Addis Page

ኢራን የሆርሙዝን ስትሬት እንደምትዘጋ በድጋሜ አስጠነቀቀች‼​ኢራን የኃይል ማመንጫዎቿ ላይ ጥቃት ከተሰነዘረ ስልታዊ ጠቀሜታ ያለውን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ሙሉ በሙሉ እንደምትዘጋና በክልሉ ...
23/03/2026

ኢራን የሆርሙዝን ስትሬት እንደምትዘጋ በድጋሜ አስጠነቀቀች‼

​ኢራን የኃይል ማመንጫዎቿ ላይ ጥቃት ከተሰነዘረ ስልታዊ ጠቀሜታ ያለውን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ሙሉ በሙሉ እንደምትዘጋና በክልሉ የኢነርጂ ተቋማት ላይ የአጸፋ ጥቃት እንደምትሰነዝር አስታወቀች።

​በሌላ በኩል፣ የእስራኤል ጦር በደቡብ ሊባኖስ የሚገኘውን የቃሲሚያ ድልድይ ማውደሙን ተከትሎ፣ የሊባኖሱ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ አውን ድርጊቱ "ለምድር ወረራ መነሻ ነው" ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ወቅታዊው ሁኔታ በቀጠናው መጠነ ሰፊ ጦርነት ሊቀሰቅስ ይችላል የሚል ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ስጋት ፈጥሯል።

Wasu Mohammed - Mereja

የምርጫ ካርድ በግድ ውሰዱ❌‼️​የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መግለጫ፡ "ዜጎችን አስገድዶ የምርጫ ካርድ ማስወጣት ሕገ-ወጥ ነው"‼️​በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግ...
23/03/2026

የምርጫ ካርድ በግድ ውሰዱ❌‼️
​የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መግለጫ፡ "ዜጎችን አስገድዶ የምርጫ ካርድ ማስወጣት ሕገ-ወጥ ነው"‼️
​በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1394/2017 መሠረት፣ ዜጎች የምርጫ ካርድ እንዲያወጡ የመቀስቀስ ሙሉ ኃላፊነት የተሰጠው ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ብቻ መሆኑ ተገለጸ።

​የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላተወርቅ ኃይሉ መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት፣ በአንዳንድ አካባቢዎች ዜጎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት እንደ ቅድመ ሁኔታ የምርጫ ካርድ እንዲያወጡ የማስገደድ ሁኔታዎች መኖራቸውን ቦርዱ ጥቆማ ደርሶታል።

​ከመግለጫው የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፦

​ነጻ ፈቃድ፦ ማንኛውም ዜጋ የምርጫ ካርድ የማውጣት መብት እንጂ የመገደድ ግዴታ የለበትም።

​የቅስቀሳ ገደብ፦ በሕግ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የመራጮች ትምህርት መስጠት የሚችለው ቦርዱ ወይም እርሱ ፈቃድ የሰጣቸው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ብቻ ናቸው።

​ሕገ-ወጥ አሰራር፦ "በየሰው ቤት እየተሄደ" የሚደረግ የካርድ ማስወጣት ቅስቀሳም ሆነ ዜጎችን በተለያዩ አገልግሎቶች አማካኝነት ተጽዕኖ መፍጠር በአዋጁ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው።

​ቦርዱ ይህን መሰል ጫናዎችና ሕገ-ወጥ ቅስቀሳዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ለሚመለከታቸው አካላት ማሳወቁን ሰብሳቢዋ አረጋግጠዋል።

አለም አቀፉ የዲጂታል ሚዲያ ኮከብ ዲላን ፔጅ (Dylan Page) ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው!በአለም አቀፍ ደረጃ በሚሊዮኖች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈውና ፈጣን የዜና መረጃዎችን በማድረስ “የ...
22/03/2026

አለም አቀፉ የዲጂታል ሚዲያ ኮከብ ዲላን ፔጅ (Dylan Page) ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው!

በአለም አቀፍ ደረጃ በሚሊዮኖች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈውና ፈጣን የዜና መረጃዎችን በማድረስ “የዜና አባት” በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ዝነኛው የቲክቶክ Content Creator ዲላን ጄምስ (Dylan Page) ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ መሆኑ ተሰማ።

ይህንን ታላቅ የምስራች በትላንትናው እለት ይፋ ያደረገው የ2025 የኢትዮጵያ የዓመቱ ምርጥ ቲክቶክሩ አዶናይ ሲሆን፣ ከዲላን ጄምስ ጋር የቅርብ ግንኙነት በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።

አዶናይ በቅርቡ ወደ ለንደን በማቅናት ከዲላን ጋር እንደሚገናኝና እ.ኤ.አ May 15, 2026 ዝነኛውን ጋዜጠኛ ይዞ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጣ አረጋግጧል።

በቲክቶክ ብቻ ከ19 ሚሊዮን በላይ ንቁ ተከታዮች ያሉት ዲላን ፔጅ ወደ ሀገራችን መምጣቱ ከዘገባቸው ባሻገር የሚከተሉትን ትልልቅ ፋይዳዎች ይኖሩታል ተብሎ ይታመናል፦

1. ዲላን ስለ ጉብኝቱ የሚያጋራቸው ይዘቶች በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የአለም ዜጎች ዘንድ ስለሚደርሱ፣ የኢትዮጵያን ታሪካዊ እና ተፈጥሮአዊ መስህቦች ለአለም ለማስተዋወቅ ተወዳዳሪ የሌለው አጋጣሚ ነው።

2.ኢትዮጵያ ሰላም፣ የእንግዳ ተቀባይ እና ለቱሪዝም ምቹ መሆኗን በአለም አቀፍ መድረክ በተጨባጭ ለማሳየት ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል ይሆናል።

3. የአለም አይን በዲላን በኩል ወደ ኢትዮጵያ የሚያርፍበት ይህ አጋጣሚ ሀገራችን በዲጂታል አለም ያላትን ተሰሚነት ከፍ ያደርገዋል።

ይህ ጉዞ ለሀገራችን ቱሪዝም እና ገጽታ ግንባታ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ይሆናል::

Via Adoney

👏👏👏

ጉርሻ page

🌴🌴🌴

በድብደባ ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁ ያላቸውን የጸጥታ እና የአስተዳደር አካላትን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።***ድርጊቱ የተፈፀመው...
21/03/2026

በድብደባ ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁ ያላቸውን የጸጥታ እና የአስተዳደር አካላትን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።
***
ድርጊቱ የተፈፀመው የካቲት 27 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 3፡30 ሠአት በንፋ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ልዩ ቦታው ካባ ጉሊት እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ነው።

ወ/ሮ እናት አበበ በመኖሪያ ቤታቸው አረቄ በመሸጥ የሚተዳደሩ ሲሆኑ በዕለቱ በአካባቢው በወንጀል መከላከል ስራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ የፖሊስ አባላት እና የወረዳ 5 አስተዳደር አመራሮች ወደ ግለሰቧ መኖሩያ ቤት በመግባት “አረቄ እዚህ መሸጥ የለበትም “ በሚል በተፈጠረ አለመግባባት የግል ተበዳይ ላይ ጉዳት ደርሷል።

ከጉዳቱ ባሻገር ለንግድ የተቀመጠ ወደ 60 ሊትር የሃበሻ አረቄ እንዲደፋ ይደረጋል። በዚህ ምክንያት የተፈጠረውን ፀብ መነሻ አድርጎ የወ/ሮ እናት አበበ ልጅ የሆነው ናትናኤል ገመዳ እናቴ እግሯ ላይ እና ሌላ አካሏ ላይ ጉዳት ደርሶባታል።

በተጨማሪም 60 ሌትር አረቄ ደፍተውብናል፤ በሚል በራሱ ቲክቶክ ፕላት ፎርም ላይ ተንቀሳቃሸ ምስል በማጋራቱ ፖሊስ የተለቀቀውን ተንቀሳቃሸ ምስል መነሻ በማድረግ ባደረገው ማጣራት በድብደባ ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁ ያላቸውን ሁለት የፖሊስ አባላትና ሦስት የወረዳውን አመራሮች በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል።

በቀጣይ የምርመራ ሂደቱ የደረሰበትን ሁኔታ ተከታትሎ ለህዝብ እንደሚያሳውቅም ፖሊስ አስታውቋል ።
*
ዘገባ፦ ኢንስፔክተር እመቤት ኃብታሙ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)

 ፦ ትራምፕ ኔቶን (NATO) “የወረቀት አንበሳ” ሲሉ ወረፉት !​የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ባሰፈሩት ጠንካራ መልዕክት፣ የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት...
20/03/2026

፦ ትራምፕ ኔቶን (NATO) “የወረቀት አንበሳ” ሲሉ ወረፉት !

​የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ባሰፈሩት ጠንካራ መልዕክት፣ የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) ያለ አሜሪካ ድጋፍ ምንም ዓይነት ወታደራዊ አቅም እንደሌለው በመግለጽ “የወረቀት አንበሳ” (Paper Tiger) ሲሉ አጣጥለዋል።

​ትራምፕ በመልዕክታቸው የጠቀሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
​የኢራን የኒውክሌር ስጋት፦ ኔቶ የኒውክሌር ኃይል ለመሆን የምትተጋውን ኢራን ለማስቆም በሚደረገው ትግል አጋር ለመሆን ፈቃደኛ አልነበረም ብለዋል።

​የወታደራዊ ድል ጥያቄ፦ አሁን ላይ ኢራን ወታደራዊ ሽንፈት ከደረሰባትና ስጋቱ ከቀነሰ በኋላ፣ ኔቶ የአለም የነዳጅ ዋጋ መናር ላይ ቅሬታ ያቀርባል እንጂ መፍትሔ ለመሆን አይሰራም ሲሉ ወቅሰዋል።

​የሆርሙዝ ስትሬት (Strait of Hormuz)፦ ለአለም ነዳጅ ዋጋ መናር ብቸኛው ምክንያት የሆርሙዝ የባህር መስመር መዘጋት መሆኑን የጠቀሱት ትራምፕ፣ ኔቶ ይህንን መስመር ለማስከፈት የሚደረገውን “ቀላል ወታደራዊ እንቅስቃሴ” ለመርዳት አለመፈለጉን ገልጸዋል።

​“ፈሪዎች!”፦ ትራምፕ አጋር ሀገራቱ አነስተኛ መስዋዕትነት በሚጠይቅ ስራ ላይ ለመሳተፍ ወደኋላ ማለታቸውን በጽኑ በመተቸት “ፈሪዎች” (COWARDS) ሲሉ የጠሯቸው ሲሆን፣ አሜሪካ ይህንን ድርጊታቸውን እንደማትረሳው አስጠንቅቀዋል።

​ይህ የትራምፕ ንግግር በአውሮፓና በአሜሪካ መከላከያ ጥምረት መካከል ያለውን ውጥረት ዳግም የቀሰቀሰ ሲሆን፣ የነዳጅ ዋጋን ለማረጋጋት በሚደረገው ጥረት ላይ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል።

 : ሐሙስ ምሽት በታብሪዝ በሚገኝ የፍተሻ ጣቢያ ላይ በተፈጸመ ጥቃት 13 የባሲጅ (Basij) አመራሮች ሲገደሉ፣ ሌሎች 18 ደግሞ ቆስለዋል ሲል በምስራቅ አዘርባጃን ክፍለ ሀገር የሚገኘው የ...
20/03/2026

: ሐሙስ ምሽት በታብሪዝ በሚገኝ የፍተሻ ጣቢያ ላይ በተፈጸመ ጥቃት 13 የባሲጅ (Basij) አመራሮች ሲገደሉ፣ ሌሎች 18 ደግሞ ቆስለዋል ሲል በምስራቅ አዘርባጃን ክፍለ ሀገር የሚገኘው የኢራን አብዮታዊ ጦር (Revolutionary Guards) አስታውቋል።

ባለስልጣናት በከተማዋ ቀራማሌክ (Qaramalek) ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰው በዚህ ጥቃት የሟቾች ቁጥር
ሊጨምር እንደሚችል ገልጸዋል።

ምንጭ: Iran International - English

 : እስራኤል በኢየሩሳሌም የዒድ በዓልን በሚያከብሩ ፍልስጤማውያን ስገድተኞች ላይ ጋዝ ቦምቦችን (Gas bombs) መተኮሷ ተሰማ !ምንጭ፦ ብሪክስ ኒውስ (BRICS News)
20/03/2026

: እስራኤል በኢየሩሳሌም የዒድ በዓልን በሚያከብሩ ፍልስጤማውያን ስገድተኞች ላይ ጋዝ ቦምቦችን (Gas bombs) መተኮሷ ተሰማ !

ምንጭ፦ ብሪክስ ኒውስ (BRICS News)

 የአሜሪካው አይነኬ ተዋጊ ጄት F-35 በኢራን ሚሳይል ተመታመጋቢት 11 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ለሶስተኛ ሳምንት በቀጠለው የዩናይትድ ስቴትስ እና የኢራን ጦርነት ትላንት ሌሊት ከፍተኛ...
20/03/2026



የአሜሪካው አይነኬ ተዋጊ ጄት F-35 በኢራን ሚሳይል ተመታ

መጋቢት 11 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) ለሶስተኛ ሳምንት በቀጠለው የዩናይትድ ስቴትስ እና የኢራን ጦርነት ትላንት ሌሊት ከፍተኛ መነጋገሪያ የሆነ ክስተት ተመዝግቧል።

በአለም ላይ ካሉ እጅግ ዘመናዊ እና በራዳር የማይታዩ ተዋጊ ጄቶች አንዱ የሆነው የአሜሪካው F-35 ላይ በኢራን የአየር መከላከያ ጥቃት መፈጸሙ ተረጋግጧል።

እንደ ሲኤንኤን (CNN) እና ሮይተርስ ዘገባ ከሆነ የዩናይትድ ስቴትስ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ቃል አቀባይ ካፒቴን ቲም ሆኪንስ ጄቱ በኢራን ላይ የውጊያ ተልዕኮ እያከናወነ በነበረበት ወቅት ጥቃት እንደደረሰበትና በአቅራቢያው ወደሚገኝ ወታደራዊ ጣቢያ በአስቸኳይ ለማረፍ መገደዱን አስታውቀዋል።

የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ (IRGC) በሰጠው መግለጫ ጄቱን የመታው "ራዳርን የማይፈልግና በሙቀት አማካኝነት ኢላማን የሚለይ" (Passive Infrared) አዲስ የቴክኖሎጂ ሲስተም በመጠቀም እንደሆነ ገልጿል።

ጥቃቱ የደረሰው በትላንትናው ዕለት መጋቢት 10 ቀን 2018 ዓ.ም (እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር መጋቢት 19 ቀን 2026) ከለሊቱ 8፡50 አካባቢ እንደሆነ ታውቋል።

አሜሪካ ጄቱ በሰላም ማረፉንና ፓይለቱም በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ብታረጋግጥም በጄቱ ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን ግን እስካሁን በዝርዝር አልገለጸችም። በሌላ በኩል የኢራን ወታደራዊ ባለስልጣናት አውሮፕላኑ "በከፍተኛ ሁኔታ ተጎድቷል" በማለት ድሉን እያከበሩ ይገኛሉ።

ይህ ክስተት ጦርነቱ ከተጀመረበት ከየካቲት 21 ቀን ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ አንድ የአሜሪካ ሰው ሰራሽ ተዋጊ አውሮፕላን በኢራን ጥቃት ሲደርስበት የመጀመሪያው ያደርገዋል።

ሁኔታው በክልሉ ያለውን ውጥረት ይበልጥ እንደሚያባብሰው ተሰግቷል።

__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን
menahiria fm

በቲክቶክና በት/ቤት የተሰራጨው ሱስ •••••••••••••••••••••••••••••••••••ታዳጊዎችን እየበላ ያለው አዲሱ ወጥመድ⁉️ወዳጄ... ታዳጊዎች "Drill Rap" እየሰሙ፣ በስፕራይ...
20/03/2026

በቲክቶክና በት/ቤት የተሰራጨው ሱስ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••
ታዳጊዎችን እየበላ ያለው አዲሱ ወጥመድ⁉️
ወዳጄ... ታዳጊዎች "Drill Rap" እየሰሙ፣ በስፕራይት ኮዳ ውስጥ "ቀይ መጠጥ" ይዘው ቲክቶክ ላይ ሲያሽቃብጡ ካየሃቸው ዝም ብለህ አትለፋቸው። ነገሩ "ሊን (Lean)" ይባላል። ለሳል ተብሎ የታዘዘን ሽሮፕ (እንደ Euphon ያሉ) ከለስላሳ መጠጥ ጋር በመቀላቀል የሚዘጋጅ "የመቃብር መንገድ" ነው።

1. "ሽሮፕ" አይደለም... "መርዝ" ነው! 🧪
እነዚህ የሳል መድኃኒቶች ውስጥ Codeine (ኮዴይን) የተባለ ንጥረ ነገር አለ። ኮዴይን ደግሞ ከሄሮይን ጋር የሚመደብ Opioid የተባለ አደገኛ ዕፅ ዘር ነው። ልጆቹ እንደ ፋሽን "ሊን" እያሉ የሚጠጡት ነገር፣ ሳያውቁት በከባድ ሱስ ተተብትበው ነፍሳቸውን ለሰይጣን እንዲሸጡ እያደረጋቸው ነው።

2. የ"ሊን" መራራ ዋጋ (The Deadly Effects)፦
ይህ መጠጥ ዛሬ "ፈገግ" ቢያደርጋቸውም፣ ነገ ግን የሚከተሉትን ይዞ ይመጣል፦
• የመተንፈስ ስራ ማቆም፦ ሳንባን በማደንዘዝ መተንፈስ እስከማቆም ያደርሳል።
• የልብ አመታት መዛባት፦ የልብ ምትን በማቀዝቀዝ ለድንገተኛ ሞት ይዳርጋል።
• የአካል ውድመት፦ በሂደት ጉበትና ኩላሊትን ሙሉ በሙሉ ያከሽፋል።
• አእምሮን ማጣት፦ በየጊዜው መጀዘብ፣ ከእውነታው ዓለም መራቅና ለሱስ ጥገኛ መሆን።
• Overdose፦ መጠኑ ሲበዛ መጨረሻው በወጣትነት መቀበር ነው!

3. "ፋሽን" ወይስ "ፍጅት"? 👁️
ዛሬ በትምህርት ቤቶችና በመንደሮች ይህ ነገር እንደ ቀልድ እየተስፋፋ ነው። ልጃችሁ ወይም ታናሻችሁ ያለ ምክንያት እንቅልፍ የሚጫጫነው፣ አእምሮው የተረበሸና እንዲህ ያሉ መጠጦችን በየቦታው የሚይዝ ከሆነ ቆም ብላችሁ መርምሩ። "የልጅ ነገር" ብላችሁ ዛሬ ችላ የምትሉት፣ ነገ ጥቁር ልብስ እንዳያለብሳችሁ!
🚨ሼር ይደረግ

አሜሪካ ወታደሮቿን ወደ መካከለኛው ምስራቅ የመላክ እቅድ የላትም - ዶናልድ ትራምፕኢራን ከአሜሪካ እና እስራኤል ጋር ወደ ግጭት የገባችበት የቀጣናው ውጥረት ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን፥ በተለይም ...
19/03/2026

አሜሪካ ወታደሮቿን ወደ መካከለኛው ምስራቅ የመላክ እቅድ የላትም - ዶናልድ ትራምፕ

ኢራን ከአሜሪካ እና እስራኤል ጋር ወደ ግጭት የገባችበት የቀጣናው ውጥረት ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን፥ በተለይም የኢነርጂ መሰረተ ልማቶችን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶች እየተፈጸሙ ይገኛሉ፡፡

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱ ተባብሶ መቀጠሉን ተከትሎ አሜሪካ ተጨማሪ እግረኛ ወታደሮችን ወደ መካከለኛው ምስራቅ ለመላክ እያጤነች ነው መባሉን ውድቅ አድርገዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ በዛሬው ዕለት ከጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናይ ታካይቺ ጋር በኋይት ሀውስ ካደረጉት ውይይት በኋላ በሰጡት አስተያየት ወታደሮቻችንን ወደየትም አናሰማራም ብለዋል፡፡

ነገር ግን ሀገራቸው እንደ አስፈላጊነቱ የትኛውንም ርምጃ ልትወስድ እንደምትችል መናገራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

ሰበር: ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ በሚያልፉ መርከቦች ላይ አዲስ ታክስ ለመጣል እየተንቀሳቀሰች እንደሆነ ተስማ::ቴህራን — የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ምክር ቤት (መጅሊስ) በሆርሙዝ የባሕር ወሽ...
19/03/2026

ሰበር: ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ በሚያልፉ መርከቦች ላይ አዲስ ታክስ ለመጣል እየተንቀሳቀሰች እንደሆነ ተስማ::

ቴህራን — የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ምክር ቤት (መጅሊስ) በሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ በኩል በሚያልፉ የንግድና የነዳጅ መርከቦች ላይ የአገልግሎት ክፍያና ታክስ ለመጣል የሚያስችል አዲስ የሕግ ረቂቅ እያዘጋጀ መሆኑ ተሰማ።

የቴህራን ተወካይ የሆኑት ሶማያህ ራፌ ለሕዝብ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፤ ወሽመጡ ለዓለም አቀፍ የንግድ ፍሰት፣ ለነዳጅና ለምግብ ምርቶች መተላለፊያነት ደህንነቱ ተጠብቆ እንዲቆይ ኢራን ከፍተኛ መስዋዕትነት እየከፈለች ነው።

በመሆኑም አገሪቱ ከዚህ ስትራቴጂካዊ መስመር ተገቢውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንድታገኝ የሚያስገድድ ሕግ በፓርላማ አባላት ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል።

እንደ ኢስና (ISNA) የዜና ወኪል ዘገባ፣ የፓርላማ አባሏ ኢራን በወሽመጡ ላይ ያላትን የሉዓላዊነት ስልጣን በዝርዝር አብራርተዋል። “እስካሁን ጠላቶቻችን ያለ ምንም ጋሬጣ ሲጠቀሙበት የነበረውን ምቾት ነጥቀናቸዋል” ያሉት ተወካይዋ፣ ይህ አዲስ አቅጣጫ ለተቃዋሚ ኃይሎች በቀላሉ የሚዋጥ እንደማይሆንም ጠቁመዋል።

ሶማያህ ራፌ አክለውም፣ ወቅታዊው ቀውስ በኢራን ወሳኝ ድል እንደሚጠናቀቅ ያላቸውን እምነት ገልጸው፤ ከድሉ በኋላ በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ማለፍ ለኢራን ባላንጣዎች ብርቱ ፈተና እንደሚሆን አስጠንቅቀዋል።

ይህ የኢራን እርምጃ በቀጣናው ባለው የንግድ ልውውጥና
በዓለም አቀፉ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች እየገለጹ ይገኛሉ።

Via BBC

ደምን በገንዘብ በሚሸጡ የጤና ተቋማት ላይ እርምጃ ይወሰዳል -የኢትዮጵያ ደም እና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎትየኢትዮጵያ ደም እና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት፥ ደም በነጻ ለታካሚዎች መድረ...
19/03/2026

ደምን በገንዘብ በሚሸጡ የጤና ተቋማት ላይ እርምጃ ይወሰዳል -የኢትዮጵያ ደም እና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት

የኢትዮጵያ ደም እና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት፥ ደም በነጻ ለታካሚዎች መድረስ እያለበት በተለያዩ የጤና ተቋማት የሚጠየቀውን ያልተገባ ክፍያ ለመከላከል ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚያደርግ አስታውቋል።

ተቋሙ አንድ ዩኒት ደም ለህክምና ዝግጁ ለማድረግ እስከ 46 ዶላር ወጪ እንደሚደረግበት የገለጸ ሲሆን፥ነገር ግን አሁንም በሀገሪቱ ያለው የደም ክምችት ከፍላጎቱ አንጻር በግማሽ ዝቅተኛ መሆኑን ጠቁሟል።

የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አምሳሉ ታዬ እንደገለጹት፤ ደም ከበጎ ፈቃደኞች በነጻ የሚሰበሰበው ለሰው ልጅ ህይወት በመሆኑ ማንኛውም የመንግስትም ሆነ የግል የጤና ተቋም ለታካሚዎች በነጻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

ሆኖም አንዳንድ ተቋማት ‘የአገልግሎት ክፍያ’ በሚል ስም ከታካሚዎች ገንዘብ እንደሚቀበሉ የሚደርሱ ጥቆማዎች እንዳሉ አመልክተዋል።

ይህን ብልሹ አሰራር ለመግታት ተቋሙ ከጤና ተቋማቱ ጋር በገባው የመግባቢያ ሰነድ መሰረት ተጠያቂነትን የሚያሰፍን ስርአት እየዘረጋ መሆኑንና በቀጣይም የደም አገልግሎትን የሚመለከት ህግ በማውጣት የቁጥጥር ስራውን ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

አንድ ዩኒት ደም ለህክምና ዝግጁ እስኪሆን ድረስ ለምን ከፍተኛ ወጪ እንደሚጠይቅ ማብራሪያ የሰጡት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ ደሙ ከተሰበሰበ በኋላ እንደ ኤች.አይ.ቪ፣ ሄፓታይተስ እና ሲፊሊስ ካሉ በደም አማካኝነት ከሚተላለፉ በሽታዎች ነጻ መሆኑን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ምርመራዎች ከፍተኛ ወጪ እንደሚጠይቁ ገልጸዋል።

ከዚህም ባለፈ ደሙን ወደ ቀይ የደም ሴል፣ ፕሌትሌት እና ፕላዝማ ለመለየት የሚሰሩ ስራዎች የሚጠይቁት የቴክኖሎጂና የኬሚካል ግብአቶች በሙሉ በውጭ ምንዛሬ የሚገዙ በመሆናቸው በአማካይ እስከ 46 ዶላር ወጪ እንደሚደረግበት አስረድተዋል።

በተጨማሪም ሀላፊው የሀገሪቱ የደም አቅርቦት ከፍላጎቱ በግማሽ እንደሚያንስ ገልፀዋል።

ሀና ሰይፉ

ethioFm

Address

Debre Birehan
Debre Birhan

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Page:

Share