ሸዋ/Shoa/

ሸዋ/Shoa/ Reflects on this Page personal Opinions and suggestion

10/10/2025

እንጅባራ ቅርንጫፍ

በአገው ምድር እንጅባራ ከተማ ትላንት መስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም ሥራ የጀመረው ቅርንጫፍ ዛሬም በድምቀት የአካባቢው ማኅበረሰብ በባሕል አልባሳት ጭምር ደምቆ የቁጠባ ሒሳብ እየከፈተ ይገኛል።

ቅርንጫፉ #አዲናስ እያለ ደንበኞቹን እያስተናገደ ይገኛል።

ማንኛውንም የአኩፋዳ መረጃ ለማግኘት https://t.me/akufadamicrofinance ይግቡ።

ስኬትን በተግባር

10/10/2025

የዕለቱ መልዕክት!

“ለማኅበረሰባችን የኤኮኖሚ እድገት እየሠራን ነው”
~ አቶ ተፈራ ወንድማገኘሁ
የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ

በዓለማችን በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ማቆጥቆጥ የጀመረው የአነስተኛ ገንዘብ ብድርና ቁጠባ (ማይክሮ ፋይናንስ) በእስያ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት በባንግላዴሽ እ.አ.አ በ1970ዎቹ በእነ መሐመድ የኑስ ገቢራዊ ምርምርና ትግበራ በመላው ዓለም ቀዳሚ የፋይናንስ አገልግሎት መስጫ ሆኗል።

እ.አ.አ በ2006 መሐመድ የኑስን ለኖቤል ሽልማት ያበቃቸው የማይክሮ ፋይናንስ ተደራሽነትና አሳታፊነት ላይ ዓለምን በማሳመናቸው እና ባመጡት የኤኮኖሚ አብዮት ነው።

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስም አድማሱን እያሰፋ በዛሬው ዕለት መስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም ብቻ 3 ቅርንጫፎችን #በደብረማርቆስ፣ #በፍኖተ-ሠላም እና #በአንጅባራ ከተሞች ከፍቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።የቅርንቻፎቹም ቁጥር 50 ደርሷል። በቅርብ ቀናት ተጨማሪ ቅርንጫፎችን እና ንዑስ-ቅርንጫፎችን በተለያዩ ዞኖች ከፍተን አገልግሎት እንሰጣለን።

ይህን በ7 ክልሎች እየተስፋፋ ያለውን የተቋሙን የፋይናንስ ተደራሽነትም በመላው የአገሪቱ ክልሎችና ኮርነር በማሳደግ ለአገር እና ለሕዝባችን ኤኮኖሚ አጋር ለመሆን እየሠራን ነው።

ስኬትን በተግባር!

የአበል ክፍያ ይፋ ሆነ‼️አዲሱ የመንግሥት ሰራተኞች የቀን ውሎ አበል አከፋፈል ይፋ ሆነ‼️የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አዲሱን የመንግሥት ሰራተኞች የቀን ውሎ አበል አከፋፈል ይፋ አድርጓል...
05/10/2025

የአበል ክፍያ ይፋ ሆነ‼️
አዲሱ የመንግሥት ሰራተኞች የቀን ውሎ አበል አከፋፈል ይፋ ሆነ‼️
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አዲሱን የመንግሥት ሰራተኞች የቀን ውሎ አበል አከፋፈል ይፋ አድርጓል።

በተጨማሪም ኮሚሽኑ ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ለመንግሥት የፌዴራል ተቋማት የሰው ሀብት እና ብቃት ሥራ አስፈፃሚዎች በአዲሱ የመንግሥት ሰራተኞች ደሞዝ እና የአበል አከፋፈል ዙሪያ መመሪያ ተሰቷል።

ለብዙ ችግሮች መፍትሔ የሚሰጥ ፕሮጀክት በደብረ ብርሃን ከተማ ሊገነባ ነው። ደብረ ብርሃን: መስከረም 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በኮሜዲያን እሸቱ መለሰ አማካኝነት የተቋቋመው "ለመጽደቅ የዘ...
05/10/2025

ለብዙ ችግሮች መፍትሔ የሚሰጥ ፕሮጀክት በደብረ ብርሃን ከተማ ሊገነባ ነው።

ደብረ ብርሃን: መስከረም 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በኮሜዲያን እሸቱ መለሰ አማካኝነት የተቋቋመው "ለመጽደቅ የዘለቄታ" የተሰኘ ሀገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅት በደብረ ብርሃን ከተማ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማስገንባት የመሠረት ድንጋይ አስቀምጧል።

ፕሮጀክቱ የአዳሪ ትምህርት ቤት፣ ፊዚኦ ቴራፒ ትምህርት ቤት፣ የተለያዩ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች፣ የመንገድ ሥራ ፕሮጀክቶች፣ የኮሜዲያን ተሰጥኦ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤት፣ ለሴቶች እና እናቶች የቢዝነስ ሥራ ማሠልጠኛ የሥራ ማዕከል ፕሮጀክቶችን በአካባቢዉ ላይ ያከናውናል ተብሏል።

በስድስት ሄክታር መሬት ላይ የሚገነባው ፕሮጀክቱ በደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር በእምዬ ምኒልክ ክፍለ ከተማ ሎሬት አፈ ወርቅ ተክሌ ቀበሌ ሥር በሚገኘው ጋንጎና ቦራሌ ንዑሥ ቀበሌዎች ላይ እንደሚገነባ ተገልጿል።

ፕሮጀክቱ ማኅበረሰቡ ለሚያነሳቸው የረጅም ጊዜ ጥያቄዎችን የሚመልስ ነው ያሉት የከተማ አሥተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ በድሉ ውብሸት ናቸው። ለብዙ ችግሮች መፍትሔ የሚኾን እንደኾነም ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ በሕዝብ ተሳትፎ የሚገነባ በመኾኑ ለሀገራችን ምሳሌ የሚኾን ነው ብለዋል። ተገንብቶ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ከተማ አሥተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ነው ያሉት።

በጤና ዕክል የመንቀሳቀስ ችግር ያለባቸው ልጆችን የሚንከባከቡ እናቶች፣ የፊዚዮ ቴራፒ ሥልጠና የሚያገኙበት እና የሥራ ዕድል መፍጠሪያ ማዕከል እንደሚኖረው የፕሮጀክቱ ሥራ አሥኪያጅ ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ ተናግረዋል።

ፕሮጀክቱ ዕውን እንዲኾን የአካባቢው ማኅበረሰብ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። ፕሮጀክቱም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ እንደሚጠናቀቅም አንስተዋል።

ምንጭ አሚኮ

04/10/2025

የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ!

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ አዳዲስ ለሚከፈቱ አዳዲስ ቅርንጫፎች፣ ንዑስ-ቅርንጫፎች እና ዋና መሥሪያ ቤት ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

የሥራ መደቦች፦

- የሒሳብ ባለሙያ (Accountant)
- ገንዘብ ያዥ (Cashier)
- የደንበኞች አገልግሎ መኮንን (Customer Service Officer)
- ጀማሪ የግዢ መኮንን (Junior Procurement Officer)
- ማርኬቲንግ እና ኮሙኒኬሽንስ መኮንን (Marketing & Communications Officer)

በማይክሮ ፋይናንስ እና በባንክ ልምድ ያላችሁ ከታች በተቀመጠው ማገናኛ (Link) እየገባችሁ ከዛሬ መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 7 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ማመልከት ትችላላችሁ።

https://forms.gle/oW8MHDQ8o4bnGTCf8

እንቁጣጣሽ ወደፊት ነው እንዴ?
03/10/2025

እንቁጣጣሽ ወደፊት ነው እንዴ?

አዲስ አበባ መስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ምአዲሱ የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ስኬል ሰንጠረዥ።እንኳን ደስ ያላችሁ!!🇪🇹🇪🇹🇪🇹
02/10/2025

አዲስ አበባ መስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲሱ የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ስኬል ሰንጠረዥ።
እንኳን ደስ ያላችሁ!!🇪🇹🇪🇹🇪🇹

ሰበር አሳዛኝ ዜና‼️ዛሬ 21/01/2018 ዓ.ም በአማራ ክልል  ምንጃር ሸንኮራ አረርቲ ማርያም ቤተክርስቲያን አመታዊ ክብረበዓልን አስመልክቶ ከጠዋቱ 2:45 ላይ እየተሰራ ያለው ቤተክርስቲያ...
01/10/2025

ሰበር አሳዛኝ ዜና‼️
ዛሬ 21/01/2018 ዓ.ም በአማራ ክልል ምንጃር ሸንኮራ አረርቲ ማርያም ቤተክርስቲያን አመታዊ ክብረበዓልን አስመልክቶ ከጠዋቱ 2:45 ላይ እየተሰራ ያለው ቤተክርስቲያን እየተጎበኘ ባለበት ሰዓት ለፊኒሺንግ የተረበረበ እንጨት ተደርምሶ እስካሁን ከ7 በላይ ሰዎች የሞቱ ሲሆን በበርካታ ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ከስፍራው ያሉ ሰዎች መረጃውን አድርሰውናል።
እስካሁን የተጎዱ እና የሞቱ ሰዎች በሰው ሀይል እየወጡ ሲሆን ሁሉም የመግስት አካላት ቀይ መስቀልን ጨምሮ ትብብር እንፈልጋለን ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
እስካሁን አስኬረን እየወጣ ሲሆን አረርቲ የሚገኙ ሙሉ የመንግሥት እና የግል ጤና ተቋሟት በተጎጂች እና በአስኬረን ሞልቷል ብለውናል።
አሳዛኝ አደጋ😥
ለተጎዱ ሰዎች መልካሙን ሁሉ እንመኛለን፣ህይወታቸውን ላጡ ነፍስ ይማር።

30/09/2025

Address

Debre Birhan

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሸዋ/Shoa/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share