Woreillu press -ወረኢሉ ፕረስ

Woreillu press -ወረኢሉ ፕረስ Environmental blog

25/10/2024

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Tolha Juhar, Zolika Beshir, Endris Mohammed, Mirtnehe Abera, BeEmnet Yetu Liji, መኑ ይኅድገነ ፍቅሮ ለክርስቶስ, Kiel Weled, አርገሸ አርገሸ, Miki Love, የአልማዝ ልጅ ቀዮ

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።መልካም በዓል ወገኖቸ
05/05/2024

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

መልካም በዓል ወገኖቸ

 #ወረኢሉ ዝግጁ #የወረኢሉ አለም አቀፍ ልማት ማህበር ከአሜሪካን ሀገር ከ #17,000 በላይ መጻህፍቶችን አጓጉዞ  #በወረኢሉ #በጃማ እና #በለገሂዳ ወረዳዎች ውስጥ ለሚገኙ የተመረጡ ትምህ...
01/08/2023

#ወረኢሉ ዝግጁ
#የወረኢሉ አለም አቀፍ ልማት ማህበር ከአሜሪካን ሀገር ከ #17,000 በላይ መጻህፍቶችን አጓጉዞ
#በወረኢሉ
#በጃማ እና
#በለገሂዳ ወረዳዎች ውስጥ ለሚገኙ የተመረጡ ትምህርት ቤቶች ድጋፍ ለማድረግ ጥቂት ቀናቶች ብቻ ይቀሩታል። #መጻህፍቶቹን የጫነው ኮንቴነር ከጅቡቲ ተነስቶ ወደ ኮምቦልቻ በመጓዝ ላይ ይገኛል። #ወረኢሉ ረቡዕ ወይም ሃሙስ ይደርሳል ተብሎ ይገመታል። ስለሆነም #የክረምት በጎ-ፈቃደኞች መጻህፍቶቹን በማውረድ እና ስርጭቱን እንድታግዙ በአክብሮት ትጠየቃላችሁ።
ሁላችንም እንተባበር

መረጃውን ያጋራን
ሄኖክ ማስረሻ ነው

ወረዳችን ውስጥ ካሉ ከንቱና ዝርክርክ መስሪያ ቤቶች አንዱ የወረዳችንና የከተማ አስተዳደሩ መብራት ሃይል አገልግሎት ነው።ሰው የማይወጣለት ሴክተርአሁንም ደዩስ በሆነ ሰው እየተመራ ያለአንድም ...
08/07/2023

ወረዳችን ውስጥ ካሉ ከንቱና ዝርክርክ መስሪያ ቤቶች አንዱ የወረዳችንና የከተማ አስተዳደሩ መብራት ሃይል አገልግሎት ነው።

ሰው የማይወጣለት ሴክተር
አሁንም ደዩስ በሆነ ሰው እየተመራ ያለ

አንድም ቀን የመብራት ችግር ሲከሰት ደንገጥ ብሎ ለማስተካከል የማይሞክሩ
ቅድመ ጥንቃቄ የማይወስዱ
ውስጡ በሙስና የተጨማለቀ ሰራተኛ የሚመራው
ብልሽትን በስንት ጉትጎታ ካስተካከሉም ዘላቂ ያልሆነ ከተወሰነ ቀን በኃላ የሚበላሽ ስራ የሚሰራ ሸንጋይ ተቋም።

በነገራችን ላይ ስለዚህ ተቋም ብዙ ሚስጥራቶች እጃችን ላይ አሉ ።

ነገር ግን እንደምክር ይሄንን ካልን ስራቸውን ለማስተካከል የማይሞክሩ ከሆነ ሚስጥራቶችን ለማጋለጥ ወደኃላ እንደማንል ይታወቅ።

አቶ ቀሲስ ተቋሙን እየመሩት ስላልሆነ አረፍ እንድሉ ወይም ቦታ ብትቀይሩላቸው እንላለን።

የተከበራችሁ የከተማ አስተዳደሩና የወረዳችን ህዝቦች
ለዚ ፔጅ አስተያየት ይሁን ተግሳፅ ካላችሁ በደስታ እንቀበላለን።

አላማችን የማይሰሩ ሰዎችን ስራቸውን እንዳስተካክሉ
ጠንካራዎችን እያበረታታን የህዝብ ችግር እንድቀረፍ ጥቆማ መስጠት መሆኑን ልብ ይሏል።

ለምትሰጡን አስተያየት እናመሰግናለን።

የሀዘን መግለጫ የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብዱ ሁሴን ድንገት ማንነታቸው ባልታወቀ  ግለሰቦች በመገደላቸው ከተማ አስተዳደሩ ጥልቅ ሀዘን ተሰምቶናል ።አቶ አብዱ የመ...
04/07/2023

የሀዘን መግለጫ

የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብዱ ሁሴን ድንገት ማንነታቸው ባልታወቀ ግለሰቦች በመገደላቸው ከተማ አስተዳደሩ ጥልቅ ሀዘን ተሰምቶናል ።

አቶ አብዱ የመንግስት የስራ ኃላፊነታቸው ለመወጣት እየሰሩ ባለበት መገደላቸውን እየገለጽን ነፍሳቸውን በጀነት እንዲያሳርፍልንና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ከተማ አስተዳደሩ ይመኛል ።
ዘገባው የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ነው

27/06/2023

ኢድ ሙባረክ
እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላም አደረሰን! አደረሳችሁ!

የተደበቀ እውነትንስ የሚያጋልጥ ?ብላችሁ ጠይቁልኝ
22/06/2023

የተደበቀ እውነትንስ የሚያጋልጥ ?

ብላችሁ ጠይቁልኝ

ልብ ሰባሪ ዜና በወረኢሉበወረኢሉ ከተማ አሰተዳዳር ንግድ ጽ/ቤትና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት በጋራ በመሆን ለወረኢሉ ከተማ አስተዳደር መንግሰት ሰራተኛ የጤፍ ማምጣት ሰራ እየሰሩ መሆኑን የሁለቱ ...
22/06/2023

ልብ ሰባሪ ዜና በወረኢሉ

በወረኢሉ ከተማ አሰተዳዳር ንግድ ጽ/ቤትና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት በጋራ በመሆን ለወረኢሉ ከተማ አስተዳደር መንግሰት ሰራተኛ የጤፍ ማምጣት ሰራ እየሰሩ መሆኑን የሁለቱ ተቋማት ሃላፊዎች ተናግረዋል።
ይሁንና የአንድ ኩንታል ጤፍ ዋጋ ከ8500 -9000 ብር እደሆነ ዋጋው በንግድ ጽ/ቤት ሃላፊው ተነግሯል።

የመንግሰት ስራተኞች መንግሰት ከገበያ ዋጋ በላይ በማቅረብ መንግሰት እራሱ ነጋዴ መሆኑን አሳይቷል ሲሉ ተናግረዋል በዚያውም ላይ አክለው የተናገሩት የኑሮ ወድነቱ ከቀናት ቀናት እየጨመረ መምጣቱንም ጭምር ተናግረዋል ለማሳያ ያክል በወረኢሉ ከተማ የአንድ ኪሎ ሺንኩርት ከአርባ ብር ወደ ሰባ ብር መግባቱንና የኑሮ ወድነቱ በዚህ የሚቀጥል ከሆነ መንግሰት ሰራተኛው አደገኛ የርሃብ ቸነፍር እንደሚያገጥመውም ስጋት አለን ሲሉ ሃሳባቸውን ሰጥተዋል።

ሰበር ዜናወያኔ ስታይል አማረን 😛😥 (እያረሩ መሳቅ አለ ...)ፍርጣጩ የአብይ አህመድ መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ወሎ ዞን ጃማ ደጎሎ ከተማ ጀግናው የአማራ ፋኖ ባደረሰበት ጥቃት መቋቋም ያቀተ...
24/05/2023

ሰበር ዜና

ወያኔ ስታይል አማረን 😛😥 (እያረሩ መሳቅ አለ ...)

ፍርጣጩ የአብይ አህመድ መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ወሎ ዞን ጃማ ደጎሎ ከተማ ጀግናው የአማራ ፋኖ ባደረሰበት ጥቃት መቋቋም ያቀተው የአብይ አህመድ መከላከያ ሰራዊት ወደ ወረኢሉ ከተማ እየሸሸ መሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ። ጀግናው የአማራ ፋኖ የህዝብ አለኝታነቱን እያስመሰከረ መሆኑን የጃማ ደጎሎ ከተማ ያሉ የመረጃ ምንጮች ገልፀዋል።

በነገራችን ላይ አሁን ያለው ዝርክርክ አሰራር በጣም ቢያስቀይመንም

የሀገር መከላከያ የሀገራችን መከታና አለኝታ መሆኑ ጥርጥር የለውም።

ባልሆነ ከንቱ አመራር የሁለት ወንድማማች ደም መፋሰስ ይቁም ባይ ነን።

ድል በሀቅ መንገድ ላይ ላሉ ጀግኖች

መከላከያ ክንዳችን💪
ፋኖም ክንዳችን💪

በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ተለቀቀ!ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ምworeilu press ወረኢሉ ፕረሰትናንት ምሽት ከመኖሪያ ቤቱ በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ የተወሰደው...
21/05/2023

በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ተለቀቀ!

ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም
woreilu press ወረኢሉ ፕረሰ

ትናንት ምሽት ከመኖሪያ ቤቱ በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ የተወሰደው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ ምሽት አምስት ሰዓት ገደማ መለቀቁን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገረ። ተመስገን ለ“ጥያቄ ትፈለጋለህ” በሚል፤ በአዲስ አበባ ሜክሲኮ አደባባይ አካባቢ ወደሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ተወስዶ ለሁለት ሰዓት ገደማ መቆየቱን ገልጿል።

ተመስገን ከዚህ ቀደም በፍርድ ቤት ነጻ በተባለበት ክስ ጋር በተያያዘ፤ ይግባኝ እንደተጠየቀበት ትናንት ምሽት በፖሊስ እንደተገለጸለት አስረድቷል። በዚህ ክስ ይግባኝ የቀረበለት ጠቅላይ ፍርድ ቤት መዝገቡን በሚያዝያ 12፤ 2015 ዘግቶት እንደነበር ተመስገን አስታውሷል። ይህም ሆኖ ጉዳዩ እንደገና በጠቅላይ ፍርድ ቤት እንደሚታይ በፖሊስ እንደተነገረው ተመስገን አክሏል።

ለዚህም ሲባል ሰኞ በአካል የፌደራል ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንዲቀርብ መጠየቁን እና ይህንኑ የሚያረጋግጥ ደብዳቤ ላይ መፈረሙንም ጋዜጠኛው አስታውቋል። ከዚህ ሂደት በኋላ የመታወቂያ ዋስ በማስያዝ ከሁለት ሰዓት እስር በኋላ መለቀቁን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አብራርቷል። በዚህ ጉዳይ ላይ ከፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ በኩል የሚገኘውን መረጃ አካትተን፤ ዝርዝር ዘገባ ለማቅረብ ጥረት እናደርጋለን።

ጋዜጠኛ ተመስገን ትናንት ግንቦት 12፤ 2015 ምሽት በአዲስ አበባ ጃንሜዳ አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ የተወሰደው በሁለት ፒክ አፕ ተጭነው በነበሩ እና የፌደራል ፖሊስ የደንብ ልብስ በለበሱ የጸጥታ ኃይሎች መሆኑን የዓይን እማኞች ቀደም ብለው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አስታውቀው ነበር። እስከ ምሽት ድረስ ከቅርብ ጓደኞቹ ጋር የነበረው ተመስገን፤ ወደ መኖሪያ ቤቱ በሚገባበት ወቅት የግቢ ዙሪያው በጸጥታ ኃይሎች ተከብቦ ማግኘቱንን የዓይን እማኞቹ ተናግረው ነበር።

ዘገባው ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

በወረኢሉ ወረዳ ስር የሚገኙ ሶስቱም ከተሞች የደረጃ ሽግግር አደረጉ=======//=======//========//========መልካም ዜና በወረኢሉ ወረዳ ውስጥ ያሉ ሁሉም ከተሞች የደረጃ ሽግግ...
20/05/2023

በወረኢሉ ወረዳ ስር የሚገኙ ሶስቱም ከተሞች የደረጃ ሽግግር አደረጉ
=======//=======//========//========

መልካም ዜና

በወረኢሉ ወረዳ ውስጥ ያሉ ሁሉም ከተሞች የደረጃ ሽግግር ማድረጋቸውን የወረኢሉ ወረዳ ከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ታምራት አሰፋ ገልጸዋል

ከተሞቹ ለደረጃው የሚመጥነውን መስፈርት አሟልተው በመገኜታቸው ካቤና ሰኞ ገበያ ንኡስ ማዘጋጃ ወደ መሪ ማዘጋጃ እና ቁልምቢ ታዳጊ ከተማ ወደ ንኡስ ማዘጋጃነት የደረጃ ሽግግር ማድረጋቸውን ሃላፊው ተናግረዋል፡፡

ዘገባው :የወረዳው ኮምኒኬሽን ነው

“የዶ/ር አብይ አህመድን የፈጠራ የአሸባሪነት ክስ እንደተለመደው በፍትህ አደባባይ ለመጋፈጥ ወስኛለሁ። በመሆኑም ወደ ሀገር ቤት እሄዳለሁ!” -አቶ ልደቱ አያሌውየአብይ አህመድን የፈጠራ የአሸ...
09/05/2023

“የዶ/ር አብይ አህመድን የፈጠራ የአሸባሪነት ክስ እንደተለመደው በፍትህ አደባባይ ለመጋፈጥ ወስኛለሁ። በመሆኑም ወደ ሀገር ቤት እሄዳለሁ!”

-አቶ ልደቱ አያሌው

የአብይ አህመድን የፈጠራ የአሸባሪነት ክስ እንደተለመደው በፍትህ አደባባይ ለመጋፈጥ ወስኛለሁ። ወደ ሀገር ቤት እሄዳለሁ። ይሄን ውሳኔዬን በአጉል ጀብደኝነት እንዳታዩብኝ። ውድ ህይወቴን እንደሚነጥቁኝ ባውቅም፣ ለለውጥ ዋጋ ከፍዬ ማለፍ እፈልጋለሁ።

ብሄር መርጦ በግፍ ጨፍጭፎ፣ በደውዘር የቀብረው አብይ አህመድ እኔን በአሸባሪነት መፈረጁ የሞራል ዝቅጠቱን ያሳያል። በ31 አመት የፖለቲካ እንቅስቃሴዬ የትጥቅ ትግል እንኳን ደግፌ አላውቅም። ያሳፍራል። አብይ አህመድ በስልጣን እና በገንዘብ የማይደለል የለም ብሎ ያምናል። እኔ እንደዚያ አይደለሁም።

Address

Woreillu
Dessie

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woreillu press -ወረኢሉ ፕረስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share