BBN

BBN እውነተኛና ተአማኒ መረጃዎችን ለማግኘት ካሰቡ ፔጁን ይቀላቀ?

26/11/2022

ወልድያ ከተማ አዲስ ሹመት አፅድቋል።

ሆኖም የተጭበረበረ የትምህርት ማስረጃ ያላቸው ሹመኞች መኖራቸው እየተገለፀ ነው።

የድርጅቱን ህገ ደንብ በመተላለፍ በኃላፊነት ቦታ ሆነው ሁለተኛ ድግሪ የተማሩ አሉ እየተባለ ነው።

ቲፎዞ የሌላቸው 3 አመራሮች ከሥራ ታግደው ከፊሎቹ ደግሞ እድገት አግኝተዋል የሚሉ አሉ።

09/11/2022

ኦሮሚያ ክልል እየደረሰ ያለው ሰቆቃ በስንዴ የተሸፈነ ይመስለኛል።

ኦነሽሜ እዚሁ ሞጆ አካባቢ መድረሱ እየተነገረ ነው።
አዲስ አበባም ገብተዋል።

20/09/2022
ከልብ የመነጨ ....
15/09/2022

ከልብ የመነጨ ....

10/09/2022

ብሶት የወለደው አበባየሁሽ
(በላይ በቀለ ወያ)
ሀ" ብለን መጣን ፣ "ሀ" ብለን
እስከመቼ እህ "ሆ" እንላለን
"ሀ" ብለን መጣን "ሀ" ብለን
።።።
አበባ አየሁሽ ለምለም ምሩን በተራ
ስልጣን አግኝተን ለምለም እኛ እስንመራ
እንኳንስ ስልጣን ለምለም የለኝም እጣ
እደጅ አድራለሁ ለምለም ኦቨር ስጠጣ
ምጠጣው ደግሞ ፣ አይደለም ጠጅ
ደጅ ያፈራውን ለምለም ብርድ ነው እንጅ😂
።።
አደይ
የኛስ ጉዳይ
ውይ ስቃይ
እቴ አበሳ እቴ አበሳዬ
አዬ እቴ አበሳዬ
ለውጥ ለውጥ ስትለኝ ከርማ
አዬ እቴ አበሳዬ
መብራት ሀይል ሁሌ ጨለማ
አዬ እቴ አበሳዬ
ውሃ ልማት ውሃ ሚያስጠማ
አዬ እቴ አበሳዬ
ይሁን ኑሮ ከተባለማ
አዬ እቴ አበሳዬ
።።።
እዬዬ
እህ
ሁሌ እዬዬ
ሲዘርፉኝ ሲቀሙኝ ፣ ጊዜ ይፍረድ ብዬ
ሀገር ያህል ነገር ፣ ከመንደር ላይ ጥዬ
በገዛ ፍርሃቴ ፣ ቀረሁ ተቃጥዬ

ከብረው ይቆዩን ከብረው
የሚሰብሩንን ሰብረው
የሚያፍኑንን አስረው
ከብረው ይቆዩን ከብረው

25/07/2022

ኢትዮ ኤፍ ኤም እንደዘገበው

የኢትዮጵያ ደምና ቲሹ ባንክ አገልግሎት ያለኝ የደም ክምችት ለአምስት ቀናት ብቻ የሚሆን ነዉ ብሏል፡፡
ቴዲ አፍሮን በከለከለ ሳምንት ደም የለም

23/07/2022

አሁን አንድ ቪዲዮ እያየሁ ነበር

ልጅቷ ስቅስቅ ብላ እያለቀሰች ነው ቃለ መጠይቁን ያደረገችው።

አዲስ አበባ የምትኖር አማራ መሆኗን አወራች። የትግራይ ተወላጅ ፍቅረኛ እንደነበራት፤ ጦርነቱ ሊጀመር ወራት ሲቀሩ ወደመቀሌ እንደሄደ፣ ወደአዲስ አበባ የማይመለስ ከሆነ እሷ መቀሌ እንደምትሄድ በተደጋጋሚ በስልክ መጠየቋን በስቅስቅታ አጅባ አወራች።
የልጁ አባት ስልክ ደወሉ፤ ከዚህ በኋላ አትደውይ አታውቂውም እርሽው አሉኝ አለች።
ፍቅረኛየም ከአማራ የተወለደ ልጅ እንዲኖረኝ ስለማልፈልግ ከአንቺ ጋር መቀጠል አልፈልግም ብሎ እንደተሰናበታትና ከጥቂት ቀናት በኋላ ትግሉን መቀላቀሉን በፌስቡክ ገፁ መለጠፉን ማየቷን አነሳች።
ከ1ወር ከ17 ቀን በኋላ ብላ እየየየዋን ይቅርታ ብላ መሰዋቱን ከወንድሞቹ ፌስቡክ አየሁ አለች።

Address

Dilla

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when BBN posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share