Addis Page

ቋሚ ሲኖዶስ ልዩልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ!ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማ...
30/04/2025

ቋሚ ሲኖዶስ ልዩልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ!

ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ በዛሬው መደበኛ ጉባኤው በሰፊው ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሰረት በጉዳዩ ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተሉትን ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

1. ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያናችንን አባቶች፣ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማህበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል።

በዚህም መሰረት ቋማ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማህበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማህበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምርውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ፣

2. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ማርያም ቤዛዊተ ዓለም” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ፣

3. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፏቸው የስሕተት ትምህርቶችና በሌሎችም መምህራን የተላለፉ ነቀፋ ያለባቸው ትምህርቶች ካሉ የሊቃውንት ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አንጻር በሚገባ መርምሮና አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርብ፣

4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኝ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር ሚዲያ የአየር ሰዓት የሰጠበትን ዝርዝር ሁኔታና ከማኅበሩ ጋር በተያያዘ አየር ላይ ያዋላቸውን ትምህርቶች የሚያሳይ ሪፖርት እንዲያቀርብ ይደረግ በማለት ቋሚ ሲኖዶስ ወስኖ የዕለቱን ጉባኤ በቅዱስነታቸው ጸሎተ ቡራኬ አጠናቋል።

Via የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት

የጦር መሳሪያ ዲፖ የወደመበት ኢሳያስ አፈወርቂ ከብርጌድ ነሃመዱ ጋር ግንኙነት ፈጥራችኋል በሚል የገዛ ሰራዊቱን ማዋከብ ጀምሯል!የኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት በጋሽ ባርካ አንተረ አቅራቢያ ሸን...
25/04/2025

የጦር መሳሪያ ዲፖ የወደመበት ኢሳያስ አፈወርቂ ከብርጌድ ነሃመዱ ጋር ግንኙነት ፈጥራችኋል በሚል የገዛ ሰራዊቱን ማዋከብ ጀምሯል!

የኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት በጋሽ ባርካ አንተረ አቅራቢያ ሸንሸላይ የሚገኘው የጦር መሳሪያ ማከማቻ የወደመው በሰራዊቱ አባላት ነው በማለት ወታደሩን ማወከብ ጀምሯል። በዚህም በድብቅ ብርጌድ ነሃመዱ ከሚባል የተቃዋሚ ሃይል ጋር ግንኙነት ያላቸው የሰራዊቱ አባላት ናቸው በጦር መሳሪያ ማከማቻው ላይ ጥቃት የፈፀሙት በሚል በጥርጣሬ የሚመለከታቸውን ለይቶ አስቀምጧል።

በቀጣይም እነዚህን ከሰራዊቱ ለይቶ በመውሰድ የመረ*ሸን ፍላጎት እንዳለውም ምንጮቻችን ነግረውናል። ይህም የሻዕቢያ መንግስት ምን ያህል በሰራዊቱ ላይ እምነት እንዳጣ የሚያመላክት ሲሆን ከሰራዊቱ ጋር እንዲህ አይነት ግጭት ውስጥ ከገባም ውድቀቱ ቅርብ እንደሆነ መገመት ቀላል ነው። ይህን ሁሉ ጊዜ በመሳሪያ ጉልበት ለቆየ መንግስት ትልቅ የጦር መሳሪያ ማከማቻ በአንድ ቀን ዶግ አመድ ሲሆን ማየትም ከፍተኛ በሆነ የስነልቦና ጫና ውስጥ እንደሚከተው ምንም አያጠራጥርም።

በአጠቃላይ ኢሳያሳ አፈርወርቂ እያበቃለት ነው!
tv/ጎህ ቲቪ

እየመጡ ነው😁🙋‍♀️
25/04/2025

እየመጡ ነው😁🙋‍♀️

የህንድ እና ፓኪስታን ፍጥጫየፓኪስታን ታጣቂዎች በጎረቤቷ ህንድ ላይ በአንድ የቱሪስት መንደር ላይ ጥቃት ሰንዝራ ከ26 በላይ ነዋሪዎችን መግደሏን ተከትሎ ህንድ ፓኪስታን የእጇን ታገኛለች ስት...
24/04/2025

የህንድ እና ፓኪስታን ፍጥጫ
የፓኪስታን ታጣቂዎች በጎረቤቷ ህንድ ላይ በአንድ የቱሪስት መንደር ላይ ጥቃት ሰንዝራ ከ26 በላይ ነዋሪዎችን መግደሏን ተከትሎ ህንድ ፓኪስታን የእጇን ታገኛለች ስትል ዝታለች።
ይህን ተከትሎ ፓኪስታን ወታደሮቿ፣ የአየር ሀይሏ፣ሙሉ ራዳሮቿ እና ሚሳኤሎቿ በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ማዘዟን አለም አቀፍ ሚዲያዎች ዘግበዋል።
ፓኪስታን ከህንድ ለሚመጡ በረራዎች የአየር ክልሏን ዘግታለች።
ህንድም በፓኪስታን የሚኖሩ የህንድ ነዋሪዎች ለቀው እንዲወጡ አዛለች።

ይህንን ትምህርት አባቶቻችን አልነገሩንም መጻሕፍቶቻችን ላይ ተጽፎ አላገኘነውም። .ብቻህን ማሰብ ስትጀምር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የብቻችን የሆነ ትምህርት የለም። በማኅበር እንማራለን ፤ በማ...
24/04/2025

ይህንን ትምህርት አባቶቻችን አልነገሩንም መጻሕፍቶቻችን ላይ ተጽፎ አላገኘነውም። .
ብቻህን ማሰብ ስትጀምር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የብቻችን የሆነ ትምህርት የለም። በማኅበር እንማራለን ፤ በማኅበር እንጸልያለን ፤ አንድ ሆነን የተዘጋጀልንን ማዕድ ቅዱስ ቊርባን እንቀበላለን ፤ በመጨረሻም የተዘጋጀልንን የተስፋ አገር እንቀበላለን።

ክርስቶስ ያስተማረ በጉባኤ ነው ፤ ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን ምንጊዜም ጉባኤአዊት ሆና ትቀጥላለች እንጅ ማንም ምንም ቢሆን የራሱን ትምህርት አምጥቶ ሊያስተምር የሚችልበት ዕድል የለውም።

የብቻው የሆነ ክርስቶስ ስለሌለው የብቻው የሆነ ትምህርትም ሊኖረው አይችልም።

ብቻህን ማሰብ ከጀመርህ ከጉባኤው የተለየ አስተምህሮ ማምጣትህ ስለማይቀር “ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ላዕለ ኵሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት” የሚለውን የሃይማኖት መግለጫ አስቀድመን እንድናውቅ መደረጉ ስለዚህ ነው።

በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚኖር ማንም ቢሆን ቤተ ክርስቲያን ካስተማረችው ትምህርት የወጣ እንደሆነ መዐርጉ ፣ የዕውቀት ደረጃው ፣ የወገኑ የሀብቱ ብዛት ሊያድነው አይችልም። በመጀመሪያ ከቃሉ የሰሙ ሰዎች “የተናገርኸውን ትምህርት አስበኸው ከሆነ አትናገረው ተናግረኸውም ከሆነ አትድገመው” ብለው ይመክሩታል። ምክራቸውን ሰምቶ በዚህ ካቆመ ይተዉታል፤ ምክራቸውን አልሰማ ብሎ ከቀጠለ ግን ወደ መምህራን ያደርሱታል፤ መምህራንንም አልሰማ ካለ ወደ ጉባኤ {ሲኖዶስ} ይቀርባል። ሲኖዶሱን ካልሰማ ተወግዞ ይለያል።

በሰሞኑ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል የሰጡትን ትምህርት በቪዲዮ አንዲት ወዳጄ ልካልኝ ተመለከትሁት፤ ምናልባት ከባልንጀሮቻቸው ጋር ተማክረውበት ከበታቾቻቸውም ጋር ተከራክረውበት የነበረ ጉዳይ ከሆነ “አስበኸው ከሆነ አትናገረው ተናግረኸውም ከሆነ አትድገመው” ሊሏቸው ይገባ ነበር።

አሁን ግን በሹክሹክታ ሳይሆን በሰገነት ላይ የተሰበከ የስሕተት ስብከት ስለሆነ ጉዳዩ ከዚህ ያለፈ ይመስለኛል። ከረፈደም ቢሆን ባየሁት መረጃ መሠረት ብዙ ሊቃውንት ሀሳብ ሰጥተውበታል ፤ ይሄ ለብፁዕነታቸው መልካም ዕድል ነው ብየ አምናለሁ። ሀሳባቸውን የገለጹ ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያን በሊቅነታቸው የምታምንባቸው ሊቃውንት እንደመሆናቸው መጠን ምክሩን ይቀበሉታል ብየ ስለማምን ነው። ሀሳቡን ሳይንቁ በቶሎ በሰገነት ላይ ያጠፉትን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በሰገነት ላይ ወጥተው ቤተ ክርስቲያኒቱን ይቅርታ ሊጠይቁ ይገባል። “አትደንግጡ” ብለውናል እንዳንደነግጥ ያድርጉን።
ይህንን ትምህርት አባቶቻችን አልነገሩንም መጻሕፍቶቻችን ላይ ተጽፎ አላገኘነውም።

ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ መጻሕፍቶቻችንን አባቶቻችንን ተቃውመዋል። ዛሬ መልስ አልጽፍም፤ ምክንያቱም መልሱን ከብፁዕነትዎ ስለምጠብቅ ነው።

#ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ

ሩሲያ የጦር መሳሪያ እና ትሮፕን ወደ ቡርኪናፋሶ ልትልክ  መሆኑ ተሰማ ❗️ ከሰሞኑን በምዕራባዉያን እርዳታ የተቋቋመው የጁንታ ቡድን መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ መሞከሩን ተከትሎ ወጣቱ መሪ ...
23/04/2025

ሩሲያ የጦር መሳሪያ እና ትሮፕን ወደ ቡርኪናፋሶ ልትልክ መሆኑ ተሰማ ❗️


ከሰሞኑን በምዕራባዉያን እርዳታ የተቋቋመው የጁንታ ቡድን መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ መሞከሩን ተከትሎ ወጣቱ መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ የሩስያውን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ዉይይቶች ማድረጋቸውን በፈረንሳይ መንግስት እርዳታ በሀገሪቱ ውስጥ የታጣቂዎች ቁጥር እየጨመረና ወደ አለመረጋጋት እየተለወጠ መምጣቱ ተከትሎ ትራኦሬ ላቀረቡት የትብብር ጥያቄ ሩሲያ አስቸኳይ የመሳርያ ዕርዳታ የጦር መሳሪያ እና ሌሎች ድጋፎችን ወደ ቡርኪናፋሶ ልትልክ መሆኑን የተለያዩ ትልልቅ የአፍሪካ ጉዳይ ዘገባ የሚሰሩ ሚዲያዎች እየዘገቡ ይገኛል ።

የሩሲያ መሪ ፑቲን ከቡርኪናፋሶ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ እ.ኤ.አ. ኦገስት 31 2023 ጋር ተገናኝተው ስለ ጠንካራ ትብብር ዉይይት አድርገዉና ለመደጋገፍ መወሰናቸው ይታወቃል ።

በዚህም መሰረት በአሁኑ ጊዜ ምዕራባዉያን ጠንሳሽነት በአጎራባች አገሮች እንደፈፀሙት ለጁንታዉ ቡድን በማስታጠቅ የጀመሩትን የመፈንቅለ መንግሥት ግልበጣ ለማስቆም የተለያዩ መሳርያዎችንና የሩሲያ የግል ወታደራዊ ኩባንያዎች (PMCs)የአፍሪካ ኮርፕስ (የዋግነር ተተኪ) ወታደራዊ ድጋፍም ለቡርኪና ፋሶ ለማድረግ ማሰቧን የሃገሪቱ ሚዲያዎች ዘግበዋል ።

ጉዳዩን አስመልክቶ መረጃ የሰጠዉ የቡርኪናፋሶው መንግስት ተወካይ መንግስታቸው
የውጭ ጣልቃ ገብነትን እና በሳህል ሃገራት ላይ የበላይነታቸውን መቼም እንደማይቀበልና
ኢኮኖሚዋ በምዕራባዊያን ይሁንታ እንዲሾር መቼም እንደማይፈቅድና ለሀገራዊና ሉዓላዊነት፣ በኢኮኖሚያዊ ነፃነት እና በማህበራዊ ፍትህ እንደማይደራደር ገልጿል ።
ትራኦሬም በበኩሉ “ህዝቤ በእውነት ነፃ እስኪወጣ ድረስ እታገላለሁ” ብሏል። ሲል የዘገበው Faso 7 Tv ነዉ ።

ከቅርብ  ወራት ወዲህ  በቻይናዋ Zhejiang province  ጎዳናዎች ላይ የሚታይ አንድ ድቡልቡል ጎማ የሚመስል እንግዳ ሮቦት አለ ።..ይህ ሮቦት ለሰአታት ወደዛ. .ወደዚ እያለ.  ሲለው...
19/04/2025

ከቅርብ ወራት ወዲህ በቻይናዋ Zhejiang province
ጎዳናዎች ላይ የሚታይ አንድ ድቡልቡል ጎማ የሚመስል እንግዳ ሮቦት አለ ።..
ይህ ሮቦት ለሰአታት ወደዛ. .ወደዚ እያለ. ሲለውም አማካኝ ቦታ መርጦ በመቆም ፡ በዛ ጎዳና የሚያልፈውን ሰው ሁሉ እጅግ ጥራት ባለው HD ካሜራ አይኖቹ ይቃኛል ።......
በዚህ መሀል ታዲያ ወንጀል የሚሰራ ወይም ፡ በፖሊስ የሚፈለግ አንድ ሰው ካገኘ በአቅራቢያው ለሚገኝ ፖሊስ ሪፖርት ያደርግና ተፈላጊውን ሰው በቅርብ ርቀት መከታተል ይጀምራል ።

በስፍራው የፖሊስ ሀይል ከሌለ ደግሞ ወንጀለኛን ለመያዝ ተብሎ በውስጡ የተገጠመውን መረብ በመተኮስ ሰውየው በመረቡ ተጠምዶ መንቀሳቀስ እንዳይችል ካደረገው በኋላ ፖሊስ መጥቶ እስኪወስደው ይጠብቃል ።...
RT-G robot ይባላል ፡ ባለፈው አመት ወደስራ የገባው ይህ ሮቦት ፡ ከፖሊሶች ጋር በህብረት በመሆን ፡ እና ብቻውንም ሮንድ በመውጣት በተጨናነቁ የገበያ ቦታዎች እንዲሁም የፀጥታ ጥበቃ በሚያስፈልግባቸው ቦታዎች እየተዘዋወረ የአካባቢውን ደህንነት ይቆጣጠራል ።
የገበያ ቦታዎችን ከዘራፊዎች ይጠብቃል ፡ በዚህ መሀል ለዘረፋ የተሰማሩ ወንጀሎች ከሆኑና ይህንን ሮቦት ሊተናኮሉት ከሞከሩ ደግሞ እራሱን ለመከላከልና ፡ ቦታውን ከዘረፋ ለማዳን የታጠቀውን የጭስ ቦንብ በመልቀቅ ፡ ወንጀለኞቹን ከስፍራው እንዲለቁ ማድረግ ይችላል ። ከጠንካራ ቁስ ስለተሰራም በምንም ነገር ሊጎዳ አይችልም ። ..

RT-G robot የፖሊስ አጋዥ ሆኖ ፀጥታን ከማስከበር ባለፈም ፡ የተፈጥሮ አደጋዎች በሚከሰቱበት ጊዜ ፡ ወደቦታው በፍጥነት ደርሶ ፡ የነብስ አድን ስራ ይሰራል ።

ይህ ሮቦት ባለበት ሰርቆ ወይም ወንጀል ሰርቶ ማምለጥ አይታሰብም ፡ በሰአት እስከ ሰላሳ ኪሎ ሜትር እየሮጠ ወንጀለኛውን ለመያዝ ይጥራል ።
በውሀ ውስጥ ይሄዳል ፡ አስቸጋሪ የተባሉ መንገዶች ሁሉ ለሱ ምንም ማለት አይደለም ።
ይህ አስቸጋሪ በሆኑ ቦታዎች ለመሰማራት በጥቅም ላይ የዋለው ይህ ሮቦት በዚህ መሰል ስራ ላይ የተሰማራና በጥቅም ላይ የዋለ የአለማችን የመጀመሪያው ሮቦት ሆኗል ...
የሰው ልጅ ሰላም ሲያገኝ ፡ የስራ ዋስትናው ሲረጋገጥ ፡ መሰረታዊ ፍላጎቱ ሲሟላ ፡ መማር መሰልጠን ፡ መስራትና ፡ አዲስ ነገር መፍጠር ይችላል ፡ ቻይና አሁን እንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ናት ።
via wasihune Tesfaye

 #ስቅለት
18/04/2025

#ስቅለት

የኮሪደር ልማት ላይ ጉዳት ያደረሱ 13 ከብቶች በቁጥጥር ስር ዋሉ በቦሌ ቡልቡላ 13 ከብቶች የኮሪደር ልማት ላይ ጉዳት በማድረሳቸው በቁጥጥር ስር ውለው የከብቶቹ ባለቤቶች ለእያንዳንዳቸው ከ...
18/04/2025

የኮሪደር ልማት ላይ ጉዳት ያደረሱ 13 ከብቶች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በቦሌ ቡልቡላ 13 ከብቶች የኮሪደር ልማት ላይ ጉዳት በማድረሳቸው በቁጥጥር ስር ውለው የከብቶቹ ባለቤቶች ለእያንዳንዳቸው ከብቶች 5ሺ ብር በጠቅላላ 65,000 ብር በቅጣት እንዲከፍሉ ከተደረገ በኋላ ተለቋል።

የወረዳው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ማህበረሰቡ ከመሰል ድርጊት እንዲቆጠብ አሳስበዋል ።

አሜሪካ በኤርትራ ጨምሮ በሌሎችም ሀገራት ያሉ ኤምባሲዎቿን ልትዘጋ ነው።አሜሪካ ወደ 30 የሚጠጉ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ዲፕሎማቲክ ጽሕፈት ቤቶቿን ልትዘጋ መሆኑን ሮይተርስ የአገሪቱን የውጭ ጉ...
16/04/2025

አሜሪካ በኤርትራ ጨምሮ በሌሎችም ሀገራት ያሉ ኤምባሲዎቿን ልትዘጋ ነው።

አሜሪካ ወደ 30 የሚጠጉ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ዲፕሎማቲክ ጽሕፈት ቤቶቿን ልትዘጋ መሆኑን ሮይተርስ የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ሰነድን ጠቅሶ ዘገበ።

የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር አብዛኞቹ በአፍሪካ እና በአውሮፓ የሚገኙ ቢያንስ 27 የአሜሪካ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎችን የሚዘጋ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ጎረቤት ሀገር #ኤርትራ አንዷ ናት።

በውሳኔው መሠረት ይዘጋሉ የተባሉት አስሩ የአሜሪካ ኤምባሲዎች ፦
- በኤርትራ፣
- በግሪናዳ፣
- በሌሶቶ፣
- በማዕካላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣
- በሉክዘንበርግ፣
- በሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ፣
- በጋምቢያ፣
- በደቡብ ሱዳን፣
- በማልታ እና በማልዲቭስ የሚገኙ መሆናቸውን ሮይተርስ የተመለከተው ሰነድ ያመለክታል።

ከሚዘጉት ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎች ባሻገር ኤምባሲ እና በርካታ ቆንስላዎችን በመያዝ ግዙፍ የዲፕሎማቲክ ሥራ በሚከናወንባቸው እንዳ ጃፓን እና ካናዳ ያሉትን ተልዕኮዎች በማዋሃድ መጠናቸውን የመቀነስም ሐሳብ አለ።

ሰነዱ ከፍተኛ ወጪ በማስወጣት ውድ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ የተመደበባቸው ናቸው ያላቸውን በሞቃዲሾ ሶማሊያ እና በኢራቅ ያሉ የዲፕሎማቲክ አባላትን መጠን የመቀነስ ሐሳብም መቅረቡን አመልክቷል።

ዶናልድ ትራምፕ ወደ ፕሬዝዳንትነት ከተመለሱ በኋላ የአሜሪካ መንግሥት በተለያዩ መስኮች ከአገሪቱ ፍላጎት ጋር አይጣጣሙም ያላቸውን ተቋማት በመዝጋት እና እርዳታዎችን በማቋረጥ ላይ ይገኛል።

የትራምፕ የቅርብ ሰው በመሆኑት ማርኮ ሩቢዮ የሚመራው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በጀት እስከ ግማሽ የሚደርሰውን እንደሚቀነስ ሮይተርስ የተመለከተውን የመሥሪያ ቤቱን ሰነድ ጠቅሶ አመልክቷል።

በዚህም ሳቢያ በበርካታ አገራት የሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎችን የመዝጋት ሐሳብ ሀሳብ ነው ያለው።

የአሜሪካ መንግሥት ለውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ከሚያወጣው ገንዘብ ወደ 30 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ለመቀነስ አቅዶ የበጀት ጥያቄውን ለአገሪቱ ምክር ቤት ለማቅረብ እየተዘጋጀ ነው።

መረጃው የሮይተርስ እና ቢቢሲ ነው።

+ ከልብ የፈለቀ መዝሙር + ሆሳዕና ‘የሚቀድሙትም ሕዝብ የሚከተሉትም። ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር’’  ይህ ታላቅ ሕዝባዊ የአ...
14/04/2025

+ ከልብ የፈለቀ መዝሙር + ሆሳዕና

‘የሚቀድሙትም ሕዝብ የሚከተሉትም። ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር’’

ይህ ታላቅ ሕዝባዊ የአንድነት ዝማሬ መቼ የተጠና ዝማሬ ነው? ይህ ሁሉ ሕዝብ አንድ መዝሙር ለመዘመር ልምምድ የጀመረው መቼ ይሆን? ይህ ልዩ የሆነ የአቀባበል ሥነ ሥርዓትስ መቼ የተማሩት ነው? የሥራ ክፍፍል ያደረጉትስ መቼ ነበር? እናንተ ልብስ አንጥፉ ፣ እናንተ ከፊት ቅደሙ ፣ እናንተ ዘንባባ ያዙ ብሎ ሥራ ያከፋፈላቸው የመዝሙሩን ሥርዓት የምስጋናውን ወግ ያሳያቸው ማን ነው? ድንገት ሕዝብ ሁሉ አንድ አንደበት ሊኖረው እንዴት ይችላል?

ጌታ ሆይ የአንተን ፊት ያዩ ሰዎች የምስጋና ትምህርት ቤት አያስፈልጋቸውም፡፡ ምስጋና እንዲሁ ዝም ብሎ ከአንደበታቸው ይፈልቃል፡፡ ከሕፃናትና ከሚጠቡት ሰዎች አፍ ለራስህ ምስጋናን ታዘጋጃለህ፡፡ የማይተዋወቁ ሰዎች ያለ ልምምድ አንድ መዝሙር ይዘምሩልሃል፡፡ ዳግም ስትመጣ በቀኝህ አቁመን እንጂ እኛም የማናውቀው አዲስ ምስጋና እናቀርብልሃለን፡፡ ፊትህን ለማየት አብቃን እንጂ ልብሳችን ብቻ ሳይሆን ልባችንንም እናነጥፍልሃለን፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ክርስቲያኖ ሮናልዶ የፊልም ካምፓኒ መከፍቱን እና ሁለት ፊልሞች መስራቱን ይፋ አደረገ....ክርስቲያኖ ሮናልዶ የራሱን ፊልም ፕሮዳክሽን መከፈቱን በይፋዊ ገፁ አስታውቋል።ሮናልዶ ከፕሮዳክሽኑ ባ...
10/04/2025

ክርስቲያኖ ሮናልዶ የፊልም ካምፓኒ መከፍቱን እና ሁለት ፊልሞች መስራቱን ይፋ አደረገ....

ክርስቲያኖ ሮናልዶ የራሱን ፊልም ፕሮዳክሽን መከፈቱን በይፋዊ ገፁ አስታውቋል።

ሮናልዶ ከፕሮዳክሽኑ ባለፈ ፊልም መስራቱን እና በፊልሙ ላይ 3 የአክሽን ፓርቶች እንዳሉት ተገልጿል።

ፊልሙ በቅርቡ ይለቀቃል 💪💪💪

Address

Debre Birehan
Debre Birhan

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Page:

Share