09/06/2026
ህንጻው የአለማችን ረጅሙ ቤተክርስቲያን ሆኗል
በነጭ መስቀል ያጌጠውና ባለፈው የካቲት ወር ላይ ግንባታው የተጠናቀቀው ይህ ማማ፤ ከተማዋን ወደ ሰማይ አንጋጦ ማሳየት ያስቻለ አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑ ተነግሯል።
ሊቀ ጳጳሱ ለዚህ ጉብኝታቸው “አይኖቻችሁን ወደ ላይ አንሱ” የሚል መሪ ቃል የመረጡ ሲሆን፣ በዕለቱ በሚያደርጉት የጸሎት ሥነ-ሥርዓት ላይ የስፔን ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝን ጨምሮ በርካታ የሀገር ውስጥና የአለም አቀፍ እንግዶች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 14ኛ በስፔን ባርሴሎና የሚገኘውን ታዋቂውን የሳግራዳ ፋሚሊያ ካቴድራል ማዕከላዊ ማማ (የኢየሱስ ክርስቶስ ማማ) ነገ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም (June 10, 2026) በይፋ ባርከው እንደሚመርቁ ተገለጸ።
የታዋቂው አርክቴክት አንቶኒ ጋውዲ (Antoni Gaudí) የሙት ዓመት መቶኛ መታሰቢያ በሚዘከርበት በዚህ ዕለት የሚከናወነው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት፤ ካቴድራሉን 172.5 ሜትር ከፍታ በማጎናጸፍ በአለማችን ላይ ረጅሙ ቤተክርስቲያን እንዲሆን አስችሎታል።
የቤተክርስቲያኑን ምስሎች ኮመንት ላይ ያገኛሉ
ምንጭ፦ Associated Press (AP)