10/08/2026
የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር የ90 ቀን ዕቅድ የክረምት ተግባራት አፈፃፀም ገመገመ።
በግምገማው የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መስፍን ልየውን ጨምሮ፣ የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ይበልጣል ባለው፣የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ብርሃኑ አላምር ፣ሁሉም የፖለቲካና የፀጥታ አመራሮች ተገኝተዋል።
የግምገማው አላማ የ90 ቀናትን ተግባራትን ዕቅድ አፈፃፀም በመገምግም ጥንካሬዎችንና በማስቀጠል ክፍተቶችን ለመሙላት እንደሆነ ተገልጿል።
አስተዳደር ም/ቤቱ የ90 ቀን ዕቅድ በማቀድ ወደ ተግባር በመግባት ከ30 ቀናት በላይ ያሳለፈ ሲሆን የዜጎች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ላይ ሰፊ ስራ እንደተሰራ ተገልጿል።
በቀሪ ቀናት ቀሪ ተግባራትን በመፈፀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።