17/09/2025
"ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ሃሳብ ለደምበጫ ዙሪያ ለወረዳ እና ለደምበጫ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሰራተኛ አባላት ስልጠና መሰጠት ጀመረ።
ደምበጫ መስከረም 7/2018 ዓ/ም(ደምበጫ ዙሪያ ኮሙኒኬሽን )
በምዕራብ ጎጃም ዞን በደምበጫ ዙሪያ እና ደምበጫ ከተማ አስተዳደር "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር " በሚል መሪ ሃሳብ መንግስት ሰራተኛ አባላት ስልጠና በደምበጫ ከተማ መሰጠት ጀምሯል ።
ስልጠናውን የደምበጫ ከተማ ምክትል ከንቲባ በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት ሲሆን የክልላችን እና የሃገራችን ብሎም የቀጠናችን ጂኦፖለቲካዊ ሁኔታ የምንረዳበት መድረክ ነው ብለዋል።
አቶ ሙሉቀን አክለውም አገራችን ኢትዮጵያ የስልጣኔ መፍለቂያ ብቻ ሳትሆን የስልጣኔ ቁንጮ የነበረች ሃገር ናት፤ስለሆነም የቀደመ ገናናነቷን ለመመለስ ብልፅግና እየሰራ ነው ብለዋል።
የደምበጫ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ልዑልሰገድ ካሳሁን የስልጠና መነሻ ሰነድ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
ስልጠናው የአባላትን አቅም የሚገነባ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።