Gedeo Daily Post

Gedeo Daily Post Gede'i Nagea Samatake Araddani💚💛❤

አገልጋዩ በድንገተኛ አደጋ አረፉ!! በኢትዮጵያ ቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ቀጠና ቃለ ህይወት ቤ/ክ ሰብሳቢ፤ የጌዴኦ ዞን የሃይማኖት ተቋማት ሥራ አስፈፃሚና አባል፤ የይርጋ ጨፌ ቃለ...
13/09/2025

አገልጋዩ በድንገተኛ አደጋ አረፉ!!

በኢትዮጵያ ቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ቀጠና ቃለ ህይወት ቤ/ክ ሰብሳቢ፤ የጌዴኦ ዞን የሃይማኖት ተቋማት ሥራ አስፈፃሚና አባል፤ የይርጋ ጨፌ ቃለ ህይወት አጥቢያዎች ህብረት ዋና ፀሐፊና በተለያዩ የወንጌላዉያን አብያተ ክርስቲያናት በተለያዩ ኃላፊነቶች ሲያገለግሉ የነበሩት አገልጋይ አቶ ዮናስ ቼካ በድንገተኛ አደጋ (ሽንት ቤት ተደርምሶ) ከዚህ ዓለም ድካም ወዳገለገሉት ጌታ ሄደዋል።

ለቤተሰቦቻቸዉ፤ ለወዳጅ ዘመድ እንዲሁም ለመላዉ የቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ምመንና ለይርጋ ጨፌ ከተማ ነዋሪዎች መጽናናትን እንመኛለን!!

08/09/2025
ህዝበ ሙስሊም የመውሊድን በዓል ሲያከብር መልካምነቱን በማሳየትና የተቸገሩትን በመረዳት ሊሆን ይገባል፦ ዶ/ር መስፍን ደምሴ‎‎የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶ/ር መስፍን ደምሴ ለመላው የእስ...
04/09/2025

ህዝበ ሙስሊም የመውሊድን በዓል ሲያከብር መልካምነቱን በማሳየትና የተቸገሩትን በመረዳት ሊሆን ይገባል፦ ዶ/ር መስፍን ደምሴ

‎የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶ/ር መስፍን ደምሴ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1ሺ 500ኛው የመውሊድ በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

‎የነቢዩ መሐመድ መወለድ ለሰው ልጆች መጥፎ ነገርን አርቆ መልካም ነገር እንዲመጣ ያደረገ ነው። ልደታቸውንም ስናከብር መልካምነታቸውን በማሰብ የተቸገሩትን በመረዳት መሆን አለበት።

‎ነብዩ ሙሐመድ የሰው ልጆችን ያለ ዘርና ሃይማኖት ልዩነት የምድር ፍጡራን ሁሉ እኩል የሚያዩ ነበሩ፤ እኛም በዓሉን ስናከብር ያለልዩነትና ያለመከፋፈል በፍቅር ማክበር ይገባናል።

‎አሁን ያለንበት ወቅት ልዩነቶችን ከማጉላት ይልቅ ከምንጊዜውም በተሻለ ሁኔታ ለሀገር ዘላቂ ሰላም፣ አንድነት፣ ልማት፣ ብልጽግና አብሮነትና ነባር የመተሳሰብ እሴቶች መጎልበት በጋራ መስራትን ይጠይቃል።

‎የይህንን በዓል የምናከብረው በቅርቡ በዞናችን በቡለና ራጰ ወረዳዎች የተከሰተው ድንገተኛ የተፈጥሮ አደጋ እጅግ በሚያሳዝንና ከፍተኛ በሆነ የውስጥ ስብራት የፈጠረ ሲሆን ደርሳችሁ ላጽናናችሁ እና ለደገፋችሁ ሁሉ ልባዊ ምስጋና እያቀሪብኩ ድጋፋችሁ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስባለው።

‎በቆየው ኢትዮጵያዊ የመተዛዘን እና የመረዳዳት ባሕል ታላቁን የመውሊድ በዓል፣ ቤታችን ሆነን ስናከብር፣ በተፈጥሮ አደጋ የተጎዱ፣ ቤቶቻቸውን ያጡ፣ ከሚኖሩበት ተፈናቅለው፣ በየቦታው የተጠለሉ ወገኖቻችንን እናስታውስ፡፡

‎በዓሉ የሰላም ና የደስታ እንዲሆን እመኛለው:: እንኳን፣ ለመውሊድ በዓል አደረሰን! አደረሳችሁ!

‎ ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!

የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መንግስቱ ተክሌ ለመላዊ እስልምና እምነት ተከታዮች ለ1500ኛ ጊዜ የሚከበረውን የመውሊድ በዓል አስመልክቶ ያስተላለፉ...
04/09/2025

የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ መንግስቱ ተክሌ ለመላዊ እስልምና እምነት ተከታዮች ለ1500ኛ ጊዜ የሚከበረውን የመውሊድ በዓል አስመልክቶ ያስተላለፉት የመልካም ምኞት መልዕክት

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1500ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም፣አደረሳችሁ አደረሰን።

የመውሊድ በዓል ስናከብር የነብዩ መሐመድን የጥንካሬአቸውን እና የመልካምነታቸውን ፈለግ ለማጠናከር ብርታት እንዲሆነን፤የተሻገሩበት መንገድ ከህይወት ታሪካቸው ለመማር ለትውልድ ብርታት እንዲሆን አስተምህሯቸውን እያስታወስን ራሳችንን እንድናይ ያደርጋል።

በዘንድሮ በመውሊድ በዓል ትዕግስትንና እውቀትን በማጣመር የነቢዩን ቃል በማስታወስ ልናከብር ይገባል።

ፈጣሪ የደከምንበትን ባርኮ የለመንነውን ሰጥቶን በከተማችን የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ የበለጠ እውን እንዲሆን እጅ ለእጅ ተያይዘን የነብዩ አስተምህሮት እንደሚለው ዕውቀትና ትዕግስትን አጣምረን እንጓዛለን።

መላዊ የከተማችን የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ሁሉ የዘንድሮን የመውሊድ በዓል በአላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ በሆነው መልካም ስራ እንደሚያሳልፉ ተስፋ አደርጋለሁ።

በዓሉን ስታከብሩ የተቸገሩትን በመርዳት፣ ማዕድ በማጋራት የወትሮ ባህላችሁን በማጠናከር በዓሉን እንድታከብሩ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።

በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ፣ በዓሉ የሰላም የጤና እና የብልጽግና እንዲሆን እመኛለሁ።

መልካም የመውሊድ በዓል ይሁን!
አቶ መንግስቱ ተክሌ
የዲላ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ

የዲላ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Dilla Town Prosperity party Branch office
አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎች እንዲደርስዎ ትክክለኛ የማህበራዊ ሚዲያ ገጻችንን Like/Share/Follow ያድርጉ።

ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/profile.php?id=100072243172957

በቴሌግራም፦https://t.me/dillatownprosperity

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
28/08/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

Address

15
Dilla

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gedeo Daily Post posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share