Dembecha zuria Communication

Dembecha zuria Communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dembecha zuria Communication, Media/News Company, Dembecha Woreda Government Communicationየደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን, Dembech'a.

በዕለት ፍጆታ ምርቶች ላይ የሚታየውን የዋጋ ግሽበት ለማስተካከል ከ18 ሚሊዮን 326 ሽህ ብር በላይ በጀት በመመደብ በጅምላ አቅራቢ ነጋዴዎችና በሸማች ማህበራት አማካኝነት የግብርናና የኢንዱ...
21/08/2025

በዕለት ፍጆታ ምርቶች ላይ የሚታየውን የዋጋ ግሽበት ለማስተካከል ከ18 ሚሊዮን 326 ሽህ ብር በላይ በጀት በመመደብ በጅምላ አቅራቢ ነጋዴዎችና በሸማች ማህበራት አማካኝነት የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለማህበረሰቡ እየቀረበ መሆኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ገለፀ።

በመምሪያው የኢንስፔክሽን ቡድን አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ ሞላ በማህበረሰቡ የዕለት ፍጆታ ምርቶች ላይ በየጊዜው እየታየ ያለው የዋጋ ግሽበት በመካከለኛና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ በሚገኘው ማህበረሰብ ላይ እያደረሰው ያለውን ጫና ለመቀነስ እንደ ምዕራብ ጎጃም ዞን 18 ሚሊዮን 326 ሺህ 400 ብር በጀት በመመደብ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ በጅምላ ነጋዴዎችና በሸማች ማህበራት አማካኝነት እየቀረበ ነው ብለዋል።

ለማህረሰቡ ከቀረቡት ምርቶች ውስጥ 477 ኩንታል ጤፍ፣90 ኩንታል ፊኖ ዱቄት እና 1ሺህ 400 ሊትር ዘይት በተመጣጣኝ ዋጋ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ማህበረሰበ ለመደገፍ የተሰራጨ መሆኑን አቶ ሀብታሙ ሞላ ተናግረዋል።

west gojjam communication

ተጨማሪ መረጃዎችን ከደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን የመረጃ መረቦች ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ይችላሉ፡፡
Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=100068667050208
Telegram ፡ https://t.me/+gd9o0kwBHcdlZmU0
Ticktock: tiktok.com/.zuria.c
youtube:https://www.youtube.com//?si=jG63-YD7Fxfs-rmX

የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ስልጠና በባሕር ዳር ከተማ ተጀመረ፡፡    "ወደ ተምሳሌት ሀገር በተሻገረ ህልም እና በላቀ ትጋት፤ አስተማማኝ ነገን መሥራት" በሚል መሪ ሃሳብ ...
20/08/2025

የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ስልጠና በባሕር ዳር ከተማ ተጀመረ፡፡

"ወደ ተምሳሌት ሀገር በተሻገረ ህልም እና በላቀ ትጋት፤ አስተማማኝ ነገን መሥራት" በሚል መሪ ሃሳብ ለክልሉ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች የሚሰጠው ሥልጠና በባሕር ዳር ተጀምሯል፡፡

ስልጠናው እስካሁን በክልሉ በተመዘገቡ የልማት እና መልካም አስተዳደር ሥራዎች አፈጻጸም፣ በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች እና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ የሚያተኩር መኾኑ ተጠቁሟል፡፡

በወቅታዊ ክልላዊ፣ ሀገራዊ፣ አሕጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያተኩረው የመሪዎቹ ስልጠና ለተከታታይ ቀናት ይሰጣል ተብሏል።

#አሚኮ

          ▬▬▬▬▬▬▬▬‎የአገር መከላከያ ሚኒስቴር በአለም አቀፍ ደረጃ ቴክኖሎጂ እየሰፋ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ የተቋሙን ተልዕኮ መነሻ በማድረግ ቴክኖሎጂን ለመጠቀም የተሟላ የአካደሚክ ...
20/08/2025


▬▬▬▬▬▬▬▬
‎የአገር መከላከያ ሚኒስቴር በአለም አቀፍ ደረጃ ቴክኖሎጂ እየሰፋ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ የተቋሙን ተልዕኮ መነሻ በማድረግ ቴክኖሎጂን ለመጠቀም የተሟላ የአካደሚክ ዕውቀት ያላቸው ምሩቃንና በመማር ላይ የሚገኙትን ወጣት ተማሪዎች ተኪ አመራሮችን ለማፍራት እና የሠራዊታችንን የማድረግ አቅሙን ለማጠናከር ያለዉን ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ ከመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና ከህብረተሰቡ፡-
‎በልዩ ሁኔታ:-
‎1ኛ. በተፈጥሮ ሳይንስ የተመረቁ፤
‎2ኛ. በማህ/ሳይንስ ትምህርት የተመረቁና በመማር ላይ ያሉትን ወጣቶች ለዕጩ መኮንንነት፤
‎3ኛ. ከ10ኛ ክፍል በላይ የትምህርት ደረጃ ያላቸዉን ለልዩ ኮማንዶ ሃይል መመልመል ይፈልጋል፡፡

‎👉 አጠቃላይ የምልመላ መስፈርቶች
‎1. የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስትን የተቀበሉ፣በህዝቦች በሉአላዊነትና አንድነት የሚያምኑና አገራቸዉን ማገልገል ሙሉ ፍቃደኛ የሆኑ።
‎2. ከማንኛውም የፖለቲካ ድርጅቶች ወገንተኝነት ነፃ የሆኑ፤
‎3. ከአሁን በፊት የመከላከያ፣የፖሊስ እና የክልል ልዩ ሃይል አባል ያልነበሩ።
‎4. ከአገራችን ሁኔታ በመነሳት የተለያዩ ኢ-መደበኛ ሀይሎች አባል ያልሆኑ፤
‎5. በወንጀል ይሁን በፍታብሔር ተከሶ የፍርድ ቤት ክርክር የሌለባቸው፣
‎6. ዜግነት ኢትዮጵያዊ የሆኑ፤
‎7. የዕጩ መኮንንነት ስልጠና ወስደው ከተመረቁ በኋላ በመኮንንነት ለማገልገል ፍቃደኛ የሆኑ።
‎8. ከየትኛዉም ሱስ ከሲጋራ፣ከጫት፣ ከሀሽሽ እና ከሌሎች ሱሶች ነፃ የሆ፤
‎9. በአካባቢው ማህበረሰብ የተመሰገነ ባሀሪ እና ስነ-ምግባር ያላቸው።
‎10. ከሚኖሩበት አከባቢ ከተለያዩ ወንጀሎችና ፀረ-ህዝብ ተግባር ነፃ ስለመሆናቸው ከአስተዳደር አካላትና ከፖሊስ የጽሁፍ ማስረጃ እና የቀበሌ የነዋሪነት መታወቂያ ማቅረብ የሚችሉ።
‎11. ሙሉ ጤንነት ያላቸውና የሚሰጠዉን የህክምና ምርመራ ማለፍ የሚችሉ፡፡
‎12. ትዳር ያልመሰረቱና ልጅ ያልወለዱ፡፡
‎13. ዕድሜ ለወንድም ለሴትም ተመልማዮች ከ18 እስከ 24፤
‎14. ለዕጩ መኮንኖች/እስከ 27 ዓመት የሆኑ፡፡

‎ 👉 አካላዊ መስፈርት
‎1. የተስተካከለ ቁመና የእግር፣ የእጅ፣ የአንገት፣ የወገብ መሰበርእና ሌሎች ችግሮች የሌለባቸው።
‎2. የአይን፣ የአፍንጫ፣ የጆሮ፣ የጥርስ እናየከንፈር መሰንጠቅ ችግር የሌለባቸው።
‎3 ከቲቪ፣ ከሚጥል በሽታ፣ ከስኳር፣ ከደም ግፊት፣ከኪንታሮት እና ከእንቅርት በሽታዎች ነፃ የሆኑና ሌሎች በተቋሙ የሚሰጡ የጤና ምርመራዎችን ማለፍ የሚችሉ፤
‎4. ቁመት ለወንድ 1.65 ለሴት 1.60 ሜትር እና ከዚያ በላይ የሆኑ።
‎5. ክብደት ለወንድ ከ45-70 ለሴት ከ 40-60 ኪ/ግራም የሆኑ

‎👉 ለዕጩ መኮንኖች አጠቃላይ የትምህርት ደረጃና ተፈላጊ ብቃት
‎የዲግሪ ምሩቅ ለሆኑ እውቅና ካለው ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የተመረቀ/ች፤
‎የዲፕሎማ ምሩቅ ከሆነ/ች ከደረጃ 1-4 (አድቫንስድ ዲፕሎማ) ሆኖ እውቅና ካለው የትምህርት ተቋም/COC/ያለው/ያላት፤
‎12ኛ ክፍል (የመሰናዶ ትምህርት) ያጠናቀቀ/ች ሆኖ በወቅቱ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ማስገባት የሚችል ነጥብ ያለው/ያላት፤
‎በማህበራዊ ወይም በተፈጥሮ ሳይንስ በ2014፣2015 እና 2016 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ማለትም 300 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ፤
‎በማህበራዊና የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት የ2014 እና የ2015 ሪሜዲያል ተምረው ያለፉ፣ ‎በማንኛውም የትምህርት መስክ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በመደበኛ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም በመማር ላይ የሚገኙ፤ ‎

👉 የምዝገባ ቀን ከነሀሴ 10/12/2017 እስከ ነሀሴ 29/12/2017 ድርስ ብቻ ይሆናል።

👉 የምዝገባ ቦታ=በደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት
👉

ትዉልድ ይማር!ቀጣይነት ያለዉ የተማረ፣ የሰለጠነ እና የተለወጠ የትዉልድ ቅብብሎሽ እንዲኖር ትምህርት ላይ መስራት ብቸኛዉ አማራጭ ነዉ።በውስጥም በውጭም ባሉ ግጭት ጠማቂዎች መመሪያ ሠጭነት በ...
19/08/2025

ትዉልድ ይማር!

ቀጣይነት ያለዉ የተማረ፣ የሰለጠነ እና የተለወጠ የትዉልድ ቅብብሎሽ እንዲኖር ትምህርት ላይ መስራት ብቸኛዉ አማራጭ ነዉ።

በውስጥም በውጭም ባሉ ግጭት ጠማቂዎች መመሪያ ሠጭነት በክልላችን ሁለት አመት የሞላዉ ግጭት ትምህርት ላይ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል።

በዉጤቱም ትምህርት ቤቶች ጉዳት አስተናግደዋል፤ ከፖለቲካ ነጻ የሆኑ መምህራን ስራ አጥ ከመሆን ባሻገር ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ህይወታቸውን አጥተዋል፤ ህጻናት ተማሪዎች ቤት እንዲዉሉ እና አልባሌ ቦታ እንዲዉሉ ሁነዋል፤ ወላጅ ቤተሰብ እጅጉን አዝነው በየመድረኩ በድፍረትና በምሬት ገልፀዋል።

ይህ አስከፊ ሁኔታ እንዲለወጥ በተከፈለው መራር ተጋድሎ ተማሪዎቻችን ወደ ትምህርት ቤት የመመለስና ትምህርት ቤቶችን ምቹ የመማሪያ ቦታ ለማድረግ አበረታች ዉጤት ተገኝቷል።

በ2018 ዓ/ም አንድም እድሜዉ ለትምህርት የደረሰ ህጻን ከትምህርት ገበታ ዉጭ እንዳይሆን እየተሰራ ነዉ።

በዛሬዉ እለትም በተመረጡ አካባቢዎች ተማሪ የመመዝገቡ ስራ በአንድ ጀምበር በርካታ ተማሪዎችን በመመዝገብ የ2018 የመማር ማስተማሩ ስራ በይፋ ተጀምሯል።

በክልላችን ከተማሪዎች ምዝገባ ጀምሮ በተሟላ ደረጃ የመማር ማስተማሩ ስራ እንዲቀጥል የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን እና ወጣቶች የትውልድ ግንባታ ስራ ነውና የያዝነው ተግባር ታሪካዊ ኃላፊነታቸዉን ሊወጡ ይገባል።

ዶ/ር መንገሻ ፈንታዉ
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ

መንግስት የቋሚ ደመወዝ ተከፋይ ዜጎችን የኑሮ ጫና ለማቃለል ቁርጠኛ አቋም ይዟል - አቶ አሕመድ ሽዴ መንግስት የቋሚ ደመወዝ ተከፋይ ዜጎችን የኑሮ ጫና ለማቃለል ቁርጠኛ አቋም ይዞ እየሰራ ነ...
18/08/2025

መንግስት የቋሚ ደመወዝ ተከፋይ ዜጎችን የኑሮ ጫና ለማቃለል ቁርጠኛ አቋም ይዟል - አቶ አሕመድ ሽዴ

መንግስት የቋሚ ደመወዝ ተከፋይ ዜጎችን የኑሮ ጫና ለማቃለል ቁርጠኛ አቋም ይዞ እየሰራ ነው አሉ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ።

የገንዘብ ሚኒስቴር የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን ወደ ሙሉ ትግበራ ማስገባቱን ተከትሎ ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ዕውቅና ተሰጥቶታል።

አቶ አሕመድ ሽዴ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ መንግስት ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያካሄዳቸው ዘርፈ ብዙ ሪፎርሞች ተጨባጭ ውጤት አምጥተዋል።

በተለይም የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙ የውጭ ምንዛሪ ግኝትን በማሳደግና ኢኮኖሚውን በማነቃቃት ዓይነተኛ ሚና መጫወቱን አንስተዋል።

የውጭ ምንዛሪ ተመን በገበያ እንዲወሰን መደረጉ በተለይም የዝቅተኛ ደመወዝ ተከፋይ ዜጎችን ጫና ውስጥ እንዳይከት መንግስት የተለያዩ ርምጃዎችን እንደወሰደ አስታውሰዋል።

መንግስት የቋሚ ደመወዝ ተከፋይ ዜጎችን የኑሮ ጫና ለማቃለል ቁርጠኛ አቋም ይዞ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው÷ ከመስከረም ጀምሮ የተደረገው ማሻሻያም የዚህ ማሳያ ነው ብለዋል።

የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሸን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) በበኩላቸው ÷ የመንግስት ተቋማትን አደረጃጀትና አሰራር በማዘመን በክህሎትና በባህሪ የበቃ የሰው ኃይል አስተዳደርና ልማትን በመዘርጋት ለሕብረተሰብ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተለያዩ ሪፎርሞች እየተካሄዱ ነው ብለዋል።

የማሻሻያ ሪፎርሙ የገንዘብ ሚኒስቴርን ጨምሮ በስምንት ተቋማት በደረጃ ሲተገበር እንደነበር ነው ያስረዱት፡፡

ከተቋማቱ መካከል የገንዘብ ሚኒስቴር የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ጨርሶ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ሙሉ ትግበራ መግባቱን አድንቀዋል።

ከሶስት ነጥብ ሶስት ሚሊየን የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ ተጨማሪ 160 ቢሊየን ብር እንደሚያስፈልግና ይህም የመንግስትን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል።

የመንግስት ሰራተኛው ሥራውን በውጤታማነት በመፈፀም ለሀገራዊ ዕድገት የድርሻውን እንዲወጣ መጠየቃቸው ታውቋል፡፡
#ኢዜአ

ከመስከረም ጀምሮ ለሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወሰነ አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወ...
18/08/2025

ከመስከረም ጀምሮ ለሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወሰነ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ፤ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው ብሏል፡፡

በዚህም ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት መወሰኑን አስታውቋል፡፡

በማሻሻያው ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4 ሺህ 760 ወደ ብር 6 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ነው ያለው።

ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21 ሺህ 492 ወደ ብር 39 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ብሏል።

የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6 ሺህ 940 ወደ ብር 11 ሺህ 500 የሚሻሻል መሆኑን ገልጿል።

ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ እንደሚደረግበት አስታውቋል።

ይህ የደመወዝ ማስተካከያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ጠይቋል ያለው ኮሚሽኑ፤ ይሄም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል ብሏል።

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሙሉ መግለጫ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፦https://www.fanamc.com/archives/299145

FBC

16/08/2025

በትምህርት ዘርፉ ላይ ያጋጠመውን ስብራት በልኩ ተረድቶ ማህበረሰቡ የሚጠበቅበትን ተሳትፎ ካደረገ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው መመለስ ይቻላል።

የተማረ የትዉልድ ቅብብሎሽ እንዳይቋረጥ ሁሉም ዜጋ የድርሻዉን ሊወጣ ይገባል።በአማራ ክልል ነሐሴ 2017 ዓ/ም ከ15 እስከ 16 በተመረጡ ከተሞችና ዞኖች፤ ነሐሴ 2017 ዓ/ም ከ19 እስከ 2...
16/08/2025

የተማረ የትዉልድ ቅብብሎሽ እንዳይቋረጥ ሁሉም ዜጋ የድርሻዉን ሊወጣ ይገባል።

በአማራ ክልል ነሐሴ 2017 ዓ/ም ከ15 እስከ 16 በተመረጡ ከተሞችና ዞኖች፤ ነሐሴ 2017 ዓ/ም ከ19 እስከ 20 በሁሉም ከተሞችና ዞኖች የተማሪ ምዝገባ ይካሄዳል!

በአማራ ክልል ላለፉት ሁለት አመታት በተከሰተዉ ግጭት ተማሪዎች ትምህርት ቤት ተገኝተዉ ትምህርታቸውን እንዳይከታተሉ ሁነዋል። መምህራን ታጥቀዉ ጫካ በሚንቀሳቀሱ ሃይሎች እንዳያስተምሩ ድብደባ፣ አፈናና ግድያ ተፈጽሞባቸዋል።

በዚህም ለዘመናት ትውልድ ሲያፈሩ የነበሩ ትምህርት ቤቶች ፈራርሰዉ፣ ተቃጥለዉና ከፍተኛ ውድመት ደርሶባቸዉ ከተማሪዎቻቸዉ ጋር ከተለያዩ ድፍን ሁለት አመት ተቆጥሯል።

በዉጤቱም መምህራን ከሚወዱት ሙያቸዉ ጋር ተለያይተዋል፤ ሴት ህጻናት ላለእድሜ ጋብቻ ተዳርገዋል፤ ወጣቶች ለህገወጥ ስደት ተዳርገዋል፤ የተማሪ ወላጆች አንገት ደፍተዋል።

እንደ ህዝብ ከገጠመን ችግር ለመዉጣት እነዚህን ሀገርና ትውልድ የሚገነባባቸው ትምህርት ቤቶች ወደ ቀደመ ተግባራቸው ለመመለስ እና ተማሪዎች ልጆቻችን ከደረሰባቸዉ ሁለንተናዊ ችግር አውጥተን ወደ አገር ተረካቢና አገር አቀፍና አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት መመለስ አሁናዊ ግዴታችን ሊሆን ይገባል።

በህም ትምህርት ቤቶቹን መልሶ በመገንባት፣ በመጠገንና የውስጥ ቁሳቁሶችን በማሟላት፤ እስከ አሁን ትምህርት ያልጀመሩ፣ ያቋረጡና በዚህ ዓመት ለትምህርት የደረሱ ህፃናትን ወደ ትምህርት ቤት አንዲመለሱና እንዲመዘገቡ ሁሉም ዜጋ የድርሻዉ ሊወጣ ይገባል።

በመሆኑም በትምህርት ስራ ላይ የሚደርስ ተፅዕኖና ሴራ የጥንተ ጠላቶቻችን የዘመናት ዕቅድና የአማራ ህዝብ በዓለም አቀፍ ተቋማት አገርን ወክሎ እንዳይቆምና እንዳይሞግታቸው የሸረቡት የዘመናት አጀንዳ ማስፈፀሚያ መሆኑን በዉል መገንዘብ ያስፈልጋል። ታሪክና ትውልድ ይቅር የማይለው እኩይ ድርጊትም ነው።

Amhara Communication

አሚኮ የሕዝብ  ጥያቄዎች እንዲመለሱ በኅብረተሰቡ እና በመንግሥት መካከል ድልድይ ኾኖ እየሠራ ነው።    ከ30 ዓመታት በፊት ሥራውን የጀመረው አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የተደራሽነት አድማሱን በ...
15/08/2025

አሚኮ የሕዝብ ጥያቄዎች እንዲመለሱ በኅብረተሰቡ እና በመንግሥት መካከል ድልድይ ኾኖ እየሠራ ነው።

ከ30 ዓመታት በፊት ሥራውን የጀመረው አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የተደራሽነት አድማሱን በማስፋት ከክልሉ አልፎ በሀገር አቀፍ እና አለም አቀፍ ደረጃ መረጃዎችን እያደረሰ ነው።

አሚኮ ያለፉት ሦስት አስርት ዓመታት ጉዞውን የሚዘክር 30ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን እያከበረ ይገኛል።

አሚኮ እንደሁሉም አካባቢዎች የምዕራብ ጎጃም ዞን ጸጋዎች በመለየት እና በማስተዋወቅ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የምዕራብ ጎጃም ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኀላፊ ልንገርህ ይታይህ ገልጸዋል።

የዞኑን የልማት፣ የሰላም እና የመልካም አሥተዳደር ጥያቄዎች እንዲመለሱ በኅብረተሰቡ እና በመንግሥት መካከል እንደ ድልድይ ኾኖ መሥራቱን ተናግረዋል።

በክልሉ ያጋጠሙ የጸጥታ ችግሮች እንዲፈቱ እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን አሚኮ ግንባር ቀደም መኾኑን አንስተዋል።

አሁን ባለው የጸጥታ ችግር ኅብረተሰቡ የሰላምን ዋጋ እንዲረዳ በማድረግ ፊቱን ወደ ልማት እንዲያዞር መሥራቱንም ጠቁመዋል።

ከዚህ በተሻለ ተደማጭነቱን ማሳደግ በሚያስችሉ ሥራዎች ላይ ትኩረት እንዲያደርግም አስገንዝበዋል።

አሚኮ ከኅብረተሰቡ ሁለንተናዊ እድገት ጋር በመተሳሰር በይዘት ራሱን ተወዳዳሪ እያደረገ የመጣ ሚዲያ መኾኑን የገለጹት ደግሞ የፍኖተ ሰላም ከተማ አሥተዳደር ምክትል ከንቲባ ጊዜው ደግአረገ ናቸው።

በከተማው ያሉ ሃብቶችን በመለየት ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ አሚኮ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበረከቱን ጠቁመዋል ።

አሁን ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በመረዳት ኅብረተሰቡ የሚያስፈልገውን በመለየት እና ትኩረት በመስጠት ተወዳዳሪ ለመኾን መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።

#አሚኮ

ብርሃን ጨለማን ያሸንፍ ዘንድ የተፈጥሮ ግዴታ ነው። ያለ ብርሃን መንቀሳቀስ፣ ለውጥ ማምጣትም ሆነ ተስፋ ማድረግና ግብ ላይ መድረስ አይቻልም።ትምህርት ደግሞ የትውልዶች ብርሃን ነው። የሀገራት...
15/08/2025

ብርሃን ጨለማን ያሸንፍ ዘንድ የተፈጥሮ ግዴታ ነው። ያለ ብርሃን መንቀሳቀስ፣ ለውጥ ማምጣትም ሆነ ተስፋ ማድረግና ግብ ላይ መድረስ አይቻልም።

ትምህርት ደግሞ የትውልዶች ብርሃን ነው። የሀገራት ፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የሚሠራበት መሣሪያ ከተባለ ትምህርት ነውና። ለዚያ ነው በሀገራት መካከል ያደጉና ያላደጉ፣ የሰለጠኑና ያልሰለጠኑ ወዘተ እየተባለ የሚከፋፈለው።

ስለዚህ ትምህርት ሀገርን ወደ ተሻለ ነገ ያሻግር ከተባለ ሁሌም ከትውልዱ መንገድ ላይ ብርሃን እንዳይጠፋ ማድረግ የሰው ልጆችን ሰብዓዊ መብት የማክበር ያክል ግዴታ ነው። ባለፉት ጊዜያት የተዘጉ ትምህርት ቤቶች ተስተካክለው እንዲከፈቱ፣ ተማሪዎችም ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመልሰው ነጋቸውን እንዲቀርፁ ሁሉም ማህበረሰብ በትብብር የየድርሻውን ሊወጣ ይገባል።

Amhara Communications

በምዕራብ ጎጃም ዞን በጃቢ ጠህናን ወረዳ በማንኩሳ አብደጎማ ቀበሌ በክላስተር እየለማ ያለ የበቆሎ ሰብል ከፊል ፎቶ፦📸 JabiTehinan Communication
13/08/2025

በምዕራብ ጎጃም ዞን በጃቢ ጠህናን ወረዳ በማንኩሳ አብደጎማ ቀበሌ በክላስተር እየለማ ያለ የበቆሎ ሰብል ከፊል ፎቶ፦

📸 JabiTehinan Communication

‎የደምበጫ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ለመጠገን ከከተማው ማህበረሰብ ጋር የምክር መድረክ ተካሄደ።‎‎በውይይቱ ላይ የደምበጫ ከተማ እና የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል...
13/08/2025

‎የደምበጫ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ለመጠገን ከከተማው ማህበረሰብ ጋር የምክር መድረክ ተካሄደ።

‎በውይይቱ ላይ የደምበጫ ከተማ እና የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።

በውይይት ላይ ተገኝተው የመነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የደምበጫ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሃለፊ አቶ አልዓዛር ተጎዴ እንደገለፁት ሁለተናዊ ስብናው የታነፀ ትውልድ ለማፍራት ትምህርት ቤቶች አይነተኛ መሳሪያ መሆናቸው ጠቅሰዉ ተሻጋሪ እና አምራች ዜጋ ለማፍራት የትምህርት ቤቶችን ገፅታ ማሻሻል ይገባል ብለዋል። ገጽታቸውን ለማሻሻል የተማሪ ወላጆች፣የንግዱ ማህበረሰብና ሁሉም ይመለከተኛል የሚል አካል ሊረባረብ ይገባል ብለዋል።

‎ የደምበጫ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በርካታ ምሁራንን ያፈራ ቢሆንም አሁን ላይ ከፍተኛ የሆነ የመፍረስ አደጋ ተጋርጦበታል ብለዋል።

‎የደምበጫ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙሉቀን መኮነን እንደገለጹት የትምህርት ተቋሙን መገንባት፣ መጠገንና መንከባከብ የሁሉም አካላት ድርሻ ሊሆን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። ትምህርት ቤቶች የልጆች የእውቀት ማእከል እና ልጆቻችን ፍሬ የሚያፈሩበት ተቋም መሆኑን ገልጸው የሰው ልጅ የመጨረሻ ግቡ ልጅ ወልዶ ፍሬ ሲያፈራ ማየት ነው ብለዋል። የትምህርት ቤቶችን ገጽታ ማሸሻል የሁሉም ሰው ተግባር ሊሆን ይገባል።

‎የደምበጫ ከተማ አስተዳደር ለትምህርት ቤቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰው የደምበጫ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በአጭር ጊዜ ታድሶ ለመማር ማስተማር ዝግጁ እንዲሆን አስፈላጊዉ ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል።

የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መስፍን ልየው እንደገለጹት በወረዳችን ብሎም በክልላችን በትምህርት ተቋም ላይ ትልቅ ስብራት ደርሶበታል። በወረዳችንም ከ48 ሺህ በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸውን ገልጸው ትምህርት ፖለቲካ አይደለም፤ ለትምህርት ሁሉም ሰው ያገባኛል ብሎ ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ገበታቸው መመለስ አለብን ነው ያሉት። የተማሪ ወላጆችም ልጆችን ወደ ትምህርት ቤት መላክ ብቻውን ግብ አይደለም። የትምህርት ቤቶችን ገጽታ መመለስና ጥገና የሚያስፈልጋቸውን በቶሎ ጠግነን ለመማር ማስተማር ስራ ብቁ ማድረግ ይጠበቅብናል። ወረዳውም ለትምህርት ቤቶች ጥገና የሚችለውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

‎በውይይቱ ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የደምበጫ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከተመሰረተ በርካታ ዓመታትን ቢያሰቆጥርም የዕድሜውን ልክ የሚመጥን የመማሪያ ክፍል የሌለው መሆኑን ተናግረው የልጆቻችን የዕውቀት ማዕከል የሆነውን ትምህርት ቤት ለመጠገን የቻልነውን ሁሉ እናደርገዋለን ሲሉ ሀሳባቸውን ሰጥተዋል። በመጨረሻም የትምህርት ቤቱን ጥገና የሚከታተሉ አብይ ኮሚቴ በማዋቀር የምክክር መድረኩ ተጠናቋል።

ገንዘብ በማሰባሰብ ሂደት በዕለቱ በኮሚቴወች ተጀምሮ መልካም ጅማሮ በማሳየት ምክክሩ ተጠናቋል።

Address

Dembecha Woreda Government Communicationየደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን
Dembech'a

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dembecha zuria Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dembecha zuria Communication:

Share