Visit Dire

Visit Dire ድሬ የፍቅር ሀገር

14/04/2026


😂የአምባገነኑ እጩ "ሁለት ገፅታ" በማስረጃ! 📹👇

ሰውዬው ግን ጤነኛ ነው? የድሬዳዋ ፖሊስ ብሎክ አደረገኝ ብሎ ፌስቡክ ላይ ሲያለቃቅስ ውሎ፣ እሱ ግን የብሎክ ፋብሪካ ከፍቷል።😂

ሲጀመር ፌስቡክ ላይ እኔን ብሎክ ካደረገኝ ቆየ፣ ማንም ሰው ትንሽ ትችት ካቀረበበት በፍጥነት ነው ብሎክ የሚያደርግ ግብዝ ሰው ነው። ይህንን አስቂኝና ግብዝነቱን የሚያሳየውን ማስረጃ ከታች በቪዲዮው አለሊችሁ።

👉ታሪኩ እንዲህ ነው…
ትላንት ምሽት ቲክቶክ ላይ ገብቶ "ፖሊስ ብሎክ አደረገኝ" እያለ ሲያማርር... "አንተስ እኔን ለምን ብሎክ አደረግከኝ?" ብቻ ስላልኩት ከጀት በፈጠነ ፍጥነት ብሎክ አረግኝ…እኔም ምኔ ሞኝ ነው ብሎክ እንደሚያደርገኝ ስላወኩ እየቀዳሁት ነበር…😂 (ቪዲዮውን ተመልከቱት)

👉አንድ ምርጫ ለመመረጥ የሚወዳደር እጩ ይቅርና ተራ ሰው እንዲህ አያደርግም። ገና ሳይመረጥ ድምጽ የሚሰጠውን ህዝብ አፍ የሚያፍን ፣ ነገ ስልጣን ቢይዝ ምን ሊያደርገን ነው? ስማ አንተ የበታችነት በሽታ ያለብህ ዶክተር መጀመሪያ ባህሪህን አስተካክል አንተ የድሬዳዋን ፖሊስ ለመውቀስ ቅንጣት ያህሎ ሞራል የለህም።

😂ብሎክ እያረጉ ምርጫ ማሸነፍ አይደለም መወዳደር እራሱ ይከብዳል፣ ትንሽ ሞራል ካለህ እራስህን ከምርጫው አግልል። 🤦‍♂️💨

በጎሮ ጉቱ ወረዳ በትራፊክ አደጋ የ9 ሰዎች ሕይወት አለፈ‎ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጎሮ ጉቱ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አልፏል።አደጋው ከአዲስ አበባ ወ...
13/04/2026

በጎሮ ጉቱ ወረዳ በትራፊክ አደጋ የ9 ሰዎች ሕይወት አለፈ

‎ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጎሮ ጉቱ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አልፏል።

አደጋው ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ ከተማ ሲጓዝ በነበረ ኮንቴነር የጫነ ተሽከርካሪ ላይ መድረሱን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡

በተከሰተው አደጋም እስካሁን የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ማለፉ ነው የተገለጸው፡፡

FBC

10/04/2026

Dire

ታማኝነት በተግባር!​በድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት አባል፣ በመደበኛ ስራቸው ላይ እያሉ በተሽከርካሪ ውስጥ ተጥሎ የተገኘንና ዋጋው 120 ሺህ ብር የሚገመት iP...
08/04/2026

ታማኝነት በተግባር!

​በድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት አባል፣ በመደበኛ ስራቸው ላይ እያሉ በተሽከርካሪ ውስጥ ተጥሎ የተገኘንና ዋጋው 120 ሺህ ብር የሚገመት iPhone ስልክ ለባለቤቱ መለሰ።

​አባሉ ስልኩን እንዳገኙ ተሽከርካሪውን ባለበት በማዘግየት ባለቤቱን ለማግኘት ጥረት ያደረጉ ሲሆን፣ ስልኩ የጠፋባቸውን ወ/ሮ እስከዳር ዮሃንስን በማግኘት በታማኝነት አስረክበዋል። ወ/ሮ እስከዳርም በፖሊስ አባሉ ተግባር መደሰታቸውንና ምስጋናቸውን ገልጸዋል።

04/04/2026

"ብዙ ሰው ይመሰክርላቸዋል"

🏟️ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የድሬዳዋ ስታዲየም የወደፊት እጣ ፈንታ!​የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዘንድሮ ወደ ድሬዳዋ ባይመጣም፣ በቀጣዩ የውድድር ዓመት ግን የከተማዋ ስታዲየም በርካታ ጨ...
01/04/2026

🏟️ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የድሬዳዋ ስታዲየም የወደፊት እጣ ፈንታ!

​የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዘንድሮ ወደ ድሬዳዋ ባይመጣም፣ በቀጣዩ የውድድር ዓመት ግን የከተማዋ ስታዲየም በርካታ ጨዋታዎችን ሊያስተናግድ እንደሚችል ተጠቆመ።⚽

የሊግ አክሲዮን ማህበሩ በቀጣይ ዓመት ውድድሩን በ"ሜዳዬ እና በሜዳው" (Home and Away) ለማድረግ ጥናት እያደረገ ይገኛል።

በዚሁ ጥናት መሰረት፣ የራሳቸው ሜዳ የሌላቸው ክለቦች ከድሬዳዋ ከነማ በመቀጠል የድሬዳዋ ስታዲየምን እንደ መነሻ ሜዳቸው ሊጠቀሙበት ይችላሉ። ይህ ከሆነ ስታዲየሙ እጅግ በርካታ ጨዋታዎችን ያስተናግዳል።

​🗣️ ይህንን የተናገሩት 👇
የሊግ አክሲዮን ማህበሩ ስራ አስፈጻሚ መቶ አለቃ ፍቃዱ ማሞ ናቸው።

የድሬዳዋ የትራፊክ ፖሊስ አባላት ዩኒፎርማቸውን ለብሰው፣ ፈገግታቸውን አክለው ከምዕመናን ጋር ማዕድ ተጋርተዋል። የሕዝብ ደህንነትን ከመጠበቅ ባለፈ፣ በደስታም ሆነ በችግር ጊዜ ከማኅበረሰቡ ጎ...
24/03/2026

የድሬዳዋ የትራፊክ ፖሊስ አባላት ዩኒፎርማቸውን ለብሰው፣ ፈገግታቸውን አክለው ከምዕመናን ጋር ማዕድ ተጋርተዋል።

የሕዝብ ደህንነትን ከመጠበቅ ባለፈ፣ በደስታም ሆነ በችግር ጊዜ ከማኅበረሰቡ ጎን መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።

​ሌሎችም ሊማሩበት የሚገባ ድንቅ ተግባር! 👏

20/03/2026

"የድሬዳዋን ፖሊስ አመራሮችና አባላትን በክፉ ዓይን የሚመለከት አካል፣ ጠላትነቱ ከጠቅላላው የድሬዳዋ ሕዝብ ጋር እንደሆነ ሊያውቀው ይገባል።"

በርቱ ጀግኖቻችን

እናቱን ጡት በመቁረጥ😭😭በገዛ እናቱና እህቱ ላይ አሰቃቂ ግድያ የፈጸመው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ​በሀዲያ ዞን ምዕራብ ባዳዋቾ ወረዳ፣ የገዛ ወላጅ እናቱን ጡት በመቁረጥ እና እህቱን በ...
20/03/2026

እናቱን ጡት በመቁረጥ😭😭

በገዛ እናቱና እህቱ ላይ አሰቃቂ ግድያ የፈጸመው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ

​በሀዲያ ዞን ምዕራብ ባዳዋቾ ወረዳ፣ የገዛ ወላጅ እናቱን ጡት በመቁረጥ እና እህቱን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወሰነ።

​እንደ ስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ መረጃ፣ ተከሳሹ ሰንበቱ መንገሻ የተባለ ግለሰብ ወንጀሉን የፈጸመው ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም በገርቦ ቀበሌ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ነው። ግድያው የተፈጸመው አስቀድሞ በታቀደ እና እጅግ ዘግናኝ በሆነ መልኩ እንደነበር በችሎቱ ተገልጿል፦

ተከሳሹ የመኖሪያ ቤቱን በሮች በመቆለፍ እናቱን በሳንጃ አንገታቸውን፣ ሆዳቸውንና ጀርባታቸውን በመውጋት እንዲሁም ጡታቸውን በመቁረጥ ለህልፈት ዳርጓቸዋል።

ድርጊቱን አይታ የጮኸችውን እህቱን በተመሳሳይ ስለታም መሣሪያ ልቧንና ጀርባዋን በመውጋት ወዲያውኑ ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርጓል።

​የምዕራብ ባዳዋቾ ወረዳ ፖሊስ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር ተከሳሹን በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ ጉዳዩ ለሕግ ቀርቧል። በችሎቱ ሂደት ላይ ዓቃቤ ሕግ የሐኪም የአስከሬን ምርመራ ውጤት እና ሌሎች ማስረጃዎች አቅርቧል።

ተከሳሹ ለፍርድ ቤት የሰጠው የእምነት ቃል ወንጀሉን መፈፀሙን አምነዋል ።

የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሾኔ ምድብ ችሎት በመጋቢት 10 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት፤ ተከሳሹ የፈጸመው ድርጊት እጅግ አሰቃቂ መሆኑን በማረጋገጥ በ1997 የወጣውን የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 539(1-ሀ) መሠረት በሞት እንዲቀጣ በሙሉ ድምፅ ወስኗል።

መረጃው 👇
https://www.facebook.com/share/p/1bwEDsyZAn/

ሰማዩ ቢያዘንብ ዝናብ ቢወርድም፣የጀግናው ፖሊስ ቃል አይታጠፍም።ብርዱን ተቋቁሞ ደህንነት ሲጠብቅ፣የፖሊስ ሰብዓዊነት ዛሬም ሆነ ድንቅ። ​ስግደቱ በመስጊድ ቢሆንም በዝናብ፣አልቀነሰም እንጂ የፖ...
20/03/2026

ሰማዩ ቢያዘንብ ዝናብ ቢወርድም፣
የጀግናው ፖሊስ ቃል አይታጠፍም።
ብርዱን ተቋቁሞ ደህንነት ሲጠብቅ፣
የፖሊስ ሰብዓዊነት ዛሬም ሆነ ድንቅ።

​ስግደቱ በመስጊድ ቢሆንም በዝናብ፣
አልቀነሰም እንጂ የፖሊስ አጋዥነት።
የድሬዳዋ ኩራት የሰላም አርበኛ፣
ለወገኑ ቆሟል ሳይተኛ በሰላም።

የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መጨመርም ሆነ ተከራይን ከቤት ማስወጣት የተከለከለ  መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር አስታወቀ፦1ኛ. ለቀጣዮቹ  6 ወራት  የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር የተከለከለ ነ...
18/03/2026

የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መጨመርም ሆነ ተከራይን ከቤት ማስወጣት የተከለከለ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር አስታወቀ፦

1ኛ. ለቀጣዮቹ 6 ወራት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር የተከለከለ ነው።

የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ መጨመርም ሆነ ተከራይን ከቤት ማስወጣት በ2016 በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ከወጡ አዋጆች አንዱ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320 መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህ አዋጅ ዋነኛ አላማው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋ ከጊዜ ወደጊዜ እየናረ እና በዜጎች ኑሮ ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ ነው።

ስለሆነም አሁን እየታየ ያለውን አላግባብ የሆነ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ ለመገደብ የነዋሪውን ቅሬታ ምላሽ ለመስጠት የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ በቀን 8/7/2018 ባደረገው መደበኛ ስብሰባው የቤት ኪራይ ጭማሪ በሚያደርጉ አከራዮች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እና ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፋል

የኑሮ ውድነቱ በመካከለኛ ምስራቅ በተፈጠረ ቀውስ በአብዛኛው አሳማኝ እና ምንም አይነት ኢኮኖሚያዊ ምክንያት የሌለው በሰው ሰራሽ ምክንያቶች የተፈጠረ ነው፡፡ የኑሮ ውድነቱም የአስተዳደሩ ነዋሪ ለከፍተኛ ችግር በመዳረጉ የተዋቀረው ግብረሃይል የተሰጠውን ሙሉ ኃላፊነት በመውሰድ ወደ ስራ ገብቷል።
ይህም ወቅታዊ ሁኔታን በመጠቀም አላግብ ለመክበር የሚደረግ ድሬዳዋዊ አብሮነትና ጨዋነትንና መተሳሰብ ጋር በፍፁም የሚቃረን ተግባር ነው።

2ኛ. በተለያዩ ምርቶች ሰው ሰራሽ እጥረት በመፍጠር የዋጋ ጭማሪ በሚያባብሱ ሕገወጥ ነጋዴዎች ላይ የተጀመረው ህግን የማስከበር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል።

የዋጋ ጭማሪውንና ህገወጥ ንግድን የሚቆጣጠር ግብረኃይል ተቋቁሞ ወደ ስራ ገብቷል።ያለአግባብ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ ግብረ ሀይሉ የማያዳግም እርምጃ እንዲወስዱም ኃላፊነት ተሰቶታል።

በግብይት ቦታዎች በምግብ ፍጆታዎች ላይ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ እንዲኖር በሚያደርጉ ደላሎች ላይም እርምጃ ይወሰዳል ።

3ኛ. የውሀ አምራች ፋብሪካዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በራሳቸው ተነሳሽነት ባደረጉት ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ አስተዳደሩ በወሰደው አስተዳደራዊ እርምጃ የፋብሪካው ባለቤቶች ይህንን አላግባብ የጨመሩት ጭማሪ ስህተት መሆኑን አምነው አስተዳደሩን ይቅርታ በመጠየቃቸው ይቅር ተብለው ቀድሞ ወደ ነበረው ዋጋ መልሰው እንዲሸጡ ቢደረግም አሁንም አንዳንድ የውሃ ፋብሪካ ድርጅቶች ከድርጊታቸው ባለመቆጠብ ዋጋ ጨምረው የሚሸጡ ከሆነና ከተደረሰባቸው በእነዚህ የውሀ ፋብሪካዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ ይወሰዳል ።

ዋጋ ጭማሪ ማድረግ ካስፈለገ አስፈላጊነቱ በጥናት ተረጋግጦና ማህበረሰቡ ያማከለ ተደርጎ ፍትሀዊ በሆነ መልኩ በህግ አግባብ ይፋ የማድረግ ስራ እንደሚሰራ አመላክተዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

Address

Lagaharree
Dire Dawa

Telephone

+252113334

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Visit Dire posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share