሰድ ውጊያው የዋግኽምራ ዞን መቀመጫ ለሠቆጣ ከተማ በ17ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እንደሆነ የክፍለ ጦሩ የህዝብ ግንኙነት ፋኖ መጎስ ተናግሯል።

አሳምነው አሳምነው ፅጌ‼️‼️
ድል ለፋኖ ድል ለአማራ ህዝብ

15/06/2024

ሰኔ 8/2016 ዓ.ም

የድረሱልኝ ጥሪ ከወለጋ!
የወለጋ አማራዎች እየተጨፈጨፉ ነው።

በዚህ ምሽት ህፃናትን ጨምሮ በርካታ አርሶ አደሮች ተገድለው አስከሬናቸው በየመንገዱ ወድቋል።

በሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን አቤ ደንጎሮ ወረዳ መንደር 20 እና መንደር 21 ላይ በርካታ የአማራ ተወላጆች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።

ግድያውን የፈፀመው መከላከያ ሰራዊት መሆኑንም ህይወታቸውን ለማትረፍ እየሸሹ ያሉ ሰዎች ለአማራ ድምፅ ሚዲያ ገልፀዋል

የአማራ ድምፅ ሚድያ ያነጋገራቸው የአከባቢው ነዋሪ የሆኑ አንዲት እናት "አከባቢው በሞርተር እና በዙ23 እየተደበደበ ነው፣ አስከሬን ማንሳት አልቻልንም። በርካታ ሰዎች በከባድ መሣሪያ ተመተው በቦታው ወድቀው የሲቃው ድምፅ እያሰሙ ነው" ሲሉ ቃል በቃል ተናግረዋል።

ጣቢያችን ያነጋገራቸው ሌላኛው የመንደር 21 አከባቢ ነዋሪ ደግሞ "አቅሙ የፈቀደለት መከላከያ ሰራዊቱ የከፈተውን ጥቃት ለመመከት አንገት ላንገት ተናንቆ እየተዋደቀ ነው።እኔና የመንደሬው ሰው መሳሪያ ያለው መሳሪያውን ይዞ፡ የሌለን ደግሞ ዱላ ይዘን ጥቃቱን ለመከላከል የቻልነውን ሁሉ እያደረግን የዋልን ቢሆንም ነገር ግን ከአቅማችን በላይ ሁኗል" ብለዋል።

ህፃናትን ጨምሮ የቆሰሉ አርሶ አደሮች የሚያነሳቸው የሚያነሳቸው አካል የለም።መከላከያ ሰራዊቱ እግር በእግር እየተከታተለ የቆሰሉትን ሰዎች በእሳት እያቃጠላቸው መሆኑንም ሌላኛው የአይን እማኝ ለአማራ ድምፅ ተናግረዋል።

ዘገባው የአማራ ድምፅ ነው!

Address

Debre Birhan

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መረጃ ከነምንጩ - ምጥን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to መረጃ ከነምንጩ - ምጥን:

Share

Category