Dembecha zuria Communication

Dembecha zuria Communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dembecha zuria Communication, Media/News Company, Dembecha Woreda Government Communicationየደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን, Dembech'a.

ጥበበ ጊዮን  ሆስፒታል  «ሪፈር» ለማቆም እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፤ታካሚዎችን ወደ ሌላ የህክምና ተቋም ሳይልክ  የተሟላ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት እየሠራ መሆኑን የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ...
14/10/2025

ጥበበ ጊዮን ሆስፒታል «ሪፈር» ለማቆም እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፤

ታካሚዎችን ወደ ሌላ የህክምና ተቋም ሳይልክ የተሟላ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት እየሠራ መሆኑን የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስታወቀ፡፡

የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር በቃሉ ውብሸት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የአውሮፓ ህብረት ባደረገው ድጋፍ የሆስፒታሉን የቀዶ ጥገና ክፍሉን የማዘመንና መሰረተ ልማቶችን የማደስ ስራ እየተከናወነ ይገኛል።

ይህም ወደአዲስ አበባና ዉጭ ሀገራት በሪፈር የሚላኩ ታካሚዎች በሆስፒታሉ እንዲገለገሉ አቅም የሚፈጥር ይሆናል። በተጨማሪም ስራው ሲጠናቀቅ አሁን ከሚያስተናግዳቸው በላይ የቀዶ ህክምና ተማሪዎችን ለመቀበልም የሚያስችለው ይሆናል፡፡

ሆስፒታሉ በጸጥታ ችግር ከደረሰበት ጉዳት በማገገም በተጠናቀቀው ዓመት በተመላላሽ 20ሺ ታካሚዎችን፤ በአጠቃላይ ህክምና መቶ ሺህ የሚደርሱ ታካሚዎችን ያገለገለ ይገኛል። ያሉት ዶክተር በቃሉ አጠቃለይም 10 ሚሊዮን ለሚደረስ ህዝብ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።

በተጨማሪ ከ300 በላይ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን ጨምሮ ከሁለት ሺ በላይ እያስተማረ እንደሚገኝና በ12 የስፔሻላይዜሽንና በሰባት የሰብ ስፔሻላይዜሽን ፕሮግራሞች ትምህርት እንደሚሰጥም ጠቁመዋል ሲል የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን ዋቢ አድርጎ Amhara Communications ዘግቧል።

ዘላቂ ሰላምን ሊያረጋግጡ በሚችሉ ወቅታዊ   ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሄደ ‎ ‎በምዕራብ ጎጃም ዞን ደምበጫ ከተማ በወቅታዊ የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ከሃይማኖት  አባቶች ጋር ዘላቂ ሰላ...
14/10/2025

ዘላቂ ሰላምን ሊያረጋግጡ በሚችሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሄደ
‎ ‎በምዕራብ ጎጃም ዞን ደምበጫ ከተማ በወቅታዊ የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ከሃይማኖት አባቶች ጋር ዘላቂ ሰላምን ሊያረጋግጡ በሚችሉ በወቅታዊ የሰላም ጉዳይ ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል።

‎የውይይት መድረኩ አላማ በአካባቢው ሊከሰቱ የሚችሉ የፀጥታ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመመከትና የህብረተሰቡን ሰላማዊ አኗኗር ለማረጋገጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ለመምከር የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል።

‎በውይይቱም ላይም አካባቢያችን አሁን ላለበት አንፃራዊ ሰላም ከፍተኛ ሚና የሚይዘው የሃይማኖት አባቶች በመሆናቸው አሁንም ቢሆን አንድነታችን በማጠንከር ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በልዩ ትኩረት ለሰላማችንና ለልማታችን መስራት ይገባናል ተብሏል ።

‎ለሰላም እንቅፋት የሆኑ በጫካ ያሉ የታጠቁ ሃይሎችም መንግስት የሚሰጠውን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደ ሰላም መመለስ እንዳለባቸው የሃይማኖት አባቶች ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተገልጿል።

‎ሰላም የሁሉም መሠረት በመሆኑ ለሰላማችን ፣ ለልማታችን በጋራ ቁመን በመዘመር ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ የሁላችን ሃላፊነት ሊሆን ይገባል ተብሏል ።

‎በከተማው የአካባቢውን ሰላም ለማረጋገጥ ከህብረተሰቡ ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥልና ከተማዋንም ከማንኛውም የሰላም መደፍረስ ለመጠበቅ የህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን በመግለፅ በህገወጥ ተግባራት ዙሪያ ወቅታዊ መረጃዎችን ለፀጥታ አካላት ማድረስ ተገቢ መሆኑ በመድረኩ ማጠቃለያ ተመላክቷል።

‎በመጨረሻም በውይይቱ በተነሱ የመፍትሄ ሃሳቦች ላይ ተመስርቶ የአካባቢን ሰላም በንቃት መከታተልና መጠበቅ ተገቢ መሆኑን ገልፀው ጸጥታን ማስጠበቅ የመንግስት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆኑ ተገልጿል ሲል ደምበጫ ከተማ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

ዜና ዕረፍትለእግርኳስ የተለየ ፍቅር የነበራቸው የዳሞት ከነማ እግር ኳስ መስራች የነበሩትን አቶ ዘነበ አሰፋን ከዚህ አለም በሞት ተለዩ።አሠልጣኝ ዘነበ አሰፋ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ትልቅ ቦታ...
14/10/2025

ዜና ዕረፍት

ለእግርኳስ የተለየ ፍቅር የነበራቸው የዳሞት ከነማ እግር ኳስ መስራች የነበሩትን አቶ ዘነበ አሰፋን ከዚህ አለም በሞት ተለዩ።

አሠልጣኝ ዘነበ አሰፋ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ትልቅ ቦታ የደረሱ ተጫዋቾች እና አሠልጣኞች ላይ የራሳቸውን አሻራ ያሳረፋ ነበሩ።

የዳሞት ከነማ እግር ኳስ ክለብ ከምስረታው ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ሊግ እንዲደርስ የአሠልጣኝ ዘነበ ሚና ግንባር ቀደም ነበር።

አቶ ዘነበ አሰፋ ዳሞት ከነማ እግር ኳስ ክለብ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ ጠንክረው በማሠልጠን በአንድ ዓመት ብቻ ከወረዳ እስከ ክልል በተደረጉ ውድድሮች ሦስት ዋንጫዎችን ለአካባቢው ሕዝብ ያስገኙ አሰልጣኝ ነበሩ።

ለተጫዋቾቸ አሠልጣኝ ብቻ ሳይኾን አባትም የነበሩ። ቁርጠኝነት እና የዓላማ ጽናት የአቶ ዘነበ መገላጫዎች ነበሩ።

በአካባቢው ስፖርት አፍቃሪያን ዘንድ "የእግር ኳሱ ንጉስ" እስከ መባል የደረሱ ስመጥር ነበሩ። ተጫዋቾችን በሥነ ምግባር ኮትኩቶ በማሳደግ እና ለሙያው ልዩ ክብር በመስጠት ይታወቁ ነበር።

አሠልጣኝ ዘነበ አሰፋ ለዳሞት ከነማ እግር ኳስ ክለብ ላበረከቱት አስተዋጽኦ በክለቡ ተጫዋቾች በከተማ አስተዳደሩ እና በአካባቢው ስፖርት አፍቃሪያን ዕውቅናና ሽልማት ተሰጥቷቸ ነበር።

የፍኖተ ሰላም ከተማ አሥተዳደር ለዳሞት ከነማ እግር ኳስ ክለብ አሠልጣኝ ዘነበ አሰፋ ለስፓርቱ ላበረከቱ አስተዋፅጾ የቤት መስሪያ ቦታ እና ልዩ ልዩ ማበረቻቻዎችን ከመስጠት በተጨማሪ የፍኖተ ሰላም ከተማ ስታዲየም በር በስማቸው የተሰይሞላቸው ነበር።

ተቋማችን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለስፖርት አፍቃሪያን መፅናናትን ይመኛል !!
West Gojjam Communications

"የዞኑን ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚተጋ የብልጽግና አባልና አመራር ለመፍጠር እየተሰራነው"- አቶ አባይ አለሙ የምዕራብ ጎጃም ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊየምዕ...
14/10/2025

"የዞኑን ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚተጋ የብልጽግና አባልና አመራር ለመፍጠር እየተሰራነው"- አቶ አባይ አለሙ የምዕራብ ጎጃም ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ

የምዕራብ ጎጃም ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ2018 በጀት አመት የ1ኛው ሩብ አመት የአባላት ኮንፈረንሰስ በሁለት ክላስተር በመክፈል እያካሄደ ነው።

የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አባይ አለሙ አስተዳድር ክላስተር ላይ በሚካሔደው ኮንፈረንስ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።

ኃላፊው በንግግራቸው ኮንፈረንሱ ፓርቲው ባለፉት ሦስት ወራት ባከናዎናቸው ስራዎች የተገኙ ስኬቶችን በማጎልበትና ጉድለቶችን በመሙላት ሁለንተናዊ ብልጽግናንን ለማረጋገጥ ያለመ ነው ብለዋል።

ብልጽግና በሁሉም ዘርፎች መሰረረታዊ ለውጥ እያመጣ የሚገኝ ፓርቲ መሆኑንም አቶ አባይ ገልጸዋል።

የዞኑ የብልጽግና ፓርቲ አባላት ፓርቲው በ2ኛው መደበኛ ጉባኤው ያስቀመጣቸውን አቅጣጫዎች ተከትለው በመስራት የህዝቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የነቃ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸውን አንስተዋል።

ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ የዞኑን ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚተጋ የብልጽግና አባልና አመራር በመፍጠ የፓርቲውን ማህበራዊ መሰረት ለማስፋት አልሞ እየሰራ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

ለውይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ የአስተዳድር ክላስተር ህብረት ሰብሳቢ አቶ እሱባለው ሁነኛው እየቀረበም ይገኛል
West Gojjam Communications

ፈተናዎች ያልበገሩት የቀለም ሰውባሕር ዳር፡ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በችግርም ውስጥ አልፎ በሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ ከቻሉ ተማሪዎች መካከል ተማሪ አማኑኤል ዓ...
13/10/2025

ፈተናዎች ያልበገሩት የቀለም ሰው

ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በችግርም ውስጥ አልፎ በሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ ከቻሉ ተማሪዎች መካከል ተማሪ አማኑኤል ዓለምነህ አንዱ ነው። ተማሪ አማኑኤል በሀገር አቀፍ ፈተናው 526 ነጥብ ማስመዝገብም የቻለ ተማሪ ነው።

ተማሪ አማኑኤል ከ9ኛ እስከ 11ኛ ክፍል በፍኖተ ሰላም ከተማ በጎጃም አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መማሩንም ይናገራል፡፡

ተማሪ አማኑኤል በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ሀገራዊ ተፈታኝ ቢኾንም በነበረው ሀገራዊ ግጭት ምክንያት ሳይፈተን መቅረቱን ይገልጻል፡፡

በ2017 የትምህርት ዘመንም በአካባቢው ትምህርት ሙሉ በሙሉ ባለመጀመሩ ሁለት ዓመት ወደ ኋላ ላለመቅረት በሚል ቁጭት መሸኛ ይዞ ወደ አንከሻ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመሄድ ትምህርት መጀመሩን ተናግሯል፡፡

"ከቤተሰብ መለየት ለኔ የመጀመሪያ ጊዜየ ቢሆንም ተምሬ ጥሩ ውጤት በማምጣት ዩንቨርሲቲ መግባት ከፍተኛ ህልሜ ነበር" ይላል ተማሪ አማኑኤል።

ማንኛውንም ችግር በመቋቋም ለመወጣት ራሱን ዝግጁ አድርጎ ትምህርት ሊያገኝበት ወደሚችለው ቦታ ማቅናቱንም ያስረዳል።

ለመማር ከፍተኛ ፍላጎት ያለው ተማሪው ወደ ሚማርበት ቦታ አቅንቶ የሚከራይ ቤት ማግኘት ችግር ኾኖበት እንደነበርም ጠቁሟል።

የተማሪ አማኑኤልን ችግር የተመለከቱ የአካባቢው ነዋሪ እና የአንከሻ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር አለሙ የኔሰው በገጠመው የኪራይ ቤት ችግር ምክንያት ትምርቱ እንዳይስተጓጎል ነጻ የመኖሪያ ቤት እንደሰጡት ይናገራል፡፡

ተማሪ አማኑኤል ከነጻ ቤት መስጠት ባለፈ ይደረግለት የነበረው ቤተሰባዊ ፍቅር እና እንክብካቤ ከቤተሰብ ርቆ መኖሩ እንዳይሰማው እንዳደረገውም ገልጿል፡፡

ይህም ትኩረቱን ሙሉ በሙሉ ለትምህርቱ በመስጠት እና በማጥናት ጥሩ ውጤት እንዲያስመዘግብ እንዳገዘው አብራርቷል።

ስለተደረገለት ድጋፍም አመሥግኗል፤ ሌሎች ተማሪዎችም ምንም አይነት ችግር ሳይበግራቸው ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም እና በርትተው በማጥናት ለውጤት እንዲበቁ መልዕክቱንም አስተላልፏል፡፡

መምህር አለሙ የኔሰው ለአሚኮ እንዳሉት ተማሪ አማኑኤል በአንከሻ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከተመዘገበ በኋላ የኪራይ ቤት በማጣቱ ትምህርቱ እንዳይቋረጥ አስፈላጊውን እገዛ አድርገዋል።

ተማሪው በወቅቱ የነበረው ውጤት ከጥሩ ሥነምግባር ጋር የተሻለ ስለነበረ ለጥሩ ውጤት እንዲበቃ በማሰብ ነጻ ቤት መስጠታቸውን ነው የጠቆሙት።

በተጨማሪም መምህር አለሙ አጋዥ መጻሕፍትን እና ቤተሰባዊ ፍቅርን በመስጠት ትኩረቱ ትምህርቱ ላይ ብቻ እንዲኾን ማድረጋቸውን ነው ያብራሩት፡፡

"ባመጣው ከፍተኛ ውጤት እና ለዚህ ውጤት በመብቃት እኔ የበኩሌን አስተዋጽኦ ማድረጌም በጣም ደስ ብሎኛል" ነው ያሉ፡፡

ይህ መደጋገፍ ጥሩ መኾኑን ገልጸው አንዱ ሌላውን ቢያግዝ ሁሉም ነገር ቀላል መኾኑን የተማሪው ስኬት ማሳያ ነው ብለዋል፡፡

በቀጣይም እሱ የነበረበትን ዶርም ሌሎች ተቸግረው ለሚመጡ ተማሪዎች ክፍት በማድረግ ድጋፍ እንደሚያደርጉም ጠቁመዋል፡፡

የተማሪ አማኑኤል ትልቅ ወንድም አቶ መብራቱ ፈንታ ወንድማቸው ስለአማኑኤል ሲናገሩ
ሙሉ ጊዜውን ለትምህርቱ የሚሰጥ፣ ሰዓቱን በአግባቡ የሚጠቀም፣ ያልገባውን መምህራንንም ኾነ ጓደኞቹን በስልክ ሳይቀር የእያንዳንዷን ነገር ለመረዳት የሚጠይቅ ጎበዝ ተማሪ ነው ብለዋል፡፡

በሀገራዊ ችግሩ ምክንያት አንድ ዓመት በማቋረጡ ለሁለተኛ ጊዜ እንዳይደገም በራሱ ተነሳሽነት ወደ አገው ግምጃ ቤት በመሄድ መማሩን ተናግረዋል።

ከቤተሰብ ርቆ ብቻውን ሆኖ መማሩ ለችግር እንዳያጋልጠው በቤተሰቡ ስጋት ነበረ ብለዋል፡፡

ይህ ስጋት ብዙም ሳይቆይ ለተማሪ አማኑኤል ነጻ የመጠለያ ዶርም በመስጠት እንደቤተሰብ ኾነው ሊያስተምሩት የሚችሉ የአካባቢው ነዋሪ መምህር አለሙ የኔሰው ፍላጎታቸውን በመግለጻቸው ከስጋት እንዳወጣቸው ተናግረዋል፡፡

ከመምህር አለሙ የኔሰው ጋር ምንም አይነት ቤተሰባዊ ግንኙነት እንደሌላቸው እና ከዛ በፊትም እንደማይተዋወቁ የተናገሩት አቶ መብራቱ መምህሩ ቤቱን ብቻ ነጻ መስጠት ብቻ ሳይኾን ቀለብ በሚዘገይበት ጊዜ የሚያስፈልገውን በማሟላት እና የሚያስፈልገውን እንክብካቤ በማድረግ ያስተማሩት የቀለም ቤተሰቦቹ እንደኾኑም አብራርተዋል።

ይህንን መልካምነት በቃላት ብቻ መግለጽ አይቻልም፤ ትልቅ ባለውለታችን ናቸው፤ በአጠቃላይ የአካባቢው ማኅበረሰብ እጅግ በጣም ጥሩ ነው ብለዋል፡፡

መምህር አለሙ ለተማሪ አማኑኤል የሚያስፈልገውን ነገር በማሟላት ያሳዩት በጎ ተግባር እንዳስተማራቸው እና እሳቸውም በትምህርት ሥራ ላይ በጎ ሥራ ለመሥራት እንዳነሳሳቸው ነው አቶ መብራቱ ፈንታ የጠቆሙት።

የአንከሻ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርእሰ መምህር ደሳለው አበራ ተማሪ አማኑኤል ዓለምነህ በ2017 መጀመሪያ ከፍኖተሰላም ከተማ በሀገራዊ ግጭቱ ምክንያት ወደ አንከሻ ትምህርት ቤት ለመማር ሲመጣ ጥሩ ውጤት እንደነበረው ተናግረዋል።

ትምህርት ቤቱም ባለው ቦታ ተማሪውን ተቀብሎ ለማስተማር እንደፈቀደለትም ነው ያብራሩት።

ተማሪ አማኑኤል የትምህርት አቀባበሉ ጥሩ እንደነበር መምህራኑ ይገልጹ እንደነበርም ጠቁመዋል።

ትምህርት ቤቱ ተማሪ አማኑኤልን ጨምሮ 40 የሚኾኑ ጎበዝ ተማሪዎችን በመምረጥ ቅዳሜ፣ እሑድ እና የምሳ ሰዓትን ጨምሮ ቤተ መጽሐፍትን ክፍት በማድረግ ሙሉ ጊዜያቸውን እንዲያጠኑ በማድረግ፣ የተመረጡ መምህራንን በመቅጠር እና ተጨማሪ ማካካሻ ትምህርት እንዲማሩ በማድረግ እገዛ ስለመደረጉም አስረድተዋል፡፡

በዚሁ ትምህርት ቤት የሥነ ዜጋ መምህር አለሙ የኔሰው ለተማሪው አስፈላጊውን እገዛ በማድረግ ያደረጉት በጎ ተግባር ለሌላውም አስተማሪ ነው ብለዋል።

ተማሪውም ጥሩ ውጤት በማምጣት የትምህር ቤቱ አንደኛ በመኾን ውጤት አስመዝግቧል ነው ያሉት፡፡ በዚህም በዞንም በክልልም ከተሸለሙ ተማሪዎች አንዱ መኾን እንደቻለም ጠቁመዋል፡፡

ርዕሰ መምህሩ ተማሪ አማኑኤል በለመደው አካባቢ ሆኖ የቤተሰብ እገዛ እና ፍቅር ሳይለየው ቢማር ኖሮ ከዚህ የተሻለ ውጤት እንደሚያስመዘግብ ጥርጥር የለኝም ነው ያሉ፡፡

በዚህም ትምህርትን ከማንኛውም ፖለቲካ ነጻ በማድረግ ለነገ ሀገር ተረካቢ የኾኑ የተማረ ትውልድ ለማፍራት ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡

#አሚኮ

አረጋውያን በወቅቱ ለሀገራችን ታሪክ እየጣሉ ለቀጣዩ ትውልድ ቅርስ እያወረሱ የሚሄዱ ባለውለታዎች በመሆናቸው ልንከባከባቸውና አክብረን ልንይዛቸው እንደሚገባ ተገለፀ።በምዕራብ ጎጃም ዞን ደምበጫ...
13/10/2025

አረጋውያን በወቅቱ ለሀገራችን ታሪክ እየጣሉ ለቀጣዩ ትውልድ ቅርስ እያወረሱ የሚሄዱ ባለውለታዎች በመሆናቸው ልንከባከባቸውና አክብረን ልንይዛቸው እንደሚገባ ተገለፀ።

በምዕራብ ጎጃም ዞን ደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ‎"የአረጋውያንን ደህንነትና መብቶች በመጠበቅ ሁለንተናዊ ሃላፊነታችንን እንወጣ" በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ35ኛ፣ በሀገራችን ደግሞ ለ34ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአረጋውያን ቀን ተከብሮ ውሏል።

በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት የሴቶች ግንዛቤ ተሳትፎ ማስፋፊያ ቡድን መሪ አቶ አድገህ ልንገርህ አረጋውያን በወቅቱ ለሀገራችን ታሪክ እየጣሉ ለቀጣዩ ትውልድ ቅርስ እያወረሱ የሚሄዱ ባለውለታዎች በመሆናቸው ልንከባከባቸውና አክብረን ልንይዛቸው ይገባል ብለዋል።

አቶ አድገህ አክለውም የአረጋውያን ቀን ሲከበር ቀኑን ለማስታወስ ብቻ ሳይሆን አረጋዊያን ለሀገራችን ትልቅ ባለውለታዎች መሆናቸውን አውቀን ልንደግፋቸውና በቀጣይም የበለጠ ለማጠነከር ታስቦ እንደሆነ ገልፀዋል።

‎የአረጋውያን ደህንነትና መብቶች ላይ ሁላችንም ያገባናል ብለን በትኩረት ልንሰራ ይገባል ያሉት አቶ አድገህ የአረጋውያንን ደህንነት እና ማህበራዊ ተሳትፎ የማረጋገጡ ጉዳይ የተቋሙ ብቻ የሚሰጥ ሳይሆን፣ የሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል ርብርብ የሚጠይቅ ነው ብለዋል።

‎ ተሳታፊዎች በበኩላቸው እንደገለጹት አረጋውያን የትውልድ መሰረት፣የሀገር ባላደራዎች በመሆናቸው ጧሪ ቀባሪ የሌላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች በመለየትመንከባከብ፣ ከሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር እየተናበቡ መስራት፣ ግብዓት ማፈላለግ፣ ስልጠና መስጠትና ማበረታታት ያስፈልጋል ብለዋል።

በወረዳችን አንዳንድ አረጋውያን ላይ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች ይደርስባቸዋል ያሉት ተሳታፊዎቹ አረጋውያን የነበሩ ወግ ባህሎች፣ ቅርሶች እንዳይጠፉ መሰረቶች ናቸው ብለዋል።

‎የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን ሃላፊ ወ/ሮ አዳነች ፀጋ እንደገለጹት በወረዳችን የአሉትን የአረጋዊያን ተደራጅተው ወደ ስራ ሊገቡ የሚችሉበትን መንገድ ተቋሙ በበለጠ በባለቤትነት ይዞ መስራት አለበት ብለዋል።

ዛሬም እንደትላንቱ የነበሩንን ወግ ባህላችንን፣ ቅርሶቻችንንና እሴቶችን የመጠበቅ ልምዳችንን ልናዳብር ይገባል ነው ያሉት። ሀገራችንን ጠብቃችሁ ለተተኪው ትውልድ ያስተላለፋችሁ እናንተ በመሆናችሁ አሁንም ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በማገናዘብ ሰላምን መስበክና ለሰላም ትልቅ ዋጋ በመስጠት ላይ ኃላፊነት አለባችሁ ብለዋል።

‎የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ነገሰ እንደተናገሩት ሀገር እንደ ሀገር እንዲቀጥል፣ ቀጣይነት እንዲኖረው የአረጋውያን ድርሻ የጎላ ነው ብለዋል።

‎በተለያዩ ቀበሌዎች ለችግር ተጋላጭ የሆኑ አረጋውያን በርካታ ናቸው ያሉት ኃላፊዋ በቀጣይ በማህበር እንዲደራጁ፣ ባህል እሴታቸውን እንዲጠብቁ፣ መብታቸው እንዲከበር፣ ሀብት ንብረታቸውን በተገቢው መንገድ እንዲጠቀሙበት በትኩረት እንሰራለን ብለዋል። በቀጣይ ከዚህ የበለጠ አረጋውያንን በየአካባቢያችን አሰባስበን ማደራጀት አለብን ብለዋል።


‎ኃላፊዋ አክለውም የተደራጁ አረጋውያን የበለጠ መጠናከር እና ያልተደራጁት ደግሞ ተደራጅተው ማህበር መመስረት እንዳለባቸውና እራሳቸው ከተረጅነት የሚወጡበትን መንገድ እንዲያመቻቹ ሁሉ የሚመለከተው የማህበረሰብ ክፍል የድርሻውን እንዲወጣ ሲሉ አሳስበዋል።

‎በመጨረሻም አረጋውያን ለሰላም መስፈን ድርሻቸው የጎላ በመሆኑ ሰላም እንዲሰፍን በትኩረት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

አረጋውያኑ ድጋፍ ተደረገላቸው!በደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት "ለአረጋዊ ደህነነትና መብቶች መጠበቅ ሁለንተናዊ ሃላፊነታችንን እንወጣ" በሚል መሪ ቃል የአረጋውያን...
13/10/2025

አረጋውያኑ ድጋፍ ተደረገላቸው!

በደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት "ለአረጋዊ ደህነነትና መብቶች መጠበቅ ሁለንተናዊ ሃላፊነታችንን እንወጣ" በሚል መሪ ቃል የአረጋውያን በዓል ያከበረ ሲሆን ደጋፊ እና አቅም ለሌላቸው አረጋውያን የፍራሽ ድጋፍ አድርጓል።

ከተለያዩ ለጋሽ አካላት ድጋፉን ያሰባሰበው ጽ/ቤቱ አጋዥ እና ድጋፍ የሌላቸውን የወረዳው አረጋውያን በመለየት ድጋፍ አድርጓል።

ድጋፉን የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሰናይት መገሰ ጽ/ቤቱን በመወከል ድጋፉን አከርክተዋል።

የደምጫ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ከትምህርት አመራሮች ጋር በመማር መስተማሩ ዙሪያ ውይይት እያካሔደ ነው።በምዕራብ ጎጃም ዞን የደምጫ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ከትምህርት አመራሮች ጋር በመማር መ...
13/10/2025

የደምጫ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ከትምህርት አመራሮች ጋር በመማር መስተማሩ ዙሪያ ውይይት እያካሔደ ነው።

በምዕራብ ጎጃም ዞን የደምጫ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ከትምህርት አመራሮች ጋር በመማር መስተማሩ ዙሪያ ውይይት እያካሔደ ይገኛል።

በውይይቱ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መስፍን ልየው በከተሞች የተጀመረውን የመማር ማስተማር ተደራሽ ለማድረግበሚደረገው ርብርብ የትምህርት ቤት አመራሩ ትኩረት ሠጥቶ እንዲሰራ አጽንኦት ሰጠው ተናግረዋል።

ትውልድ ያለትምህርት ሀገር ያለ ፤ትውልድ አይገነባም ያሉት አምክትል አስተዳዳሪው በታሪክ አጋጣሚ መሪ ስንሆንና አስተማሪዎች ስንሆን ሀገር ተረካቢ የተማረ ትውልድ የመቅረጽ ሃላፊነት አለብን ሲሉ አብራርተዋል።

አቶ መስፍን አያይዘውም የመምህርነትን ሙያ ያከበሩ የሚያስከብሩ ጋወን የናፈቃቸው ስነ ምግባር ያላቸው መምህራን እንዳሉ ሁሉ አንዳንድ ሃላፊነት የጎደላቸው ትምህርት እነዳይጀመር የሚሰሩ የግል ፍላጎት የበለጠባቸው መምህራን አልፎ አልፎ አይጠፉም ሲሉ ጠቁመው አልፈዋል።

በውይይትመድረኩ የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ምክትል
አስተዳዳሪ አቶመስፍን ልየው፣ የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ይበልጣል ባለው የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የአቅም ግንፓታና ፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ብርሃኑ አላምር፣ የደምበጫዘ ዙሪያ ወረዳ ት /ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አላዛር ተጎዴ ፣ርዕሳነ መምህራን እና ሱፐር ባይዘሮች ተገኝተዋል።

18ኛው ሰንደቅ አላማ ቀን በምዕራብ ጎጃም ዞን በድምቀት ተከብሯል።18ኛውን ሰንደቅ አላማን ቀን " ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ የከፍታ ዘመን ብስራት ለብሄራዊ አንድነታችን ለሉዓላዊነታችንና ...
13/10/2025

18ኛው ሰንደቅ አላማ ቀን በምዕራብ ጎጃም ዞን በድምቀት ተከብሯል።

18ኛውን ሰንደቅ አላማን ቀን " ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ የከፍታ ዘመን ብስራት ለብሄራዊ አንድነታችን ለሉዓላዊነታችንና ለህዳሴያችን "በሚል መሪ ቃል የምዕራብ ጎጃም ዞን የመንግስት ሰራተኞችና የፖሊስ አባላት በጋራ በመሆን ህብረ ዝማሬውን በመዘመር አክብረዋል።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ተሾመ ብዙ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የሉዓላዊነታችን፣የአንድነታችንና የህብረ ብሄራዊ መገለጫችን ስለሆነ ሁሌም የምናከብረውና የምንዘምርለት ባንዲራችን ነው ብለዋል።

የምዕራብ ጎጃም ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ እሱባለው ሁነኛው ሰንደቅ ዓላማችን የማንነታችንና የእኩልነታችን መገለጫች ስለሆነ ከዛሬ 400 አመት በፊት ጀምሮ በትምህርት ቤቶችና በተቋማት በድምቀት እየተከበረ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

አቶ እሱባለው አክለውም የሰንደቅ አላማን ቀን ሁሉም ሰራተኛ በየተቋሙ በውይይት በማክበር የሰንደቅ አላማን ክብር ለትውልድ የምናስተላልፍበትና እኛም ለሀገራችን ህልውና ጠንክረን የምንሰራበት ሊሆን እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
West Gojjam Communications

በደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት አዘጋጅነት "ለአረጋዊ ደህነነትና መብቶች መጠበቅ ሁለንተናዊ ሃላፊነታችንን እንወጣ" በሚል መሪ ቃል የአረጋውያን በዓል  እየተከበ...
13/10/2025

በደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት አዘጋጅነት "ለአረጋዊ ደህነነትና መብቶች መጠበቅ ሁለንተናዊ ሃላፊነታችንን እንወጣ" በሚል መሪ ቃል የአረጋውያን በዓል እየተከበረ ይገኛል።

ደምበጫ ጥቅምት3/2018 ዓ/ም(ደምበጫ ዙሪያ ኮሙኒኬሽን)

በምዕራብ ጎጃም ዞን ደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የወረዳው ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት "ለአረጋዊ ደህነነትና መብቶች መጠበቅ ሁለንተናዊ ሃላፊነታችንን እንወጣ" በሚል መሪ ቃል በአገር አቀፍ ደረጃ ለ34ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአረጋውያን በዓል እያከበረ ነው።

በበዓሉ ላይ የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ነገሰ፣የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኢንስፔክሽን ና ስነምግባር ኮሚሽን ሃላፊ ወ/ሮ አዳነች ፀጋ፣ጥሪ የተደረገላቸው አረጋውያን እና የተቋሙ ሰራተኞች ተገኝተዋል።

ማህበረሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ ዘላቂ ሰላምን ማስፈን እንደሚገባ ተገለጸበማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሁለቱ ጭልጋና አይከል ከተማ አመራሮች በዘላቂ ሰላምና ልማትን በማስቀጠል ዙሪያ የውይይት መ...
12/10/2025

ማህበረሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ ዘላቂ ሰላምን ማስፈን እንደሚገባ ተገለጸ

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሁለቱ ጭልጋና አይከል ከተማ አመራሮች በዘላቂ ሰላምና ልማትን በማስቀጠል ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂደዋል።

የልማት ተግባራት የሚከናወነው መጀመሪያ ሰላም ሲረጋገጥ ነውና ለዛለቂ ሰላም የአካባቢውን ሰላም ወዳድ ማህበረሰብ በመያዝ ሰላማችን ዘላቂነት እንዲኖረው መስራት እንዳለበት ተነስቷል።

አመራሩ ቁርጠኛ በመሆን ቀበሌ ድረስ በመውረድ ማህበረሱ ጋር የህዝብ ግንኙነቶችን በማጠናከርና የቀበሌ መዋቅሩን በማጠናከር ዘላቂ ሰላምን በማስፈን ማህበረሰባችን በሰላም ወጥቶ እንዲገባና የልማት ተግባሩን እንዲያከናወን በትኩረት መሰራት እንዳለበትም ተገልጿል።

በመድረኩ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን ሙሀመድ (ዶ.ር)፣ የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና መሬት መምርያ ኃላፊ አቶ አላምተገኝተዋል እና የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፋሲል ሰንደቁ ተገኝተዋል።

መረጃው የጭልጋ ኮሙኒኬሽን ነው።

የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለማት ትርጉም፦18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በነገው ዕለት በመላ ሀገሪቱ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል፡፡ቀኑ “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣...
12/10/2025

የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለማት ትርጉም፦

18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በነገው ዕለት በመላ ሀገሪቱ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል፡፡

ቀኑ “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሃሳብ ነው የሚከበረው፡፡

በኢፌዲሪ ሕገ መንግስት መሰረት የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለማት እና በሰንደቅ ዓላው መሀል ላይ የሚገኘው ዓርማ ትርጉም ምንድን ነው?

1. አረንጓዴው ቀለም፡- የሥራ፣ የልምላሜና የዕድገት ምልክት ነው፡፡

2. ቢጫው ቀለም፡- የተስፋ፣ የፍትሕና የእኩልነት ምልክት ነው፡፡

3. ቀዩ ቀለም ፡- ለነፃነትና ለእኩልነት መስፈን የሚደረግ የመስዋዕትነትና የጀግንነት ምልክት ነው፡፡

እንዲሁም በሰንደቅ ዓላማው መሀል ላይ የሚገኘው ዓርማ ትርጉም ከታች እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

1. ክብ የሆነው፡- ሰማያዊ መደብ ሰላምን ያመለክታል፡፡

2. ቀጥታና እኩል የሆኑት መስመሮች፡- የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንዲሁም የሐይማኖቶችን እኩልነት ያመለክታሉ፡፡

3. ቀጥታና እኩል ከሆኑት መስመሮች የተዋቀረው ኮከብ፡- የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በመፈቃቀድ የመሠረቱትን አንድነት ያመላክታል፡፡

4. ቢጫ ጨረሩ ደግሞ ፡- በመፈቃቀድ አንድነት ለመሰረቱት ብሔር፣ ብሔረሰቦች የፈነጠቀውን ብሩህ ተስፋ ይጠቁማል፡፡

ኤፍ ኤም ሲ

Address

Dembecha Woreda Government Communicationየደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን
Dembech'a

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dembecha zuria Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dembecha zuria Communication:

Share