Daily News ET

Daily News ET daily news on Ethiopia.

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ 11 ወራት ከውጭ ንግድ  7 .2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መገኘቱ ተገለፀ እየተጠናቀቀ ባለው የበጀት ዓመት የመጀመሪያ 11 ወራት ኢትዮጲያ  7.2 ቢሊዮን ዶላር ማግ...
11/06/2025

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ 11 ወራት ከውጭ ንግድ 7 .2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መገኘቱ ተገለፀ

እየተጠናቀቀ ባለው የበጀት ዓመት የመጀመሪያ 11 ወራት ኢትዮጲያ 7.2 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ አስታወቁ፡፡

ሚኒስትሩ ይሄን ያስታወቁት የፌደራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ውይይት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እየተደረገበት ባለበት ወቅት ነው፡፡

ከባለፈው አመት ተመሳሳይ በጀት አመት ከተገኘው የ3. 3 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ጋር ሲነፀፃር የ118.2 በመቶ እድገት እንዳሳየ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጲያ ከውጭ ንግድ ገቢ የተገኘ እጅግ ከፍተኛ ውጤት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ለዚህ ውጤት መገኘት የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያው ጉልህ ሚና መጫወቱን የገን ዘብ ሚኒስትሩ አያይዘው አንስተዋል፡፡

የጦርነት ሥጋት ያጠላበት የኢትዮጵያና የኤርትራ ሰሞነኛ ውጥረትኩዌት፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ፣ ግሪክ፣ ኒካራጓ፣ የመንና ሱዳንን ጨምሮ በርካታ አገሮች የእንኳን አደረሳችሁ የደስታ መግለጫ ...
30/05/2025

የጦርነት ሥጋት ያጠላበት የኢትዮጵያና የኤርትራ ሰሞነኛ ውጥረት

ኩዌት፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ፣ ግሪክ፣ ኒካራጓ፣ የመንና ሱዳንን ጨምሮ በርካታ አገሮች የእንኳን አደረሳችሁ የደስታ መግለጫ መልዕክት መላካቸው እንደሌላው ጊዜ የመገናኛ ብዙኃንን ቀልብ አልገዛም፡፡ ሌላው ቀርቶ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርም ሆነ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ማርኮ ሩቢዮ የደስታ መልዕክት መላካቸውም ቢሆን ብዙም ትኩረት አላገኘም ነበር፡፡ ዘንድሮ 34 ዓመቱን የደፈነው ቅዳሜ ግንቦት 16 ቀን 2017 ዓ.ም. የተከበረው የኤርትራ የነፃነት በዓል ከዚህ ሁሉ ይልቅ በሌላ መንገድ የሚታወስ ሆኖ ነው ያለፈው፡፡ ከአገሪቱ የነፃነት በዓል እኩል በፕሬዚዳንታዊ ሥልጣን የቆዩት የዕድሜም የሥልጣንም ባለፀጋው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ፣ በዓሉ በአስመራ በደማቁ ሲከበር ያስተላለፉት መልዕክት ነው የአየር ሞገዱን ከሁሉ በላይ ተቆጣጥሮት የነበረው፡፡

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ የእንኳን አደረሳችሁ መግለጫ ኤርትራ ደማቅ ታሪክና ባህል ያላት ብቻ ሳይሆን፣ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ሰላምና ብልፅግና እንዲሰፍን እንደ አሜሪካ የምትፈልግ አገር መሆኗን ዕውቅና እንደሚሰጠው ያትታል፡፡ ይሁን እንጂ የኢሳያስ አፈወርቂ የበዓሉ መልዕክት በብዙ ታዛቢዎች ዘንድ በአፍሪካ ቀንድ አዲስ ጦርነት የማስጀመሪያ ፊሽካ ተደርጎ ነው የተወሰደው፡፡ ኢሳያስ አገራቸው ኤርትራ ከጎረቤት ኢትዮጵያ ጋር ለምታደርገውና ለአይቀሬው ጦርነት የ ‹‹ክተት ሠራዊት፣ ምታ ነጋሪት›› አዋጅ እያወጁ ይሆን ወይ የሚለውን በርካቶች በየራሳቸው የተለያዩ ግምቶች ሲሰጡት ሰንብተዋል፡፡ የፕሬዚዳንቱ ንግግር ለምን ትኩረት ሳበ ከሚለው ጀምሮ፣ የተላለፉ መልዕክቶች ለምን ዋና የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኑ የሚሉ ጉዳዮችን በተመለከተ ንግግሩን በጥንቃቄ መመርመር የሚጋብዝ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ሕመም ከጀመረ ከ80 ዓመታት ወይም ከሦስት ትውልድ ያላነሰ ዕድሜ መቆጠሩን የጠቀሱት ኢሳያስ እንደ አሜሪካና ሶቪየት ኅብረት ባሉ አገሮች ጣልቃ ገብነትና የተዛባ ፖሊሲ የተነሳ፣ በኢትዮጵያ ለአገረ መንግሥት ምሥረታ አጋጥመው የነበሩ ዕድሎች ሲመክኑ መቆየታቸውን ያወሳሉ፡፡ በሒደት የተፈጠረው የብሔር ፌዴራላዊ ሥርዓት የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሕመም እንዳጠናውና ብዙ ቀውስም እንዳስከተለ ነው የተናገሩት፡፡

ኢሳያስ ይህን ብለው ሲያበቁም፣ ‹‹የዛሬ ሰባት ዓመት በኢትዮጵያ ተፈጥሮ የነበረው የፖለቲካ ለውጥ ወይም ሪፎርም በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን፣ በኤርትራና በሌሎች ጎረቤት አገሮች ሕዝቦች ዘንድ ጭምር በጎ ተስፋ የፈጠረ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ ይሁን እንጂ ይህን ያልወደዱ የውጭ ኃይሎች ያሳደሩት ጫና እና የእነሱን ጫናም ለመቀበል የብልፅግና መንግሥት በመፍቀዱ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ከባድ ቀውስ ያስከተለ ጦርነትና ግጭት እንዲከሰት አድርጓል፤›› ብለዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ አገራቸው ለመደገፍ እንደሞከረች ገልጸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የኤርትራ ሕዝብና መንግሥት በኢትዮጵያ የመጣው ለውጥ እንዳይደናቀፍ ድጋፍ ማድረጋቸውን እንደማይፀፀቱበት የጠቀሱት አቶ ኢሳያስ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ከባድ ጦርነት ኤርትራ ጦሯን ማስገባቷንና የኢትዮጵያን መንግሥት መደገፏንም በዚሁ መንገድ ሊታይ የሚገባው መሆኑን ነው ያስረዱት፡፡

‹‹ጥቂት ጊዜ እንደቆየ የኢትዮጵያን ሪፎርም እንመራለን የሚሉት ብልፅግናዎች ማንነታቸው በገሀድ መታየት ጀመረ፡፡ የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነትን ተከትሎ በሌላ ማንነት ሲከሰቱ ባለፉት ጥቂት ዓመታት እናያቸው ጀመር፡፡ ዛሬ ኃላፊነት የጎደለው አጀንዳና አቋም እያራመዱም ይገኛሉ፡፡ የውኃ አጀንዳን በመቀስቀስ አንድ ጊዜ የዓባይ ውኃ ሌላ ጊዜ ደግሞ ቀይ ባህር፣ እንዲሁም የባህር በር ይላሉ፡፡ ሲፈልጉ የኦሮሞ ሕዝብን የማይወክለውን የኦሮሙማ ርዕዮተ ዓለምን ያራግባሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የኩሻዊያንና የሴማዊያንን ጠላትነት አጀንዳ ያቀጣጥላሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የአፋርን መሬት ለሚፈልጉት የብሔር ግጭት መቀስቀሻ አጀንዳነት ሊያውሉት ይቃጣቸዋል፤›› በማለት ነው ጠንከር ባሉ ቃላት የኢትዮጵያ መንግሥትን የተቹት፡፡

የኢትዮጵያን መንግሥት በጠጣር ቃላት ሲተቹ የተደመጡት ኢሳያስ አፈወርቂ በማሳረጊያቸው፣ የመከላከያ ኃይል ጠንካራ ዝግጅትን አስፈላጊነት በትኩረት አውስተዋል፡፡ ኤርትራ በመከላከያ ብቻ ሳይሆን በሁለንተናዊ አገራዊ ጥንካሬዎች ራሷን እንደምታዘጋጅ ያብራሩ ሲሆን፣ አገራቸው ለሚመጣው ነገር ሁሉ ምላሽ መስጠት የሚያስችል ሁለንተናዊ ጥንካሬ በመፍጠር ላይ ተግታ እየሠራች ስለመሆኑ አስምረውበታል፡፡ ይህ የኤርትራ ነፃነት በዓል ላይ የተነገረው የኢሳያስ መልዕክት ደግሞ ለአይቀሬው ጦርነት አገራቸው እየተሰናዳች ስለመሆኑ አመላካች ነው ተብሎ በሰፊው መነጋገሪያ ሆኗል፡፡

ተቃዋሚ ፖለቲከኛው ጃዋር መሐመድን ጨምሮ የመንግሥት ባለሥልጣኑ ብርሃኑ ሌንጂሶ (ዶ/ር)፣ የሚዲያ ሰዎችና በርካታ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች ተዋንያን የኢሳያስ አፈወርቂን ንግግር በተለይም ‹‹ኦሮሙማ›› ብለው ስለጠሩት ርዕዮተ ዓለም ስህተት በሰፊው ሲተቹ ሰንብተዋል፡፡ ከዚህ በመለስ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል (ኦፌኮ) ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ፣ የኤርትራውን ፕሬዚዳንት ንግግር ጠብ ጫሪና ተንኳሽ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

‹‹አቶ ኢሳያስ የኢትዮጵያን ጠንካራ አገር ሆኖ መኖር አይፈልጉም፡፡ ኢሳያስ ኦሮሙማን እንደ ርዕዮተ ዓለም ቆጥረው መወንጀላቸው ስህተት ነው፡፡ ኦሮሙማ የኦሮሞ ሕዝብ እሴት፣ ባህልና ማንነት እንጂ ርዕዮተ ዓለም አይደለም፡፡ ብልፅግና የኢትዮጵያ መንግሥት ነው እንጂ ከኦሮሞ ሕዝብ ብቻ የወጣ የፖለቲካ ሥርዓት አይደለም፡፡ ኢሳያስ ከዚህ ባለፈም የሴማዊያንንና የኩሻዊያንን ግጭት ማንሳታቸው በኢትዮጵያ ሕዝቦች መካከል የተቧደነ ጦርነት ለመለኮስ የተደረገ ጥረት ነው፤›› በማለት ነው አቶ ሙላቱ ያስረዱት፡፡

ከተለያየ አቅጣጫ ለኢሳያስ ንግግር የሚሰጡ መልሶች በቀጠሉበት በዚህ ወቅት ለፕሬዚዳንቱ በእንግሊዘኛ ግልጽ ደብዳቤ ብለው ሰፊ መጣጥፍ ያስነበቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው የፖለቲካ ሳይንስ መምህር መብራቱ ከለቻ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ጠለቅ ያሉ ሐሳቦችን አስፍረዋል፡፡ ‹‹ፕሬዘዳንት ኢሳያስ ስለውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነት ያወራሉ፡፡ ይሁን እንጂ የእሳቸው ጦር ኢትዮጵያ ጦርነት ውስጥ ገብቶ መሳተፉና ከፍተኛ ጭፍጨፋና ዕልቂት መፈጸሙ ጣልቃ ገብነት ካልተባለ ሌላ የውጭ ጣልቃ ገብነት ከየት ሊመጣ ነው?›› በማለት መብራቱ (ዶ/ር) ይሞግታሉ፡፡ ኢሳያስ የሌለ የእጅ አዙር ጣልቃ ገብነት ትርክት በመሳል በጎረቤት ኢትዮጵያ ጦር አስገብተው የፈጸሙትን ወንጀል ለመሸፋፈን መሞከራቸው፣ እጅግ አደገኛና ጨካኝ አቋም መሆኑን ነው ጸሐፊው የጠቀሱት፡፡

‹‹ኢትዮጵያ በብሔር ፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ገብታለች ብለው ኢሳያስ መናገራቸው ተገቢነት የለውም፡፡ የብሔር ፖለቲካ ቀውስ ፈጥሮ ከሆነም የኢትዮጵያ ብዝኃነትን በአግባቡ የማስተናገድ ችግር ከገጠማት እሱን ማስተካከል ለእኛው ለኢትዮጵያውያን የሚተው የቤት ሥራ እንጂ፣ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ እርስዎን ሊያስጨንቅና ከንፈር ሊያስመጥጥ የሚገባው ጉዳይ መሆን የለበትም፡፡ ከብሔር ፖለቲካ በተጨማሪም ስለኦሮሙማ ርዕዮተ ዓለም፣ እንዲሁም ስለኩሽና ሴም ግጭት ማንሳትዎም ቢሆን የመነጨው እርስዎ ብዝኃነትን ለሚያስተናግድ ፖለቲካ ያለዎትን ጥላቻ እንጂ ሌላ አይደለም፤›› በማለት ነው የፖለቲካ መምህሩ ኢሳያስን የሚተች ሐሳባቸውን ያንፀባረቁት፡፡

በኢትዮጵያ ወገን ከተሠለፉ መንግሥትን ከሚቃወሙና ከሚደግፉ መካከል በርካታ ልሂቃን የኢሳያስን ንግግር በመተቸት በተጠመዱበት በዚህ ወቅት ግን፣ የኤርትራው መሪ መልዕክት ጥቂት የማይባሉ ሰዎችን በተቃራኒው ጮቤ ሲያስረግጣቸው ታይቷል፡፡ ኤርትራም ሆነ መሪዋ ኢሳያስ የተከተሉት አቋም ትክክል ስለሆነ ጥፋተኛውና ሊወገዝ የሚገባው፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ነው የሚሉ ድምፆችም ሲስተጋቡ ነበር፡፡

አንዳንድ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችና ማኅበራዊ አንቂ ነን የሚሉ ወገኖች የኤርትራን 34ኛ የነፃነት በዓል አከባበር ደማቅነት አጉልተው የሚያሳዩ ቪዲዮዎች፣ ፎቶዎችና መረጃዎች በማጋራት ሥራ ተጠምደው ሰንብተዋል፡፡ የአስመራ ከተማው የምሽት ርችት ተኩስ ምሥል ከሁሉ በላይ ከፍተኛ ትኩረት አግኝቶ ነበር፡፡ ለመሬት ቀረብ ብለው የሚበሩ ጄቶች ድምፆች ሲያጓሩ የሚደመጥበትና በአስመራ ስታዲየም የተስተናገደው የባህር ኃይል፣ የምድር ኃይልና የሌሎች ወታደራዊ ክፍሎች ሠልፎች ምሥሎችም ቢሆኑ በሰፊው ሲጋሩ ታይተዋል፡፡ የነፃነት በዓሉ ላይ የቀረበው ሙዚቃና ድግስ ሁሉ አንድ በአንድ በሰፊው ሲሠራጭ ነው የሰነበተው፡፡

የኤርትራ ደጋፊ ነን የሚሉ ወገኖች፣ ‹‹ኤርትራ ሁሉም ወጣት ተሰዶ ባዶዋን የቀረች አገር ሆናለች፡፡ ወጣቱ የግዳጅ ውትድርና ጠልቶ ከአገር በመሰደዱ የቀሩ ዜጎች አዛውንቶችና አረጋዊያን ብቻ ናቸው፡፡ አገሪቱ ዛሬ የሚዋጋ ኃይል የሌላት ደካማ ናት፤›› ብለው የሚናገሩና ኤርትራን ሊያጠቁ የሚሞክሩ ሁሉ ይህን የመሰለ ጦርና ኃይል አደርጅተናል የሚሉ መልዕክቶች የሚያስተላልፉ መረጃዎችን በሰፊው በማሠራጨት ተጠምደው ነው የሰነበቱት፡፡

ከዚህ ጎን ለጎን ደግሞ ‹‹ጽምዶ›› እየተባለ ስለሚጠራውና የኤርትራና የሕወሓት አዲስ የፖለቲካ ጋብቻን መግለጫ ሆኖ በማገልገል ላይ ስለሚገኘው የትብብር ፖለቲካ በሰፊው ሲያራግቡ የሰነበቱም ነበሩ፡፡ ሻዕቢያና ሕወሓት አሁን ዳግም የፖለቲካ መቀራረብና ትብብር መጀመራቸውን የሚናገሩት እነዚሁ ወገኖች የትግራይና የኤርትራ አዋሳኝ ድንበሮች መከፈታቸውንና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትና መቀራረብ እንደገና መጀመሩን እየተናገሩ ነው፡፡ እነዚህ ወገኖች ከዚህ በተጨማሪም በሻዕቢያና በአማራ ፋኖ ኃይሎች መካከል ግንኙነትና ወዳጅነት መጠናከሩን በማከል ጭምር፣ የኢትዮጵያ መንግሥት በሰሜን ኢትዮጵያ አቅጣጫ ጦርነት ቢከፍት በተባበረ ክንድ ለመመከት የተዘጋጀ ጥምር ግንባር/ቅንጅት ስለመፈጠሩ ለማስገንዘብ ሲጣጣሩ ነው የታዩት፡፡

ስለዚሁ ጉዳይ የተጠየቁት ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የፖለቲካ ተንታኝ በበኩላቸው፣ ሻዕቢያን ከሕወሓት ሊያቀራርብ የሚችል አጋጣሚ እንደተፈጠረው ሁሉ ሻዕቢያን ከፋኖ ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያመች አጋጣሚ መኖሩን በመጥቀስ ነገር ግን የፋኖ ኃይሎች ከሕወሓት ጋር በጋራ ተባብረው ይሠራሉ የሚለው ግምት አስቸጋሪ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ‹‹ከሰሞኑ ፋኖዎች የራሳቸውን የመደራደሪያ ነው ያሉትን የጋራ አቋም በጽሑፍ ይፋ አድርገዋል፡፡ ከዚህ አቋም መረዳት እንደቻልኩት ደግሞ የፋኖ ጥያቄ ከሕወሓትም ሆነ ከሻዕቢያ ጉዳይ ጋር የማይገናኝና በጋራ ለመሥራትም እንቅፋት መሆኑን ነው፤›› በማለት ገልጸዋል፡፡

የኤርትራው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ በዚህ ደረጃ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ጠንካራ ትችትና ውግዘት ለማሰማት የፈለጉት ምን አስበው፣ እንዲሁም ምን ተማምነው ነው የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ተንታኙ የራሳቸውን ግምት አስቀምጠዋል፡፡

‹‹ሻዕቢያ አሁን የሠለጠነና የውጊያ ልምድ ያለው ጦር ባለቤት የሆነውን የሕወሓትን ኃይል አጋርነት አግኝቶ ቀርቶ፣ በትግራይ ጦርነት ወቅትም ቢሆን የእኔ ዕርዳታ ባይኖር የኢትዮጵያ መንግሥት ተሸንፎ ነበር የሚል ግምገማ አለው፡፡ ይህ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናትም ሆነ የጦር አመራሮች ጭምር የሻዕቢያ ውለታን ሲያወድሱ ከመታየታቸው ጋር ተዳምሮ ጠንካራ እምነት ሆኗል፡፡ ሻዕቢያ ከዚህ በተጨማሪም የሱዳን፣ የግብፅና የሳዑዲ ዓረቢያ ድጋፍ እንደሚኖረውም በደንብ ያሠላ ይመስላል፡፡ የኢትዮጵያ በጦርነት መዳከምና ዓለም አቀፍ መቀነስ በቅርብ ጊዜ በባህር በር ጥያቄ ጉዳይ ከጎረቤት አገሮች ጋር ከገባችበት ውጥረት ጋር ተዳምሮ፣ ሻዕቢያ በቂ ዝግጅት አለኝ የሚል በራስ መተማመን እንዲፈጠርበት የሚጋብዝ ነው፡፡

ይሁን እንጂ ኢትዮጵያም ብትሆን ወደ ጦርነት ከተገባ ደጋፊ አጋሮች እንደሚኖሯት መገመት ቀላል ነው፡፡ ሱዳን ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ናት፡፡ የሳዑዲ ዓረቢያና የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ ተቃራኒ ጎራ ለይቶ በሱዳን ጦርነት መሠለፍ ግጭቱ ከሁለት ዓመታት በላይ ሳይበርድ እንዲቀጥል ምክንያት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በኢትዮጵያም ቢሆን አንዴ ጦርነቱ ከፈነዳ ጎራ ለይቶ የሚያዋጋ ደጋፊ ወገን ማግኘት አይቸግርም፤›› በማለት ነው የኤርትራና የኢትዮጵያ ሰሞነኛ ውጥረት ወደ ከፋ ቀውስ ሊያመራ የሚችልበት ዕድል የተዘጋ አለመሆኑን ያብራሩት፡፡

ኤርትራ ነፃና ሉዓላዊ አገር ሆና ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ ባለፉት 34 ዓመታት፣ በዙሪያዋ ካሉ በርካታ አገሮች ጋር ስትጋጭና ስትዋጋ ነው የኖረችው፡፡ በቀይ ባህር ባሉት በሀኒሽ ደሴቶች ይገባኛል ከየመን ጋር እ.ኤ.አ. በ1995 ተዋግታለች፡፡ ከዚያ ወዲህ ደግሞ እ.ኤ.አ. ከ1996 እስከ 1998 የሱዳን ተቃዋሚዎችን ደግፋ የሱዳን መንግሥትን ስትዋጋ ቆይታለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ1998 እስከ 2000 ደግሞ ከኢትዮጵያ ጋር በባድመ ድንበር ይገባኛል የተነሳ ከባድ ጦርነት ስታካሂድ ቆይታለች፡፡ እ.ኤ.አ. በ2008 ዓመት በራስ ዱሜራ ድንበር ይገባኛል የተነሳ ከጂቡቲ ጋር ወደ ግጭት ገብታለች፡፡ ከእነዚህ ሁሉ በተጨማሪም በሶማሊያ የእርስ በእርስ ግጭት ውስጥ ጣልቃ በመግባት ከኢትዮጵያ ጋር የእጅ አዙር ግጭት ውስጥ ገብታ መቆየቷ፣ እንዲሁም በሶማሊያ የሚንቀሳቀሱ ቀጣናዊ ሥጋት የደቀኑ አሸባሪ ኃይሎችን ስትደግፍ መኖሯም በታሪክ መዛግብት ሰፍሮ ይገኛል፡፡

የፕሬዚዳንት ኢሳያስ መንግሥት በተከተለው ቀጣናዊ ግጭትና ውጥረትን በሚያጭሩ ፖሊሲዎች የተነሳ፣ ኤርትራ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ማዕቀብ ስትማቅቅ እንደኖረች ይወሳል፡፡ ከአሥር ዓመታት በላይ የዘለቀውን በኤርትራ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ ለማስነሳት ኢትዮጵያ በቅርብ ዓመታት ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ በይፋ እስከ መጠየቅ የደረሰ ዕርምጃ ወስዳለች፡፡ ይህ ደግሞ የሆነው አዲሱ የዓብይ አህመድ (ዶ/ር) መንግሥት ከአስመራ መንግሥት ጋር ዕርቅ በማውረዱ እንደሆነ ይታወሳል፡፡ የኤርትራና የኢትዮጵያ መንግሥታት ከ20 ዓመት በኋላ ዳግም መታረቅ በወቅቱ ቢደግፍም ወዲያው ወደ መቃወም የገባው የሕወሓት ቡድንም የሁለቱ አገሮች መንግሥታት መቀራረብ ትግራይን ለመውጋት ሆን ተብሎ የተጀመረ ጥረት ነው የሚል ተቃውሞ ወደ ማቅረብ መግባቱ ይታወሳል፡፡

ይህ ደግሞ በሕወሓትና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል የተፈጠረውን አለመተማመን እያሰፋው ሄዶ ከባድ ውጥረት መፍጠሩ በሒደትም ከባድ ጦርነት ማስከተሉ አይዘነጋም፡፡ በዚህ ጦርነትም የኤርትራ ኃይል ከኢትዮጵያ ጎን የተሠለፈ ሲሆን፣ ሕወሓት በጦርነቱ ወቅትም ሆነ ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ የኤርትራ፣ የአማራና የኢትዮጵያ መንግሥት ኃይሎችን የጠላትነት ስም ሲሰጣቸው መቆየቱም አይዘነጋም፡፡ አሁን ግን ይህ የኃይል አሠላለፍ የተለወጠ ሲሆን፣ ሻዕቢያ ከሕወሓትና ከአማራ ፋኖ ኃይሎች ጋር ተባብሮ ጦርነት ሊከፍት ነው የሚል ስሞታ ተደጋግሞ ይደመጣል፡፡

የትግራይ ፖለቲካን በቅርበት የሚከታተሉት ጌታቸው አሰፋ (ፕሮፌሰር) ዩኤምዲ በተባለው በግል የማኅበራዊ ገጽ ሚዲያቸው ላይ ስለኤርትራና ስለኢትዮጵያ የጦርነት ዳግም መፈጠር ሥጋት የሕዝብ አስተያየት መጠይቅ ለተከታታዮቻቸው አቅርበው እንደነበር፣ ቅዳሜ ለንባብ በበቃው የሪፖርተር እንግሊዘኛ ጋዜጣ ላይ ሐሳባቸውን አጋርተዋል፡፡

እሳቸው ቃለ መጠይቁን እስከሰጡበት ቀን ድረስ ወደ 521 ሰዎች ድምፃቸውን መስጠታቸውን የገለጹት ጌታቸው (ፕሮፌሰር)፣ ከእነዚህ መላሾች መካከልም 57 በመቶዎቹ በኤርትራና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ጦርነት ቢፈጠር ትግራይ መሳተፍ የለባትም የሚል ስሜት ማንፀባረቃቸውን ጠቁመዋል፡፡ ትግራይ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጎን መቆም አለባት ያሉት 27 በመቶ መሆናቸውን የተናገሩት ፕሮፌሰሩ፣ ቀሪዎቹ አነስተኛ የ11 በመቶ አኃዝ ያላቸው አስተያየት ሰጪዎች ግን ከኤርትራ ጎን ተሠልፎ የኢትዮጵያ መንግሥትን መውጋት ይሻላል ማለታቸውን በመለስተኛ የሕዝብ አስተያየት መገምገሚያ ሙከራቸው ለማወቅ እንደቻሉ አብራርተዋል፡፡

‹‹እኔ ጦርነት አላበረታታም፣ ጦርነትም መቼም የትም ቢሆን አልደግፍም፡፡ ነገር ግን የጦርነቱ መምጣት አይቀሬ ከሆነ ግን በግሌ የትግራይ ሕዝብ ከኢትዮጵያውያን ጎን ሆኖ ሻዕቢያን ቢያስታግስ እመርጣለሁ፡፡ ሻዕቢያን ማስታገሱ ለትግራይም፣ ለኢትዮጵያም ሆነ ለኤርትራና ለቀጣናው ጭምር ትልቅ እፎይታ የሚሰጥ ነው፤›› በማለት ነበር ጌታቸው (ፕሮፌሰር) ለሪፖርተር ሐሳባቸውን ያጋሩት፡፡

ኤርትራና ኢትዮጵያ አሁን ወደ አይቀሬው ጦርነት እያዘገሙ ነው የሚሉ ስለሁኔታው የሠጉ አንዳንድ ወገኖች በበኩላቸው፣ ይህ ጦርነት የሚካሄድበት ዋና የመስተናገጃ ቦታ ሊሆን የሚችለው ደግሞ ከጦርነት ገና ያላገገመው ሰሜን ኢትዮጵያ መሆኑ ብዙ እንደሚያሳስባቸው ይገልጻሉ፡፡ የኤርትራና የኢትዮጵያ ወደ ጦርነት መግባት እንደ ከዚህ ቀደሞቹ ጦርነቶች ሊሆን እንደማይችል የሚጠቅሱት እነዚህ ወገኖች፣ ወደ ጦርነቱ አንዴ ከተገባ ለሁለቱም ኃይሎች የመጨረሻቸው ሊሆን እንደሚችል ያሰምሩበታል፡፡ ሱዳን ውስጥ ያልበረደ ትኩስ ጦርነት እያለ ምሥራቅ አፍሪካ ቀንድ በብቁ ውጥረቶች በሚገኝበትና ከቅርብም ከሩቅም የራሳቸውን ፍላጎት አንግበው የተሠለፉ ኃይሎች በበዙበት በዚህ ወቅት፣ ሁለቱ አገሮች ሌላ ዙር ጦርነት ማስተናገድ ፈጽሞ እንደማይችሉ በመጠቆም ሁለቱም አካላት ሆኑ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የሰላም አማራጭ መፍትሔዎችን እንዲያማትሩ ነው የሚያሳስቡት፡፡

Ethiopian Reporter - ሪፖርተር
በዮናስ አማረ
May 28, 2025

የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት እና ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊና የጽህፈት ቤት ኃላፊ ከስልጣናቸው መነሳታቸውን ተገለፀ "የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባዶ መሬት ይዘወርበታል" ተብሎ የሚነገር...
04/05/2025

የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት እና ልማት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊና የጽህፈት ቤት ኃላፊ ከስልጣናቸው መነሳታቸውን ተገለፀ

"የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባዶ መሬት ይዘወርበታል" ተብሎ የሚነገርለት ይህ ተቋም፤ የተለያዩ ኃላፊዎች ለአጭር ጊዜ የሚቆዩበት እንደሆነ ይታወቃል።

አሁን ደግሞ የቢሮ ኃላፊው አቶ ሲሳይ ጌታቸውና የጽህፈት ቤት ኃላፊው አቶ ካሊድ ነስረዲን ከትናንት ሚያዚያ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከኃላፊነታቸው እንደተነሱ ተገልጿል።

በከንቲባ አዳነች አቤቤ ደብዳቤ ከስራቸው የተነሱት ሁለቱ ኃላፊዎች ቀጣይ ማረፊያ የት እንደሆነ አልታወቀም።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ያሉ ባዶ ቦታዎች፤ ለሊዝ ሽያጭ፣ ለምደባ፣ ለኢንቨስተር የሚሰጡት በዚህ ቢሮ ሲሆን የከተማ አስተዳደሩ ካሉት ወሳኝ እና ቁልፍ ተቋማት ውስጥ አንዱ ነው።

የባህር ላይ ውንብድና በጣና ሀይቅ ላይ! በ07/08/2017 ዓም ጣና ነሽ ተብላ የምትጠራውን ግዙፍ ሰው ጫኝ መርከብ ጣና ሀይቅ ላይ ከደልጊ ወደ ባህር ዳር ህዝብ ጭና በመምጣት ላይ እያለች ...
27/04/2025

የባህር ላይ ውንብድና በጣና ሀይቅ ላይ!

በ07/08/2017 ዓም ጣና ነሽ ተብላ የምትጠራውን ግዙፍ ሰው ጫኝ መርከብ ጣና ሀይቅ ላይ ከደልጊ ወደ ባህር ዳር ህዝብ ጭና በመምጣት ላይ እያለች በፈጣን ትንንሽ ጀልባዎች የታጠቁ ዘራፊወች በመምጣት መርከቡን በማስቆም የተሳፋሪዎችን ስልክ በማደበሪያ እንዲያስገቡ በማድረግ እስከ 800,000 ሽህ ብር የደረሰ ብርን ከአንድ በሬ ነጋዴ ላይ ጭምር በመዝረፍ የሁሉን ተሳፋሪ ገንዘብ ወስደው ሄደዋል።

በየብስ ነኪ ያጣው ሽፍትነት በሀይቁ ላይም ተጀምሯል ይህ ለከተማው ለአካባቢው የጀልባ ትራስፖርት ለቱሪስቶች ጭምር ስጋት የሚፈጥር ትልቅ ውንብድና በአጭር ካልተቀጨ መዳረሻው ውድቀት ይሆናል።

ይህ ድርጊት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተስፋፋ መምጣቱን እና ትንንሽ ጀልባወችን ከቦታ ቦታ የሚንቀሳቀሱ የአካባቢው ነጋዴዎችን እንደሚዘርፉ መረጃ ደርሶናል ::

(ከሹፌሮች አንደበት)

በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ መግለጫ፤*****የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)  ብሔራዊ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በወቅታዊ ክልላዊ ሀገራዊና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ሰ...
27/04/2025

በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ መግለጫ፤
*****
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ብሔራዊ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በወቅታዊ ክልላዊ ሀገራዊና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ የሚከተለውን መግለጫ አውጥቷል።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በቅርቡ ባካሄደው 3ኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተዋቀረው የብሄራዊ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በወቅታዊ ክልላዊ ሀገራዊና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ አቋም የወሰደ ሲሆን ጉባኤውን ተከትሎም እንደ አዲስ መታገል ያለበትን የትግል ነጥቦች ነቅሶ ተነጋግሯል። ከዚህ ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን የተራዘመ ግጭት የገመገመ ሲሆን የአማራን ህዝብ ሁለንተናዊ ቀውስ ውስጥ ለመክተት ግጭት እየጠመቁ ያሉ እና የአማራ ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች እንዲዘነጉ የሚያደርጉ ኃይሎች ን አሰላለፍ በመለየት አቋም ላይ ደርሷል።

ሁለት አመት ያስቆጠረው የአማራ ክልል የጸጥታ መታወክ ያስከተለው መጠነ ሰፊ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ፤ የህዝባችን መሰረታዊ ጠላቶች የሆኑ ውጫዊ ሀይሎች ጭምር ግጭቱን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ተዋናይ እየሆኑ መምጣታቸው አብንን በእጅጉ ያሳስበዋል፡፡ በክልሉ በቀጠለው ግጭት በተኩስ ልውውጥ አያሌ ንጹሀኖች ህይወታቸውን አጥተዋል፣ ቆስለዋል፣ ከቀያቸው ተፈናቅለዋል፣ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል፣ ፖለቲካ ውስጥ የሌሉ መምህራኖችና ተማሪዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተረሽነዋል፣ የባለሀብቶችና የታዋቂ ሰዎች ደህንነት አደጋ ላይ ወድቋል፣ ህዝቡ በተራዘመ የኢኮኖሚ ድቀት ውስጥ ገብቷል፡፡ በዚህም የተነሳ የአማራ ህዝብ ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገም የነቃ ተተኪ ትውልድ እንዳይኖረው እና ከአሁኑ የማህበረ-ኢኮኖሚ ፈተና ይልቅ የነገው እየከፋ አንዲመጣ በጠላቶቹና ተላላኪዎቹ በስፋት እየተሰራበት ይገኛል። በዋናነት የአማራ ልጆች በእውቀት፣ በክህሎትና በስነ-ምግባር ታንጸው ተወዳዳሪ እና ሐገር ተረካቢ እንዳይሆኑ እየተደረገም ይገኛል።

በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ በመሆናቸው የተነሳ ህጻናት ልጆች ያለ እድሜ ጋብቻ ውስጥ እየገቡ እንደሆነ እና የህጻናት መደፈር ስለመበራከቱ መረጃዎች እየደረሱን ይገኛሉ፡፡ ግጭቱ የጤና መሰረተ ልማቶችና በጤና አገልግሎት ላይ ሰፊ አደጋ በመጋረጡ በህክምና እጦት ህዝብችን ለሞትና ለማይድን ህመም እየተዳረገ ይገኛል፣ ወዘተ። በኢኮኖሚው ረገድ ሲታይ አቅም ያላቸው የክልሉ ባለሀብቶች ተሰደዋል፣ የሸቀጥ ዝውውር በከፍተኛ ሁኔታ በመስተጓጎሉ የኑሮ ውድነት ተባብሷል፣ በርካታ መሠረተ ልማቶች ወድመዋል፡፡ የአማራ ክልልን ኢንቨስትመንት የመሳብ እምቅ አቅም እና የቱሪዝም ኢኮኖሚውን በመጎተቱ የህዝቡ የመልማት እድል እየተነጠቀ ይገኛልም፡፡ ይህም የአማራ ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች እንዲመለሱ የሚደረገውን ትግል አንዲደበዝዝ እያደረገ ሲገኝ ህዝባችንም ለአጠቃላይ የጸጥታ ስጋት ተዳርጎ ይገኛል፡፡

በመሆኑም ይህንን ለመጭው ዘመን ጭምር የሚተርፍ ዳፋ ያለው ተግባር በማያሻማ ሁኔታ እያወገዝን ሁሉም የሚመለከተው አካል ይህ አይነትና መሰል ድርጊቶች በአፋጣኝ እንዲታረሙ እንዲታገል እና ህዝባችንን ለመታደግ እንደ አዲስ ለጀመርነው እንቅስቃሴ ሁለንተናዊ ድጋፍ እንዲያደርግ እናሳስባለን። እንዲሁም በውጊያ ቀጠና እና በከበባ (Hostage) ውስጥ የሚገኘው ህዝባችን ለከፍተኛ ሁለንተናዊ ጉዳት የተዳረገ ሲሆን ሁሉም ኃይሎች የንጹሀንን ከለላ በሚያረጋግጥ መልኩ እንዲንቀሳቀሱ በጥብቅ እያሳሰብን ችግሩ በውይይትና የሰላምን አማራጭ በማስቀደም እንዲፈታ አበክረን እንመክራለን።

አብን የሀገራዊ ምክክሩ ስትራቴጂካዊ መፍትሄ የምናፈልቀበት አንዲሆን ይመኛል፡፡ በመሆኑም የብሄራዊ ምክክር ጉዳይ በብዙ ውትወታ እና የፖለቲካ ትግል የተገኘ ሀገራዊ መድረክ መሆኑ ታውቆ ህዝባችንን እንወክላለን የሚሉ ኃይሎች ሁሉ በሂደቱ ላይ በንቃት በመሳተፍ በአግባቡ እንዲጠቀሙበት አደራ እያልን ይህንኑም በንቃት የምንከታተል መሆኑን አያይዘን እንገልጻለን።

በሌላ በኩል የአብን ስራ እሰፈጻሚ ኮሚቴ የአማራ ክልልን የወያኔ የጥፋት ድግስ የጨዋታ ሜዳ ለማድረግ ከዚህም ከዛም የተጣቀሱ ያልተቀደሱ ጋብቻዎች መፈጸማቸውንና የሚደረጉ የጦርነት ቅስቃሳና ፕሮፓጋንዳወችን በተመለከተ ጥልቅ ግምገማ አድርጓል፡፡ ወያኔ የፖለቲካ ትርክት፣ አደረጃጀት እና የህግ ማዕቀፍ ዘርግቶ፣ ተቋማት አቋቁሞ በአማራ ህዝብ ላይ ስርዓታዊ ግፍ ሲፈጽም የኖረ ድርጅት መሆኑ የሚታወቅ የቅርብ ዘመን ታሪካዊ ሀቅ ነው፡፡ ይህ ታሪካዊ የአማራ ህዝብ ጠላት በ2017 ዓ.ም. ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁምራን አስመልከቶ ያንጸባረቀው የወራራ አቋም የህዝባችንን አንጻራዊ ነጻነት በኃይል የመንጠቅ እኩይ አላማን ያነገበ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡

በመሆኑም በተጠቀሰው አካባቢ ባለው የአማራ ህዝብ ላይ ዳግም ሊፈጽም ያለመውን የዘር ማጽዳት፣ የዘር ማጥፋትና በ2014 ዓ.ም ማይካድራ ላይ የተፈጸመን የጦር ወንጀል ዳግም የማስቀጠል አላማ እንዲያቆም አበክረን እንገልፃለን:። ወልቃይትን አስመልክቶ የወያኔ ትንኮሳና የጦርነት ቅስቀሳ ከሰብአዊነት ጉዳይና ከሀገራዊ ሰላምና ጸጥታ ጋር በቀጥታ የሚገናኝ በመሆኑ የሚከተለውን ጥሪ ለሚመለከታቸው አካላት አናቀርባለን፡፡

1. የፌደራሉ መንግስት እና መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ህዝብ ያገኘው አንጻራዊ ነጻነት፣ ሰላምና መረጋጋት በዘላቂነት እንዲጸና እና አካባቢው የህወሃት የጦርነት አጀንዳ ሰለባ አንዳይሆን ከሰላም ወዳዱ ከወልቃይት ህዝብ ጎን አንዲሆን አበክረን አንጠይቃለን፡፡

2. በራያ አካባቢወች በህዝብ ትግል የተገኘውን ድል ማጽናት ያልቻለው መንግስት በፈጠረው ክፍተት የወያኔ ሀይሎች ዛሬም ድረስ ህዝባችንን በተራዘመ መከራ ውስጥ ያስገቡት ቢሆንም ህዝባችን ዕለት በዕለት መስዋዕትነት እየከፈለ ለነጻነቱ የሚያደርገውን መዋደቅ መንግስት እውቅና እንዲሰጠውና ለወያኔ የተጋለጠውን ህዝባችንን ህልውና እንዲያስጠብቅ እናሳስባለን።

3. የአማራና የትግራይ ህዝቦች የረጂም ዘመን ታሪካዊና ባህላዊ ቁርኝት ያላቸው መሆናቸው የማይሻር ሀቅ ሲሆን፤ በወያኔ ሃይል የተሳሳተ ትርክት ምክንያት የተፈጠረውን ነውረኛ ማህበራዊ አጥር (wall of shame) ማፍረስ እጅጉን ያስፈልጋል። እስካሁን የተፈጠሩ ቅራኔዎች በሰላማዊ መንገድ በሀቀኛ ውይይትና ድርድር እልባት እንዲያገኙ፤ የትግራይ ህዝብ ከወያኔ የ50 ዓመታት የነጣይ ትርክትና የአፈና ቀንበር መንጭቆ ነጻነቱን ለማወጅና አዲስ መስመር ለማስቀመጥ የሚያደርገውን የከበረ የትግል ጅማሮ እውቅና እየሰጠን ይገደናል ከሚሉ ሰላማዊ የትግራይ ሀይሎች ጋር ተቀራርበን የምንሰራ መሆኑን እንገልጻለን።

አብን ከአማራ ህዝብና ከቀጣናዊ የሰላም መረጋገጥ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም አንጻር በሻዕቢያ አሁናዊና የትላንትና ዘመን ሁኔታ ላይ ሰፊ ግምገማ አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት ሻዕቢያ ከፍጥረቱ ጀምሮ ከአማራ ህዝብ ብሎም ከኢትዮጵያን የፖለቲካ ማህበረሰብ ህልውና አንጻር በበጎ ሊመዘገብለት የሚያስችል ታሪክ የሌለው ኃይል መሆኑ ይታወቃል። አሁን ላይም በአማራ ክልል እንዲሁም በኦሮምያ ክልል አንዳንድ አካባቢወች የሚስተዋለውን የጸጥታ ችግር ለማባባስ ከሚሰሩ ኃይሎች ጋር የአጋርነት ዝንባሌ እንዳለው መረጃዎች የሚያሳዩ ሲሆን የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ተቀጽላ በመሆን በሀገሪቱ ብሄራዊ ጥቅም ላይ ያለመታከት የሚሰራ በመሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ አጥብቆ ሊያወግዘውና ሊታገለው ይገባል:።

ትላንት ኢትዮጵያ በተዳከመችበት ዘመን ሻዕቢያና ወያኔ መሩ የጣምራ ሀይሎች የፖለቲካ መድረኩን በተቆጣጠሩበት ዘመን በተናጥል ስምምነት እና በሁለትዮሽ በመመሳጠር በሽግግር መንግስት ወቅት የተገንጣይነት አጀንዳውን የኢትዮጵያ ህዝብ ባልተሳተፈበት በቀላሉ እንዲያሳካ ተደርጓል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ፓርቲያችን አብን ኤርትራ የሚባለው ሐገር የተመሰረተበት ታሪካዊ ሂደት ቅቡልነት ላይ ጥያቄ ያለው ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያ ሐገራችን ታሪካዊ ይዞታዋ ከሆነው የባህር በር የተገፋችበት የሸፍጥ አካሄድ እንደገና ይፋና ቀዳሚ ሀገራዊ አጀንዳ ሆኖ እንዲያዝ ይጠይቃል።

በአጠቃላይ ግምገማም ሻዕቢያ የኢትዮጵያ እና የቀጠናው መልክዓ-ፖለቲካ (geopolitics) ጉዳዮች ከሰላማዊ ውይይትና ድርድር ይልቅ በግጭትና በጦርነት ብቻ መፈታት አለባቸው የሚል ሃላፊነት የጎደለውና አውዳሚ የሆነ ባህል እንዲንሰራፋ ግንባር ቀደም ሚና ሲጫወት መቆየቱ፣ ኤርትራም ሀገር ከሆነች በኋላም ቢሆን ይሄን አመለካከት በፊታውራሪነት የሚያራምድ ሀይል መሆኑ፣ ባጠቃላይም በህዝቦችና በሀገራቱ መካከል ከፍትሃዊ አማካኝና ከትብብር ይልቅ ተናጥላዊ ጥቅምን በሴራ እና በሃይል የማስፈፀም እንቅስቃሴ ውስጥ ገብቶ በዛው የቀረ ሃይል መሆኑ አለም ያወቀው ሀቅ ሆኗል።

በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን ግጭት በተመለከተ አሁይም አጽንኦት ልንሰጠው የምንወደው ጉዳይ ከታሪክ፣ ከፖለቲካና ከሞራል ፍልስፍና አኳያ፣ እንዲሁም አሁን ካለው የኢትዮጵያ ነባራዊ ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር፣ "ጦርነት የችግሮች መፍቻ ብቸኛው መንገድ ነው" የሚለው ሃሳብ የተሳሳተ መሆኑይ አስምረን እንገልጻለን። ይህንንም ከታሪካዊ እውነታዎች አንጻር ከተመለከትን ኤርትራ ከ1963 - 1983 ዓ.ም ለ 30 ዓመት ያካሄደው ጦርነት ለኤርትራ ህዝብ አምጥቶታል የሚባለው ነጻነት በተጨባጭ ሚዛን ሲለካ ህዝቡ ለሰፊ አፈና ከመዳረጉ በቀር ዛሬም ለነጻነቱ የሚታገል መሆኑ ግልጽ ነው። "ነጻነት" ተብሎ ከበሮ የሚደለቅለትም ታሪካዊ ክስተት የሻዕቢያን የጥቂት ግለሰቦችና የነሱን አምባገነናዊ አገዛዝ ከማፅናት ባለፈ ቅንጣት አዎንታዊ ፋይዳ እንዳሌለው፣ ይባስ ብሎም ተጨማሪ ዘግናኝ የሰብዓዊ መብት ረገጣ እና የሰዎችን ፍልሰት ያስከተለ መሆኑ የሚታወቅ ሀቅ ነው። ሌላው ታሪካዊ እውነታ በደቡብ ሱዳን የምናየው ሲሆን እንደዛው በጦርነት የተገኘው ነፃነት ከ10 አመት በላይ የዘለቀ የእርስበርስ ውጊያ ማስከተሉ እና ከ400,000 በላይ ሰዎችን ለሞት የዳረገ መሆኑን ማስታወስ ያስፈልጋል።

አብን ኢትዮጵያ ከጦርነት አዙሪት ወደ ሰላም ማድረግ ስለሚገባት ሽግግር ላይ መክሯል፡፡ ኢትዮጵያና ሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ታሪኮች እንደሚስረዱት የብሄር ይዘት ያላቸው ግጭቶችና ጦርነቶች በማህበረሰቦች ግንኙነት ላይ አሉታዊ ጠባሳ ጥሎ ስለሚያልፍ በቀጣይ አብሮነት ላይ ተግዳሮችን የሚፈጥር ነው፡፡ በዚህ ረገድ በህወሀትና ኦነግ ጥምረት በኢትዮጵያ ውስጥ ለረጂም ዘመን የተገባበት የግጭት አዙሪት አስተማሪ ተሞክሮ የሚሆን ነው፡፡ በሚሊዬን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሞት እና መፈናቀል ምክንያት ከመሆኑም በላይ ባጠቃላይ የነበረው ዑደት የሚያስገነዝበው የግጭትና የጦርነት አማራጭ መቋጫ እንደማይኖረው አብን ይገነዘባል፡፡

በተለይ የብሄር ይዘት ያለው ግጭትና ጦርነት በማህበረሰቦች ግንኙነት ላይ አሉታዊ ጠባሳ ጥሎ ስለሚያልፍ በቀጣይ አብሮነት ላይ ተግዳሮት የሚፈጥር ነው። በዚህም ረገድ በህወሀትና ኦነግ ጥምረት በኢትዮጵያ ውስጥ ለረጂም ዘመን የተገባበት የግጭት አዙሪት አስተማሪ ተሞክሮ እነንደሚሆን፣ በሚሊዬን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሞት እና መፈናቀል ምክንያት ከመሆኑም በላይ ባጠቃላይ የነበረው ዑደት የሚያስገነዝበው የግጭትና የጦርነት አማራጭ መቋጫ እንደማይኖረው ሲሆን መንግስትን ጨምሮ ሁሉም አካል ይህንን በማጤን ሀገራችንና ህዝባችን በዘላቂ እፎይታ ውስጥ እንዲገባ የልተሄደበትን መንገድ ሁሉ አሟጦ መጓዝ ያስፈልገናል።

እንደሚታወቀው በተለይ የርስበርስ ጦርነት አሸናፊም ተሸናፊ የሌለውና አጠቃላይ ድል ሊያጸና ማይችል፤ ይልቁንም ተጨማሪ ሞት እና ውድመት ከማስከተሉም በላይ ዘላቂ ቅራኔ የሚፈጥር መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ከዚህም ረገድ የቅርቡን ህወሀት መር ሁለት ዙር ጦርነት በትግራይ፣ በአፋር እና በአማራ ክልል ህዝቦች ያስከተለው ሰብአዊ፣ ስልቦናዊና ቁሳዊ ቀውስ ለዚህ በቂ ማሳያ ነው፡፡ "የሰላማዊ ትግል አይሰራም" በሚል አንዳንዶች የሚያራምዱት ሃሳብ ትክክል እንዳልሆነ በ2010 ዓ.ም በኢትዮጵያ ህዝቦች የተደረገው ሰላማዊ ትግል የስርዓት ለውጥ ማምጣቱ በማሳያነት ሊጠቀስ የሚችል ሲሆን ሂደቱም በኢትዮጵያ ህዝቦች መካከል የተሻለ መቀራረብንና የአንድነት መንፈስን የፈጠረ ነበር፡፡ ስለሆነም ከግጭትና ከጦርነት አዙሪት ለመውጣትና በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የሀገራዊ ውይይት ሂደቶች ጤናማነት፣ የህግ የበላይነት መረጋገጥ፣ ማህበረሰባዊ የጋራ እሴቶችን ማጎልበት መጠቀም፣ እና የኢኮኖሚ እድሎችና መፍጠርና ማስፋት አንደሚያስፈልግ አብን ያምናል፡፡

የጦርነት አማራጮች በሂደትም ይሁን በመጨረሻ የግለሰቦችና የጠባብ ቡድኖች ጥቅም ማስፈፀሚያ የመሆን እድሉ ሰፊ ሲሆን ከህዝብ ጥቅም ይልቅ የስልጣን ሽኩቻ መድረክ መሆኑ አንደማይቀር፣ ይሄን እውነታ በኤርትራ፣ በሱዳን፣ በደቡብ ሱዳን እና በኢትዮጵያ ውስጥ ከነበሩትና አሁንም ካሉት ሁኔታዎች በቀላሉ መገንዘብ እንደሚቻል አብን ሁሉይም ወገን እያስታወሰ "ጦርነት ክብር ይሰጣል" ለሚሉ አካላትም መልሱ "ጦርነት ክብር አይሰጥም፣ ጦርነት የሚያስከትለው ተጨማሪ ሞት እና ውድመት ብቻ መሆኑ"፣ በዚህም ረገድ ህወሀት መራሽ የሆኑት ሁለት ዙር የትግራይ ጦርነቶች ውድመት እንጂ ሰላም፣ አንድነት እና ክብር አላመጡም። ስለሆነም ሁልጊዜም ቢሆን የሰላም አማራጮችን በመከተል የግጭትና ጦርነት አዙሪትን መስበር እንደሚገባ አብን ሁሉይም ሀይሎች በአጽንኦት ማሳሰብ ይወዳል።

በተለይ የህግ የበላይነትን ማረጋገጥና ከሌሎች የማህበረ-ኢኮኖሚ መስኮች ጋር አመጋግቦ በመስራት የሁላችንም አጀንዳ የሆነውን የህዝብን ሰላም መመለስ የሚቻልበት እድል አለ ብለን እናምናለን፡፡ የህግ የበላይነት መረጋገጥ፣ የህግ የበይነትን የማስፈን ስምሪቶች በህዝብን አመኔታና ተሳትፎ የታጀቡ በማድረግ፣ የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራዎችን በሰላማዊ ኮሚዩኒኬሽን ማገዝና እና ይህን ክንውን ከማህበረ-ኢኮኖሚ መርሃግብሮች ጋር ማስተሳስር አንዱና ዋናው የሰላም መንገድ ነው ብለን እናምናለን፡፡ በማህበረ-ኢኮኖሚው ዘርፍ የኢትዮጵያዊንን የጋራ ታሪኮችና የጋራ እሴቶች ለሰምና ለሀገራዊ አንድነት መጠቀም እና በግጭት ወይም በጦርነት ተሳታፊ አካላትን መቀነስ የሚያስችል የኢኮኖሚ አማራጮችን ማስፋት ብሎም የስራ እድሎችን መፍጠርን የሚመለከት ሲሆን መንግስት እና መሰል አካላት በነዚህ ቁልፍ ተግባራት ላይ አበክረው አንዲሰሩ አብን ጥሪ ያቀርባል፡፡

በመጨረሻም የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ /አብን/ ብሄራዊ አስፈጻሚ ኮሚቴ ፓርቲው በቅርቡ ያካሄደው ደማቅ ጉባኤ የተመራበትን አካሄድና ዲሲፕሊን፣ የፈጠረውን ሰላማዊ መድረክ እና የተሰጠውን አመራር ያደነቀ ሲሆን ፓርቲው ራሱን ከውስጥ የትግል ጎታቾችና የሌላ አጀንዳ ተሸካሚወች ያጸዳበትን ሂደት "ታሪካዊና ቆራጥ" እርምጃ ሲል አውስቶታል። ጉባኤው በአባላትና ደጋፊወቻችን ዘንድ የፈጠረውን የታደሰ ተስፋና የትግል ቁርጠኝነት ስራ አስፈፃሚው ያደነቀ ሲሆን ይህም ለቁርጠኛ ትግል ስንቅ እንደሚሆነው ገምግሟል።

ብሄራዊ አስፈጻሚ ኮሚቴውም ከወቅታዊ ጉዳዮች በተጨማሪም የፖርቲውን መዋቅሮች እና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ሃይሎች ጋር ተቀራርቦ ለመወያየት፣ በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የአማራ ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኙ ለማስቻል በቀረበው እቅድ ዙሪያ በሰፊው ተወያይቶ አጽድቋል። በመጨረሻም ጠንካራ ሀገር እንዲገነባ፤ የአማራ ህዝብም ከገባበት ውስብስብ ችግር እንዲወጣ ራሱን መልሶ የማይናወጥ የልማትና የሰላም አለኝታ እንዲሆን ለማስቻል በምናደርገው የትግል ሂደት ይገደናል የሚሉ ዜጎች ሁሉ ድጋፋቸውን እንዲሰጡን፣ በተለይ የፌዴራል መንግስት ትልቅ ሀላፊነት ያለበት እንደመሆኑ ሰላም እንዲሰፍን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል የሰላም እድሎችን ሁሉ አሟጦ እንዲጠቀም ጥሪ እናቀርባለን።

ሚያዝያ 19/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሩሲያ እና ዩክሬን ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረባቸውን ተናገሩ❗️የትራምፕ የመካከለኛው ምስራቅ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን...
26/04/2025

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሩሲያ እና ዩክሬን ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረባቸውን ተናገሩ❗️

የትራምፕ የመካከለኛው ምስራቅ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ለሶስት ሰዓታት ያህል ከተወያዩ በኋላ ነው ትራምፕ መግለጫውን የሰጡት፡፡

ተስፋ የተሞላበት ውይይት መደረጉን፤ ሩሲያ እና ዩክሬን ተገናኝተው ስምምነቱን በቶሎ መጨረስ እንዳለባቸው የተናገሩት ትራምፕ፤ በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ከስምነት ተደርሷል፤ ደም መፍሰስም መቆም አለበት ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ፤ ሞስኮ ላይ ከፍተኛ ጫና መደረግ አለበት እያሉ ነው፡፡

ዋሽንግተን ባቀረበችው የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት ኬይቭ የተወሰኑ ግዛቶቿን በሩሲያ ቁጥጥር እንዲሆኑ ትፈቅዳለች።

ሩሲያ በፈረንጆቹ 2014 የክሬሚያን ግዛት በይዞታዋ ስር እንድታስቀጥል እንደሚፈልጉ ትራምፕ ገልጸዋል።

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ግን ይህንን ሀሳብ እንደማይቀበሉት እየተናገሩ ነው፡፡ ሩሲያ በፈረንጆቹ 2022 ልዩ ዘመቻ በሚል ወደ ዩክሬን ከገባች ጀምሮ 20 በመቶ የዩክሬንን ግዛት መቆጣጠሯ ይታወሳል ፡፡
ቢቢሲ፤ ዘ ጋርዲያን እና ኤዥያ ዋን ዘግበውታል ፡፡

የፍርድ ቤት ውሎ ሚያዚያ 9 ቀን 2017 ዓ.ምየአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ ፤ በእስር ላይ የሚገኙ ሲሆን ስዩም ተሾመ የተባለ ግለሰብ  የስም...
17/04/2025

የፍርድ ቤት ውሎ
ሚያዚያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም

የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ ፤ በእስር ላይ የሚገኙ ሲሆን ስዩም ተሾመ የተባለ ግለሰብ የስም ማጥፋት ወንጀል ፈጽሞባቸዋል። ይህን ተከትሎም እነዚህ የሕዝብ ተወካዮች በአቶ ስዩም ተሾመ ላይ የወንጀል ክስ አቅርበዋል።

ምንም እንኳን ግለሰቡ ፍርድ ቤት እይዲቀርብ ቢታዘዝም ችሎት ለመቅረብ ፈቃደኛ አልሆነም። በዛሬው ዕለትም በተመሳሳይ ፍርድ ቤት ሳይቀርብ ቀርቷል።

ይህንን ተከትሎም አቶ ዮሐንስ እና አቶ ክርስቲያን በችሎቱ ያደረጉት ንግግር ቀጥሎ ይቀርባል

"እውነት ለመናገር ስዩም ተሾመ ፍርድ ቤት አይቀርብም። እንደፈለገ ይሳደባል፤ ስም ያጠፋል፤ እናንተን ዳኞችን በተለይም የመሃል ዳኛው ከኛ ጋር የግል ግንኙነት እንዳላቸው አድርጎ በመግለፅ የሀሜት ተግባሩን ቀጥሏል። ለዚህም የሚሆን ማስረጃ በሲዲ አያይዘን አቅርበናል።

መንግስት ፈቅዶለት እንደሚሳደብና ችሎት እንደሚደፍር ነው የምቆጥረው። ከጅቡቲ ጎበዜን አመጣሁ የሚል ፖሊስ አዲስ አበባ ላይ የተቀመጠውን የመንግስት አክቲቪስት ማቅረብ አልቻልኩም የሚለው ስላቅና አሳፋሪ ነው።

ተከሳሽ ስዩም ተሾመ መንግስት መኪና የመደበለት፣ ቤት የሰጠው።፣ አጃቢ የመደበለት፣ የወር ደመወዝ የሚቆርጥለትና በሁሉም የመንግስት ሚዲያዎች በተለይም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ቋሚ የመንግስት ተንታኝ የሆነን ሰው ነው ፖሊስ አጣሁት የሚለው።
ንጹህ ኢትዮጵያውያንን በተለይም አማሮችን እኛን የምክርቤት አባላትን ጨምሮ ከየቦታው ለቅሞ መደበኛ በሆኑና ባልሆኑ የማገቻ ቦታዎች ለምሳሌ በሰመራና በአዋሽ አርባ አሰቃይቶ ፍትህ ያሳጣው ፖሊስ ለስዩም ተሾመ ከለላ እያደረገ ነው።

ይህ የሚያመለክተው በሕግ ፊት ሁሉም ዜጎች እኩል ናቸው የሚለውን መርህ የሚጻረር ነው። መንግስት የራሱን ደጋፊዎች ከሕግና ከፍትህ በላይ ያደርጋቸዋል። ተቃወሙኝ የሚላቸውን ደግሞ ሕገ ወጥ በሆነ መልኩ እያሰቃየ ይገኛል።
እና የኢትዮጵያ የፍትሕ ሥርዓት ደብል ስታንዳርድ ነው የምንለው ለዚህ ነው። እንዳይቀርብ እያደረገ ያለው የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ከኮሚሽነሩ ጀምሮ እንዲጠየቅልን እናመለክታለን።"
አቶ ዮሐንስ ቧያለው

" ስዩም ተሾመ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ሚዲያ አማካሪ ሲሆን ፖሊስ ይህንን ሰው ማቅረብ ያልቻለው ስዩም አንደኛ ደረጃ ዜጋ ስለሆነ ነው። አንደኛ ደረጃ ዜጎች ከሕግ በላይ ሥለሆኑ ፍርድ ቤት መቅረብ አይችሉም። ፍርድ ቤት ተገደው የሚቀርቡት ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዜጎች ብቻ ናቸው። ስዩም አማራ ቢሆን ኖሮ ተገዶ ይቀርብ ነበር ። ምክንያቱም በአሁኑ ወቅት አማራ ሶስተኛ ዜጋ ሆኗልና።

ሁለት መቶ አማራዎችን ከወቅታዊ ጉዳይ ጋር በተገናኘ በሚል ጓዳ ጎድጓዳ ውስጥ ገብቶ በእስር ቤት እያጎረ ያለ ፖሊስ እና አቃቢ ሕግ ስዩም ተሾመን አዲስ አበባ ውስጥ ተሰውሯል ሲባል ያሳፍራል፤ ሞት በሚያስቀጣ አንቀፅ ተከሰን አቶ ስዩም የተባለው ግለሰብ ችሎቱን ከውጭ ሆኖ ተፅዕኖ የሚፈጥርበት ከሆነ ውጤቱ ከወዲሁ የሚታወቅ ነው "

አቶ ክርስቲያን ታደለ

በሁለቱ የሕዝብ ተወካዮች ላይ የስም ማጥፋት ወንጀል የፈጸመው አቶ ስዩም ተሾመ ሚያዝያ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ተገዶ እንዲቀርብ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

አብን ዛሬ ጠቅላላ ጉባኤ አድርጓል===================የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ዛሬ መጋቢት 28, 2017 ዓ.ም. ባደረገው ፫ኛው ጠቅላላ ጉባኤ 5 የቁጥጥር ኮሚሽን እና 45...
06/04/2025

አብን ዛሬ ጠቅላላ ጉባኤ አድርጓል
===================
የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ዛሬ መጋቢት 28, 2017 ዓ.ም. ባደረገው ፫ኛው ጠቅላላ ጉባኤ 5 የቁጥጥር ኮሚሽን እና 45 የምክር ቤት አባላትን መርጧል።

ምክር ቤቱም ዶክተር በለጠ ሞላን የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ መልካሙ ፀጋዬን ምክትል አድርጎ ሰይሟል።
Negarit - ነጋሪት

መረጃ❗️ከነገ ሰኞ ጀምሮ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትና ፌደራል ፖሊስ ወደ ትግራይ ክልል ከተሞች እንደሚገባ የወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ። የፌደራል መንግስቱ ለዚህ ውሳኔ የደረሰው ከትላንቱ በጀ...
30/03/2025

መረጃ❗️

ከነገ ሰኞ ጀምሮ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትና ፌደራል ፖሊስ ወደ ትግራይ ክልል ከተሞች እንደሚገባ የወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ። የፌደራል መንግስቱ ለዚህ ውሳኔ የደረሰው ከትላንቱ በጀነራል ታደሰ ወረደና በጠ/ሚር አብይ አህመድ ውይይት በተደረሰ ስምምነት እንደሆነ ነው ያገኘነው መረጃ የሚያመላክተው።

የትግራይ ይሄ ህዝብ ከሻዕብያና ከሻዕብያ ተላላኪ ሽብር ፈጣሪ ቡድኖች ለመከላከል የፌዴራል ፖሊስ ና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በዋና ከተማ መቐለ፣ ዓዲግራት፣ ዓድዋና ሽሬ ዜጎችን ዋስትና ለማረጋገጥ ሙሉ ሀይል ይገባሉ።

የሻቢያ የስለላ መዋቅር   ***በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሁሉንም የመንግስት እና የግል ተቋማት መፈተሽ አለበት። ባለፉት ስድስት አመት በተለያየ የስራ መስክ የተቀጠሩ ግለሰቦች ማንነታቸው ይፈተሽ...
26/03/2025

የሻቢያ የስለላ መዋቅር
***
በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሁሉንም የመንግስት እና የግል ተቋማት መፈተሽ አለበት። ባለፉት ስድስት አመት በተለያየ የስራ መስክ የተቀጠሩ ግለሰቦች ማንነታቸው ይፈተሽ።የደህንነት ምርመራ እና ምንጠራ የሚያስፈልጋቸው ተቋማት

- ንግድ ባንክ እና ሁሉም ባንኮች (አማራ ባንክ፣ ስንቄ ባንክ) ጭምር ለምን የሽመለስ ቢሮ አይሆንም
- ብሔራዊ ባንክ
- በተለያዩ ሚዲያ ውስጥ የሚሰሩ ግለሰቦች ማንነት መፈተሽ
- መርካቶች ገበያ ውስጥ ያሉ ነጋዴዎች መለየት
- ነጋዴ መስሎ የተሰገሰገ እንዳይኖር
- አስመጪ እና ላኪ የሚል ማዕረግ የተሰጠው
- ማህበራዊ ጉዳይ ላይ የሚሰሩ ጋዜጠኞች በጥንቃቄ ተከታተሉ በተለይ ኦርቶዶክስ ደግፈው የሚጮሁ፣ ሙስሊም ደግፈው፤ ጴንጤ መስለው ከአቅም በላይ የሚጮህ የሻቢያ ቅጥረኛ ስለሚሆን ተይዞ መፈተሽ አለበት።
- አዲስ አበባ ጅቡቲ ተመላላሽ ሹፌር (ሁሉንም ማንነት ፈትሹ)
- አፋር ክልል ወደ ትግራይ የሚሄዱ ሹፌሮች እርግጠኝ ትግራዋይ መሆናቸው እና ለውጭ ሃይል ጋር ምንም አይነት ንክኪ እንደሌላቸው ማጣራት
- በሚንስትር መስሪያ ቤት ውስጥ (በጻሃፊነት፣ በጥበቃ) የተሰማሩ ሰዎች ማንነት በትክክል ፈትሹ፤ መንጥሩ
- ወታደራዊ መስመር መኮንኖች ከአስር አለቃ ጀምሮ ማንነታቸው መርምሩ
- ፌድራል ፖሊስ እና አዲስ አበባ ፖሊስ ውስጥ የሚሰሩ ሰዎች ማንነት ማጣራት፣ የቀድሞዎቹንም አዲሶቹንም በደንብ መፈተሽ፤ ጸሃፊ፣ ሃላፊ የለም።
- ከጅቡቲም ይሁን ከአፋር ክልል የትኛውም ሹፌር ፎቶ እና ቪዲዬ መቅረጽ እንደሌለበት መመሪያ መስጠት ያንን ተላልፎ የተገኘ....ቅጣት
- ኤርፖርት እና አየር መንገድ ሰራተኝነት ውስጥ ያሉ የደህንነት ሰዎች መመርመር
- ግምሩክ ላይ ያሉ ሰዎች የመለየት ስራ መስራት
- በየተቋማቱ ባለሞያ ተብሎ የተቀጠሩ ግለሰቦች ማንነት በጥንቃቄ ማለየት እና ማወቅ
- በNGO ውስጥ የሚሰሩ ለምን ሹፌር አይሆንም ማንነቱ መርምሩት

📛 ቀንደኛ የብልጽግና ደጋፊ መስለው ያዙኝ ልቀቁኝ የሚል በቲክቶክ፣ ፌስቡክ እና በተለያየ ማህበራዊ ቦታ ላይ የብልጽግና ደጋፊ መስሎ ሌሎች ማህበረሰብ የሚሳደብ፣ ባለጌ ንግግር የሚናገር በብዛት የሻቢያ ቅጥረኞች መሆናቸው ልንረዳ ይገባል። ሻቢያ በማህበራዊ ጉዳይ እና ፖለቲካ ሰዎችን አመሳስሎ ያስገባል። ቆነጃጅት ሴቶች ለሱሰኛ ወንዶች የመላክ ልምድ አለው 📛 ደጋፊም ይሁን ተቃዋሚ፤ ማንነቱ በግልጽ መታወቅ አለበት።

👉 ሻቢያ ለስለላ የሚጠቀመው አምቼ ኤርትራውያንን ነው። አምቼ ኤርትራውያን ማለት ግማሽ ኢትዮጵያዊ፤ ግማሽ ኤርትራዉ የሆኑትን ማለት ነው። በየኤምባሲው፣ በየፌስቡክ እና ቲክቶኩ አብዬዬዬዬዬ የሚለው ሁሉ እያስመሰለ ስለሚሆን ማንነቱ መታወቅ አለበት። እስከ ምንጅላቱ ድረስ ይጣራ! አብቹዬ እኔ ልደፋለህ የሚለው፤ አማራ ደግፉ ኦሮሞ ህዝብ የሚሳደብ፤ ኦሮሞን ደግፎ አማራን ማህበረሰብ የሚሳደብ ከሆነ 1000% የሻቢያ ሰላይ ነው። የእኛ ደንቆሮ ብሔርተኛ የፈለገ ቢሆን ህዝብን በድፍረት አይናገሩም። ማህበረሰብ ቆሽሻ በሆነ መንገድ የሚሳደቡት የሻቢያ ሰላዬች ናቸው።

👉 ሃገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎች አሳስተው ሊጠልፏቸው ይችላል፣ በተቃዋሚው ውስጥም ሰዎች ሊያስገቡ ይችላሉ እናም የራሳችን ወጣቶች ዝም ብሎ ማንገላታት ሳይሆን የሃገር ደህንነት ማስረዳት፣ ማስተማር ያስፈልጋል።

****
ወጣቶች በሚኖሩበት አካባቢ በንቃት እንዲከታተሉ ማድረግ
አሻግሬ ጌታቸው

   ሙሳ ቢሂ አብዲ የኢትዮጵያና የሶማሌላንድን የባህርበር ስምምነት  በዛሬው እለት ለፓርላማ  አቅርበዋል። "ሁለታችንም የምንፈልገው ይታወቃል ኢትዮጵያ ባህር በር ትፈልጋለች፣ እኛም እድሜ ዘ...
09/06/2024

ሙሳ ቢሂ አብዲ የኢትዮጵያና የሶማሌላንድን የባህርበር ስምምነት በዛሬው እለት ለፓርላማ አቅርበዋል።

"ሁለታችንም የምንፈልገው ይታወቃል ኢትዮጵያ ባህር በር ትፈልጋለች፣ እኛም እድሜ ዘመናችንን ሀገር ለመሆን ታትረናል ።" #ያሉት✅ ...ለፓርላማው ባደረጉት ንግግር "ስምምነት ከሰሞኑን ይፈፀማል ከኢትዮጵያ ጋር ግልፅ የሆነ ስምምነት ላይ ደርሰናል ኢትዮጵያ የባህር በር ታገኛለች እኛም የሀገርነት እውቅና ከኢትዮጵያ ይሰጠናል ሁሉም ስምምነቶች አልቀዋል መፈረም ብቻና ለፓርላማዎቻችን ማፅደቅ ነው የቀረን ብለዋል።

ሁለቱ ሀገራት የተግባር እንቅስቃሴዎችን እያደረጉ ሲሆን የሶማሌላንድ ፖሊስ ኦፊሰሮች በኢትዮጵያ ሀዋሳ ከተማ ስልጠና መውሰድ ጀምረዋል።

#በተጨማሪም የሶማሌላንድ አየር መንገድ ለማቋቋም ዝግጅት የተጀመረ ሲሆን #ሶማሌላንድ 4 የመለማመጃ አነስተኛ አውሮፕላኖችን መግዛቷን ፕሬዝዳንት ሙሳ ቢሂ ተናግረዋል።
#ኢትዮጵያዊነት Ethiopiawinet ✅

Address

Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Daily News ET posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share