Dembecha zuria Communication

Dembecha zuria Communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dembecha zuria Communication, Media/News Company, Dembecha Woreda Government Communicationየደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን, Dembech'a.

"ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ  ለደምበጫ ዙሪያ ለወረዳ እና ለደምበጫ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሰራተኛ አባላት ስልጠና መሰጠት ጀመረ።ደምበጫ መስከረም 7/2018 ዓ/ም...
17/09/2025

"ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ ለደምበጫ ዙሪያ ለወረዳ እና ለደምበጫ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሰራተኛ አባላት ስልጠና መሰጠት ጀመረ።

ደምበጫ መስከረም 7/2018 ዓ/ም(ደምበጫ ዙሪያ ኮሙኒኬሽን )

በምዕራብ ጎጃም ዞን በደምበጫ ዙሪያ እና ደምበጫ ከተማ አስተዳደር "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር " በሚል መሪ ሃሳብ መንግስት ሰራተኛ አባላት ስልጠና በደምበጫ ከተማ መሰጠት ጀምሯል ።

ስልጠናውን የደምበጫ ከተማ ምክትል ከንቲባ በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት ሲሆን የክልላችን እና የሃገራችን ብሎም የቀጠናችን ጂኦፖለቲካዊ ሁኔታ የምንረዳበት መድረክ ነው ብለዋል።

አቶ ሙሉቀን አክለውም አገራችን ኢትዮጵያ የስልጣኔ መፍለቂያ ብቻ ሳትሆን የስልጣኔ ቁንጮ የነበረች ሃገር ናት፤ስለሆነም የቀደመ ገናናነቷን ለመመለስ ብልፅግና እየሰራ ነው ብለዋል።

የደምበጫ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ልዑልሰገድ ካሳሁን የስልጠና መነሻ ሰነድ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።

ስልጠናው የአባላትን አቅም የሚገነባ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

16/09/2025
ታላቁ የህዳሴ ግድብ የታሪካዊ ጠላቶቻችን ሴራ በመበጠስ የኩራታችን ምንጭ የሆነውን አደዋን የደገመ የማንሰራራታችን ምልክት ነው፡-የምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እድሜዓለም አንተነህበ...
16/09/2025

ታላቁ የህዳሴ ግድብ የታሪካዊ ጠላቶቻችን ሴራ በመበጠስ የኩራታችን ምንጭ የሆነውን አደዋን የደገመ የማንሰራራታችን ምልክት ነው፡-

የምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እድሜዓለም አንተነህ

በፍኖተ ሰላም ከተማ ታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን በማስመልከት ህዝዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶእድሜዓለም አንተነህ በድጋፉ ላይ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል።

ዋና አስተዳዳሪው በንግግራቸው ታላቁ የህዳሴ ግድብ የአይችሉንም ትርክት የሰበረ የሁላችን የመተባር ውጤት ነው ብለዋል።ግድቡ ከመጀመሪያው ጀምሮ የህዝብ ድጋፍ ያልተለየው ኢትዮጵያዊያን በመተባበርና በመደመር ያሳካናው ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል።

ታላቁ የህዳሴ ግድብ የታሪካዊ ጠላቶቻችን የዘመናት ሴራ የበጠሰ የኩራታችን ምንጭ የሆነውን አደዋን የደገመ መሆኑንም ነው ያነሱት።

ግድቡ መላ ኢትዮጵያዊያንን በአንድ ላይ የደመረና ያስተሳሰረ የታሪካዊ ጠላቶቻችን ሴራ የበጠሰ የማንሰራራታችን ምልክት መሆኑንም ነው አቶ እድሜዓለም የገለጹት።

ህዳሴ የነገ ማንሰራራታችን በማያሻማ ሁኔታ ያመላከተ ታሪካዊ አርማችን ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ህዝቡ ድጋፉን በማጠናከር ልማትን መደገፉን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

የፍኖተ ሰላም ምክትል ከንቲባ አቶ ጊዜው ደግ አደረገ በበኩላቸው ታላቁ የህዳሴ ግድብ የዘመናት ቁጭታችንን የካሰ የመቻል ምሳሌያችን ነው ብለዋል።

ግድቡ የሁላችንም ነው ያሉት ምክትል ከንቲባው
የብዙ አመታት ፍላጎትና ምኞታችን የሆነው የህዳሴ ግድብ አካል በመሆናችን ደስታ ይሰማናል ብለዋል።

west Gojjam communication

16/09/2025
16/09/2025
16/09/2025

የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን አስመልክቶ በደምበጫ ከተማ የተደረገው የድጋፍ ሰልፍ በተንቀሳቃሽ ምስል!

የደምበጫ ማህበረሰብ ከሊስትሮ እስከ ባለሃብት ፤ ከሊቅ እስከ ደቂቅ፤ ካለው ሳይሆን ከሌለው እያዋጣ ፤ከኪሱ እየቀነሰ ቦንድ እየገዛ የተሳተፈበት ስለሆነ እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አለን።አቶ ሙ...
16/09/2025

የደምበጫ ማህበረሰብ ከሊስትሮ እስከ ባለሃብት ፤ ከሊቅ እስከ ደቂቅ፤ ካለው ሳይሆን ከሌለው እያዋጣ ፤ከኪሱ እየቀነሰ ቦንድ እየገዛ የተሳተፈበት ስለሆነ እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አለን።

አቶ ሙሉቀን መኮነን
የደምበጫ ከተማ ምክትል ከንቲባ

የደምበጫ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ሙሉቀን መኮነን ታላቁ የኢትዮጵ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን አስመልክቶ በደምበጫ ከተማ በተካሄደው የየድጋፍ ሰልፍ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የደምበጫ ማህበረሰብ ከሊስትሮ እስከ ባለሃብት ፤ ከሊቅ እስከ ደቂቅ፤ ካለው ሳይሆን ከሌለው እያዋጣ ፤ከኪሱ እየቀነሰ ቦንድ እየገዛ የተሳተፈበት ስለሆነ እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አለን ብለዋል።

አቶ ሙሉቀን አክለውም የህዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ መመረቅ የሀገራችን የድህነት ኩስመና ማብቂያ፣የዕድገታችን ማማ፣የቀጠናችን የጅኦ ፖለቲካ መቀየሪያ እና መዘወሪያ፣በሀገር አቀፍ እና በአህጉር አቀፍ ብቻ ሳይሆን በአለም አቀፍ ደረጃ በራስ አቅም ጀምሮ በራስ አቅም የመፈጸም እና የመልማት ብቃት እና አቅማችንን ያሳየንበት ነው ብለዋል።

ግድቡ የነገ ኢኮኖሚያችንን በአለም ካደጉ ሀገሮች ተርታ ለመሰለፍ የመሰፈንጠሪያ እስፕሪንግ ቦርድ ፣ያሸናፊነት እና የተገዳዳሪነት መንፈስ እና ስነልቦና ጫና የፈጠርንበት ፤የህዳሴ ግድባችንን ጀምሮ ከመገንባት ባለፈ ተጠናቆ በኢትዮጵያ ቀን አቆጣጠር ብቻ በምትታወቀው ቋግሜ 4 ቀን በይፋ የተመረቀ በመሆኑ የዘላለም ጠላቶቻችን በአለም አደባባይ እየየአቸውን ቢያቀልጡትም ለእኛ እና ለኢትዮጵያችን ደስታ ስለሆነ እንኳን ደስ አለን እንኳን ደስስ አላችሁ ነው ያሉት።

የደምበጫ ማህበረሰብ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ገንዘብ አዋጦ ለግድቡ ግንባታ የሚጠበቅበትን ከማድረግ ባለፈ ግድቡ መጠናቀቁንና መመረቁን አስመልክቶ ዛሬ በአደባባይ ወጥቶ ደስታውን በመግለፁ በከተማ አስተዳደሩ ስም ላቅ ያለ ምስጋና አለኝ ብለዋል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ የልማት አርበኝነት የታየበት ፤የሁሉም ኢትዮጵያውያን የላብ እና የደም ጠብታ ውጤት ነው   አቶ ሙላት ፈረደ የምዕራብ ጎጃም ዞን መንገድ መምሪያ ሃላፊየም...
16/09/2025

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ የልማት አርበኝነት የታየበት ፤የሁሉም ኢትዮጵያውያን የላብ እና የደም ጠብታ ውጤት ነው

አቶ ሙላት ፈረደ
የምዕራብ ጎጃም ዞን መንገድ መምሪያ ሃላፊ

የምዕራብ ጎጃም ዞን መንገድ መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙላት ፈረደ ታላቁ የኢትዮጵ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን አስመልክቶ በደምበጫ ከተማ በተካሄደው የየድጋፍ ሰልፍ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ የመላ ኢትዮጵያውያን የዘመናት የቁጭት ውጤት ፤ የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያውያን ውድ ስጦታ፤ ይቻላልን በተግባር ያሳየንበት የዘመኑ ታላቅ የጀግንነት አኩሪ ገድል እንዲሁም የልማት አርበኝነት የታየበት የሁሉም ኢትዮጵያውያን የላብ እና የደም ጠብታ ውጤት ነው ብለዋል።

አቶ ሙላት አክለውም የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ከልማት ስራዎች ድል ሁሉ የበላይ የሚያደርጉ በርካታ ምክንያቶች ያሉ ቢሆንም ልዩ የሚያደርገው ግን ብዙ ኢትዮጵያውያን ደማቸውን እና ላብቸውን የገበሩበት በመሆኑ ነው ብለዋል።

የህዳሴ ግድብ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ፣ በርካታ የክልል የፀጥታ ሃይሎቻችን በርካታ ሰራተኞቻችን ዋጋ ከፍለዋል ። በውጭ ጠላቶቻችን ሴራ በውስን የውስጥ ባንዳወዎች ትብብር ለውጡ ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ የህዳሴ ግድቡ ማቴሪያል እንዳይጓጎዝ ጥረት ያደረጉ ቢሆንም የመከላከያ ሰራዊት አባላት እየሞቱ ለዚህ አኩሪ ድል ያደረሱን ስለሆነ ክብር ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ አትችሉም ስንባል ፤የሀገርና የህዝብ የመቻል አቅም ያሳየንበት ጠላቶቻችን ለዘመናት ሸርበውብን የነበረን ሴራ የበጣጠሰ፣ያስደነገጠ እና አንገት ያስደፋ ፣አብረን የመቆማችን ልክ ለአለም የገለጠ ፤መላ ኢትዮጵያውያንን በማይበጠስ ገመድ አንድ ላይ ያስተሳሰረ የአንድነታችንና የአብሮነታችን ምሰሶ ህብር ገመድ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።

የህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቅ በታላቁ መፅሐፍ መፅሐፍ ቅዱስ ላይ የተነገረው ትንቢት የተፈፀመበት እውነተኛ የፈጣሪያችን ህያው ምስክር ነው ብለዋል።

በመጨረሻም አቶ ሙላት ሰላም ለድጋፍ ሰልፍ የተገኙ አካላትን አመስግነዋል።

የሕዳሴ ግድብን መጠናቀቅ በማስመልከት በደምበጫ ከተማ የድጋፍ ሰልፍ  መካሄዱን ቀጥሏል።ደምበጫ መስከረም( 6/ 2018 ደምበጫ ዙሪያ ኮሙኒኬሽን) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ ለምረ...
16/09/2025

የሕዳሴ ግድብን መጠናቀቅ በማስመልከት በደምበጫ ከተማ የድጋፍ ሰልፍ መካሄዱን ቀጥሏል።

ደምበጫ መስከረም( 6/ 2018 ደምበጫ ዙሪያ ኮሙኒኬሽን)

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ ለምረቃ መብቃቱን በማስመልከት ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በደምበጫ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በድጋፍ ሰልፉ መርሐ የምዕራብ ጎጃም ዞን መንገድ መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙላት ፈረዳ፣ የምዕራብ ጎጃም ዞን ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ ኤፍሬም ክፍሌ ፣የደምበጫ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ሙሉቀን መኮነን ፣ የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መስፍን ልየው ፣ የደምበጫ ከተማ አስተዳደርና የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች፣ የከተማ ነዋሪወች፣ የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ሰራተኞች፣የደምበጫ መንግስት ሰራተኞች እና የደምበጫ ከተማ ነዋሪወች ተገኝተው ደስታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ ለምረቃ መብቃቱን በማስመልከት ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በደምበጫ ከተማ መካሔድ ጀምሯል፡፡በድጋፍ ሰልፉ ላይ የዞን አመራሮች፣ የደምበጫ ከተማና የደምበጫ ዙ...
16/09/2025

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ ለምረቃ መብቃቱን በማስመልከት ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በደምበጫ ከተማ መካሔድ ጀምሯል፡፡

በድጋፍ ሰልፉ ላይ የዞን አመራሮች፣ የደምበጫ ከተማና የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ አመራሮች ፣የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ፣ ወጣቶች፣ የደምበጫ ከተማና የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ሰራተኞችና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተው ድጋፋቸውን እያሳዩ ነው።

በድጋፍ ሰልፉ ላይ ▪️ ግድባችን የዓባይ ዘመን ትውልድ የተጋድሎ ሰንደቅ!

🔹በራስ አቅም፥ በአፍሪካዊነት ኩራት የተገነባ ሐውልት!

▪️ ግድባችን ለተፋሰሱ ሀገራት በረከት እንጂ ጉዳት አይደለም!

🔹ግድባችን በኢትዮጵያዊነት ኅብር ፀንቶ የመቆም አሸናፊነታችን ኒሻን!

▪️ ግድባችን በወጀብ ውስጥ ሳንናወጥ በቁርጥ ቀን በፅናት እንድንቆም ያደረገን የአንድነታችን ውል መቀነት!

🔹ግድባችን የመቻል ማሳያ የማንሰራራት ጅማሮ ምልክት!

▪️ የውጭ ተጽዕኖ ያልበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነት ላይ የቆመ ግድብ!

🔹ግድቡን ማጠናቀቅ የአሸናፊነት አክሊል መድፋት ነው የሚሉ መልዕክቶች እየተስተጋቡ ነው።

በደምበጫ ከተማ  ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው። በድጋፍ ሰልፉ ላይ የደምበጫ  ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተው ድጋፋቸውን እያሳዩ ነው።በድጋፍ ሰልፉ ላይ እየተስተጋቡ ያሉ መፎክሮች▪️ ግድባ...
16/09/2025

በደምበጫ ከተማ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው። በድጋፍ ሰልፉ ላይ የደምበጫ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተው ድጋፋቸውን እያሳዩ ነው።

በድጋፍ ሰልፉ ላይ እየተስተጋቡ ያሉ መፎክሮች

▪️ ግድባችን የዓባይ ዘመን ትውልድ የተጋድሎ ሰንደቅ!

🔹በራስ አቅም፥ በአፍሪካዊነት ኩራት የተገነባ ሐውልት!

▪️ ግድባችን ለተፋሰሱ ሀገራት በረከት እንጂ ጉዳት አይደለም!

🔹ግድባችን በኢትዮጵያዊነት ኅብር ፀንቶ የመቆም አሸናፊነታችን ኒሻን!

▪️ ግድባችን በወጀብ ውስጥ ሳንናወጥ በቁርጥ ቀን በፅናት እንድንቆም ያደረገን የአንድነታችን ውል መቀነት!

🔹ግድባችን የመቻል ማሳያ የማንሰራራት ጅማሮ ምልክት!

▪️ የውጭ ተጽዕኖ ያልበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነት ላይ የቆመ ግድብ!

🔹ግድቡን ማጠናቀቅ የአሸናፊነት አክሊል መድፋት ነው የሚሉ መፎከሮች እየተስተጋቡ ነው።

የ12ኛ ክፍል ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎች ይፋ ሆኑ********************የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎ...
15/09/2025

የ12ኛ ክፍል ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎች ይፋ ሆኑ
********************

የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል፡፡

ዌብ ሳይትና ቴሌግራም አድራሻ የሚጠቀሙ ተፈታኞች ጊዜያዊ ሰርቲፊኬታቸውን ወዲያውኑ አውርደው (download አድርገው) መውሰድና መጠቀም እንደሚችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል፡፡

የ2017 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተፈተኑ ተፈታኞች በሚከተሉት አድራሻዎች ዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ፡፡

ውጤት ለመመልከት አድራሻዎች:-

1. በዌብ ሳይት፡ https://result.eaes.et
2. በቴሌገራም፡ https://t.me/EAESbot
3. በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡ 6284

Address

Dembecha Woreda Government Communicationየደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን
Dembech'a

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dembecha zuria Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dembecha zuria Communication:

Share