
21/08/2025
በዕለት ፍጆታ ምርቶች ላይ የሚታየውን የዋጋ ግሽበት ለማስተካከል ከ18 ሚሊዮን 326 ሽህ ብር በላይ በጀት በመመደብ በጅምላ አቅራቢ ነጋዴዎችና በሸማች ማህበራት አማካኝነት የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለማህበረሰቡ እየቀረበ መሆኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ገለፀ።
በመምሪያው የኢንስፔክሽን ቡድን አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ ሞላ በማህበረሰቡ የዕለት ፍጆታ ምርቶች ላይ በየጊዜው እየታየ ያለው የዋጋ ግሽበት በመካከለኛና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ በሚገኘው ማህበረሰብ ላይ እያደረሰው ያለውን ጫና ለመቀነስ እንደ ምዕራብ ጎጃም ዞን 18 ሚሊዮን 326 ሺህ 400 ብር በጀት በመመደብ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ በጅምላ ነጋዴዎችና በሸማች ማህበራት አማካኝነት እየቀረበ ነው ብለዋል።
ለማህረሰቡ ከቀረቡት ምርቶች ውስጥ 477 ኩንታል ጤፍ፣90 ኩንታል ፊኖ ዱቄት እና 1ሺህ 400 ሊትር ዘይት በተመጣጣኝ ዋጋ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ማህበረሰበ ለመደገፍ የተሰራጨ መሆኑን አቶ ሀብታሙ ሞላ ተናግረዋል።
west gojjam communication
ተጨማሪ መረጃዎችን ከደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን የመረጃ መረቦች ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ይችላሉ፡፡
Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=100068667050208
Telegram ፡ https://t.me/+gd9o0kwBHcdlZmU0
Ticktock: tiktok.com/.zuria.c
youtube:https://www.youtube.com//?si=jG63-YD7Fxfs-rmX