Amhara press

Amhara press Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amhara press, Media/News Company, Wollo, Dessie.

በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ ሳይንት ወረዳ በሚገኝ ቤተክርስቲያን ላይ በደረሰ ጥቃት አገልጋዮችና ምዕመናን ተገደሉ 😥በአማራ ክልል በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በቀጠለው ግጭት...
08/03/2026

በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ ሳይንት ወረዳ በሚገኝ ቤተክርስቲያን ላይ በደረሰ ጥቃት አገልጋዮችና ምዕመናን ተገደሉ 😥

በአማራ ክልል በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በቀጠለው ግጭት፣ በአንድ ቤተክርስቲያን ላይ በተሰነዘረ ጥቃት በርካታ ዜጎች ተገደሉ።

በክልሉ በደቡብ ወሎ ዞን፣ ሳይንት ወረዳ በተተኮሰ ከባድ መሣሪያ አምስት የቤተክርስቲያኗ አገልጋዮች መገደላቸው ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪም ከ26 በላይ በሚሆኑ የቤተክርስቲያኗ ምዕመናን ላይ ከቀላል እስከ ከባድ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል።

ጥቃቱ የደረሰው በወረዳው በሚገኘው የነገሥት አትሮንሰ ማርያም ገዳም ውስጥ፣ የዕለቱ ቅዳሴ ከተጠናቀቀ ከደቂቃዎች በኋላ የቤተክርስቲያኑ አባቶች እና ምዕመናን ወደ ደጀ ሰላም እያመሩ በነበሩበት ወቅት መሆኑ ተነግሯል። በተተኮሰው በዚህ ከባድ መሳሪያም የቀድሞ የገዳሙ አስተዳዳሪ፣ ሦስት ዲያቆናት እና አንድ አቃቤ መገደላቸው ታውቋል።

ለጥቃቱ እስካሁን ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም። ይሁን እንጂ፣ የቤተክርስቲያኑ ምዕመናን ከባድ መሳሪያውን የተኮሱት የመንግሥት ኃይሎች ሊሆኑ እንደሚችሉ ያላቸውን ጥርጣሬ ገልጸዋል። በአንጻሩ፣ የመንግሥት ምንጮች ጥቃቱን "ጽንፈኛ" ሲሉ በሚጠሯቸው የፋኖ ታጣቂዎች እንደተፈጸመ አድርገው ከሰዋል ይሁን እንጂ በጉዳዩ ላይ እስካሁን ድረስ የአካባቢው የመንግሥት አመራሮች የሰጡት ምንም ዓይነት ይፋዊ መግለጫ የለም።

ይህ ጥቃት የተፈጸመው ትናንት ቅዳሜ፣ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሆን፣ ገዳሙ በአካባቢው ከሚገኙ ዕድሜ ጠገብ ታሪካዊ ገዳማት መካከል አንዱ መሆኑ ይታወቃል።

22/10/2025

የሙፍቲን የደግነትና የሰብአዊነት ሁለንተናዊ ሌጋሲ ለማስቀጠል አራት ፕሮጀክቶች በሂደት ላይ ናቸው፦

1- የሀይማኖት ትምህሮት ማዕከል

ሀይሌ ጋርመንት አካባቢ ያለውን 8000 ካሬ ሜትር ያህል ቦታቸውን ሙፍቲ ለመስጊድና ለዲን ትምለህርት ማዕከልነት "ወቅፍ" ስላደረጉ የ500 ሚሊየን ብር ግኖባታ ለማሳረፍ ዲዛየኑ ተሠርቶ አልቋል። በአላህ ፈቃድ ወደፈንዶ ሬይዚንግና ግንባታ እንቅሶቃሴ በቅርቡ ይገባል።

2- የቁርአን ተፍሲር

ሙሉውን ቁርአን የፈሰሩበት ሥራ ኤዲቲንግና ሌሎች ሥራዎቹ የተጠናቀቀ ሲሆን በቅርቡ ለህዝብ ይለቀቃል።

በተጨማሪም ይኸንኑ ሥራቸውን በመጽሀፍ መልክ የማዘጋጀቱ ተግባር በሂደት ላይ ነው።

3- የህይወት ታሪክ ዝግጅት

የህይወት ታሪካቸውን በአማርኛና በዐረብኛ ለማዘጋጀት የታቀደ ሲሆን የአማርኛው ቅጅ ሥራ በመገባደድ ላይ በመሆኑ በሳምንታት ጊዜ ውስጥ ወደ ህትመት ይገባል። ኢንሻአላሀ።

የአረብኛው ቅጅም እርሱን ተከትሎ ይታተማል።

4- ሀገር አቀፍ የምስጋና ቀን

የሙፍቲን ክብርና የዘመናት አገልግሎት የሚመጥን ሀገር አቀፍ የምስጋና ቀን ከረመዳን በፊት ተዘጋጅቶ ሙፍቲን ለማመስገን ታቅዶ እንቅስቃሴ የተጀመረ ሲሆን የርሳቸው ማረፍ በዝግጅት ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ቢኖረውም ከዳር ለማድረስ በአዘጋጆቹ በኩል ቁርጥ ውሳኔ ያለ በመሆኑ ዕወን ይሆን ዘንድ ጥረቶች የሚቀጥሉ ይሆናል።

ሙፍቲ ለነዚህ ፕሮጀክቶች ይሁንታ (ኢጃዛ) የሰጡ ሲሆን የቁርአን ተፍሲራቸው ጋር የተያያዙ ሥራዎች መጠናቀቃቸውን ከማረፋቸው አሥር ቀናት ቀደም ብሎ አይተው ተደስተዋል።

እነዚህ ፕሮጀክቶች በታቀደላቸው ጊዜ ዕውን ይሆኑ ዘንድ የሁሉም ወገን ትብብር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ፕሮጀክቶችን በመምራት ላይ ያለው ኮሚቴ በጽኑ ያምናል።

https://t.me/hassentaju

ኦርቶዶክስ ነኝ...አቶ ሳዊሮስ ከሚያሳልመኝ ሀጂ ሙፍቲ ዱዓ ቢያደርጉልኝ እመርጣለሁ!🙏 እናንተስ?
07/10/2025

ኦርቶዶክስ ነኝ...
አቶ ሳዊሮስ ከሚያሳልመኝ ሀጂ ሙፍቲ ዱዓ ቢያደርጉልኝ እመርጣለሁ!🙏 እናንተስ?

አማራ ክልል ኮሽ ሲል፦ስልጤው……
07/10/2025

አማራ ክልል ኮሽ ሲል፦

ስልጤው……

06/10/2025
05/10/2025

ትናንት በመካነ ሰላም ደረሰ የተባለውን ሃይማኖት ተኮር ግጭት እንዴት እኔደተዘገበ ስቃኝ ነበር። ብልፅግና ሰሞኑ በአማራ ክልል ከደረሰበት ሽንፈት ማግስት የመጣች መሆኑንም ከግምት አስገብቼ ነገሩን ታጣቂዎች ፈፀሙት ለማለት አይቻልም። ይልቁንስ ብልፅግና እጅ እንዳለበት ይሸታል።

በትግራይ ጦርነትም ወቅት ብልፅግና አቅዶና አስልቶ የሃይማኖት ተቋማትን በማጥቃት ይታወቅ ነበር።

26/06/2025

የኢትዮጵያ አሁናዊ ገፅታ

22/04/2025

Re

Address

Wollo
Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share