14/10/2025
ጥበበ ጊዮን ሆስፒታል «ሪፈር» ለማቆም እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፤
ታካሚዎችን ወደ ሌላ የህክምና ተቋም ሳይልክ የተሟላ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት እየሠራ መሆኑን የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስታወቀ፡፡
የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር በቃሉ ውብሸት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የአውሮፓ ህብረት ባደረገው ድጋፍ የሆስፒታሉን የቀዶ ጥገና ክፍሉን የማዘመንና መሰረተ ልማቶችን የማደስ ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
ይህም ወደአዲስ አበባና ዉጭ ሀገራት በሪፈር የሚላኩ ታካሚዎች በሆስፒታሉ እንዲገለገሉ አቅም የሚፈጥር ይሆናል። በተጨማሪም ስራው ሲጠናቀቅ አሁን ከሚያስተናግዳቸው በላይ የቀዶ ህክምና ተማሪዎችን ለመቀበልም የሚያስችለው ይሆናል፡፡
ሆስፒታሉ በጸጥታ ችግር ከደረሰበት ጉዳት በማገገም በተጠናቀቀው ዓመት በተመላላሽ 20ሺ ታካሚዎችን፤ በአጠቃላይ ህክምና መቶ ሺህ የሚደርሱ ታካሚዎችን ያገለገለ ይገኛል። ያሉት ዶክተር በቃሉ አጠቃለይም 10 ሚሊዮን ለሚደረስ ህዝብ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተጨማሪ ከ300 በላይ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን ጨምሮ ከሁለት ሺ በላይ እያስተማረ እንደሚገኝና በ12 የስፔሻላይዜሽንና በሰባት የሰብ ስፔሻላይዜሽን ፕሮግራሞች ትምህርት እንደሚሰጥም ጠቁመዋል ሲል የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን ዋቢ አድርጎ Amhara Communications ዘግቧል።