ሸዋ/Shoa/

ሸዋ/Shoa/ Reflects on this Page personal Opinions and suggestion

ከውስጥ የማይጠፋው መምህር የደምስ አበራ ሞርዴ  ላይ የደረሰው ግፍ
25/05/2025

ከውስጥ የማይጠፋው መምህር የደምስ አበራ ሞርዴ ላይ የደረሰው ግፍ

ከውስጥ የማይጠፋው  መምህር  ደምስ አበራ ሞርዴ ላይ የደረስው  ግፍበቦታው የነበራችሁ የነበረው  ግፍ ላኩልን
25/05/2025

ከውስጥ የማይጠፋው መምህር ደምስ አበራ ሞርዴ ላይ የደረስው ግፍ

በቦታው የነበራችሁ የነበረው ግፍ ላኩልን

እኛና ብልጽግና ወስነናል
24/05/2025

እኛና ብልጽግና ወስነናል

ይበል ነው ጠንካራ ተቋማት ያስፈልጉናል
23/05/2025

ይበል ነው ጠንካራ ተቋማት ያስፈልጉናል

ንጋት ኮርፖሬት እስከ መጋቢት 2017 ዓ.ም መጨረሻ 6,460 ሠራተኞች በሥራ ላይ ይገኛሉ። ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ቀዳሚ ተግባራችን ነው።

21/05/2025

(መሠረት ሚድያ)- ሰሞኑን የጤና ባለሙያዎች በመላው ኢትዮጵያ እያካሄዱት ካለው የስራ ማቆም አድማ ጋር በተያያዘ ባሳለፍነው ሳምንት ግንቦት 6, 2017 ዓ/ም የቢቢሲ 'Focus on Africa' ፕሮግራም ላይ በመ...

ቤተሳይዳ የሚባል ሌባ በሸዋ በወሎ የሚነግድ እንዲሁ ደስ ሲለው ተራኛ ነኝ የሚል  #መምህር ታዴን አሳስሮታል ፣ትላንት ጄምሮ የቤተ ክህነቱን ፍጥጫ የብልጽግናን ሩጫ መረጃ ለኢትዮ ፎረም አደረ...
18/05/2025

ቤተሳይዳ የሚባል ሌባ
በሸዋ በወሎ የሚነግድ እንዲሁ ደስ ሲለው ተራኛ ነኝ የሚል
#መምህር ታዴን አሳስሮታል ፣ትላንት ጄምሮ የቤተ ክህነቱን ፍጥጫ የብልጽግናን ሩጫ መረጃ ለኢትዮ ፎረም አደረሰብን እያለ ሲያላዝን ነበር

እኔን ወንድሜን አየ ይሕቺ ሐገር አየ ግፍደግ አደረጉ የሚል ብአዴን አይጠፋም እኮ
18/05/2025

እኔን ወንድሜን አየ ይሕቺ ሐገር አየ ግፍ

ደግ አደረጉ የሚል ብአዴን አይጠፋም እኮ

(መሠረት ሚድያ)- ኢሳያስ በላይ ማነው ?

14/05/2025
10/05/2025

የዛሬ 7 አመት 10 ሺ ብር ደሞዙ 344 ዶላር ነበር። አሁን 6.05 ዶላር ነው። ለምን? የብርና የዋጋ ግሽበት።

፩ኛ፣ የብር ግሽበት የደሞዝ ቅናሽ ላይ ያለው ተጽዕኖ።

10 ሺ ብርን በ29 ስታካፍለው ዶ/ር አብይ ስልጣን በያዘ ዓመት 10ሺ ብር 344.83 USD ዶላር ነበር።

ዛሬ 7 አመት የብር ማሽቆልቆል ቦሀላ 10ሺን /136 ብር ስታካፍለው 73.53 USD ይመጣል። ይሄንን በቀላሉ $1=29 birr ነበር አሁን ደግሞ $1= 136> አድርገህ ማካፈል ነው።

፪ኛ፣ የዋጋ ግሽባትን በደሞዝ ላይ ያለውን ተጽዕኖ ደግሞ እንይ።

የኢትዮጵያ ዋጋ ግሽበት ከ37% ገደማ ነበር። ለዚህ ሂሳብ በአማካይ 30% እንበለውና እናስላው። ይህ ማለት ደሞዝ በ30% በአመት እየቀነሰ ነው ማለት ነው።
10 ሺ ብር ደሞዝ ከ7 አመት የኢኮኖሚ ፓሊሲ በሗላ በ inflation ስታሰላው 823 birr ይሆናል።

ይህ ማለት አንድ ሰራተኛ ደሞዙ 10ሺ ብር ሳይሄን 823 ብር ነው።

ልድገመው!

ዛሬ በዋጋ ግሽበት ብቻ የአንድ ሰው ደሞዝ ከ10,000 ወደ 823 ብር ተቀንሷል።

እዚህ ላይ ላቁም ወይስ የዋጋ ግሽበትንና የብርን መውደቅ አብረን እንስራው?

እኔ ኢትዮጵያ ውስጥ ቤቱን ሲያፈርሱበት ለምን ከማለት ይልቅ ከፍቶት የሚታነቅም ሰው ስላለ ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው እንዳይሆን።

ይሁንና 823 birr/ 136 birr ስታካፍለው የምታገኘው= $6.05 USD ነው።

ስለዚህ የዛሬ 7 ዓመት 10 ሺ ብር ደሞዝተኛ አሁን ደሞዙ 6.05 ዶላር ነው።

ዶክተሮቹ መቼም በሂሳብ A ወይንም B ሳያመጡ ህክምና ኮሌጅ አልገቡም። ስለዚህ ደሞዛቸው ከ344 ዶላር ወደ 6 ዶላር መውረዱን ለማወቅ ግዜ አይፈጅባቸውም። አሁን የደሞዛቸው ማሻሻያ 344*136 መሆን አለበት። ማለትም 46,784 ብር። ይህ ያስማማል።

ሌላው 6ዶላር ተቀብሎ ገብቶ ሚስቱን ብሩን ቀልብ አታሳጭው የሚል ደግሞ ብዙ ነው:-) ሚስቶች በ6 ዶላር 6 ቤተሰብ በሚመግቡት በጸሎት በረከት መሰለኝ:-)
©yared Hailemeskel

እጎኑ የነበሩ ወንድሞቹ እንዲህ የሚሆኑት የሚሰቃዩት በእውኑ  ጽንፈኛ ስለሆኑ ነው   #ብአዴን -ብልጽግና
03/05/2025

እጎኑ የነበሩ ወንድሞቹ እንዲህ የሚሆኑት የሚሰቃዩት በእውኑ ጽንፈኛ ስለሆኑ ነው
#ብአዴን -ብልጽግና

#ዜናመሠረት አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያሌው በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ጥቃት ተፈፀመባቸው

(መሠረት ሚድያ)- ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እስረኞች ወደ ማደሪያቸው ከገቡ በኋላ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ላይ ቀይ ቦኔት የጫኑ የፌደራል ፖሊሶች ቁልፍ ሰብረው ገብተው አቶ ክርስቲያን ታደለን እና አቶ ዮሐንስ ቧያሌውን ከእስር ቤታቸው እንዳስወጧቸው እና እስከ ሌሊቱ 7:00 ሰዓት ድረስ ሜዳ ላይ አስተኝተው እንዳሳደሯቸው ምንጮቻችን ለመሠረት ሚዲያ ገልፀዋል።

በተመሳሳይ ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ፣ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፣ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፣ ፕሮፌሰር መዓረጉ ቢያበይን እና ዶ/ር ሲሳይ አውግቸው ይሄው ድርጊት የተፈፀመባቸው መሆኑን አርብ ሚያዚያ 24 ቀን 2017 ዓ/ም ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርበዋል።

"ቀይ ቦኔት የጫኑ የፌደራል ፖሊሶች ምሽት 12:00 ሰዓት በሩን በኃይል ከፍተው ከገቡ በኋላ ሁላችንንም እጃችንን ወደ ላይ እንድናደርግ አዘው ሜዳ ላይ በሰልፍ አቁመውን በመሳሪያ ሲያስፈራሩን ነው ያደሩት" ሲሉ ነው ለፍርድ ቤቱ የገለፁት።

"ቀደም ሲል በምርመራ ወቅት ድብደባ የፈፀሙብን የመንግስት ሹማምንት ከሁለት ዓመት በኋላ የቂሊንጦ ማረሚያ ቤትን አጥር ጥሰው፣ የተኛንበትን ቤት በር በኃይል ሰብረው እስከ ሌሊት 7:00 ሰዓት ድረስ ሜዳ ላይ አሰልፈውን አሳድረውናል። ሕይዎታችን አደጋ ላይ መሆኑን ሕዝባችን እንዲያውቅልን" ሲሉ አሳስበዋል።

አቶ ዮሐንስ ቧያሌው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ ከአንድ አመት በፊት በአዋሽ አርባ ወታደራዊ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት የከፋ የጤና መታወክ ገጥሟቸው እንደ ነበር ይታወቃል። በመሆኑም ጤናቸው ገና ሳያገግም በድጋሜ ሜዳ ላይ ተሰልፈው እንዲያድሩ መደረጉ ለባሰ የጤና እክል ተጋልጠዋል ሲሉ ምንጮቻችን ለመሠረት ሚዲያ ተናግረዋል።

የፌደራል ፖሊሶች የማረሚያ ቤቱን አጥር ሰብረው ለምን እንደገቡ እና በሽብር የተጠረጠሩ እስረኞችን ለምን ከክፍላቸው አስወጥተው ሜዳ ላይ እንዳሳደሯቸው የታወቀ ነገር የለም።

መረጃን ከመሠረት!

Address

Debre Birhan

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሸዋ/Shoa/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share