Dembecha zuria Communication

Dembecha zuria Communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dembecha zuria Communication, Media/News Company, Dembecha Woreda Government Communicationየደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን, Dembech'a.

ከ43 ሺህ በላይ የከተማው ነዋሪዎች የፋይዳ ዲጂታል ብሔራዊ መታወቂያ ተጠቃሚ ሆነዋል። በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር የመንግስትና የግል አገልግሎቶችን ለማዘመን በተከናወነ...
09/06/2026

ከ43 ሺህ በላይ የከተማው ነዋሪዎች የፋይዳ ዲጂታል ብሔራዊ መታወቂያ ተጠቃሚ ሆነዋል።

በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር የመንግስትና የግል አገልግሎቶችን ለማዘመን በተከናወነው የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባ ሥራ ከ43 ሺህ በላይ የሚሆኑ የከተማው ነዋሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ከተማ አስተዳደሩ ገልጿል።

ያነጋገርናቸው የብሔራዊ መታወቂያ ተጠቃሚ የሆኑ ነዋሪዎች ለእያንዳንዱ ግለሰብ አንድ ጊዜ ብቻ የሚሰጠውና 12 አሃዝ የፋይዳ ቁጥር ያለው ነው ይህ መታወቂያ በርካታ ጥቅሞችን ከመስጠቱ ባሻገር ብልሹ አሠራሮችን በመከላከል ረገድም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።

ነዋሪዎቹ እንደገለጹት፣ የቀበሌ መታወቂያ በተለያዩ ቦታዎች ሊወጣ የሚችል በመሆኑ ለተለያዩ የማጭበርበር ድርጊቶች ተጋላጭ ነበር። ብሔራዊ መታወቂያው ግን ሙሉ ባዮሜትሪክ መረጃ (አሻራ) ስለሚይዝ ከአንድ በላይ ጊዜ ማውጣት የማይቻል ሲሆን ለብድር ፣ለዋስትና እና ለሌሎች ዘመናዊ አገልግሎቶችም ጠቃሚ መሆኑን ገልጸዋል።

የፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ በየነ እንደገለጹት፣ ብሔራዊ መታወቂያ አዲስ የመንግስት ኢኒሼቲቭ በመሆኑ ማኅበረሰቡ በስፋት ተጠቃሚ እንዲሆን ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ተከናውነዋል።

መታወቂያው የሚሰጥባቸውን ቦታዎችና ሂደቶች በተቀናጀ መንገድ ለማስተዋወቅ የተሠራው ሥራ ጉልህ የግንዛቤ ለውጥ በማምጣቱ በርካታ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ሆነዋል ብለዋል።

በተጨማሪም የብሔራዊ መታወቂያውን እስከ ሰኔ 20 ድረስ ከባንክ ሥርዓት ጋር በማስተሳሰር የሚገኙ ጥቅሞችን በመጠቀም ሁሉም ነዋሪዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

የፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ወርቁ በላይ በበኩላቸው፣ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ማኅበረሰቡን የዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ በማድረግ አሠራሮችን ለማዘመን የታለመ የመንግስት ኢኒሼቲቭ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ መታወቂያ ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከል፣ የንግድ ሥርዓቱን ለማዘመን እና ትክክለኛ የሕዝብ ቁጥር መረጃን ለማግኘት ጠቃሚ ሲሆን፣ በተደረገው የቅንጅት ሥራ ከ43 ሺህ በላይ የከተማው ነዋሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ ተጠቃሚ ሆነዋል በዚህም የተያዘው እቅድ መቶ በመቶ መፈጸሙን ተናግረዋል።

#ፍኖተ ሰላም ኮሙኒኬሽን

የምዕራብ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 የሀገር አቀፍ እና ክልላዊ አቀፍ ፈተና ቅድመ ዝግጅት አስመልክቶ ከፈተና ግብረ ሀይል ጋር ዞናዊ የምክክር መድረክ በፍኖተሰላም ከተማ እየተካሄደ...
09/06/2026

የምዕራብ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ የ2018 የሀገር አቀፍ እና ክልላዊ አቀፍ ፈተና ቅድመ ዝግጅት አስመልክቶ ከፈተና ግብረ ሀይል ጋር ዞናዊ የምክክር መድረክ በፍኖተሰላም ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ የተገኙት የምዕራብ ጎጃም ዞን ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሙላት ጌታቸው በዘንድሮ ዓመት ለሚሰጠው ክልል አቀፍና ሀገር አቀፍ ፈተና በሰላማዊ መንገድ እንዲሰጥ የፈተና ግብረ ሀይል አባላት ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ጠንካራ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ይገባል ብለዋል።

ዞኑ ዘላቂ ሰላም ከመገንባት ጎን ለጎን የመማር ማስተማር ሂደቱን በማስቀጠል ለክልልና ለአገር አቀፍ ፈተና ማዘጋጀት መቻሉ በጥንካሬ የሚገለጽ መሆኑን ኃላፊው አንስተዋል።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ የስጋት ደሴ እንዳሉት በ2018 በዞኑ የ6ኛ፣የ8ኛ እና የ12 ክፍል ክልል እና ሀገር አቀፍ ፈተና በሁለት ዙር ይሰጣል ብለዋል።

በ2017 በነበረው ክልልና አገር አቀፍ ፈተና ጥንካሬዎችን በዚህ ዓመት በማስቀጠል ውስኑነቶችን ደግሞ እንዳይደገሙ የፈተና ግብረ ሀይሉ በጥንቃቄ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል።

የመምሪያ ኃላፊው አቶ የስጋት ክልላዊ የ6ኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 9/2018 የሚሰጥ ሲሆን ከሰኔ 11 እስከ ሰኔ 12/2018 የ8ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥ መሆኑን ይፋ ያደረጉ ሲሆን ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም ድረስ ደግሞ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይሰጣል ብለዋል።

በዘንድሮ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ወረቀት መሠረት ያደረገ እና በበየነ መረቭ መሠረት የሚሰጥባቸውን የ12ኛ ክፍል ትምህርት ቤቶችን ይፋ አድርገዋል።

#ፍኖተሰላም #ትምህርት #ፈተና2018
West Gojjam Communications

‎የአመጋግብ ስርዓትን በማሽሻል ህፃናትን ከመቀጨጭና ከመቀንጨር መታደግ እንደሚገባ ተገለፀ። ‎‎በምዕራብ ጎጃም ዞን የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት የሰቆጣ ቃል...
08/06/2026

‎የአመጋግብ ስርዓትን በማሽሻል ህፃናትን ከመቀጨጭና ከመቀንጨር መታደግ እንደሚገባ ተገለፀ።

‎በምዕራብ ጎጃም ዞን የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት የሰቆጣ ቃል-ኪዳን ፕሮግራም አተገባበር በሚመለከት ስልጠናዊ ግምገማ አካሂዷል።

‎የስልጠናዊ ግምገማ መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት ያቀረቡት የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት የሴቶች ግንዛቤና ንቅናቄ ተሳትፎ ቡድን መሪ አቶ አድገህ ልንገርህ በወረዳችን እየተሰራ የሚገኘው የስርዓተ ምግብ ማሻሻል ፕሮግራም ውጤታማ እንዲሆን፣ አዕምርውና ጤናው የተጠበቀና የተስተካከለ ትውልድ ማፍራት እንዲቻል አጋር አካላት በቅንጅት በመስራት በ2022 ዓ/ም ህፃናትን ከመቀንጨርና ከመቀጨጭ ነፃ ማድረግ እንደሚቻል አስገንዝበዋል።

‎ወረዳችን ትርፍ አምራች ቢሆንም የአመጋግብ ስርዓታችንን በማሸሻል የነገውን ትውልድ መገንባትና የተስተካከለ ቁመና ያለው ትውልድ መፍጠር የስፈልጋል። ባለድርሻ አካላት ቀጣይ ተልኮ ወስደን ድጋፍና ክትትሉን የበለጠ አጠናክረን መስራት ይገባል ብለዋል።

‎ተሳታፊዎች በበኩላቸው የሰቆጣ ቃል ኪዳን ወደወረዳችን የመጣው ዘግይቶ ቢሆንም ባለን ጊዜ እና በወሰድነው ስልጠና መሰረት አቅም ያነሳቸውን ነፍሰ ጡርና የሚያጠቡ እናቶችን ከታላሚ ቀበሌዎች በመለየትና በመመልመል የበግና የዶሮ ድጋፍ እንዲደረግላቸው አድርገናል ብለዋል።

‎ተሳታፊዎቹ አክለውም የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ወደ ወረዳችን ምጣቱ የንጹህ መጠጥ ውሃ እንድናገኝ አድርጎናል፤ ለተቸገሩትም ደርሶልናል በማለት አመስግነዋል።

‎የሰቆጣ ቃልኪዳን አስተባባሪ አቶ አስቻለ እንደገለጹት የሰቆጣ ቃልኪዳን ፕሮግራም እየሰራ ያለው ነፍሰ ጡር፣ የሚያጠቡ እናቶች እና ከ2 ዓመት በታች ያሉ ህፃናት አመጋግባቸውን እንዲያሻሽሉ በማድረግ የአስተሳስብ ለውጥ እንዲያመጡ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

‎ባለድርሻ አካላት ተናቦና ተቀናጅቶ መስራት ያስፈልጋል ያሉት የፕሮግራሙ አስተባባሪ ሃላፊነት የተሰጣቸው ተቋማት ክፍቶችን እየሞሉ፣ እያስተካከሉና እየገመገሙ ስራዎችን መስራት እንደሚገባ አመላክተዋል።

‎የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶችና ወጣቶች ማህበራዋ ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ነገሰ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ ቀጣይነት እንዲኖረው ታላሚ ቀበሌዎችን ሞዴል አድርጎ በቀጣይ ደግሞ ወደ ሌሎች ቀበሌዎች እንዲሰፋ ማድረግ እና የተሰሩ ስራዎች ዘላቂነት እንዲኖራቸው በቅንነት ተቀብሎ መተግበርና ውጤታማ ስራ መስራት ይገባል ብለዋል።

‎በነፍሰጡር እና በሚያጠቡ እናቶችና በህፃናት ስም የመጣውን ፕሮጀክት ለታለመለት ዓላማ ማዋል ከምንም በላይ የህሌና ርካታ ይሰጣል ነው ያሉት።

‎በመጨረሻም ድጋፍ የተደረገላቸውን በጎችና ዶሮዎች እንዲንከባከቧቸው፣ እንዲሁም የአዝርት ግብዓቶችን በአግባቡ እንዲጠቀሟቸው ተከታታይነት ያለው ድገፍና ክትትል ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ለሚመለከተው አካላት አሳስበዋል።

‎የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ አላምር የሰቆጣ ቃል ኪዳን ወደ ወረዳችን የመጣው ብዙ ችግሮች በመኖራቸው ነው ብለዋል።

‎ የስርዓተ ምግብ የሚሸሻለው ግብርና፣ ጤና እና ሌሎችም ላይ በስፋት መስራት ስንችል ነው። ፕሮግራሙ በዘላቂነት ብዙ ስራዎችን እየሰራ ነው ያሉት አቶ ብርሃኑ ለፕሮጀክቱ ምቹ ሁኔታ ፈጥረን መስራትና ቀጣይነት እንዲኖረው በተሻለ መንገድ ሰርተን ስንገኝ ነው ብለዋል።

‎በመጨረሻም የፕሮጀክቱን ዓላማን ማሳካትና ህፃናትን ከመቀንጨርና ከመቀጨጭ መታደግ ያስፈልጋል እና ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታችሁን ተወጡ ሲሉ አሳስበዋለ።

የአካባቢያቸውን ሰላም በማስጠበቅ ውጤታማ ሥራ ያከናወኑ ዞኖች፣ ብሔረሰብ አሥተዳደሮች እና ከተማ አሥተዳደሮች በ30ኛው የሚሊሻ ምስረታ በዓል ላይ የተደረገላቸው ዕውቅና እና ምስጋና በምስልአማ...
08/06/2026

የአካባቢያቸውን ሰላም በማስጠበቅ ውጤታማ ሥራ ያከናወኑ ዞኖች፣ ብሔረሰብ አሥተዳደሮች እና ከተማ አሥተዳደሮች በ30ኛው የሚሊሻ ምስረታ በዓል ላይ የተደረገላቸው ዕውቅና እና ምስጋና በምስል

አማራ ኮሙዩኒኬሽን

በደምበጫ ከተማ አስተዳደር እና ዙሪያ ወረዳ አመራሮች 7ኛው አገራዊ ክልላዊ ምርጫ መጠናቀቁን በማስመልከት "ኢትዮጵያ መርጣለች ህዝቦቻም አሸንፈዋል"በሚል መሪ ቃል ስፖርታዊ ውድድር ተካሄደ‎‎...
07/06/2026

በደምበጫ ከተማ አስተዳደር እና ዙሪያ ወረዳ አመራሮች 7ኛው አገራዊ ክልላዊ ምርጫ መጠናቀቁን በማስመልከት "ኢትዮጵያ መርጣለች ህዝቦቻም አሸንፈዋል"በሚል መሪ ቃል ስፖርታዊ ውድድር ተካሄደ

‎​በደምበጫ ከተማ ባህል፣ ቱሪዝም እና ስፖርት ጽሕፈት ቤት አስተናጋጅነት የተዘጋጀው ዘመናዊ የስፖርት ውድድር በደምበጫ ከተማ በአካሉ አምባው ስታዲየም በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል።

‎በዚህ መርሀግብር የሁለቱም ጎረቤታማ ወረዳ አመራሮች መካከል የእርስ በርስ ትስስርንና ወዳጅነትን የሚያጠናክሩ የእግር ኳስ እና የመረብ ኳስ ጨዋታዎች ተካሂደዋል።
‎በዕለቱ በተደረጉት ጨዋታዎች ላይ ብርቱና ፉክክር የተስተዋለ ሲሆን በእግር ኳስ ጨዋታ ደምበጫ ከተማ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ በድል አጠናቋል። በመረብ ኳስ ውድድር ደምበጫ ዙሪያ ወረዳ አሸናፊነት የእለቱን የውድድር ጨዋታ የበላይነት ተጠናቋል።

‎የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት የሰቆጣ ቃል ኪዳን አተገባበር  የሚመለከት ስልጠናዊ ግምገማ እያካሄደ ነው።‎‎የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም እንደ ወረዳ 9 ተቋማ...
07/06/2026

‎የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት የሰቆጣ ቃል ኪዳን አተገባበር የሚመለከት ስልጠናዊ ግምገማ እያካሄደ ነው።

‎የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም እንደ ወረዳ 9 ተቋማትን በማቀፍ መቀንጨርንና መቀጨጭን ለማስቀረት ስራ እየሰራ ይገኛል።

‎እንደ ወረዳ 3 ቀበሌዎችን በመምረጥ የተሞክሮ ማዕከል ለማድረግ ሰፊ ስራ እየተሰራ ሲሆን እንደ ወረዳ በተቋሙ የተሰሩ ስራዎችን አፈፃፀም አስመልክቶ ግምገማዊ ስልጠና ለሚመለከታቸው አካላት እየሰጠ ነው።

‎በመድረኩ ተገኝተው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሰናይት እንደተናገሩት የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም በሶስት ታላሚ ቀበሌዎች ከተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች፣የሐይማኖት አባቶች፣ ለጤና ኤክስቴሽን ባለሙያዎች፣ ለነፍሰጡርና ለሚያጠቡ እናቶች እና ሌሎችም ስልጠና በመስጠት ድጋፍና ክትትል እያደረግን ነው ብለዋል።

‎ወ/ሮ ሰናይት አክለውም እንደ ተቋም ድጋፍና ክትትል እያደረግን ያለ ቢሆንም ዛሬ ላይ በፕሮግራሙ የተሰሩ ስራዎችን የምንገመግምበት፣ መስተካከል ያለባቸውን የምናስተካክልበት እና ስራዎችን በጥልቀት የምንገመግምበት ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

"ሚሊሻ የሰላም ምንጭ እና የሕግ መከታ ነው"  የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን 30ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን የማጠቃለያ መርሐ ግብር በባሕር ዳር አካሂዷል። የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻ...
06/06/2026

"ሚሊሻ የሰላም ምንጭ እና የሕግ መከታ ነው"

የአማራ ክልል ሚሊሻ ኮሚሽን 30ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን የማጠቃለያ መርሐ ግብር በባሕር ዳር አካሂዷል።

የክልሉ ሚሊሻ ኮሚሽን ኮሚሽነር አስቻለ አላምሬ የሚሊሻ ኃይል ሕዝባዊ ሚሊሻ ተብሎ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የውጭ እና የውስጥ ጠላትን በመመከት ከፍተኛ ሀገራዊ ገድል መፈጸሙን ተናግረዋል።

የአሁኑ የአማራ ክልል ሚሊሻም ላለፉት ዓመታት ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመኾን የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ ግንባር ቀደም መስዋዕትነት ከፍሏል ብለዋል። "ሚሊሻ የሰላም ምንጭ እና የሕግ መከታ እንደኾነም" ገልጸዋል።

አሁንም የውስጥ እና የውጭ ጽንፈኛ ኃይሎች በሕዝብ እና በመንግሥት ላይ የከፈቱትን ጦርነት ለመመከት ከፍተኛ ዋጋ እየከፈለ ይገኛል ነው ያሉት።

በቀጣይ ሀገራዊ እና ክልላዊ የቤት ሥራዎችን ከግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚገባ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር የሌላት ሀገር በመኾኗ ከአጎራባች ሀገራት ጋር በሰላም የመኖር እና አብሮ የማደግ ጥያቄ እንዳላት ጠቁመዋል። መላው ሕዝብ እና የሚሊሻ አባላት በቅንጅት በመሥራት የአካባቢያቸውን ሰላም ማረጋገጥ እንዳለባቸውም ጥሪ አቅርበዋል።

ሕዝቡ ለሠራዊቱ የሚያደርገው ድጋፍ የራሱን ሰላም እና ሕይወት በባለቤትነት የመጠበቅ ጉዳይ እንደኾነም አንስተዋል።

በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአሥተዳደር ዘርፍ አሥተባባሪ አማኑኤል ፈረደ (ዶ.ር) በዓሉ የተጀመረውን የሕግ ማስከበር ሥራ ይበልጥ ለማጠናከር፣ ዝግጁነትን ለማደስ እና ለክልሉ ዘላቂ ሰላም በጋራ ለመቆም አዲስ ቃል የሚገባበት ነው ብለዋል።

የአማራ ሚሊሻ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የሀገር ድንበር ጠባቂ፤ የሕዝብ ደኅንነት አሥከባሪ እና በችግር ጊዜ ፈጣን ምላሽ ሰጭ በመኾን ማገልገሉን ተናግረዋል።

ከሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ከፌዴራል ፖሊስ እና ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በሀገራዊ ሉዓላዊነት እና በክልላዊ የጸጥታ ፈተናዎች ወቅት የማይረሳ የታሪክ አሻራ ማሳረፉንም ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት የክልሉ መንግሥት የሰላም ጥሪዎችን እና የሕግ ማስከበር ሥራዎችን እያስቀጠለ ይገኛል ነው ያሉት። የሕዝብን ሰላም፣ ሕይወት እና ንብረት አደጋ ላይ የሚጥሉ አካላትን ለመከላከል መንግሥት ባለው ቁርጠኛ አቋም ውስጥ የሚሊሻው ሚና ከፍተኛ መኾኑንም ጠቁመዋል ሲል አሚኮ ዘግቧል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ኮሙኒኬሽን የመረጃ መረቦች ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ይችላሉ፡፡
‎Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=100068667050208
‎Telegram ፡ https://t.me/+gd9o0kwBHcdlZmU0
‎Ticktock: tiktok.com/.zuria.c
‎youtube:https://www.youtube.com//?si=jG63-YD7Fxfs-rmX/b

የፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳር የልማት ፕሮጀክቶችን በጊዜና በጥራት ለማጠናቀቅ እየሰራ መሆኑን ገለጸ። የከተማ አስተዳደሩ ከተማና መሠረተ ልማት ጽሕፈት ቤት  የ2018 በጀት ዓመት የፕሮጀክት ...
06/06/2026

የፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳር የልማት ፕሮጀክቶችን በጊዜና በጥራት ለማጠናቀቅ እየሰራ መሆኑን ገለጸ።

የከተማ አስተዳደሩ ከተማና መሠረተ ልማት ጽሕፈት ቤት የ2018 በጀት ዓመት የፕሮጀክት አፈጻጸም ግምገማዊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩም በከተማ አስተዳደሩ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶችን በጊዜና በጥራት ለማጠናቀቅ የጋራ መግባባት መፈጠሩ ተገልጿል።

የከተማና መሠረተ ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ወርቅነህ ድረስ እንደገለጹት፣ በግንባታ ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችን ክረምት ከመግባቱ በፊት ለማጠናቀቅ ቅድሚያ እንደሚሰጥ ገልጸው፣ ቀጣይ የልማት ዕቅዶችም ከማኅበረሰቡ ጋር በመመካከር እንደሚዘጋጁ አስታውቀዋል።

መድረኩ የልማት ፕሮጀክቶችን በተቀመጠላቸው የጊዜ ሰሌዳና የጥራት ደረጃ ለማጠናቀቅ የጋራ ግንዛቤና ቁርጠኝነት የተፈጠረበት መሆኑንም ገልጸዋል።

በመድረኩ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው፣ የገቢ አሰባሰብን ማጠናከር፣ ፕሮጀክቶችን በጥናትና በማኅበረሰብ ተሳትፎ ማቀድ እንዲሁም የልማት ሥራዎችን በወቅቱ ማጠናቀቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።

መረጃው የፍኖተ ሰላም ከተማ ኮሙኒኬሽን ነው

"ምርጫውን ለማደናቀፍ የውጭ ባዳዎች እና የውስጥ ባንዳዎች ያደረጉት ዕቅድ ከሽፏል" የሰላም ሚኒስትር ሙሐመድ እድሪስ የሰላም ሚኒስትር ሙሐመድ እድሪስ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል...
06/06/2026

"ምርጫውን ለማደናቀፍ የውጭ ባዳዎች እና የውስጥ ባንዳዎች ያደረጉት ዕቅድ ከሽፏል" የሰላም ሚኒስትር ሙሐመድ እድሪስ

የሰላም ሚኒስትር ሙሐመድ እድሪስ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫው እንዳብራሩት ለውጡን የማይፈልጉ አካላት ሀገራችን እንዳትረጋጋ ዘመናዊ ቴክኖሎጅን እና ሚዲያን በመጠቀም የተለያዩ አፍራሽ ተግባራትን ሲያከናውኑ ቆይተዋል።

የመንግሥትን ሥልጣን በኀይል ለመንጠቅ የሚፈልጉ ኀይሎች የውጭ ባዳዎችን ተልዕኮ ተቀብለው አፍራሽ ድርጊቶችን ሲያከናውኑ መቆየታቸውን አብራርተዋል። በቅርቡ የተካሄደውን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫን ለማደናቀፍም አለን በሚሉት አማራጮች ሁሉ ሞክረው አልተሳካላቸውም ብለዋል።

ሕዝቡን "ምርጫ ካርድ እንዳታወጡ፣ በምርጫ ድጋፍ እንዳትሳተፉ፣ እንዳትመርጡ" የሚል የተለያዩ የማስፈራሪያ ፕሮፖጋንዳዎችን ሲነዙ መቆየታቸውን አንስተዋል። ሕዝቡ ግን ሁሉንም ጥሪዎች ባለመቀበል አሸንፏቸዋል ነው ያሉት።

ሕዝቡ ሀገርን የሚያስቀጥል ቅቡልነት ያለው መንግሥት ያስፈልገኛል በሚል ጽኑ ዕምነት ካርድ ከማውጣት ጀምሮ ድምጹን እስከመስጠት ድረስ ቁርጠኝነቱን ማሳየቱን ገልጸዋል።

ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ የሚፈልገውን መርጧልም ነው ያሉት። በዚህም "ምርጫውን ለማደናቀፍ ያደረጉት የውጭ ባዳዎች እና የውስጥ ባንዳዎች ዕቅድ ከሽፏል" ብለዋል።

ምርጫውን ለማደናቀፍ ሞክረው አልሳካላቸው ያሉት እነዚህ ኀይሎች የሽብር ድርጊቶችንም ጭምር መሞከራቸውን ጠቁመዋል። በሸኔ የሽብር ቡድን በኦሮምያ ክልል አርሲ ዞን አስኮ ወረዳ የተፈጸመው የሽብር ድርጊትም ለዚህ በማሳያነት አንስተዋል።

ይህም ኾነ ብለው የኅብረተሰቡን አብሮነት ለመሸርሸር ያለመ ስለመኾኑም አንስተዋል። ድርጊቱ አሳዛኝ መኾኑን ገልጸው በጽኑ የሚወገዝ ነው ብለዋል። ሁሉም ሊያወግዘው እንደሚገባም ተናግረዋል።

ግጭቱ ሲከሰት ነዋሪዎችን ለመጠበቅ እና ድርጊቱን ለመከላከል ሲታገሉ የመንግሥት የጸጥታ ኀይሎችም መስዋትነት ከፍለዋል ነው ያሉት።

ከዚህ ጋር በተያያዘ በተለያዩ የመገናኛ አማራጮች የሚተላለፉ መረጃዎች ኀላፊነትን በመውሰድ፣ አብሮነትን እና አንድነትን በማይሸረሽር መልኩ መኾን እንዳለበትም ነው ያስገነዘቡት።

የሰላም ሚኒስቴር ከተለያዩ አካላት ጋር በመቀናጀት ችግሩን ለማርገብ በርካታ ሥራዎችን መሥራቱን አብራርተዋል። መንግሥት ከሃይማኖት አባቶች ጋር ተቀናጅቶ እየሠራ እንደሚገኝም አንስተዋል።

በቀጣይም የእነዚህን ኀይሎች ሴራ በመበጣጠስ አብሮነታችንን በማጎልበት ከመንግሥት ጋር ተቀናጅቶ መሥራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ዘገባው የአሚኮ ነው።

Address

Dembecha Woreda Government Communicationየደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን
Dembech'a

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dembecha zuria Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dembecha zuria Communication:

Share