ኑረል ኢስላም ሚዲያ Nuralislam Media

ኑረል ኢስላም ሚዲያ Nuralislam Media ወጣትነትህን ተጠቀምበት
ዲናዊ ትምህርት ለሁለት አገር ስኬት!!
ግሩፓችንን ለማግኘት
T.me/nuralislammediachats
ለገንቢ አስተያየትዎ
T.me/nuralislamtubecomentbot
T.me/nuralislambot

06/03/2023

ዕለተዕለት ለብዙ ሃጃችን ብዙ እንኳትናለን፣እንለፋለን፣እንፈጋለን። ግን ያ የምንለፋበት ሃጃ ዱንያን ብቻ ያለመነው ወይስ ለአኺራም ጭምር ነው? ራሳችንን ወደ መጥፎ ሁኔታ ለመክተት ሌት ተቀን ደፋ ቀና የሚሉ ጠላቶች አሉን።እነሱም ነፍስያ እና ሰይጣን ናቸው።በነዚህ ዛሬ ብንፈተን ወደ ኸይር ስራዎች ከተሽቀዳደምንና እጃችንን ያዝ የሚያደርግ ከባድ ፈተና ሲገጥመን ራሳችንን ዝቅ በማድረግና ለሀያሉ ጌታችን አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ እጃችንን ከፍ በማድረግና በመዋደቅ የራህመቱን ደጅ እናንኳኳ።
ምንም ምክንያት ቢገጥመን አስርም ቢሆን የዱንያ ሀጃ ፊታችን ቢደቀን ከኸይር ስራዎች እና ከጀመአ ውልፍት ማለት የለብንም። አለዚያ ወደ ነፈሰበት የምንነፍስ ከሆነ አወዳደቃችን ከባድ ነው።

እነሆ በወንጀል የቆሸሸች ልብ የምትጸዳበት፣የታጠፉ እጆች የሚዘረጉበት፣ምላሶችና ልቦች በቁርአን የሚረጥብበት ውድና የተከበረው ተናፋቂው ወር እየተጠጋን ነው።ስንቱ የረመዳንን መምጫ ሳይመለከት ወደ አኺራ የሄደ አለ፣ስንቱ በአሁን ሰአት በከፋና በማይድን ህመም የአልጋ ቁራኛ የሆነ አለ።እኛ አላሁ ሱ.ወ ለኛ በአፊያ እድል ሰጥቶናል ግን ወሩን ለመቀበል ተዘጋጅተናልን?ምን ያህል ራሳችንን አዘጋጅተናል?አሁንም አልረፈደም።የበደለንን ንጹህ የሆነ ይቅርታን እንበል፤ያስቀየምናቸውን አውፉ እንበል፤የተጣላን እናስታርቅ፣ጀመአን ከመበታተን ይልቅ እናጠናክር፤ምላሳችንን በቁርአን እንግራ፤የማይነጥፍ አጅር ከአላህ እናፍስ ዘንድ።
ወሩን የኸይር፣የፍቅርና የእውነተኛ ውዴታ ወር ያድርግልን።አሚን!!

✍ወንድም አንዋር ሱሴ
🕌رمضان مبارك

20/02/2023

ርብቃ ማይኒር አስደናቂ ታሪኳን እንዲህ ትተርክልናለች
………………………………………………

(አንብበው ሲጨርሱ አስተማሪ ታሪክ ስለሆነ ሼር ማድረግ አይዘንጉ)

°
"እስልምናን ከተቀበልኩ 8 አመታት ተቆጥረዋል..
ከአባቴ ጋር እጅግ የጠበቀ ግንኙነት አለኝ ጓደኛዬም ጭምር ነው ሁሉ ነገር በሰለጠነ መልኩ በግልፅ እናወራለን ..
°
እስልምናን ለምን እንደተቀበልኩ ? በምንስ ምክንያት እስልምና ከካቶሊክ የክርስትና እምነት ተሽሎ ምርጫዬ እዳደረኩት ? ይጠይቀኛል እኔም እስልምና ትክክለኛ ሃይማኖት መሆኑን ለምን እንደመሰከርኩ ዘርዝሬ አስረዳዋለሁ ..
°
በእስልምናን ውስጥ በየዕለቱ ያወቅኩትን ያጠናሁትን ሀዲሶችን እንዲሁም የቁርአን አንቀፆችን ሁልጊዜም ለአባቴ እነግረዋለሁ ..

አባቴም ስለ እስልምና የበለጠ የማወቅ ፍላጎት አድሮበታል ዳእዋ በሚሰጥበት ቦታዎችም ይዤው በመሄድ ትምህርቶችን እንከታተላለን እቤት ገብተንም በሰማነው ትምህርት ዙሪያ እንወያያለን ..

አባቴ በእስልምና መማረኩ ገብቶኛል አንድ ቀን ሸሀዳ እንደሚይዝም እርግጠኛ ሆኜ መናገር እችላለሁ ..
°
በእንዲህ ሁኔታእንዳለን
አንድ ወቅት አባቴ ስራ ቦታ ቢሮው ውስጥ እንዳለ እራሱን ስቶ ይወድቃል ..
አምቡላንስ ተጠርቶ ወደ ሆስፒታል ድንገተኛ ክፍል ይወስዱታል ..

ሆስፒታል ደርሶ ምርመራ ሲያደርግ የጉበት ካንሰር ይገኝበታል እንዲሁም ካንሰሩ ወደ ሌላ የሆድ ዕቃው አንጀቱ መዛመቱን ይደርሱበታል ..
°
በዚህ ካንሰር የሚያዙ አብዛኛው ተጠቂዎችን ለሞት የሚዳርጉ ሲሆን የአባቴም በሽታ አደገኛ ደረጃ ላይ የደረሰ አስጊ ነበር ..

°
ከሆስፒታል ስልክ ተደውሎ ዜናውን ስንሰማ እኔ እና እናቴ እጅጉን ደነገጥን ..
ተያይዘንም ወደ ሆስፒታል ጉዞ ጀመርን ..

በጉዞ ላይ ሳለሁ .. " በእስልምና ፍቅር መውደቁን እንዲሁም ሸሃዳ ለመቀበል በዝግጅት ላይ መሆኑን አይቶ አላህ የአባቴን ነፍስ እንደ ሙስሊም አድርጎ ይቀበላት ይሆን ? እልያኩ አስባለሁ
ለእናቴም ሸሃዳውን ይዞ ቢሆን ኖሮ ምን ነበረበት ብዬ በቁጭት ነገርኳት
°
ሆስፒታል ደረስን እናቴ ቀድማ ገባች እኔ መጠበቅ ጀመርኩ

ከቆይታ በኃላ እናቴ ተመልሳ በመምጣት አባትሽ ሊያይሽ ይፈልጋል አለችኝ ..
°
እናቴ ስለ ሸሃዳ ያነሳሁትን ለአባቴ ነግራው ኖሯል ..

እንደገባሁም በተዳከመ ድምፅ .. አሁንም ጊዜ አለኝ ሸሃዳ አሲዢኝ ብሎ ጠየቀኝ ..

በሆስፒታል አልጋው ላይ የአላህን አንድነት የሙሀመድ ( ሰ.ዐ.ወ ) መልእክተኝነት እንዲመሰክር አደረኩት ..
ሀሳብ ቀለል አለኝ ..
°
አባቴ በአንድ ጎኑ ተኝቶ ካንሰሩ በተወሰነ የአካል ክፍሉ እንዲሰበሰብ ይረዳው ዘንድ ሳምንታት ቆይቶ አደገኛውን ቀዶ ጥገና ለማድረግ ፕሮግራም ተያዘ ..
የቀዶ ጥገናው ቀን እስኪደርስ አጫጭር የቁርአን ሱራ አጠና .. ሱረቱል አል -ኢኽላስን በቃሉ ሀፍዞት በተደጋጋሚ ያነበንበዋል ..
°
የቀዶ ጥገናው ቀን ደረሰ በዚህ በሽታ የተጠቁ ብዙዎች የመዳን እድል እንደሌላቸው ስለተነገረኝ ብሰጋም እስልምናን በመቀበሉ ደስተኛ ሆኛለሁ ..
ወደ ቀዶ ጥገና ክፍል ወሰዱት ..

ከቆይታ በኃላ ዶክተሮች ብቅ አሉ ..
መርዶ ሳይሆን የምስራች ነበር የነገሩን ..
°
ስውነቱ ሲቀዱት እጅጉን በሚገርም ሁኔታ ካንሰሩ ከተሰራጨበት የስውነት ክፍሉ ጠፍቶ አንስተኛ በሆነች ቦታ ቁጭ ብሎ እንዳገኙት እና ሊያስረዱት የማይችሉት ተአምር እንደገጠማቸው በመግለፅ አባቴ ሙሉ በሙሉ ከካንሰር ነፃ መሆኑን ገለፁልኝ ..

አዎን የአላህ ተምአር ነው ..
አልሃምዱሊላህ ከበሽታ ነፃ የሆነውን ሙስሊሙን አባቴን ይዤ በደስታ ሆስፒታሉን ለቀን ወጣን።"

✿ «ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያካፍሉ»






09/02/2023

✍ታረቀን

ከመጠን በላይ ልቆ የኛ ወንጀላችን፣
ሙሀባ ቀንሶ ርዶ ፍቅራችን፣
ራሳችንን አንግሰን በሀራም ዙፋን፣
መሬቱም ራደ በሰራነው ወንጀል፣
ለንጹሀንም ተረፈ ህጻን ትልቅ ሳይል።
ሌላው የሚገርመው የሶርያ አገር፣
በእንቅርት ጆሮ ደግፍ ሆኖ ንብርብር፣
በነጮች ተንኮል በጦር ስትማገድ፣
ስቃዩአን አባሰው የመሬቱ መራድ።
አንዴ በኮረና አንዴ በጦርነት፣
ፈተናችን በዝቶ በዱንያ መሬት።
ምንኛ ከፍቶ ነው ምንኛ ብንወርድ፣
ወንጀላችን በዝቶ መሬታችን ሲርድ።
ህሊና ይኑረን አንዴ እናገናዝብ፣
ከወንጀል እንራቅ እንግዛ አደብ።
በተውባ እንመለስ በዱአ በስቲግፋር፣
በላአው ተነስቶ በሰላም እንድንኖር፣
በዲናችን እውቀት በፍቅር በልጽገን፣
በህብረት እንቁም በአብሮነት በኢማን!!

✍አንዋር ሱሴ
የካቲት 02/2015 ዓ.ል
ምሽት 01:39

03/02/2023

ሁሉም ሰው ይወዳት የነበረች ልጃገረድ
ታሪክ !
ነገር ግን ማን አገባት ??
አብረን እናንብበው ...
አንድ ወጣት ለአባቱ እጅግ በጣም ቆንጆና ልቡ
የተረታላት ፡ ልጃገረድ እንዳየና እርሷን ማግባት
እንደሚፈለግ ይነግረዋል ።
አባትም በጣም በመደሰትና በመጓጓት የታለች
ይህቺን ልጃገረድ አሁን አጭልሃለው ይለውና
ተያየዘው ወደ ልጅቷ ዘንድ ያመራሉ ፡ እዛም
እንደደረሱ አባትየው ያያትና : ልጄ ሆይ ! ለዚህች
ልጃገረድ አንተ አትሆናትም ለርሷ የሚያስፈልጋት
እንደ እኔ ጠንካራና ልምድ ያለው ሃላፊነት
ሊጣልበት የሚችል ሰው ነው ሊያገባት የሚገባው
ይለዋል ! ልጁ በአባቱ ሁኔታ በጣም ግራተጋብቶ
የለም አባቴ ይህችን ልጃገረድ እኔ ነኝ ማገባት
ያለበኝ ይለዋል ! ሳይግባቡ ይቀሩ እና ህግ
እንዲዳኛቸው ወደ ፖሊስ ጣብያ ያመራሉ ! እዛም
እንደደረሱ ሁኔታወን ለጣብያው አዛዥ ያስረዱታል !
የጣብያው አዛዥም ልጅቷ እንድት ቀርብና ከሁለት
አንዳቸውን እንደትመርጥ በማለት ጣብያ ድረስ
እንደትመጣ ያደርጋል ! አዛዡም ልጅቷን ሲያያት
በውበቷ እጀግ በጣም ይማረክና ፡ ይህች
ልጃገረድማ ለእናንተ አትገባም እርሷ ምትገባው
እንደኔ የሃገረን ሃላፊነት ለተረከብ ሰው ነው
የምትገባው ! እኔ ነኝ ማገባት ያለበኝ ይላቸውና
ሳይግባቡ ስለቀሩ ፡ እንዲዳኛቸው ጠቅላይ
ሚኒስቴሩ ጋር ያመራሉ !! ሚኒስቴሩም ልክ
እንዳያት ልቡ ይደነግጥላታና እንደዝች አይነቷን
ውብ ልጃገረድማ እንደኔ ሚንስቴር የሆነ ብቻ ነው
ሊያገባት የሚገባው ! ሰለዚህ እኔ ነኝ የማገባት
ይላቸውና ሳይግባቡ ስለቀሩ ነገሩ ፕሬዝደንቱ ቢሮ
ይደርሳል !! ፕሬዝደንቱም ልክ ሲመለከቷት
ልባቸው ውስጥ ትገባለች ! እርሳቸውም እኔ ነኝ
የማገባት እርሷ ምትገባው ለኔ ብቻ ነው !! ይሉና
ሁሉም ሲጨቃጨቁ ፡ ልጅቷ ሃሳብ እንዳላት
ትነግራቸዋለች ፦ ሁላቸውም ከርሷ ስር
እንዲሮጡና የደረሰባት ሰው እንደሚያገባት
ትነግራቸዋለች !! በዚህ ሃሳብ ሁሉም
ተስማምተውበት ሩጫ ላይ ሳሉ ! ሁሉም ተራ
በተራ እየወደቁ ጉድጓድ ውስጥ ይገባሉ ! ታድያ
ከገቡበት ጉድጓድ ላይ ቆማ ማን እንደሆንኩ
አወቃችሁኝ ? እኔ ዱንያ ነኝ !! እኔ ነኝ ሁሉም ሰው
ከስር ስሬ የሚሮጠውና እኔን ለማግኘት
የሚሽቀዳደመው !!ለኔ ሲሉ ከዲናቸው የሚዘናጉት
ሞኝነታቸው !! እኔንም ሳያገኙኝ አኺራቸውንም
ያጣሉ ትላለች !!
እኛስ?
ለአላህ ብለው ሼር ያርጉት

23/01/2023

✍የረመዳን ናፍቆት

የመዕሲያው ጉም መሬትን ሲያፍናት፣
አየሩ ሲበከል መጨካከን ሲያጥናት።
ራስ ወዳድነት ዙፋን ላይ ሲነግስ፣
ወሩ መጣሁ ይላል ጉሙን ሊገረስስ።
ልባችን ጨቅይቶ በወንጀል ክምር፣
በስሜት እየሄድን ቅንጣትም ሳናፍር።
ክፉኛ ጠፍንጎን የሰይጣን ሰንሰለት፣
ሃያእ ስነምግባር ወንድማማችነት፣
ከኛ ላይ እየሸሸ ወረሰን ስሜት።
በዲን እየቀለድን ሀራምን ተዳፍረን፣
ከወንጀል ሊያጠራን ደረሰ ረመዳን፣
ሰይጣን ሊጠፈነግ በራህመቱ ወር፣
በረካው ሊሰፍን በኢማን ክምር።
ናፍቆቱ ገደለን ቀኑ ርቆብን፣
ቀልባችን ጓጉታለች ተመኝታ አንተን፣
ረመዳን ሸህሩል መግፊራህ፣
በሊግና ረመዳን ያረቢ በእዝነትህ!!!!

✍አንዋር ሱሴ
ጥር15/2015 ዓ.ል
ጠዋት 2:15

18/01/2023

አልሀምዱሊላህ ‼

ቢ ሮ አችንን ተረክበናል ‼

በዛሬው እለት አድስ የተመረጡት የደብብ ወሎና የደሴ ከተማ እስልምና ጉዳይ ምክር ቤት በፊት ከነበሩቱ መጅሊሶች የቢሮ ርክክብ አደረጉ ።

በካባድ ውሽንፍር ፊት በፅናት መቆም ቀላል ነገር አይደለም ውሽንፍሩ መዝነብ ሲጀምር የመብረቅ ነጎድጓዱ ዙሪያውን ያጓራል

የደሴ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳይ ምክር ቤት እና የደቡብ ወሎ እስልምና ጉዳይ ምክር ቤት ከባዱን ውሽንፍር ፊት ለፊት ተጋፍጦ ያሉሏባልታ ወሬወች፣ ውሸቶችና ተራ የሆኑ የስም ማጥፋት ነጎድጓዶች ዙሪያውን ቢያጓሩበትም ሁሉንም በጣጥሶ በማለፍ ይሄው በዛሬው እለት የሙስሊሙ ማህበረሰብ ሀብት የሆነውን የደሴ ከተማንና የደቡብ ወሎን እስልምና ጉዳይ ምክርቤት ቢሮ ተረክቧል ።

ይህ ነገር እውን እንዳይሆን ሰሞኑን ላይስማሙ ተስማምተው ፣ሳይግባቡ ተግባብተው በፍፁም አንድ ይሆናሉ ብለህ የማታስባቸው እሳትና ጭድ የሆኑ ግለሰቦች አለ የተባለ ሀይላቸውን ተጠቅመው ብዙ ለፍተዋል፣ደክመዋል ፣አሲረዋል ፣በውሸት ስም አጥፍተዋል ጀሊሉ አይሳነውምና ልፋታቸውን፣ ሴራቸውንና ተንኮላቸውን የተበተነ አቧራ አደረገባቸው ።

ጥቂት ሁነው ሳለ ራሳቸውን እንደ ህዝብ ቆጥረው ህዝብ ተቆጥቷል ብለው ለማወናበድና ለማምታታት ብዙ ፃፋ፣ብዙ አወሩ ፣ብዙ ሞከሩ ግና አልተሳካም ።

በጣም የሚገርመው ምርጫው በማረ ሁኔታ መመረጡ ያላስደሰታቸው ና የነሱ የግል ፍላጎት ሳይሟላላቸው የቀሩ ግለሰቦች ሁሉንም ዞኖች አጠናቀን ደሴ ፣ደቡብ ወሎና ኮንቦልቻ ይቀረናል እና ለምርጫ ተዘጋጁ ብለው የዋህ አጫፈሪዎቻቸውን እና አላማችንን ያሳኩልናል ያሏቸውን ጮቤ ያስረገጡና ያስፈነደቁ ግለሰቦች የዛሬዋን ቀን ሲያዩ ምን ብለው ይሆን⁉

የዛሬው ቀን እውን እንድሆን ብዙ ተለፍቷል ፣ብዙ መስዋት ተከፍሏል ፣ብዙዎች ከሀገር ተባርዋል ፣በዙዎች ታስረዋል ፣ተገርፈዋል ።

ማህበረሰቡ ለህዝብ መገልገያ ይሆናል ብሎ ከሰራው ቢሮውስጥ ተቀምጠው ትዕዛዝ በመስጠት በጊዜው ከነበረው የህውሀት አ* ው* ሬ ስርአት ጋር በመተባበር በርካታ ግፎች በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ እንድስተናገዱ የአህባሽ አውሬዎች የአንበሳውን ድርሻ ተዋጥተዋል ።

ዛሬ ግን ይህ ቢሮ እንደትላንቱ ሴራ፣ ተንኮልና ለህብረተሰቡ የማይጠቅሙ ስበሰባወች አይካሄዱበትም ከዚህ ቢሮ ውስጥ ትላልቅ ሀሳቦች ይፈልቃሉ ፣ለኢስላምና ለሙስሊሞች የሚጠቅሙ ትዕዛዛቶች እና እቅዶች በሰፊው በስራ ላይ ይውላሉ።

በዛሬው እለት ቢሯችሁን የተረከባችሁት የደሴ ከተማና የደብብ ወሎ እስልምና ጉዳይ ምክር ቤት አሚሮቻችን ክፋትን ላሳዯችሁ ፍቅራችሁን ፣ጭካኔን ላሳዯችሁ እዝነታችሁን፣ ሴራና ተንኮል ሲሸርቡባችሁ የነበሩትን በጎነታችሁን፣ የተመቀኟችሁንና ይሄን ቦታ እንድያቲዙ ሲታገሏችሁ የነበሩትን ስራችሁን በማሳየት ፣በፍቅር፣በአንድነት ፣በመልካም ስነምግባርና በሀቅ ላይ ሁናችሁ ለኢስላምና ለሙስሊሙ ማህበረሰብ የተሻለን ስራ ሰርታችሁ እንደምታሳዩን በመተማመን አደራ እላችሗለሁ ።

የደሴ ከተማና የደቡብ ወሎ ሙስሊም ማህበረሰብ ይመሩኛል ብለህ ከፊት ለፊት ያስቀመጥካቸው ልጆችህ የትኛውንም መስዋት ከፍለው ሊያገለግሉህ ቆርጠው ተነስተዋልና ሲሳሳቱ እያረምክ ሲሰሩ እያመሰገንክ ከመሪዎችህ ጎን በመሆን አብሮነትህን ልታሳዯቸው ይገባል።

አሚሮቻችን መልካም የስራ ዘመን ይሁንላችሁ።

14/01/2023

ለአሏህ ብለን ሼር እናረገው

ለምን አትሰግድም ወንድሜ?
ለምን አትሰግጂም እህቴ? በዱንያ_ላይ፦
1• እስካልሰግድክ ድረስ ከእድሜህ ላይ በረካ ይነሳል ...
2• እስካልሰገድክ ድረሰ ከፊትህ ላይ ኑር
ይገፈፋል...
3• እስካልሰገድክ ድረስ ምትሰራው ስራ ሁሉ ተቀባይነት የለውም.
4• እስካልሰገድክ ድረስ ዱዓህ ተሰሚነት አያገኝም.
5• እሰካልሰገድክ ድረስ ሌሎች ሚያደርጉልህ ዱዓም አይጠቅምህም. ስትሞት፦
1• እስካለሰገድክ ድረስ እማትረባና የተዋረድክ ሆነህ ትሞታለህ.
2• እስካልሰገድክ ድረስ እንደተራብክ ትሞታለህ.
3• እሰካለሰገድክ ድረስ እንደተጠማህ ትሞታለህ. የባህርን ውሃ እንዳለ ብትጠጣ ጥምህን
አይቆትጥልህም. ቀብር_ውስጥ፦
1• እስካለሰገድክ ድረስ ጎንና ጎንህ እስኪተላልፈ ድረስ ቀብርህን አሏህ ያጠብብሃል.
2• እስካለሰገድክ ድረስ ቀብርህ ውስጥ እሳት ተቀጣጥሎብህ ነጋ ጠባ ትሰቃያለህ.
3• እስካለሰገድክ ድረስ በቀን አምስት ጊዜ ከእባብ ጋር ቀጠሮ ይኖርሃል ! የፈጅርን ሰላት ባለመስገድህ ሲያሰቃይህ ዙሁር ይደረሳል፤የዙሁርን ሰላት ባለመሰገድህ ሲያሰቃይህ አስር ይደርሳል ፤እንደዚህ እያለ ስቃይህ ይቀጥላል (አንድ ጊዜ ምትመታው እሰከ 70 ክንደ ያህለ መሬት ውስጥ ያሰምጠሃል).. የቂያማለት፦
1• እስካለሰገድክ ድረስ ወደ ጀሃነም እሳት . በፊትህ እየተጎተትክ ትወሰዳለህ .
2• እሰካልሰገድክ ድረስ አሏህ ፊት ቆመህ ስትተሳሰብ አሏህ (ሱ,ወ)
በቁጣ አይን ይመለከትህና ፊትህ ላይ ያለ ስጋ ይነሳለ.
3• እስካልሰገድክ ድረስ ከአሏህ (ሱ.ወ) ጋር የምትተሳሰበው ሂሳብ የከፋ ይሆነንና ወደ ጀሃነም እሳት እንደትወረወር ይደረጋል . ወንድሜ አሁንም አትሰግድም ?? እህቴ አሁንም አትሰግጂም ?? ያአሏህ ይህንን ፁሁፍ ላዘጋጀውም
ላነበብነውም ወንጀላችንን ማረን… በሂወት ያሉና የሌሉትንም ወንድምና እህቶቻችንንም ወንጀል ማርልን!!!
ለአሏህ ብለን #ሼር እናረገው አናውቅም በዚህች ሰበብ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ሂዳያ ያገኙና እኛም በጭንቁ የቂያማ ቀን ይጠቅመን ይሆናል፡፡
ቢያንስ #ለ15 ሰው ሸር እናድርግ።

12/01/2023
🔴ገራሚ እና አስተማሪ ታሪክ🔴ኢብን አሳኪር ታሪኩ ላይ ዘግቦታል➡️አህመድ ቢን አማር እንዲህ ይላል:-ከአንድ አስተማሪ ጋር ሆነን ጀናዛ ለመሸኘት ወጣን ከአስተማሪው ጋር ተማሪዎቹም ነበሩ በመን...
11/01/2023

🔴ገራሚ እና አስተማሪ ታሪክ🔴

ኢብን አሳኪር ታሪኩ ላይ ዘግቦታል

➡️አህመድ ቢን አማር እንዲህ ይላል:-
ከአንድ አስተማሪ ጋር ሆነን ጀናዛ ለመሸኘት ወጣን ከአስተማሪው ጋር ተማሪዎቹም ነበሩ
በመንገድ ላይ ውሾች ተሰባስበው ሲጫወቱ ና ሲላፉ ተመለከተ
ከዛም ወደ ተማሪዎቹ ዞር ብሎ እነዚህ ውሾችን ተመልከቱ በመሀከላቸው ያለው ስርአት እንዴት ደስ ይላል አላቸው

ከዛም ጀናዛውን ቀብረን ስንመለስ መንገድ ላይ በክት ተጥሎ ውሻዎቹ በዙሪያው ተሰብስበዋል።አሁን ግን አንዱ ውሻ ሌላኛውን ያባርራል።ሁሉም ለራሱ ለመብላት ሌላውን ያርቃል
አስተማሪው ወደ ተማሪዎቹ ዞረና እንዲህ አላቸው
"ዱንያ በመሀከላቹ ከሌለች ወንድማማች ትሆናላችሁ።በመሀከላቹ ዱንያ ካለች ልክ ውሾቹ በበክቱ ላይ እንደተጣሉት ትጣላላቹህ"

📕ሙኽተሰር ታሪኽ ዲሚሽቅ ሊብኒ አሳኪር 1/378

08/01/2023

( وَقَالَ يَا أَسَفَىٰ عَلَىٰ يُوسُفَ وَابْيَضَّتْ عَيْنَاهُ مِنَ الْحُزْنِ فَهُوَ كَظِيمٌ )

《 በዩሱፍ ላይ ዋ ሐዘኔ ! አሉ 》

ሌሎች ልጆቻቸው ሁሉም ከጎናቸው አሉ ዩሱፍ ሲቀር …

~ አንዳንዱን ክፍተት አንድ ሰው እንጅ አይሞላውም

~ እሱ እንጅ ሌላ አይተካውም •

﴿وَأَخَاف أَنْ يَأْكُلَهُ الذِّئْب وَأَنْتُمْ عَنْهُ غَافِلُونَ﴾

《 ከርሱ የዘነጋችሁ ስትሆኑ ተኩላ ይበላዋል ብዬ እፈራለሁ》 አሏቸው ።

~ ተኩላ የሚለውን ቃል ከአባትዬው ሰሙ ለብልሃታቸው ተጠቀሙበት…

~ ገዳይ ቀስትን ጠቋሚ አትሁን ተርቢያ የምታደርገውን ተውጂህ ስታደርግ •

( اذهبوا فتحسسوا من يوسف وأخيه)...

ሂዱና የየሱፍንና የወንድሙን ( ወሬ ) ተከታተሉ አፈላልጉ

ዩሱፍን ልጅ እያሉ ከአመታት በፊት ነው ያጧቸው ፍለጋ ግን ቀጥለዋል… !!

~ የይሆናል ፍልስፍና ካወሩህ

~ በአሏህ ላይ ያለህን መተማመን ንገራቸው •

"فأرسل معنا أخانا
" ወንድማችንን ከኛ ጋር ላከው ካልሆነ ስፍር ተከልክለናል… "

~ ጥቅም ያገኙ ስለነበር " ወንድማችን " አሉ

"إن ابنك سرق" ...

~ ጉዳያቸው ሲጠናቀቅ " ልጅህ " አሉ ።

~ ብዙዎች ዘንድ የንግግር ዘያቸው ጥቅም ሲኖርና ሳይኖር ይለያያል !
‏{فَأسرَّها يُوسُفُ فِي نَفْسِه}

" ዩሱፍም ንግግራቸውን በነፍሱ ውስጥ ደበቃት… "

~ አንዳንዴ የቅርብ ሰዎቼ ከምትላቸው የሚያቆስል ንግግር ትሰማለህ…

~ እንዳልሰማህ ሆነህ እለፈው
ለመልስ አትቸኩል

በዝምታ ውስጥ ጥልቅ የሆነ መልካም ነገር አለ ።

🌺🌺🌺🌺

06/01/2023

✍ባለጸጋው

ስለ ኒዕማህ ላውራ በሰጠኸኝ አንደበት፣
ተወርቶ ባይዘለቅ የጸጋህ ልኬት፣
እስቲ ልተንፍሰው ምስጋናዬን አቅርቤ፣
በኢባዳ በተውባ አንተኑ ቀርቤ።
አቅሜ ሲከዳኝ ሰዎች ሲንቁኝ፣
ህመሙ እየጠና በሽታ ቢከበኝ፣
ድካሙ በዝቶብኝ ቤት ቢያውለኝ።
ቀርበህ ጠገንከኝ ደርሰህ ከጎኔ፣
ዛሬ ላይ ጠቀመኝ አንተኑ ማመኔ፣
ዛሬ የረዳኝ ሰው ነገ ይሰለቻል፣
አንተኑ የያዘ ከቶ መቼ ያዝናል።
ሂክማህ ረቂቅ ነው ቃላት የማይገልጹት፣
መጠኑ አይታወቅ የጸጋህ በረከት፣
ምስጋና ይድረስህ ሰማይን ሰንጥቆ፣
ወንጀል እና ጥፋት ከልባችን ፍቆ።
ደካሞች ብንሆንም የሌለን ብርታት፣
ባለጸጋው ካለን የለም መተኛት።
አመታት ፈጅተው በዱንያ ቢታሰስ፣
የዋልከውን ውለታ ማንም ችሎ አይመልስ።
ድንቅ ነው ችሎታህ የለውም እንከን፣
ምስጋና ይገባህ ያረቢ ያረህማን!!!!

✍አንዋር ሱሴ
ታህሳስ28/2015ዓ.ል
ረፋድ 05:59

30/12/2022

✍ጁሙአ

ከቀናት መካከል አላህ የባረከው፣
በአምልኮ ኢባዳ ቀኑ የሚደምቀው።
ልብ የሚበራበት ተጊጦ በኢባዳ፣
መስጅድ ለመሄድ ነፍስ ስትሰናዳ።
በተባረከው ዕለት በየመል ጁሙአህ፣
አላህ ለመገዛት ጸድተህ ሸዋር ወስደህ፣
ንጹህ ልብስ ለብሰህ ሽቶውንም ነስንሰህ፣
መስጅዱን ረግጠህ ቁርአኑን ስታነሳ፣
ልብህ ሲረካ አላህን ስታወሳ።
ጆሮህም አዳምጦ የኢማሙን ኹጥባ፣
ነፍስህ ስትደሰት ከወንጀሏ ታጥባ።
አንድነቱ ገኖ በጋራ ስንሰግድ፣
ሙሉ ጤና ሰጥቶን ጁሙአ ስንሄድ።
አልሃምዱሊላህ እንበል እድል ስለሰጠን፣
ያላገኘው ሞልቷል በየዙሪያችን፣
ጥበቡ ረቂቅ ነው እጅጉ የተዋበ፣
በዲነል ኢስላም ስሩ የጠነከረ፣
ዛሬ ጁሙአ ሰግደን፣
ከአጅሩ ተቋድሰን፣
ዛሬ እናብጅ የኛ ነጋችንን!!

✍አንዋር ሱሴ
ታህሳስ21/2015ዓ.ል
ረፋድ04:37

Address

Dessi

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኑረል ኢስላም ሚዲያ Nuralislam Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ኑረል ኢስላም ሚዲያ Nuralislam Media:

Share