Wollo Ethio Media

Wollo Ethio Media ኢትዮጲያ ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር���

"ጦርነት እንዲጀመር አልፈልግም፤ ከተጀመረ ግን አሰብ ደርሶ የሚመለስ የኢትዮጵያ ወታደር የለም!" _ ጀነራል ሰሞራ የኑስጀነራሉ ከሰሞኑ የአፍሪካ ቀንድ የውጥረት ምንጭ የሆነው የቀይ ባህር ጉ...
02/11/2025

"ጦርነት እንዲጀመር አልፈልግም፤ ከተጀመረ ግን አሰብ ደርሶ የሚመለስ የኢትዮጵያ ወታደር የለም!" _ ጀነራል ሰሞራ የኑስ

ጀነራሉ ከሰሞኑ የአፍሪካ ቀንድ የውጥረት ምንጭ የሆነው የቀይ ባህር ጉዳይ ላይ ሰጡ የተባለው አስተያየት ነው።

ጦርነት የማይቀር ሆኖ ከተጀመረ ውጤቱ በአሰብ ብቻ የሚገታ አይሆንም። ጦርነቱ ከተነሳ የሻዕቢያን መንግስት የሚቃወሙ ሌሎች የኤርትራ ኃይሎች ሙሉ ኤርትራን ከአስተዳደሩ ነጻ ለማውጣት ስለሚፈልጉ "አሰብን ብቻ ይዞ የሚመለስ ሰራዊት አይኖርም" ብለዋል።

የባህር በር ጉዳይ በዋናነት የሚነሳው እንደ ሀገር መውጫ መግቢያ ስላጣን እና ስለታፈንን አይደለም፤ የወደብ ኪራይ ክፍያ ስለበዛብንም አይደለም፤ የህዝብ ቁጥራችን ብዙ በመሆኑም አይደለም፤ አስ...
02/11/2025

የባህር በር ጉዳይ በዋናነት የሚነሳው እንደ ሀገር መውጫ መግቢያ ስላጣን እና ስለታፈንን አይደለም፤ የወደብ ኪራይ ክፍያ ስለበዛብንም አይደለም፤ የህዝብ ቁጥራችን ብዙ በመሆኑም አይደለም፤ አስር ድስት ስለተጣደ ወይንም ስላልተጣደም አይደለም። መውጫ መግቢያ አጣን ብለን የላሙ-ኬንያ ወደብ ወይንም ፖርትሱዳን ይገባናል አላልንም፣ ኒውዮርክ ወይንም ኬፕታውን ወይንም ሌላ ይገባናልም አላልንም።

ይልቁንም አሰብን ጠቅሰን የባህር በር ይገባናል የምንለው አሰብ የኢትዮጵያ አካል ስለሆነ ብቻ ነው። አላግባብ ከኢትዮጵያ የተወሰደ ስለሆነ፣ ሉአላዊነትን ያላረጋገጠ የሽግግር መንግስት በተናጥል ውሳኔ አሳልፎ የሰጠው ስለሆነ፣ ተገንጣይና አስገንጣይ ተባብረው በአንድነት የፈጸሙት ታሪካዊ በደል ስለሆነ ነው የአሰብን የኢትዮጵያ አካል አለመሆንን የማንቀበለውና አሰብ ተፈጥሯዊ የኢትዮጵያ የባህር በርነቱ ዳግም ሊረጋግጥ ይገባል የምንለው።
ይህንን ጥያቄ ለማንሳትም ይሁን እንደ ሀገር በዚህ ጥያቄ ዙሪያ ለመታገልና ጥያቄውን ለማስመለስ ከዚህ የተሻለ ግዜስ ከአሁንቀደም ነበር ወይ? አይመስለኝም! (ለዚህም ብዙ ምክንያትና ሰፋ ያለ ትንታኔ ሊቀርብለት ይችላል)።

Yes, as a country, we might have taken a long way in the wrong direction, but it is time now that we got to turn around as we do.

Remember also, Vitamin Sea is a vital necessity. It helps heal wounds, maintain good health. So, we need it !

ይሄው ነው!

21/04/2024

የአማራው በረሄርተኛ ሃይልን አለማድነቅ አይቻልም‼

★★★//🍂//★★★

(ማሳሰቢያ:— ሙስሊም ሆናችሁ በኮመንት የምትሳደቡትን ያለ ምንም ምህረት ወደ ብሎክ እንደማስገባ ይታወቅ)

የአማራው ብሄርተኛ ሃይል ድብቅ ፍላጎትና የትግል ፕሮፓጋንዳውን ክፋት ለመረዳት የከበደው ሙስሊም በብዛት ይታያል።

የአማራ ብሄርተኛው ሃይል ክልሉ ውስጥ ሙስሊሙ በብዛት የሳሳበት አካባቢ ላይ ሙስሊሙን ያግታል፣ ገንዘብ ይዘርፋል፣ ይገድላል፣ ያፈናቅላል፣ መስጅድ ያፈርሳል ያቃጥላል፣ ሀሪማ ይቀማል፣ የታቀደ ኦፕሬሽን ሰርቶ በየሙስሊሙ ቤት እየገባ ጥቃት ያደርሳል። መልሶ ይህን የሰራው መንግስት ነው፣ ፋኖ በዚህ ሰኣት ምን ሊጠቀም ይህን ይሰራል? የሚል ለልጆች የተሰራ ፕሮ ጋንዳ ይሰራል፣ በአማራ ክልል ያሉ ሙስሊም አመራሮችን አቀነባባሪዎች አድርጎ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ለመምታት ይሰራል። አሊያም አህመድን ጀበልን ከኦሮሚያ ወስዶ ጎጃም ላይ ያሳድርና አህመድንና ውሃብያ ኦሮሞዎች ናቸው ብሎ ድርሰት ፅፎ መንጋውን ያስከትላል።

ክልሉ ውስጥ ሙስሊሞች በሚበዙበት አካባቢ ደግሞ ሙስሊሙን በጎጃምና በጎንደር እንደሚያደርገው በወሎ መግደል፣ ማፈናቀል እንደማይችል የወሎ ሙስሊም ዴሞግራፊን በቅጡ የሚረዳ ጎበዝ ስብስብ ነው። ስለዚህ ጥይቱን ትቶ በፕሮፓጋንዳ ይሰልበዋል።

የሙስሊም አማራውን በኦሮሚያ በብዛት መጨፍጨፍ፣ መፈናቀል ደግሞ ደጋግሞ ፕሮፓጋንዳ በመስራት፣ "ወላሂ ከእንግዲህ አማራ አልሆንም!" የምትል ህፃን አኢሻ ፈጥሮ ሰፊ ቅስቀሳ ያደርጋል!

በቢሮክራሲው እጅግ አሳፋሪና ቅኝ ግዛት በሚመሰል መልኩ ሙስሊሙን ይጨቁናል፣ ከመዋቅር ያጠራል፣ ያባርራል፣ የመሬት፣ የሀብት ሽሚያ ውስጥ ገብቶ ሰፊ ስራ ይሰራል። ወሎ ዩኒቨርስቲን ምሳሌ ብናነሳ በግቢው ውስጥ አንድም የመካከለኛው አመራር ፖዚሽን ላይ ሙስሊም የለም።

ለትግላቸው አስጊ ያልሆነ፣ የመወሰንና የአመራር ፖዚሽን ላይ ያልሆነን ሙስሊም የመንግስት ሰራተኛን ለቅመው እየገደሉ ለመንጋቸው ባንዳ ተላላኪ ላይ እርምጃ ወሰድን ብለው ጀስቲፋይ ያደርጉላቸውና ፋኒት የሰይዲ ልጅ መጥታ ታዝግሃለች‼

የአማራ ብሄርተኛ ትግል «የቀራንዮ መዳረሻችን" ሀቲት ፣ "አራሽ ተኳሽ፣ ቀዳሽ" ሞቶ ወሎ ላይ ሲደርሱ ጥቂት ያሻሽሏትና " አራሽ፣ ተኳሽ፣ ቀዳሽ፣ ሰጋጅ!“ ሲሉ እና ፋኖ ሰይዲን እና ፋኖ ማሜን ፊት ለፊት ይዘው በመምጣት የ"ሀበሻ አማራ ናው፣ የነጃሽ ተራራ ነው!“ ቂሷ እያስነገሩ ይመጣሉ።

ይህ በካውንተር ፕሮፓጋንዳ ኦቨር ዶዝ የነፈለለ እስላም መጨረሻውን ሳያገናዝብ "የተገደልነው በአማራነታችን እንጅ በእስላምነታችን አይደለም!" እያለ/እያለች የቡልሃ መንጢቅ ይዛ ታደርቅሃለች። ወለጋ ላይ ጎጃሜ ሰፋሪ፣ ትግሬ ሰፋሪ፣ ወሎየ ሰፋሪ እያለ ወሎየው ሰፋሪ ብቻ ተለይቶ ለምን እንደተጨፈጨፈ ለማስተዋልና የጎጃሜ ሸኔና ፋኖ እጅ ሊኖር እንደሚችልንኳ ማስተዋል አይችሉም።

በወሎ ኦሮሞ ሙስሊሞች ላይ ቀጥታ የፕሮክሲ ዋር ካውንተር ፕሮፓጋንዳን ሃይል ይጠቀምና የሸኔ፣ የኦሮሙማ ተላላኪና ኤጀንት ነው ብሎ ሰፊ ፕሮፓጋንዳ ይሰራና እስላሙን ጭምር በእስላም ወንድሙ ላይ አስዘምቶ መስጅድ ሲያስቃጥለው ያድራል‼

የአማራው ብሄርተኛና የአሃዳዊው ሃይል የፕሮፓጋንዳ አቅም እንኳን እኛን መንግስትን እንዴት እንደሚያንቀጠቅጥና አደገኛ የፕሮፓጋንዳ ፍሬሚንግ መሀንድስ እንደሆነ የማይረዳ የአማራ ክልል በርካታ ሙስሊም የፕሮፓጋንዳው ሰለባ ሆኖ መጠቀሚያ ሆኖ የነገ አስለቃሹን ሊያነግስ እንዴት ፊዳ እየሆነ እንደሆነ ስታየው ታዝናለህ!

የነሰይድ ድራርን ታሪክ ለፋኖ ሰጥታ እሷ ፋኒት ኻውለት ሆና የአሱሃቦቹን ታሪክ የሸኾቹን ማዲህ ወስዳ ለዘመነ ካሴ ሰጥታ በመንዙማ ስታሽሞነሙነው ስታይ ምንያክል ሙድ እንደያዙብን ይገለጥልሃል‼

ወንድሜ ምንድን አገኘህ?
ሽታየ ሳልስምህ ስትሄድ ሳላይህ
ቀረህ አሉኝሳ ለየት ብለህ
የናቴ ልጅ አንዱ በየት ላግኝህ
እሜዳ ጣሉህ ወይ ገደል ሰደዱህ
ለጅብም ሰጡህ ወይ አሞራ በላህ
ብቻህን ሆንክና እት እንደሌለህ
ክንዴ ፊዳ ልሁን ልሂድ አብሬህ

እያለች በመንዙማ የፋኖን እንቅስቃሴ ልታሰልም ስትፍገመገም ታያታለህ‼

የአማራውን ክልል ሙስሊም በጋራ እንዳያስብ የኮሌክቲቭ እሳቤውን በማሳጣት አሊያም የጋራ ግብ እንዳይኖረው እንደየአካባቢው ተጨባጭ በቅጡ የተቀረፀ የትግል ስልት እያደረገ እጅግ የሚደንቅ ስኬት ላይ ነውና በእስላሙ ግልብነት በብሄርተኛው አማራ ስኬት እየበሸቁ አለመደነቅ አይቻልም‼

ሙሐጅሩ መሃመድ አቡ ከውሰር  እየገባችሁ ላይክ አድርጉለት
03/03/2024

ሙሐጅሩ መሃመድ አቡ ከውሰር እየገባችሁ ላይክ አድርጉለት

ሰበር የድል ዜና!!በአሜሪካ የባይደን አስተዳደር ኢትዮጵያን ለመወንጀል ለወራት ስታረቀው የቆየችው እና ሊፀድቅ የነበረው  የ"ትግራይ የዘር ማጥፋት አዋጅ" ማሻሻያ ከብሄራዊ መከላከያ ፍቃድ ህ...
07/12/2021

ሰበር የድል ዜና!!

በአሜሪካ የባይደን አስተዳደር ኢትዮጵያን ለመወንጀል ለወራት ስታረቀው የቆየችው እና ሊፀድቅ የነበረው የ"ትግራይ የዘር ማጥፋት አዋጅ" ማሻሻያ ከብሄራዊ መከላከያ ፍቃድ ህግ (NDAA) ተወግዷል!!!!

The "declaration of genocide in Tigray" amendment has been removed from the National Defense Authorization Act (NDAA).

ይህ የሆነው ኢትዮጵያዊ እና ኤርትራዊ ዲያስፖራ: አፍሪካዊያን እና መላው የ እንቅስቃሴ ደጋፊዎች ለአሜሪካ ኮንግረስ አባላት ስልክ በመደወል ኢሜይል በመፃፍ እንዲሁም ተደጋጋሚ የተቃውሞ ሰልፍ በመውጣት ባደረጉት ከፍተኛ ተጋድሎ ነው!(ደጀኔ አሰፋ)

ግብፃዊ የፖለቲካ ተንታኝ አህመድ አልብሔይሪ.!« ከገባንብት ጭንቀት ከፈጣሪ በታች ያወጣናል ብለን ተስፋ ያደረግነው በህወሓት ሀይል ነበር.»! ደስታችንን ሳናጣጥም ነገሮች ባልጠበቅነው መንገድ...
06/12/2021

ግብፃዊ የፖለቲካ ተንታኝ አህመድ አልብሔይሪ.!

« ከገባንብት ጭንቀት ከፈጣሪ በታች ያወጣናል ብለን ተስፋ ያደረግነው በህወሓት ሀይል ነበር.»! ደስታችንን ሳናጣጥም ነገሮች ባልጠበቅነው መንገድ የጠበቅነው ብረሀን ወደጨለማ ተቀይሮ መጣ።

እኛ የተከተልነው የአለምን ሚዲያዎች ዘመቻ ብቻ አልነበረም። አሜሪካና አውሮፓውያን የአብይን መንግስት አይፈልጉትም ነበር። ይህንን እኛም ይሁን መንግስታችን ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ባደባባይ ይመሰክሩት ነበር።

ኢትዮጵያዊያን ትግላችን ከምዕራባውያን ጋር ነው ሲሉ እኛም በአሜሪካና በአውሮፓዎች ተማምነን አለም ሲከተለውን የነበረውን ሁሉ ተከትለን የህወሓትን ግስጋሴ እየተከተልን መፈንጠዝ ይዘን ነበር። ምን ዋጋ አለው። የተመኘነው ብረሀን ጨለማ ሆኖ ተቀይሮ መጣብን። ከዚህ ድቅድቅ ጨለማ ወጣን ብለን ፈጣሪን ሳናመሰግን፣ በመጨረሻ ሰአት አብይ አሕመድ እና ቻይና ጨዋታውን ቀየሩት። ደስታችንን ጨለማ ውስጥ ከተቱት።
አለቀለት የተባለው የአብይ አሕመድ ስረአት
አለምን ባስገረመ ፍጥነት ተመልሶ በማጥቃት ሙሉ በመሉ የትግራይ ክልልን ሊቆጣጠራት ትንሽ ቀናቶች ብቻ ናቸው የሚቀሩት። የህወሓት ሀይል ተንኮታኩቶ ተኗል። ስምና ንፋስ ላይ የቀረ ጉም ሆኗል። በንፋስ የታጠረ ጉም መጨረሻው ትነት እንጅ ዝናብ አይወጣም። ትርፍ ዳመና ብቻ ነው። ከዚህ ቡኋላ ሁሉም ነገር አክትሟል።
የኛ ህልምና'' በህወሓት ላይ ያለን ተስፋ አብሮ ጠፍቷል።
ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ የኢትዮጵያን ህዝብ በዙሪያው አሰልፎ በክብር ፣ በፍቅርና በልዩ እንክብካቤ የመሪነት ምሰሶ ችካሉን ማንም እንዳያነቃንቀው አድርጎ ተክሎታል።
የእኛንም ህልምና ምኞት ዳግም እንዳያንሰራራ አድርጎ አብሮ ቀብሮታል ።
በኢትዮጵያ ላይ የጣልነው ተስፋ በዚህ መልኩ ተቋጭቷል። ሲሲ ዛሬ ግብፅን እቀይራለሁ እያለ በቴሌቪዥን ቀጥታ ስርጭት ላይ ሲያለቅስ ነበር። ለምን አያለቅስ .? በደንብ ያልቅስ እንጅ፣ በወሬ ተበልተን መጨረሻችን እንዲህ ከሆነ ለምን አያስለቅስ፣

ግብፃዊ የፖለቲካ ተንታኝ አህመድ አልብሔይሪ፤ በሸርቅ ቴሌቪዥን ላይ የተናገረው

ሱሌማን አብደላ

የአልጀዚራ ጋዜጠኛ መሀመድ ተወከልየኢትዮጵያ መከላከያ ስራዊት በማንኛውም ቀንና ሰአት ዋና ከተማዋን መቀሌን ጨምሮየቀሩ ቦታዎች ይቆጠራል።በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ላይ ጋዜጠኛ ሆኘ ለዚሁ ለምሰራ...
04/12/2021

የአልጀዚራ ጋዜጠኛ መሀመድ ተወከል
የኢትዮጵያ መከላከያ ስራዊት በማንኛውም ቀንና ሰአት ዋና ከተማዋን መቀሌን ጨምሮ
የቀሩ ቦታዎች ይቆጠራል።

በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ላይ ጋዜጠኛ ሆኘ ለዚሁ ለምሰራበት አልጀዚራ ሚዲያ ዜና ልሰራ ባድሜ ተገቸ በወቅቱ የሆነውን አይቻለሁ።

የሯንዳና የሱዳንን የአፍጋኒስታን የኢራቅን የሊቢያን ጦርነቱ ተዟዙሬ ሁላቸውንም ዜና ሰርቻለሁ። እዚህ ቡርቃና ጭፍራ ግንባር ግን ያየሁት ለየት ያለ ነው። የሰው ልጅ እንዲህ በጅምላ መሞትን ግን አይቼ አላቅም። እንዳለ ገና ወጣቶች ናቸው። ከዚህ ከኋላየ ትንሽ ራቅ አለ ቦታ ላይ ህዝቡ ሦስት ቀን ሙሉ ቀብሮ ያልጨረሰው ሙታን አለ።

ይሄ ሁሉ የትግራይ ወጣት እረግፎ ምን እንደሚገኝ አላቅም። ብቻ እንዴት ብየ ልገልፀው የማልችለው አስከፊ የሆነ ሞትን አይቻለሁ። ያልሰለጠኑ ወጣቶችን አፍሶ ጦርነት ላይ መማገድ ለምን አስፈላጊ እንደሆነ መልስ የለለው ጥያቄ ነው።

ለህዝብ የሚታገል ሰው ወይም ድርጅት ምንም የጦርነት ብቃት የየላቸውን ልጆች እሳት ላይ ማግዶ ማስፈጀት የህዝብ ተሟጋችነቱ እምኑ ላይ እንደሆነ አላቅም። የኢትዮጵያ መከላከያ ስራዊት የተደራጀ ነው። ብቃት ያለው ሰራዊት ነው። የምስራቅ አፍሪካ ግዙፉ ሰራዊት ነው። በእግር ውጊያ አለም ያደነቀው ወታደር ነው። አሸባሪዎች ገና ለገና የኢትዮጵያ መከላከያ ስራዊት የሚለው ስሙ ሲነሳ በፍረሀት የሚሸነፉለት ሰራዊት ነው። ምንም ብቃት የለለውን የህዝብ ልጅ ከቤቱሰቡ በግዳጅ ቀምቶ እዚህ ሰራዊት ፊት አምጥቶ መማገድ ለአሸናፊነት የሚደረግ ትግል ወይም ውጊያ አይደለም። ህዝብን ለማስጨረስ የሚደረግ ውጊያ ነው።
ጋዜጠኛዋ ጥያቄ፦ መሀመድ እንደው አሁን ምን አይነት እንቅስቃሴ ይታየሀል ውጊያው ምን ላይ ደርሷል ትላለህ .?

መልስ መሀመድ፦
የትኛው ጦርነት ነው ? ጦርነቱኮ አብቅቷል።
እንዳለ የትግራይ ሰራዊት እየተባለ የሚመጣው ሁሉ ተማግዶ ተጨርሷል። አሁን የቀሩት መውጫ እየፈለጉ ነው። የመንግስት ወታደሮች እየተከታተሉ መሳሪያ እየተረከቡ ነው። የዘረፉትን ንብረትና መሳሪያ ይዘው እንዳይሄዱ መንግስት ዙሪያውን አጥሮ እጅ ስጡ መሳሪያ አስረክቡ እያላቸው ነው። በተለያዩ የእምነት ቦታቸው ውስጥ እጃቸውን የሰጡ አሉ። አሁንም እየሰጡ ነው። የሚሻለውም ይሄ ነው። ይሄ ጦርነት አለም ስም እንደሰጠው የትግራይ ስራዊት ተብሎ በሚዲያ እንደሚነገረው አይደለም። አጠቃላይ ጦርነቱ አቅማቸው ከማይፈቅደው የኢትዮጵያ ወታደር ጋር የትግራይን ወጣቶች በግድ እየማገዱ ማስጨረስ ነበር። ከሚነገረው ጀርባ ካሜራ ያላየው ብዙ ነገር አለ። የትግራይ ህዝብ ወታደር
TDF ተብሎ የሚነገረው ነገርና መሬት ላይ ያለው የተለያየ ነው።
ጋዜጠኛዋ ጥያቄ፦ መሀመድ ስለዚህ ጦርነቱ አብቅቷል .? የትግራይ ተገንጣይ ቡድን ተሸንፏል ነው የምትለው ?

መልስ መሀመድ
አዎ የትግራይ ታጣቂዎች ተሸንፈዋል። ህዝብ አስጨርሰው በድንጋጤ ቆመዋል። መከላከያ ስራዊቱ በቅርብ ቀን ዋና ከተማዋን መቀሌን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ ይቆጣጠራል። ዝግጅቱም ለዚያ እንጅ በአማራ እና በአፋር ግንባር ያለው ጦርነት አብቅቷል። እንደነገርኩሽ'' የመንግስት ወታደር እየተከተለ መሳሪያ መልቀምና የፈረሱ መዋቅሮችን ማደራጀት የህወሓት
ሀይል የያዙት መሳሪያ እየተከለ ማስቀረት
ነው የያዘው። ፊትለፊቱ ቆሞ የሚዋጋው ሀይል የለም። ህወሓቶች መጀመሪያ በነበሩት ውጊያዎች ላይ ያላቸውን ሀይል አስጨረሰዋል። ከትግራይ እስከ ደብረሲ ቡርቃ ጭፍራ ድረስ ሲገቡ በመቶሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች እየማገዱ ነው።
ጥያቄ ጋዜጠኛዋ፦ መሀመድ የአብይ ወታደር እንዴት ይሄንን ሀይል ባጭር ጊዜ አግኝቶ በፍጥነት ጦርነቱን ማሸነፍ ቻለ?

መልስ መሀመድ
የአብይ ሳይሆን የኢትዮጵያ መከላከያ ስራዊትና የኢትዮጵያ ህዝብ መዋጋት ከጀመረ አመት አልፎታል። ዛሬ አይደለም ሀይል የነበረው አጠቃላይ ጦርነቱ የህልውና ጦርነት ተደርግ ነው በኢትዮጵያውያን የተወሰደው። በዚህ ጦርነት ላይ መሳሪያ ያለው ብቻ ሳይሆን የለለውም ህዝብ ዋጋ ከፍሏል። ገንዙቡን ሂውቱን ማንነቱን ፆታውን ገብሯል።
የቆመ ከብተ ሳይቀር ዋጋ ከፍቷል። ያነ'' ነው ጦርነቱ የተጠናቀቀው።

አብይ ያደረገው መልሶ ያለውን ሀይል አደራጅቶ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ተጠቅሞ ጦርነቱ ህዝብና አገር ሳይጎዳ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ አዲስ ስልት ይዞ ወደጦር ሜዳ ገብቷል። ጦርነቱ በትንሽ መሰዋዕትነት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲጠናቀቅ የነደፈው የጦር ቀመር ውጤት አምጥቷል። ከዚህ ቡሀላ በኢትዮጵያ መከላከያ ስራዊት እዝነት እንጅ
የህወሓት ሀይል የሚድነው በአሸናፊነት አይደለም። ይህ ጦርነት ዘመኑ በፈጠረው የረቀቀ ቴክኖሎጂ የሚታገዝ ጦርነት ነው። እንዳልኩሽ የኢትዮጵያ መከላከያ ስራዊት በማንኛውም ቀንና ሰአት መቀሌን ጨምሮ ሌሎችን ቦታቸው የሚቆጣጠርበት አቅም አለው። እፊቱ ላይ ሊያቆመው የሚችል ሀይል የለም። እንዳይኖር አድርጎ ነው ውጊያውን ቀይሶ እየተራመደ ያለው።

ሱሌማን አብደላ

ትንሽ ድል የተገኘ ሲመስል ከልክ በላይ በመስከር፣ ትንሽ ነገሮች መስመር የሳቱ ሲመስል ተስፋ ቆርጦ በመነጫነጭ የሚገኝ አጠቃላይ ድል የለም። ድል የሚገኘው ጉድለት ሲኖር እሱን ተጋግዞ በመሙላ...
30/10/2021

ትንሽ ድል የተገኘ ሲመስል ከልክ በላይ በመስከር፣ ትንሽ ነገሮች መስመር የሳቱ ሲመስል ተስፋ ቆርጦ በመነጫነጭ የሚገኝ አጠቃላይ ድል የለም። ድል የሚገኘው ጉድለት ሲኖር እሱን ተጋግዞ በመሙላት ነው። ያልተረጋጋ አዕምሮ እንኳን ጉድለት ሞልቶ ድልን ማምጣት፣ ድሉን በአግባቡ ማጣጣም አይችልም!!
ተረጋጋ!!

ከመቀሌ እስከ ውጫሌ የነበረው ማፈግፈግ ለደሴ፣ኮምቦልቻና ሀይቅ ትልቅ ስጋት ይዞ መጥቷል።ቢሆንም በድል ይጠናቀቃል።በራስ አቅም መሆን ያለበትን ለመፈፀም ነገ በማለዳ ሀይቅ ከተማ እንገናኝ።የደ...
17/10/2021

ከመቀሌ እስከ ውጫሌ የነበረው ማፈግፈግ ለደሴ፣ኮምቦልቻና ሀይቅ ትልቅ ስጋት ይዞ መጥቷል።ቢሆንም በድል ይጠናቀቃል።በራስ አቅም መሆን ያለበትን ለመፈፀም ነገ በማለዳ ሀይቅ ከተማ እንገናኝ።የደቡብ ወሎና የሰሜን ወሎ ዞን ጥምር ኮሚቴ ባስተላለፈው መልዕክት ሁሉም በጠዋት ሀይቅ እንዲገኝ ጥሪ አቅርቧል።
========================

  : የሱዳን ሉአላዊ ምክርቤት ሊቀመበር ጀነራል አብዱልፈታህ ቡረሀን፣ አሁን ያለው የሱዳን መንግስት ከመበተን በስተቀር ለሱዳን ምንም መፍትሔ የለውም አሉ። ጀነራሉ ዛሬ በሰጡት ሳምንታዊ መግ...
11/10/2021

: የሱዳን ሉአላዊ ምክርቤት ሊቀመበር ጀነራል አብዱልፈታህ ቡረሀን፣ አሁን ያለው የሱዳን መንግስት ከመበተን በስተቀር ለሱዳን ምንም መፍትሔ የለውም አሉ።

ጀነራሉ ዛሬ በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ላይ አሁን ያለው የሱዳን መንግስት ያለው የመጨረሻ እድል መበተን ብቻ ነው አሉ። ሱዳን ውስጥ ከፍተኛ የሆነ አመፅ ከተቀሰቀሰ ዋል አደር ያለ ሲሆን የሀገሪቱ ፈላጭ ቆራጭ ከሆኑት ውስጥ አንዱ ጀነራል ቡረሀን ናቸው። ጀነራሉ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ላይ በሲቪልና በወታደራዊ መንግስቱ የሚመራው የሽግግር ምክርቤት ያዋቀረው የአብደላ ሀምዱቅ መንግስት መፍራረሱን ተናግረዋል። ከዚህ ቡሀላ ማንም በየሰፈሩ እየተደራጀ መንግስት ልሁን ቢለን አንሰማውም፣ ውሻ ስለጮ ዝሆን መውደቅ አይችልም ሲል ቃል በቃል ተናግሯል። ሱዳን አሁን ባለው ደረጃ ሙሉ ለሙሉ የመንግስት አገልግሎት የተቋረጠባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች ይበዛሉ። የቤጃ ጎሳዎች የሀገሪቱ ብቸኛውን ወደብ በመዝጋታቸው አገሪቱ ወደቀውስ ውስጥ ገብታለች።

ሰላም ቅን ለሆኑት የሱዳን ህዝቦች ሁሉ ይሁን !

Via ሱሌማን አብደላ

Address

Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wollo Ethio Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Wollo Ethio Media:

Share