Wollo Media House WMH

Wollo Media House WMH This page aims to discuss the fate of Wallo, give logical, rationale and timely response to the ene

ደሴና ኮሪደር ልማትእኔ እሥሚገባኝ ከወሎ ባህል_አምባ_ሮቢት ቧንቧ ውኃ ያለው መንገድ ሥራ የተጀመረው የኮሪደር ልማት አጀንዳ ሳይመጣ ነው ምናልባት ትንሽ የማሥፋት ሥራ ተጨምሯል::  ነገር ግ...
05/04/2025

ደሴና ኮሪደር ልማት

እኔ እሥሚገባኝ ከወሎ ባህል_አምባ_ሮቢት ቧንቧ ውኃ ያለው መንገድ ሥራ የተጀመረው የኮሪደር ልማት አጀንዳ ሳይመጣ ነው ምናልባት ትንሽ የማሥፋት ሥራ ተጨምሯል:: ነገር ግን ድሮ የተሠሩ ሥራዎችን ሁሉ እየለጠፋ የኮሪደር ልማት እያሉ ህዝብን ማደናገር ተገቢ አይመሥለኝም:: ድልድይ ተብላ በፌሥቡክ የምትቀርበው ነገርም ሮቢት ገበያን ከሥላሴ ጋር የምታገናኝ ሚጢጢየ ድልድይ ነች:: ቧተ ክህነቱንና ገበያውን ብቻ ነው የምታገናኘው:: የተሠራችውን ለቤተ ክርሥቲያኗ ብቻ ነው:: ለቤተ ክርሥቲያኗ መሠረራቱ ችግር የለውም:: ነገር ግን የኮሪደር ልማቱ ፍሬ አድርጎ ማቅረብ የደሴን ህዝብ ከመናቅ የመነጨ ነው::

ባጭሩ ሁለት ነገሯችን ማለት እፈልጋለሁ::

1] በሚድያ ጋጋታ ደሴ በኮሪደር ልማቱ የለለ እንደተለወጠች እያሥመሠልን ህዝብ ባናደናግር:: ደሴ እንደሆነች እርጅና እንደተጫጫናት ናት:: ያለማች ከተማን የኮሪደር ልማቱ ተጠቃሚ እንደሆነችና እንደለማች አድርጎ አለመሥራትን በሚድያ መሸፈን ካለማልማት የበለጠ በደል ነው:;

2] ኮሪደር ልማትን በተመለከተ እንደ ጅግጅጋና ጅማ ከመሳሰሉ ከተሞች
ልምድ ብንወሥድ:: እነዚህን ከተሞች ማየታችን ልምድ ማገኘት ብቻ ሳይሆን ደሴ ላይ የኮሪደረር ልማት አለመጀመሩን እንረዳ ነበር:: ይህ ደግሞ በአልሠራንም መንፈስ ተግተን እንድንሰራ ይረዳናል::

  ................ Vs  🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥የወሎ ህዝብ በሳሙኤል ዘሚካል መንፈስ ሿሿ ለመስራት ስምሪት የተሰጠው ሳሙኤል ሞላልኝ የወሎን ገበሬ ከነቤተሰቡ አፈናቅሎ 300ሄክታር ...
06/05/2024

................ Vs

🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
የወሎ ህዝብ በሳሙኤል ዘሚካል መንፈስ ሿሿ ለመስራት ስምሪት የተሰጠው ሳሙኤል ሞላልኝ የወሎን ገበሬ ከነቤተሰቡ አፈናቅሎ 300ሄክታር የእርሻ መሬትን ከተማ ካልገነባሁ በሚል አደገኛ የሴራ ፕሮጀክቱን ፀንሶ ተነስቷል።
ለዘመናት የመልማትና የመሰረት ልማት ግንባታዋ ተዳፍኖባት የቆየችው ደሴ ከተማን የመንገድ መክፈትና የቢሮ ማስዋብ ስራዎችን በመስራት የህዝቡን አይንና ጆሮ ከያዘ በኋላ ህዝብ በዚያ እንዲራኮትና እንዲያምነው አድርጎ ደሴን የሚያክል ሌላ አንድ ግዙፍ ከተማ የመመስረት ዕቅድን ይዞ ተነስቷል።
የወሎ ህዝብ እሴቱን ባህሉን ክብሩን ጠብቆ ለዘመናት መቆየቱና በሃይማኖት አቧድነው የሃይማኖት አክራሪነትን ፈጥረው ሊያለየዩት የተሳናቸው ድኩማኖች የህዝቡን መሰረታዊ የባህል ትስስር ቦንድ ለመበጠስ የወሎን መንፈስ ከስም መጠሪያው ጀምሮ መምታት በሚል ፕሮጀክታቸው በርካታ አርሶ አደሮችን (ባለመሬቶችን ፊዳ አድርጎ ወሎን ከነ ስሙ ለመሰዋት ለእርድ ቀርበዋል)።
ከአድማ ብተና እስከ ቦሩ ሆስፒታል የሚመሰረተው ( wollo infographic city)በሚስጥር የተያዘ ካቢኔው ራሱ ሚስጥሩን የማያውቀው በውጭ ባለሃብቶች ግዙፍ ገንዘብ አፍሳሽነት የሚተገበር ከተማ ነው። ይህ ከተማ የወሎ ባህልና እሴት እንዲሁም ስያሜ ነቀለ ተከላ ስራን በእጅጉ ያግዛሉ ተብሎ ተስፋ የተጣለበት ነው።
መስራትን የሚችሉበት ኮንስፖይራቶች ገና የተወለደ ህፃን ልጅ የመመልመልና በሚፈልጉት መልክና ልክ አድርገው የማሳደግና ለሚሽናቸው ማዘጋጀት የሚችሉ ስውሮች ሳሙኤል ሞላልኝን ለዚህ ፕሮጀክታቸው አስፈፃሚነት መልምለው እኛንም አስተኝተው ከፍተኛ የሆነ የገፅታ ግንባታ ስራን ሲሰሩለትና ለዚህም ተባባሪ ሲያደርጉን ቆይተዋል። ሳሚ በሳሙኤል ዘሚካኤል መንፈስ የወሎን ህዝብ በማደንዘዝ እጅግ ቅብ የሆኑ የልማት ስራዎችን በማንቦግቦግ ሿሿ ለመስራት ጫፍ ላይ መድረሱን ደርሰንበታል።
ወያኔን እንጦሮጦስ የከተተው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጉዳይ (ለገበሬዎች ግድ የሌለው)የኢኮኖሚ መሰረታችን ግብርና ሁኖ ሳለ የህንፃ ግንባታዎችን ማስፋፋትና የኦሮሚያን አርሶ አደር በገፍ ማፈናቀል መሆኑን ልብ ይሏል።
ይሄኛው የወሎ ፕሮጀክት ደግሞ ወሎን ለማጥፋት በራሳችን ሪሶርስ በመጠቀም የወሎን ገበሬ አፈናቅሎ በመበተን ያለምንም ወጭ በራሳችን ሃብትና ንብረት እንዲሁም ማጎሳቆል የሚፈፀም ነው።
ለዚህ ፕሮጀክታቸው 300ሄክታር መሬት ለ800ሺ ነዋሩዎች ግንባታ ለማድረግ ታቅዷል። ከተማ አስተዳደሩም ሆነ ሳሚ ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ አይሰጡም። ሳሚ በተልዕኮ የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ደግሞ በእንኩሮነት ለመረጃው ባላቸው ርቀት (ምንም ግንዛቤ የሌላቸው በመሆኑ)አያውቁትም የሚረዱት የላይኛውን የፖለቲካ ጨዎታ ቅብ ነው።
የ2007 ዓም CSA የህዝብና ቤት ቆጠራ መረጃ እንኳን አይተን ብንገምት አይደለም ቤት የሌለው የደሴ ህዝብ ራሱ 800ሺ የሚደርስ አይደለም።
ስለዚህ የሚገነቡ ቤቶች ለማንና እንዴት ነው? ለምንስ ይህ ሁሉ አርሶ አደር ይፈናቀላል ብትሉት ሳሚ መልስ የለውም።
ውድ የወሎ ህዝብ ሆይ ጉዳዩን በትኩረት ተከታተለው እምነትህንም አንስተህ የተለመደ መነፀርህን ግጠም የወሎ ህዝብ ላይ ጥላቻ ያላቸው ጥገቶች አስተኝተውህ የልባቸውን እንዲሰሩ መፍቀድ አይገባም።

በመምህርት ትዝታ ገረመው ላይ እየደረሰ ያለው ዘመቻ የሚያሳየው በአሁኑ ወቅት የዩኒቨርሲቲ መምህራን ለምነው እንኳን መብላት እንደማይችሉ ነው፡፡ አንድ ሃቅ መታወቅ ያለበት መምህሯ ወሎ ዪኒቨር...
01/04/2024

በመምህርት ትዝታ ገረመው ላይ እየደረሰ ያለው ዘመቻ የሚያሳየው በአሁኑ ወቅት የዩኒቨርሲቲ መምህራን ለምነው እንኳን መብላት እንደማይችሉ ነው፡፡ አንድ ሃቅ መታወቅ ያለበት መምህሯ ወሎ ዪኒቨርሲቲን አልከሰሰችም አልወቀሰችም፡፡ ወሎ ዩኒቨርሲቲ እስራ ነበር ነው ያለችው፡፡ ስለዚህ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ባለስልጣናት ሳትጠሩ አቤት! ወይ! አትበሉ፡፡ ጉዳዩ ወሎ ዩኒቨርሲቲን አይመለከትም፡፡

ይልቁንም ይህ ጉዳይ የሚያሳየው የኢትዮጵያ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ያሉበትን የኢኮኖሚ ደረጃ ነው፡፡ እህታችን አውጥታ ተናገረችው እንጅ እውንታው ሁሉም መምህር ልመና የሚያስወጣ ድህነት ውስጥ ነው ያለው፡፡

ብዙ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ከልመና በማይተነነሱ ጥቃቅን የንግድ፣ የድለላና የጉልበት ስራ ላይ ተሰማርተው ነው ያሉት፡፡ እኔ ታክሲ ረዳት ሆነው ተጨማሪ ገቢ ለማገኘት የሚሰሩ የዩኒቨርሲቲ መምህራንን አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ ጉዳዩ የመምህርት ትዝታ ብቻ ሳይሆን የሁሉም የኒቨርሲቲ መምህራን ጉዳይ ነው፡፡

ጉዳይ Wollo University ወሎ ዩኒቨርሲቲ ጉዳይም አይደለም፡፡ ወሎ ዩኒቨርሲቲ አርፈህ ተቀመጥ ማንም አልጠራህ!
ጉዳዩ የትምህርት ሚኒስተር Ministry of Education እና ሀገሪቱን የሚመራው መንግስት የሲቪል ሰርቪስ ነው፡፡ የትምህርት ሚኒስተር በጉዳዩ እሰብበት! በራሃብ የሚንገላታ የዩኒቨርሲቲ መምህር እንደት ስለሚያስተምረው ትምህርት ጥራት እንደሚያስብ እንግድህ ያየ የሰማ ይፍረድ!

08/02/2024

What Abiy Ahmed Ali did today will bring some improvement to the security of the country. Redwan is a person capable of leading the security sector.

11/03/2023

Wollo Media House በአድስ መልኩ አድማሷን አስፍታ አቅሟን አጎልብታ ተዓማኝነት ያለችውን መረጃዎች ልታካፍላችሁ ዳግም ከች ብላለች።

ፔጃችንን ላይክና share በማድረግ አስተዋውቁል።
ወሎ ሚድያ ሀውስ
የድምፅ አልባዎች ድምፅ

03/07/2022

ሞታችን ቀጣይ.... ለቅሷችን ግን አንድ ሰሞን ብቻ ሆኖ እንደትስ ከተጋረጠብን የጥፋት ድግስ እንድናለን!?!?

20/06/2022

ወሎ ላይ የሚሰራ ግልፅ ሴራ አለ። በወለጋና በወሎ ወሎየውን የሚጨደጭፉ አካላት የሚሰሩት ተነባው ና ተመካክረው ነው። በተለይ ሰሞኑን ኦሮምያ ዞን በፋኖ የተረሸኑ ወገኖችን የሚያሳይ ቪድዮ መውጣቱን ተከትሎ ይሄን ዜና ለማደብዘዝ በሚመስል መልኩ ወለጋ ላይ 200 በላይ ዜጎች በግፍ መጨፍጨፋቸው የሚነግረን ነገር አለ።

አርጡማም በአፍቃሪ ሚኒሊካዊያን የተገደልን እኛው ወለጋም በሸኔና በኦህድድ የተገደልን እኛው !!እንደው ለዘላለም ጥያቄ የሆነብኝ ነገር ወሎ ምን በድሎ ይሆን እንድህ መኖሪያም መቀበሪያም ያጣው...
20/06/2022

አርጡማም በአፍቃሪ ሚኒሊካዊያን የተገደልን እኛው ወለጋም በሸኔና በኦህድድ የተገደልን እኛው !!
እንደው ለዘላለም ጥያቄ የሆነብኝ ነገር ወሎ ምን በድሎ ይሆን እንድህ መኖሪያም መቀበሪያም ያጣው ??
always Wollo ??

 #የአድሱ ዞን ጉዳይለግዜው ምዕራብ ወሎ (ሊባል የታሰበው ምስራቅ ግዮን ነው) የተባለው ከደቡብ ወሎ ዞን ተቆርሶ ይመሰረታል የተባለው አድሱ ዞንን በተመለከተ የተደበቁ ነገሮችን ማጥራትና መጋ...
15/04/2022

#የአድሱ ዞን ጉዳይ

ለግዜው ምዕራብ ወሎ (ሊባል የታሰበው ምስራቅ ግዮን ነው) የተባለው ከደቡብ ወሎ ዞን ተቆርሶ ይመሰረታል የተባለው አድሱ ዞንን በተመለከተ የተደበቁ ነገሮችን ማጥራትና መጋፈጥ ያስፈልጋል።

የተወሰኑ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ወረዳዎች ተወላጆች ተመካክረን አድሱ ዞን ስለሚያስከትለው መዘዝ ለመንግስትና ለህዝብ ማስገንዘብ ያስፈልጋል ብለን አምነናል። በዚሁ መሰረት ሀሳባችንና ስጋታችን እንደሚከተለው አቅርበናል።

አድሱ ዞን ለመመሰረት ሀሳቡ መንሸራሸር ከጀመረ ቢያንስ 10 አመት አልፎታል። ጅምሩ ላይ ደቡብ ወሎ ዞን ስለሰፋ የአስተዳደርና የልማት ጥያቄዎችን በቀላሉ ለመፍታት እንድቻል ደቡብ ወሎ ዞን ለሁለት ይከፈል ከሚል ቅንነት የመነጨ ሀሳብ ነበር። ከለውጡ በህዋላ ግን ይህ ሀሳብ በተወሰኑ የቦረና ሊህቃን እና በክልሉ የሚሰሩ የጎጃም ባስልጣናት ተጠልፎ አለማውን 100% በሚባል መልኩ ስቷል። ይህን ዞን እነሱ በፈለጉት መልኩ ለማስፈፅ የአንድ ወይም የሁለት ወረዳዎች ሊህቃን በአካል እየተገኙ፣ በማህበራዊ ሚድያው ግሩፕ እየፈጠሩ በህቡዕ ማሴር ከጀመሩ ቆይተዋል። የነዚህ ሊህቃን ግቦች የሚከተሉት ናቸው። አንኛ የአድሱ ዞን መቀመጫን መንደራቸው መውሰድና አድሱን ዞን እንደፈለጉ መበዝበርና ማዘዝ ነው። ሁለትም አድሱ ዞን ሲፈጠር የምትገኝን ስልጣን መለቃቀም። ሶስተኛ አድስ የሚፈጠረውን ዞን በጎጃም ስነ ልቦና ቀርፆ ከወሎ እንድፈታ ማድረግ ቀስ በቀስ ደግሞ ወሎየነትን ማክሰም ወሎን ማጥፋት ነው። ይህ ቡድን መካነሰላም፣ ሳይንትና ወግዲን ሙሉ በሙሉ ወስዶ ሌሎች ወረዳዎችን ደግሞ ለሱ በሚመቸው መልኩ እያፈረሰ አድስ ወረዳ እየፈጠረ የቋመጠላትን ዞን መፍጠር ነው። ለምሳሌ እንድፈርሱና እንድቆረሱ ከተፈረዳዎች ወረዳዎች መካከል ለጋንቦ፣ መቅደላ፣ ተንታና ከላላ ይገኙበታል (ከታች ያለውን የቡድኑን ካርታ ተመልከቱ)።
በመሰረቱ በዚህ ሀገሪቱ ማጥ ውስጥ በገባችበት ወቅት አድስ ዞን (ያውም ለአንድ ወረዳ ሊህቃንን ብቻ ሲባል) መመስረት እጅግ አደገኛ አካሄድ ነው ብለን እናምናለን። ይህ ጉዳይ ደቡብ ወሎ ዞንን ብቻ ሳይሆን አማራ ክልልን ጭምር ወደለየለት ትርምስ የሚወስድ ነው። የቦረና ሊህቃን ያልገባቸው ነገር እነሱ ጥቅማቸውን ለማስከበር በህቡዕ ከ5 አመት በላይ ሲመክሩ የሌላው ወረዳ ተወላጅ ቁጭ ብሎ ይጠብቀናል ብለው ማሰባቸው ነው። መቅደላ አንባ ዩኒቨርሲቲን በጉልበትና ባለስልጣናትን በማማለልና በማስፈራራት ለመውሰድ ሲሞክሩ የተፈጠረውን ነገር የረሱት ይመስላሉ። ለማንኛውም የቦረና ሊህቃን በህቡዕ በሚመክሩት መልኩ አድሱን ዞን ለመመስረት መሞከር በአካባቢው የለየለት ደም መፋሰስ እንድመጣ መፍቀድ ነው። ይህን ጉዳይ የሚመለከታቸው ወረዳዎች፣ የደቡብ ወሎ ዞን፣ አማራ ክልል እና የፌደራል መንግስቱ በደንብ ሊያስቡበት በአንክሮ ሊከታተሉት ይገባል። ስለዚህ የመጀርያው ነገር በዚህ ሰዓት አድስ ዞን አያስፈልግም። ህዝቡ ያለው የልማት ጥያቄ እንጅ አድስ ዞን ይመስረትልን የሚል ጥያቄ አይደለም።

ሁለተኛ የዞኑ መመስረት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ የዞኑ መቀመጫ መወሰን ያለበት በሚመለከታቸው በሁሉም ወረዳዎች ህዝብ ምርጫ (referendum) እንጅ ከ10 የማይበልጡ የአንድ ወረዳ ሊህቃን በፈለጉት ወይም በወሰኑት አይደለም። በመሰረቱ የአድሱ ዞን መቀመጫ ካልሆነች የተባለችው መካነሰላም ለአድሱ ዞን መቀጫነት ቀርቶ ለምርጫ እንኳ መታጨት የለባትም። ምክናየቱም:
1ኛ ጅኦግራፊያዊ አቀማመጧ ከምዕራብ ወረዳዎች ጠርዝ ላይ ነው። ስለዚህ ለየትኛውም ወረዳ አመች አይደለችም።
2ኛ) ከተማዋ ከፍተኛ የውሃ ችግር አለባት። እንኳን ዞን ከተማ ሁና ተጨማሪ ሰው ተጨምሮባት አሁን ኗሪዎቿ ውሃ የሚያገኙት በ15 ቀን አንድ ቀን ነው። ከዚህም በተጨማሪ በተፈጥሮ ሃብትና በቆዳ ስፋት ወረዳዋን ብዙ ወረዳዎች ይበልጧታል። ስለዚህ ከተማዋ ያለምንም ውድድርና ምርጫ ዋና ከተማ ልትሆን ቀርቶ ምርጫ ውስጥም መግባት የለባትም። እነሱ የሚሉት ድሮም አውራጃ ስለነበረች ብሎ ከተማዋ የተሻለ መሰረተ ልማት ስላላት ወዘተ የሚል ነው። ይህ ደግሞ እንደት እንደማይሰራ እናስረዳ። አውራጃነትን በተመለከተ ወረዒሉ፣ ተንታም አውራጃ ነበሩ። ስለዚህ አውራጃ በሚለው አመንክዮ እነዚህ ከተሞችም የአድሱ ዞን መቀመጫ መሆን አለባቸው ማለት ነው። ከተማዋ የለማች ነው የሚለው አመንክዮ ዞንነትን መሸከም የሚችሉ ብዙ ከተሞች አሉ። በተጫማሪም ዞን ከሆኑ በህዋላ መልማት ይችላሉ።

ስለዚህ አድሱ ዞን ምስረታ በጥቂት ሊህቃን ተጠልፎ የብጥብጥ አጀንዳ ሊሆን ስለሆነ አራቱም የመንግስት እርከኖች ማለትም የሚመለከታቸው ወረዳዎች፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ አማራ ክልልና የፌደራሉ መንግስት ደም ከመፋሰሱ በፊት ነገሩን ትኩረት ሰጥተው ሊያዩትና መፍትሄ ሊሰጡት ይገባል።

አገር በእብዶች ስብስብ ስትመራ ትርፉ አሁን የደረስንበት መድረስ ነው !! #ደደቦች
24/03/2022

አገር በእብዶች ስብስብ ስትመራ ትርፉ አሁን የደረስንበት መድረስ ነው !!
#ደደቦች

27/01/2022

በእርግጥም አፋሮች ስለተወረሩ ከመዋጋት ውጭ አማራጭ የላቸውም።
ነገር ግን መንግስት ህዝቡን ከወራሪ መታደግ ካልቻለ በህይወት ስለመኖሩ ምን ማረጋገጫ አለን!?!?
በአፋሮች መወረር መንግስትን ትታችሁ ህወሃትን የምትወቅሱ "ብጹእ አማንያን" ትገርሙኛላችሁ!!!

የYasin Mohamed Ali ን ወንድም የደበደቡትም ሆነ ቤቱን የዘረፉት የቀረርቶና የፎቶ እንድሁም የድል አጥቢያ አርበኞች እንደሆኑ ጥርጥር የለንም፡፡ የጎጃሙ እስስት የባለሃብትና የነዘመነ...
11/12/2021

የYasin Mohamed Ali ን ወንድም የደበደቡትም ሆነ ቤቱን የዘረፉት የቀረርቶና የፎቶ እንድሁም የድል አጥቢያ አርበኞች እንደሆኑ ጥርጥር የለንም፡፡ የጎጃሙ እስስት የባለሃብትና የነዘመነ ቡድን ከዚህም በላይ ያደርጋል ፡፡ ለምን ??

1-ወሎ ላይ ድሞግራፊክ Change ለማምጣትና በወሬ ብቻ ደም ሰጠልህ በሚል የጎጃሙ ቡድን ደሴና ኮቻ ላይ ለመውሰድ ያሰበውን የቤት መስሪያ ቦታ ሊያስቆመው የሚችለው ማን ሊሆን እንደሚችል ስለሚያውቅ ቀድሞ የማሸማቀቅ ስራ ለመስራት

2- የወሎ ህብረት አመራሮችን በማሸማቀቅ ተስፋ እንድቆርጡ ለማድረግ

3-ህዝቡ ላይ ሌላ ፍርሃትን በመልቀቅ ቀና ብሎ እንዳያይ ለማድረግና የተጀመረውን የጎጃም የበላይነት ለማስቀጠል

እና መሰል ምክንያቶች ይኖሯቸዋል፡፡ ነገር ግን አንድ የሳቱት ነገር ከዚህ በኋላ #ወሎ ላይ ገራገርነት ላይመለስ ማክተሙንና ፍርሃት ደግሞ ያልተፈጠረበት ህዝብ መሆኑን ነው፡፡
የወሎን መሬቱን በጀቱንና ሃብቱን መመኘት ከምኞት የዘለለ እንደማይሆን እናረጋግጥላችኋለን !!

#ሁላችንም ወሎ ህብረት ነን
#ሁላችንም ያሲኖ ነን
ገብስነት

Address

Dessie

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wollo Media House WMH posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Wollo Media House WMH:

Share