Kobo Reporter - ቆቦ ሪፓርተር

Kobo Reporter - ቆቦ ሪፓርተር Delivers true and verified news. https://youtube.com/channel/UCBzYmwJjRG_twORbnuWj5kA

አደገኛ ሁኔታ ሊከሰት እንደሚችል አስጠንቀቁ‼️ደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ፣ ሕወሓትን በድጋሚ በምርጫ ቦርድ የማስመዝገብ ፍላጎት እንደሌለው በድጋሚ አስታውቋል። ቡድኑ፣ ቦ...
27/04/2025

አደገኛ ሁኔታ ሊከሰት እንደሚችል አስጠንቀቁ‼️

ደብረጺዮን ገብረሚካኤል የሚመሩት የሕወሓት ክንፍ፣ ሕወሓትን በድጋሚ በምርጫ ቦርድ የማስመዝገብ ፍላጎት እንደሌለው በድጋሚ አስታውቋል።

ቡድኑ፣ ቦርዱ የሠረዘው የቀድሞ ሕጋዊ ሰውነቱ ካልተመለሰለት፣ አደገኛ ሁኔታ ሊከሰት እንደሚችል አስጠንቅቋል።

ፌደራል መንግሥቱ ጉዳዩን ወደ ቴክኒካዊ ጉዳይ እያወረደው ይገኛል በማለት የከሰሰው ቡድኑ፣ መንግሥት የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት መንፈስ እንዲያከብር ጠይቋል።

(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዓለም ቤተክርስቲያናት ምክር ቤት በኢትዮጵያ ውስጥ በድሮን የሚፈፀመውን ጥቃት አወገዘ፡፡ የምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ ቄስ ዶክተር ጄሪ ፒላይ በመግለጫቸው ከቀናት በፊት በአማራ ...
27/04/2025

(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዓለም ቤተክርስቲያናት ምክር ቤት በኢትዮጵያ ውስጥ በድሮን የሚፈፀመውን ጥቃት አወገዘ፡፡

የምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ ቄስ ዶክተር ጄሪ ፒላይ በመግለጫቸው ከቀናት በፊት በአማራ ክልል በአንድ ትምህርት ቤት ለማህበራዊ እንቅስቃሴ በተሰባሰቡ ሰዎች ላይ በተፈፀመ ጥቃት ከመቶ በላይ ሰዎች መገደላቸውን ገልፀው ይህ ከቅርብ ወራት ወዲህ የተፈፀሙ ተመሳሳይ ጥቃቶች አንዱ አካል መሆኑን አስረድተዋል፡፡

‹‹ሰላማዊ ሰዎች በብዛት በሚገኙበት ቦታ ተመሳሳይ ጥቃት መፈፀም መቆም አለበት›› ያሉት ዋና ፀሀፊው እንዲህ አይነቱ ጥቃት በአለም አቀፍ ህግ እንደሚያስጠይቅና ከሞራል አኳያም ጥያቄ እንደሚያስነሳ ጠቁመዋል፡፡

ጨምረውም በግጭቱ ውስጥ እየተሳተፉ ያሉት ሁሉም አካላት አለም አቀፍ ህጎችን እንዲያከብሩና ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት ከመፈፀም እንዲታቀቡ አሳስበዋል፡፡

26/03/2025

ዱሮ ትምህርት ቤት ከማይረሱኝ
“ኢትዮጵያ መርፌ ታመርታለች ፣ ግን መርፌ መብሻው ስለሌላት ኬኒያ ተበስቶ ነው የሚመጣው “
የሚለው ነው😂 እናንተስ?

አሁን ይሄ ሆዱን ገልብጦ የቆመው ካፒቴን ተብየው እግር ኳስ ተጫዋች ነው?በሬ ነጋዴ ነው?አሳ አስጋሪ ነው?ምንድን ነው ቆይ?ምንድን ነው የምትለን ግን አለ ቴዲ😂😂
22/03/2025

አሁን ይሄ ሆዱን ገልብጦ የቆመው ካፒቴን ተብየው እግር ኳስ ተጫዋች ነው?በሬ ነጋዴ ነው?አሳ አስጋሪ ነው?ምንድን ነው ቆይ?
ምንድን ነው የምትለን ግን አለ ቴዲ😂😂

የዶ/ር ደብረ ፅዮን ቡድን የመቀሌ ኤፍ ኤም የሬዲዬ ጣብያን ተቆጣጠረ 2017 በደብረፂዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ክንፍን የሚደግፉ የትግራይ ኃይል አባላት መቀለ ኤፍኤም 1...
15/03/2025

የዶ/ር ደብረ ፅዮን ቡድን የመቀሌ ኤፍ ኤም የሬዲዬ ጣብያን ተቆጣጠረ 2017

በደብረፂዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ክንፍን የሚደግፉ የትግራይ ኃይል አባላት መቀለ ኤፍኤም 104́.4 እና የከተማዋን ከንቲባ ጽህፈት ቤት ሐሙስ፣ መጋቢት 3/2017 ዓ.ም. ተቆጣጥረዋል።

በተመሳሳይም ይኸው የህወሓት ክንፍ ከዚህ ቀደም በከተማው ምክር ቤት ተመርጠዋል ያላቸውን ረዳኢ በርሔን (ዶ/ር ) ድጋሚ የከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።

በደብረፂዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ክንፍን የሚደግፉ የትግራይ ኃይል አባላት መቀለ ኤፍኤም 104́.4 እና የከተማዋን ከንቲባ ጽህፈት ቤት ሐሙስ፣ መጋቢት 3/2017 ዓ.ም. ተቆጣጥረዋል።
በተመሳሳይም ይኸው የህወሓት ክንፍ ከዚህ ቀደም በከተማው ምክር ቤት ተመርጠዋል ያላቸውን ረዳኢ በርሔን (ዶ/ር ) ድጋሚ የከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።
በፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ከዚህ ቀደም በሌላኛው የህወሓት ክንፍ የተሾሙትን ከንቲባ እንቅስቃሴ በማገድ አቶ ብርሐነ ገብረየሱስን የመቀለ ከንቲባ አድርጎ መሾሙ ይታወሳል።
በሁለቱ የህወሓት ክንፎች መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ አንድ ሚሊዮን የሚጠጋ ነዋሪዎች ያሏት መቀለ ያለ ከንቲባ እና ያለ ሕዝባዊ አገልግሎት ለአራት ወራት ቆይታለች።
በደብረ ፂዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የህወሓት ክንፍን የሚደግፉ የትግራይ ሠራዊት አዛዦች መሪነት በተለያዩ የትግራይ ክልል ከተሞች እና ወረዳዎች የሚገኙ የጊዜያዊ አስተዳደር መዋቅሮችን በማፍረስ ጽህፈት ቤቶችን ተቆጣጥረዋል።
እንዲሁም በጊዜያዊ አስተዳደሩ ተሹመው የነበሩ አመራሮችን በመተካት ላይ ይገኛሉ።እየተሾሙ ያሉት አመራሮች በትግራይ ጦርነት ከመቀስቀሱ በፊት ምርጫ ተካሂዶ የተቋቋመው ምክር ቤት የሾማቸው አመራሮች ናቸው።
ለሁለት ዓመት የዘለቀውን የትግራይን ጦርነት የቋጨው የሰላም ስምምነት ተከትሎ የፌደራል መንግሥቱ ተቀባይነት የለውም ባለው ምርጫ የተቋቋመው የትግራይ መንግሥት እንዲፈርስ ተደርጓል።
ሆኖም ጊዜያዊ አስተዳደሩን ለማቋቋም በፈጀው ስድስት ወራት ውስጥ ሕገወጥ በተባለው ምርጫ የተሾሙ አመራሮች የክልሉ ከተሞች እና ዞኖችን ሲያስተዳድሩ ቆይተዋል።
የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ የጊዜያዊ አስተዳዳደሩን መሪነት የተረከቡት አቶ ጌታቸው ረዳ አብዛኞቹን አመራሮች በማንሳት በራሳቸው ሾመዋል።
ከዚህ ቀደም የነበሩ የከተማ እና የዞን አመራሮች ከመንግሥት ሥራ በበለጠ የፓርቲውን ተግባራት አስቀድመዋል በማለት በአዳዲስ አመራሮች መተካታቸውም ይታወሳል።
"እኔ በምክር ቤቱ የተሾምኩ ሕጋዊ ከንቲባ ነኝ። በመቀለ ከተማ እና በሌሎች ከተሞች ማቋቋሚያ አዋጅ 341 ማንኛውም ከንቲባን የሚሾመው አሸናፊው ፓርቲ ነው" ሲሉ አዲሱ የመቀለ ከንቲባ ረዳኢ በርሔ መናገራቸውን የክልሉ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
"ሉዓላዊ ሥልጣን የሕዝብ መሆኑ እየታወቀ ይሄንን በመጣስ የከንቲባውን ጽህፈት ቤት በመዝጋት ሕዝብ አገልግሎት እንዳያገኝ ተደርጓል" ያሉት ከንቲባው "አሁን ግን በምክር ቤቱ የተመረጠው ከንቲባ ሥራውን በይፋ ጀምሯል" ሲሉ አስታውቀዋል።
ካለፈው ዓመት አጋማሽ ወዲህ በህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መካከል በተፈጠረው አለመግባባት፤ ፓርቲው በሊቀመንበሩ ዶ/ር ደብረፂዮን ገብረ ሚካኤል እና በምክትል ሊቀመንበሩ ጌታቸው ረዳ በሚመሩ ቡድኖች ተከፍሎ እየተወዛገበ ይገኛል።
ለወራት በገለልተኝነት ከቆዩት የትግራይ ሠራዊት አዛዦች መካከል አብዛኞቹ በደብረፂዮን ለሚመራው ወገን ድጋፍ መስጠታቸውን ተከትሎ በክልሉ ውስጥ ስጋት ተፈጥሯል።

ክብር ያልጋረደው ሰብዕናይህ ከታች የምትመለከቱት ፎቶግራፍ ከአራት ዓመታት በፊት ያነሳሁት ነው፡፡የጓደኛችን ዮሐንስ ዚሮቲ ወላጅ እናት ወ/ሮ እቴነሽ ፍሬው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈው ሃዘን ተ...
26/02/2025

ክብር ያልጋረደው ሰብዕና

ይህ ከታች የምትመለከቱት ፎቶግራፍ ከአራት ዓመታት በፊት ያነሳሁት ነው፡፡የጓደኛችን ዮሐንስ ዚሮቲ ወላጅ እናት ወ/ሮ እቴነሽ ፍሬው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈው ሃዘን ተቀምጠን ሳለ በሁለት ጊዜ ምርጫዎች ላለፉት 8 ዓመታት የአፍሪካ ህብረት ዋና ሊቀመንበር የነበሩት የተከበሩ ሙሳፋኪ ማሃማት ለቅሶ ደርሰውን ነው፡፡
ነገሩ እንዲህ ነበር፡፡

እናታችንን በቀበርን ማግስት ነው፡፡አንድ የህብረቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊ ቀደም ብሎ በመገኘት ሊቀመንበሩ ለቅሶ ለመድረስ ሊመጡ መሆኑን ለጆን ሹክ ሲለው ሃዘንተኛው ጓደኛችን ደንገጥ ብሎ በሀገራችን ባህል እና ወግ መሰረት "አረ አይገባም.."እያለ ሲግደረደር አየነው፡፡ ሰውየው ካለባቸው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊነት እና ፕሮቶኮል አንፃር መምጣት አይጠበቅባቸውም፡፡ስለዚህ በእኛ በኩል የጆን ሰውየው እንዳይመጡ መከላከሉ ተገቢ ነው ብለን አምነናል፡፡ማሰባቸው ራሱ ትልቅ ነገር ነው እንደማለት ስናሞጋግሳቸው ቆየን፡፡ይሁን እንጂ ድንገት አንድ ሞተረኛ ሰፈር ድረስ በመምጣት መንደሩ መኪና የሚያስገባ መሆኑን አለመሆኑን አረጋግጦ ሲመለስ የሊቀመንበሩ ለቅሷችን ላይ መገኘት እርግጥ መሆኑን አወቅን እና እሳቸውን የሚመጥን አቀባበል ለማድረግ ጭንቅ ጥብብ አልን፡፡

እስኪ አስቡት፡፡የአፍሪካ ህብረት ዋና ሊቀመንበር ሀዘናችንን ሀዘናቸው አድርገው ወንድማችንን ለማፅናናት ቄራ ድረስ ሲመጡ፡፡እኔ መቁነጥነጥ ከጀመርኩ ቆይቻለሁ፡፡ከጆን በስተቀር ለሁሉም የቤተሰብ አባላት መመሪያ እና የሥራ ስምሪት እየሰጠሁ ማዋከብ ጀመርኩኝ፡፡ሥራ ነገሬ ጆንን ከሃዘን ድባብ ያወጣው ይመስላል፡፡ደጅ ወጥቼ ፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦዎች ሁሉ "ካልተደፈኑ" አልኩኝ፡፡ አይገርምም…ማንም ስልጣን ሳይሰጠኝ ራሴን በራሴ በመሾም ሰፈርተኛው ንቅንቅ እንዳይል አዘዝኩኝ፡፡አቤት ማሽቋለጥ፡፡🤔

ከ30 ደቂቃ ጥበቃ በኋላ ከፊት አንድ ሞተረኛ እየመራቸው ክቡርነታቸው ቅንጡ በሆነች ጥቁር መርሰዲስ ቤንዝ ስፕሪንተር መኪና ብቅ አሉ፡፡ሌላ ቀን በክብር እንግድነት በተገኙበት ቦታ ሁሉ ቀደም ብሎ እየተንቀሳቀሰ እያንዳንዷን ቅፅበት ፎቶ የሚያነሳቸው ጆን ነበረ፡፡ዛሬ እሱ ሃዘን ላይ ነው፡፡ይሁን እንጂ እሳቸው እሱን ብለው ሰፈራችን የተገኙበት አጋጣሚ ፎቶ ሳይነሳ መቅረት ስላልነበረበት ዘመኑ ያፈራውን የተንቀሳቃሽ ስልክ ካሜራ በመጠቀም ይሔንን ምስል ለታሪክ አስቀረሁት፡፡ቄራ በተለይም 09 በዚህ ታሪካዊ ኹነት ልትኮሩ ይገባል፡፡ድፍን አፍሪካ ለቅሶ እንደደረሰን የቆጠርንበት አጋጣሚ ነው፡፡ለክቡር ሊቀመንበር ቡና አፍልታ ያቀረበችላቸው የጆን ታናሽ እህት ትዕግስት ነበረች፡፡ደጋግመው ፉት ካሉላት በኋላ ጥሩ ቡና መሆኑን ከምስጋና ጋር ገልፀውላታል፡፡

እኒህ ሰው በከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ትልቅ ባለስልጣን ቢሆኑም ዝቅ ብለው ሀዘን የጎዳውን ሰው ለማፅናናት በዚህ ልክ መገኘታቸው ለብዙዎች ጥሩ ትምህርት ይመስለኛል፡፡በአሁኑ ሰዓት ክቡር ሙሳፋኪ ማሃማት የሊቀመንበርነት ዘመናቸውን ጨርሰዋል፡፡እኛም ጉዳዩ ከወንድማችን ሥራ ጋር እንዳይያያዝ ላለፉት አራት አመታት ጠብቀነው ያቆየነውን መረጃ በዋዛ እና ቁምነገር በዚህ ሁኔታ ስናካፍላችሁ አንድም ክብር ያልሸፈነውን የኒህን ታላቅ ሰው ሰብዕና እንድትመለከቱልን በማሰብ ነው፡፡Thank You Mr M***a faki Mahamat AU Chairperson እናታችን ወ/ሮ እቴነሽ ፍሬው እና አባታችን ጋሽ አድማሱ ነፍሳችሁ በሰላም ትረፍ፡፡መላው ልጆቻቸው መፅናናት ይሁንላችሁ፡፡
ሰለሞን ግርማ
የካቲት 18 ቀን 2017ዓ.ም.

ይሄማ ተልእኮ ተሰጥቶት ነው የመጣው ፥ በአፍሪካ ህብረት ተሰብሳቢዎች ፊት ሂድና አዋርዳቸው ተብሎ ተልኮ ነው ፥ በደንብ ይመርመር!!AB Bella
13/02/2025

ይሄማ ተልእኮ ተሰጥቶት ነው የመጣው ፥ በአፍሪካ ህብረት ተሰብሳቢዎች ፊት ሂድና አዋርዳቸው ተብሎ ተልኮ ነው ፥ በደንብ ይመርመር!!
AB Bella

ማህበራዊ ሚድያ ላይ ትችት በማቅረብ የሚታወቀው ሰመረ ካሳዬ (ሰመረ ባርያው) ታሰረ (መሠረት ሚድያ)- በቅርብ አመታት ማህበራዊ ሚድያ ላይ የሚለቀቁ ቪድዮዎችን መነሻ በማድረግ ትችት እና ሽሙ...
02/02/2025

ማህበራዊ ሚድያ ላይ ትችት በማቅረብ የሚታወቀው ሰመረ ካሳዬ (ሰመረ ባርያው) ታሰረ

(መሠረት ሚድያ)- በቅርብ አመታት ማህበራዊ ሚድያ ላይ የሚለቀቁ ቪድዮዎችን መነሻ በማድረግ ትችት እና ሽሙጥ በማቅረብ የሚታወቀው ሰመረ ካሳዬ (ሰመረ ባርያው) በትናንትናው እለት በፀጥታ አካላት አዲስ አበባ ውስጥ ተይዞ እንደታሰረ ታውቋል።

የመሠረት ሚድያ ምንጮች እንደጠቆሙት ሰመረ ትናንት እኩለ ቀን ገደማ ምሳ ከጓደኞቹ ጋር በልቶ እየወጣ በነበረበት ወቅት በፀጥታ አካላት ተይዞ ተወስዷል።

ሰመረ ብዙውን ግዜ ትችት የሚያቀርበው በማህበረሰቡ ዘንድ ጥያቄ በሚያስነሱ እና አነጋጋሪ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሆኖ ሳለ ለእስር መዳረጉ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው። ከዚህ በፊት ተመሳሳይ ስራዎቹን በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ሲያቀርብ እንደነበር ይታወሳል።

በተመሳሳይ መልኩ ገጣሚ እና የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅ ምስራቅ ተረፈ ከትናንት በስቲያ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም በፖሊስ ለጥያቄ ትፈለጊያለሽ ተብላ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንደተወሰደች መሠረት ሚድያ መዘገቡ ይታወሳል።

መረጃን ከመሠረት!

02/02/2025

ጅቡቲ አፋር ላይ ድሮን ተኩሳ ብዙ ህዝብ አለቀ

በሽረ ከተማ የሆነው ምንድን ነው።በትግራይ ክልል በተፈጠረው የፖለቲካ አለመረጋጋትን ወደ ባሳ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያልሙ ህልመኞች ህዝቡ ጦርነት ይነሳል በሚል ስጋት ተሰልፎ ከንግድ ባንክ ብር...
02/02/2025

በሽረ ከተማ የሆነው ምንድን ነው።

በትግራይ ክልል በተፈጠረው የፖለቲካ አለመረጋጋትን ወደ ባሳ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያልሙ ህልመኞች ህዝቡ ጦርነት ይነሳል በሚል ስጋት ተሰልፎ ከንግድ ባንክ ብር እያወጣ ነው በማለት በአካባቢው ስጋት ለመፍጠር ቢዋሹም እውነታው ግን ሌላ ነው።

በሽረ-እንዳስላሴ ከተማ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲህ ተሰልፎ ብር የሚያወጣው ህዝብ የአለም ምግብ ፕሮግራም WFP (world food programme) ህዝቡን ለመርዳት በማሰቡ ለ31 ሺህ ተጠቃሚዎች ለእያንዳንዳቸው 9200 ብር እንዲሰጥ በመወሰኑ ያንን ብር ለመውሰድ የተሰባሰቡ የአለም ምግብ ፕሮግራም ተረጂዎች ናቸው።

መረጃውን ያገኘነው ከKdus Zenawi Meles

30/01/2025

ያልተጠበቀ ውሳኔ በፕሬዝዳንቱ ወሰኑ....

Address

Demt'a

Telephone

+251333310987

Website

https://www.facebook.com/Abyssinia365

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kobo Reporter - ቆቦ ሪፓርተር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Kobo Reporter - ቆቦ ሪፓርተር:

Share