Dire Tv - አማርኛ

Dire Tv - አማርኛ This is the official Dire Dawa Administration Mass Media Enterprise (Dire Tv - አማርኛ) page - where you can get all the latest news in Amharic.

You can follow us Here.

 #ዜና | የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ለፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የድሬዳዋ ሁሉአቀፍ ማረሚያና ማረፊያ ቤት 500 ያህል መፃህፍት ድጋፍ አበረከተ ።  | ታህሳስ ...
11/12/2025

#ዜና | የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ለፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የድሬዳዋ ሁሉአቀፍ ማረሚያና ማረፊያ ቤት 500 ያህል መፃህፍት ድጋፍ አበረከተ ።

| ታህሳስ 02 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ጋር በመተባበር የንባብ ቀን ፣ ስልጠና እና የፓናል ውይይት በድሬዳዋ ሁሉአቀፍ ማረሚያና ማረፊያ ቤት ተካሂዷል ።

“የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት" በሚል መሪ ቃል በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የድሬዳዋ ሁሉአቀፍ ማረሚያና ማረፊያ ቤት የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት የተዘጋጀ የንባብ ቀን ፣ ስልጠና እና የፓናል ውይይት ተካሂዷል ።

የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የማረም ማነፅና ተሀድሶ ልማት ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል ሉባባ ጀማል በወቅቱ እንደገለፁት ማረሚያ ቤት ዘርፈ ብዙ ስራዎች የሚሰራበት ማዕከል እንደሆነ ገልፀዉ ታራሚዎች የፅሞና ጊዜ በመዉሰድ መፅሀፍትን ማንበባቸው ያለዉን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ገልፀዋል።

ኮሚሽነር ሉባባ አከሰለውም ታራሚዎች እራሳቸዉን በእዉቀት ማዳበር እንዳለባቸው አፅዕኖት ሰተዋል፤የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎትንም ላደረጉት ድጋፍም አመስግነዋል ።

በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የድሬዳዋ ሁሉአቀፍ ማረሚያና ማረፊያ ማዕከል አዛዥ ረዳት ኮሚሽነር ሙላት ጫንያለዉ በበኩላቸው አገልግሎቱ በማረሚያ ቤቱ የሚገኙ የህግ ታራሚዎችን የንባብ ባህል ለማሳደግና ታርመው ከህብረተሰብ ጋር ሲቀላቀሉ አምራች ዜጎች ይሆኑ ዘንድ የንባብ ልምዳቸውን እንዲያጎለብቱ ላደረገው ድጋፍ በተቋሙ ስም አመስግነዋል።

ኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ አባተ ካሳዉ በበኩላቸው ማረሚያ ቤት ታራሚዎች የሚታነፁበት እና የሚታረሙበት ለቀጣይ ህይወታቸው የሚዘጋጁበት እራሳቸዉን አስተምረዉ አብቅተዉ የሚወጡበት ማዕከል መሆኑን ገልፀዉ መድረኩ የንባብ ባህልን በማዳበር እራሳቸዉን በእዉቀት እንዲያዳብሩ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል ።

"ማረሚያ ቤትን በመፃህፍት ማደራጀት እና ንባብ" በሚል መሪ ሀሳብ ገለፃ በደራሲ ሊዲያ ተስፋዬ እንዲሁ ተሞክሯቸዉን ደግሞ ደራሲና ጋዜጠኛ ኢሳያስ ሆርዶፋ ለታራማዎች አጋርተዋል ።

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ለድሬዳዋ ሁሉአቀፍ ማረሚያና ማረፊያ ቤት 500 ያህል መፅሐፎችን ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ይህም በገንዘብ ሲተመን ከሁለት መቶ ሰላሳ ሺ ብር በላይ እንደሚሆን ተገልጿል።

በተያያዘም በመድረኩ ወጣቱ ደራሲ ሚካኤል ካሳሁንም የታራሚዎችን ስብዕና ይቀይራል በማለት በስነ አእምሮ ዙሪያ የፃፈዉን ሀያ ሁለት መፃህፍት በስጦታ አበርክቷል ።

በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከድሬዳዋ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር " የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት በሚል መሪ ቃል በድሬዳዋ ሳቢያን 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የተዘጋጀ የንባብ ክበባት ምስረታ ላይ በመገኘት ለተማሪዎች ለመማር ማስተማር ምቹ የሆኑ ወደ ሁለት መቶ ሀያ ገደማ መፃህፍትችን ለትምህርት ቤቱ ድጋፍ አድርገዋል ።

አገልግሎቱ በተጨማሪም ለድሬዳዋ አስተዳደር እምርታ ቤተ መፅሀፍት ስድስ መቶ ስልሳ ስምንት መፃህፍትን በስጦታ አበርክተዋል። ድጋፍ የተደረገላቸዉ አካላት ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋናቸዉን አቅርበዋል ።

ሰላም ይኄይስ
ምስል፦ሀየሎም አለበል

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
👉በቴሌግራም ፦
https://t.me/+6C5aVWGZeL4wOWM0

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

11/12/2025

ነገ አርብ ማታ ከ1 ሰአት ዜና በኋላ ይጠብቁን

 #ዜና | 4ተኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ከወላጆችና አሳዳጊዎች ባሻገር የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ዘመቻው የተሳካ እንዲሆን ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን ይወጡ ዘንድ የድሬዳ...
11/12/2025

#ዜና | 4ተኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ከወላጆችና አሳዳጊዎች ባሻገር የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ዘመቻው የተሳካ እንዲሆን ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን ይወጡ ዘንድ የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ጥሪ አቀረበ።

| ታህሳስ 02 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ 4ኛው ዙርን የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻን አስመልክቶ ለባለድርሻ አካላት የዘመቻ ንቅናቄ መድረክ ተካሂዳል ።

ፖሊዮ በሀገራችን ለበርካታ ህፃናት የአካል ጉዳትና ሞት ምክንያት ከሆኑት በሽታዎች አንዱ በመሆኑ በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በዘመቻ መልክ የሚሰጠውን ክትባት በአግባቡ ተደራሽ ለማድረግ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ሚና የጎላ መሆኑን በመድረኩ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ ር ፅገሬዳ ክፍሌ ገልፀዋል።

ሀላፊዋ አክለውም የ4ተኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ የሚሰጠው ከ5 አመት በታች ለሆኑ ህፃናት ከታህሳስ 3 እስከ 6፥2018 ዓ ም ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ 5.4 ሚሊዮን ያህል ህፃናት በዘመቻው እንደሚከተቡና በአስተዳደሩ ደግሞ 109 ሺህ ያህል ህፃናት በዘመቻው እንደሚከተቡ ገልፀዋል።

ዶ/ር ፅገሬዳ አያይዘው እንዳስታወቁት በዘመቻው ከዚህ ቀደም በ2ኛው እና በ3ዙር ክትባት ዘመቻ ያልተከቡ ህፃናት በ4ተኛው ዙር ክትባት ዘመቻ በከተማና በገጠር ጤና ተቋማትና ቤት ለቤት ት/ቤት በባለሞያዎች እንደሚሰጥ ጠቅሰው ከዘመቻው ባሻገርም በሰሞኑ የተከሰቱ ተያያዥ ትኩሳትና የደንጊና የወባ ጨምሮ ለህፃናት ልየታ የሚደረግ መሆኑን አስታውቀዋል።

በመጨረሻም ሀላፊዋ 4ኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ከወላጆችና አሳዳጊዎች ባሻገር የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ሚና የጎላ በመሆኑ ዘመቻው እንዲሳካ ሁሉም ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል ።

በመድረኩ ላይ ስለ በሽታው ምንነት መንስኤ መከላከያ መንገዶቹ ያተኮረ ፅሁፍ የቀረበ ሲሆን በቀረበው ፅሁፍም ከሚመለከታቸው አካላት ውይይት አድርገዋል።

በውይይት መድረኩ የአስተዳደሩ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባላት፣የሴቶች፣ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ተወካዮች፣ጤና ቢሮ አመራሮችና ባለሞያዎች እንዲሁም ሌሎችም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።

ሣራ አብዱራሂም
ካሜራ፦ እስራኤል ሙሉ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
👉በቴሌግራም ፦
https://t.me/+6C5aVWGZeL4wOWM0

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር እና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል የፍትህ ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች በድሬዳዋ አስተዳደር አቀባበል ተደረገላቸው።  | ታህሳስ 02 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳ...
11/12/2025

#ዜና | የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር እና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል የፍትህ ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች በድሬዳዋ አስተዳደር አቀባበል ተደረገላቸው።

| ታህሳስ 02 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር እና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል የፍትህ ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች ድሬዳዋ ገብተዋል።

ዛሬ ድሬዳዋ ከገቡት የፍትህ ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች መካከል የአዲስአበባ ከተማ መስተዳድር ይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ተስፋዬ መለሰ እና የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ኩምሳ አራርሳ ይገኙበታል።

ከአዲስ አበባ መስተዳድር እና ከኦሮሚያ ክልል የተውጣጣው የፍትህ ዘርፍ ልዑክ ድሬዳዋ ዓለም ዓቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ የአስተዳደሩ ይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት ፕሬዚዳንት ነጂብ ኢድሪስ እና የአስተዳደሩ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሀመድን ጨምሮ ሌሎች የፍትህ ዘርፉ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ልዑካን ቡድኑ በድሬደዋ በሚኖረው ቆይታ በድሬዳዋ አስተዳደር የፍትህ ስርዓት ሪፎርምና በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ዙሪያ ወንጀልን ለመከላከል እየተወሰዱ ስላሉ እርምጃዎች ተሞክሮ እና ልምድ ልውውጥ ለማድረግ እንደሆነ ታውቋል።

ጁሊየት ተድላ
ምስል፦ምንተስኖት ደረጀ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
👉በቴሌግራም ፦
https://t.me/+6C5aVWGZeL4wOWM0

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | የፊታችን ታህሳስ 19 የሚከበረውን የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓልን አከባበር ድሬዳዋ ለሚገኙ እንግዶች የሚደረግን መስተንግዶ አስመልክቶ በቅድመ ዝግጅቱ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር...
11/12/2025

#ዜና | የፊታችን ታህሳስ 19 የሚከበረውን የቁልቢ ገብርኤል የንግስ በዓልን አከባበር ድሬዳዋ ለሚገኙ እንግዶች የሚደረግን መስተንግዶ አስመልክቶ በቅድመ ዝግጅቱ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ።

| ታህሳስ 02 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በበዓሉ ላይ ለሚታደሙ ምዕመናን ነዋሪው በተለመደው የድሬዳዋ የእንግዳ ተቀባይነት እሴት መስተንግዶ ያደርግ ዘንድ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ ጥሪ አቅርበዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት የቁልቢ ገብርኤል የንግስ ክብረ በዓልን አስመልክቶ ለንግስ ወደ ከተማዋ የሚገቡ እንግዶችን ለመቀበል የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮችን አሰመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄዷል።

በውይይት መድረኩም የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ በወቅቱ እንደገለጹት ወደ አስተዳደሩ የሚገቡ እንግዶችን ለመቀበል የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በተለይም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የትራንስፖርት፣ ሆቴሎች፣ የንግድ ድርጅቶች እንዲሁም ጸጥታውን በማስጠበቅ በዓሉን በደማቅ ሁኔታ በአንድነት ለማክበር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ወደ ድሬዳዋን ለሚገቡ እንግዶች ከተማዋን በማስተዋወቅ ረገድ በአስተዳደሩ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎችን በአግባቡ በማስጎብኘትና መረጃ በመስጠት የከተማዋን ገጽታ መገንባት እንደሚገባ የተናገሩት ደግሞ የአስተዳደሩ የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንደሰን አባይ ናቸው።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በወቅቱ እንደገለፁት ወደ አስተዳደሩ የሚመጡትን እንግዶች በከተማዋ ለሚኖራቸው ቆይታ ተገቢውን አገልግሎት እና መስተንግዶ እንዲያገኙ ለማድረግ እየተደረገ ያለውን ጥረት አድንቀው እንግዶቹን ለመቀበል ዝግጁ እና ተባባሪ እንደሆኑ አረጋግጠዋል።

ስንታየሁ አበራ
ምስል፦ናትናኤል ገ/ዮሐንስ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
👉በቴሌግራም ፦
https://t.me/+6C5aVWGZeL4wOWM0

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | የሐረርጌ ቡናን በዓለም ገበያ ጥራትና ተወዳጅነቱን ለማላቅ የመልከአ ምድር አመላካች ሥራ ሊሰራ ነው   | ታህሳስ 02 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋየኢትዮጵያ አምሯዊ ንብረት ባለስል...
11/12/2025

#ዜና | የሐረርጌ ቡናን በዓለም ገበያ ጥራትና ተወዳጅነቱን ለማላቅ የመልከአ ምድር አመላካች ሥራ ሊሰራ ነው

| ታህሳስ 02 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የኢትዮጵያ አምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የቡናን የንግድ ምልክት ክፍተቶች ለመሙላት የሚያስችል በመልከአ ምድር አመላካች ምንነትና አካባቢው ላሉ ምርቶች ባለው ጠቀሜታ ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል።

በኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የማህበረሰብ እውቀት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ታደሰ ወርቁ በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ወደ ውጭ በምትልከው የቡና ምርት ከተለያዩ የአለም ቡና ላኪ ሀገራት የሚገጥማትን ከፍተኛ ውድድር ለማሸነፍ የቡና ጥራትና ተወዳጅነትን ለመጨመር ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው።

በተለይም የቡና ምርታችንን ካሉት የጥራት መጠበቂያ አማራጮች መካከል አንዱ የሆነውን የመልከአ ምድር አመላካች ሥራ በመስራት እና የንግድ ምልክት ክፍተቶችን በመሙላት የቡናን ጥራት ጣዕም በመጨመር ተወዳጅነቱን ማላቅ አለብን ብለዋል።

ለዚህም ደግሞ በዘርፉ ከተሰማሩ ባለሞያዎችና ተመራማሪዎች ጋር በጋራ መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።

በተለይ በአለም ከሚወደደው ቡናችን የሐረርጌ ቡና ተጠቃሽ መሆኑን አዉስተው የሀረርጌ ዙሪያውና አካባቢው የቡናን ተጨማሪ እሴት የሚጨምሩ የመልከአ ምድር አመላካች ሁኔታው በደንብ መታየት እና መጠናት እንዳለበት ጨምረው ገልጸዋል።

በመድረኩ የመቻራ ግብርና ምርምር በቡና ጣዕም እና ጥራት ዙሪያ የተጠና ጥናት ተሞክሮ እንዲሁም የአእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን የቡናን ጥራት ይበልጥ ለመጠበቅ ያለውን አማራጭ የዳሰሱ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በግንዛቤ ማስጨበጫው የተሳተፉት የዘርፉ ባለሞያዎች እና የምርምር ተቋማት ተወካዮች በበኩላቸው የኢትዮጵያ የቡና ጥራትና ተወዳጅነትን በመጨመር በዓለም ተወዳዳሪነታችንን ለማላቅ ሰፋ ያለ የጥናትና ምርምር ስራ እንደሚያስፈልግ ነው የገለፁት።

ኢትዮጵያም ለውጭ ገበያ በምትልከው የቡና ምርት ላይ የተለያዩ እሴቶችን በመጨመር ተፈላጊና ተወዳጅነትን በማሳደግ ዓለም በደረሰበት ደረጃ ልክ መሰራት እንደሚገባው አክለው ጠቁመዋል።

በመድረኩ ከምስራቅ እና ምዕራብ ሐረርጌ እንዲሁም ከግብርና ቢሮ፣ ከቡናና ሻይ ባለስልጣን ፣ ከድሬዳዋ እና ከሐሮመያ ዩኒቨርስቲ የተወጣጡ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

ነጃት ተገኔ
ምስል ፦ አዳነ ለማ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
👉በቴሌግራም ፦
https://t.me/+6C5aVWGZeL4wOWM0

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | በአስተዳደሩ የገጠር ቀበሌዎች የተረጂነት አስተሳሰብን በማስወገድ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተሰሩ የሚገኙ የልማት ስራዎች አበረታች ውጤት እያስገኙ መሆኑ ተገለ...
11/12/2025

#ዜና | በአስተዳደሩ የገጠር ቀበሌዎች የተረጂነት አስተሳሰብን በማስወገድ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተሰሩ የሚገኙ የልማት ስራዎች አበረታች ውጤት እያስገኙ መሆኑ ተገለፀ።

| ታህሳስ 02 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የምርታማ ሴፋቲኔት መርሀግብር ተጠቃሚዎች ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር የሚያስችሉ የመስኖ ሞተሮች ፣ምርጥ ዘር እና የግብርና አልባሳት ድጋፍ ተደርጓል።

1997 በሀገራችን ዝናብ አጥር በሆኑ አካባቢዎች የሚኖሩ አርሶ እና አርብቶ አደሮች ከተረጂነት በመውጣት የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡ የተጀመረው ልማታዊ የሴፍቲኔት ፕሮግራም በአሁን ወቅት በ5 ምእራፎች አሰራሮችን የማጠናከር እና የማጥራት እንዲሁም በማስመርቅ ከእርዳታ የማላቀቅ ስራ እየተከናወነበት ይገኛል።

በዚህ ምእራፍ የገጠር ምርታማ የሴፍትኔት ፕሮግራም ተጠቃሚዎች በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡ የውሃ መሳቢያ ሞተሮች ፣ምርጥ ዘር እና የግብርና የስራ ቦታ ድህነትን መጠበቂያ አለባሳት ድጋፍ ተደገርጓል።

በአስተዳደሩ ዋሂል ክላስተር ሁላሁሉል ቀበሌ ነዋሪ እና አመራር የሆኑት አቶ ቃሲም ጣሂር የምርታማ ሴፊትኔት ፕሮግራም በመጠቀም በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ እየሰሩ መሆኑን ገልፀው የተደረገው ድጋፍ ከተረጂነት በመውጣት ወደተሻለ የኑሮ ምእራፍ ለመሸጋገር ከፍ ያለ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል።

የአስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በአስተዳደሩ የገጠር ክላስተሮች ስር የሰደደ የምግብ ዋስትና ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች ባጭር ጊዜ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡ የምርታማ ሴፍቲኔት ፕሮግራሞች እየተተገበሩ ይገኛሉ ብለዋል።

በፕሮግራሙ በአስተዳደሩ የመልማት አቅም ባለቸው አካባቢዎች የሚገኙ የጤፍ የእርሻ መሬቶችን ወደ ስራ በማስገባት እና የተፈጥሮ ጥበቃ ስራ ተግባራዊ በማደዘድረግ አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን የገለፁት ከንቲባው አረሶ አደሮች የተደረገላቸውን ድጋፍ በአግባቡ በመጠቀም ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር የሚያደረጉትን ጉዞ ማፋጠን ይገባቸዋል ሲሉ ገልፀዋል ።

በምክትል ከንቲባ ማእረግ በአስተዳደሩ ምክር ቤት የመንግስት ቋሚ ተጠሪ እና የብልፅግና ፓርቲ የድሬደዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በበኩላቸው የአገራችንን መልካም ገፅታን ያጠለሸውን ከእርዳታ ተጽዕኖ ለመላቀቅ በአገር አቀፍ ደረጃ ሰፋፊ ፕሮግራሞች ተቀርፀው እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልፀው በአስተዳደሩ የተገኙ ውጤታማ ስራዎችን የመደገፍ እና የታዩ ውስንነቶችን የማረም ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ገልፀዋል ።

የድሬዳዋ ግብርና፣ውሃ፣ማእድንና ኢነርጂ ቢሮ ሀላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ በበኩላቸው አሰተዳደሩ አርሶ አደሩን ከጠባቂነት ተላቆ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ በተለይም የመስኖ ሀብቱን እንዲጠቀም እየተሰራ መሆኑን አስታውቀው ፥ ተደረገው ድጋፍ አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን በማረጋገጥ ከተረጂነት እንዲወጣ እና ወደ ተሻለ የኑሮ እርከን እንዲሸጋገር ያስችለዋል ብለዋል።

በዝግጅቱ ላይ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለ ድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ሠራዊት ተኮላ
ምስል፦ሰላም ሰይፉ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
👉በቴሌግራም ፦
https://t.me/+6C5aVWGZeL4wOWM0

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | 4ተኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ወላጆችና አሳዳጊዎች ልጆቻቸውን በማስከተብ ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ አሳሰበ።  | ታህሳስ ...
11/12/2025

#ዜና | 4ተኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ወላጆችና አሳዳጊዎች ልጆቻቸውን በማስከተብ ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ አሳሰበ።

| ታህሳስ 02 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ 4 ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል ።

የፖሊዮ በሽታ በሀገራችን ለብዙ ህፃናት ህመም ፥የአካል ጉዳትና ሞት ምክንያት ከሆኑት በሽታዎች አንዱ በመሆኑ በሽታው ለመከላከልና ለመቆጣጠር በዘመቻ መልክ የሚሰጠውን ክትባት በአግባቡ ስናስከትብ ነው ያሉት የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ፅገሬዳ ክፍሌ ለጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።

ሀላፊዋ አክለውም የ4ተኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት የሚሰጠው ከ5አመት በታች ለሆኑ ህፃናት ከታህሳስ 3-6/2018 ዓ ም መሆኑን ገልፀው
በሀገር አቀፍ ደረጃ 5.4 ሚሊዮን ህፃናት በዘመቻው እንደሚከተቡና በአስተዳደሩ 109 ሺህ ያህል ህፃናት በዘመቻው እንደሚከተቡ ገልፀዋል ።

ዶ/ር ፅገሬዳ አክለው እንዳስታወቁት በዘመቻው ከዚህ ቀደም በ2ኛው እና በ3ዙር ክትባት ዘመቻ ያልተከቡ ህፃናት በ4ተኛው ዙር ክትባት ዘመቻ በከተማና በገጠር ጤና ተቋማትና ቤት ለቤት እንደሚሰጥ ጠቅሰው ከዘመቻው ባሻገርም በሰሞኑ ትኩሳትና ደንጊና ወባ ጨምሮ ለህፃናት ልየታ የሚደረግ መሆኑን አስታውቋል ።

በመጨረሻም ሀላፊዋ 4ኛው ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ወላጆችና አሳዳጊዎች ልጆቻቸውን በማስከተብ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ለወላጆችና ለአሳዳጊዎች ጥሪ አቅርበዋል ።

ሣራ አብዱራሂም
ካሜራ፦እስራኤል ሙሉ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
👉በቴሌግራም ፦
https://t.me/+6C5aVWGZeL4wOWM0

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | የድሬ ፍሬዎች በጎ አድራጎት ድርጅት በገንደ አዳ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ምገባ መርሃግብር አከናወነ።  | ታህሳስ 02 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋበምገባ መርሃግብሩ...
11/12/2025

#ዜና | የድሬ ፍሬዎች በጎ አድራጎት ድርጅት በገንደ አዳ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ምገባ መርሃግብር አከናወነ።

| ታህሳስ 02 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በምገባ መርሃግብሩ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር እንዳሉት በገንደ አዳ አካባቢ ዙሪያ ያሉት የማህበረሰብ ክፍሎች ልጆችን ለማገዝ ድርጅቱ ለሚያደርገው ድጋፍ አስተዳደሩ እገዛ የሚያደርግ መሆኑን አስታውቀዋል።

በዚህ የተማሪዎች ምገባም ማህበረሰባችን ለማገዝ ጥረት የሚያደርጉ ቅን ልቦና ያላቸው ዜጎች አሁንም ድረስ መኖራቸውን ያሳያል ብለዋል። በውጪ ያሉ የድሬዳዋ ተወላጆችም በሚችሉት ሁሉ የአቅማቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የድሬ ፍሬዎች በጎ አድራጎት ድርጅት ባለቤት አቶ ወሰን ቢራቱ በበኩላቸው በ2017 ዓ.ም ሁለት ሺ ተማሪዎችን በ20 ትምህርት ቤቶች ስንመግብ ነበር ያሉ ሲሆን ዘንድሮ ላይ ሌሎች ትምህርት ቤቶችን በመጨመር 2ሺ 200 ያህል ተማሪዎችን በመመገብ ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የድሬ ፍሬዎችን በጎ አድራጎት ድርጅት ከዋች ኤንድ ፕሬይ እንዲሁም ኤስኤንቪ ከተሰኘ የሆላንድ ኤምባሲ የልማት ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን የምገባ ፕሮግራሙን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ላይ በምገባ መርሃግብሩ ተደራሽ እንድንሆን በተደጋጋሚ የምናነሳው የትራንስፖርት ችግርን ለመቅረፍ በድሬዳዋ አስተዳደር ወጪ የታደሰ መኪና ተበርክቶልናል ሲሉም ተናግረዋል።

ዳዊት አያሌው
ምስል፦አሚን ሸሪፍ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
👉በቴሌግራም ፦
https://t.me/+6C5aVWGZeL4wOWM0

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

11/12/2025
 #ዜና | "ሀገርን አስቀድሙ ከዚያ ታሸንፋላችሁ!" - አትሌት ቀነኒሳ በቀለ  | ታህሳስ 01 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋአትሌት ቀነኒሳ በቀለ በፍሎሪዳ በሚካሄደው 46ኛው የዓለም አገር አቋ...
10/12/2025

#ዜና | "ሀገርን አስቀድሙ ከዚያ ታሸንፋላችሁ!" - አትሌት ቀነኒሳ በቀለ

| ታህሳስ 01 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በፍሎሪዳ በሚካሄደው 46ኛው የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና ላይ የሚሳተፈውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ሱሉልታ በመገኘ ውጤታማ የአገር አቋራጭ ውድድር ልምዱን አካፍሏል።

የረጅም ርቀት የምንጊዜም ድንቅ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በ25 ዓመታት የአትሌቲክስ ሕይወቱ በዓለም የሀገር አቋራጭ የሰራው ታሪክ ከሁሉም የላቀ ነው።

ቀነኒሳ ፈታኝ በሆነው ውድድር ለኢትዮጵያ 11 ወርቅ እና 1 የነሐስ ሜዳሊያ በማስመዝገብ በዓለም የሚስተካከለው የለም።

በተደጋጋሚ ጉዳት ያሰበውን ያህል በማራቶን ስኬታማ መሆን ያልቻለው የ43 ዓመቱ ጀግና አትሌት ከወር በፊት የኒውዮርክ ማራቶንን አቋርጦ ከወጣ በኋላ ራሱን ከውድድር ማግለሉ ሲነገር ቆይቷል። ኢትዮጵያን በወከለባቸው ውድድሮች ከ34 ሜዳሊያዎች በላይ ማስመዝገብ የቻለው "ቀነኒ ኬኛ" ለወጣት አትሌቶች በድል የተሽቆጠቆጠ የዓለም አገር አቋራጭ ውድድር ተሞክሮውን አካፍሏል።

የዓለም አገር አቋራጭ ንጉሱ "አቦ ሸማኔ" በፍሎሪዳ በሚካሄደው 46ኛው የዓለም አገር አቋራጭ ቻምፒዮና ላይ የሚሳተፈውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ሱሉልታ በመገኘ ውጤታማ የአገር አቋራጭ ውድድር ልምድ አካፍሏል።

"በራሳችሁ ተማመመኑ፣ አገርን አስቀድሙ፣ በቡድን ስሩ፣ ያላቹን አቅም እወቁ ከዛ ማሸነፍ ትችላላችሁ" በማለት ለአገር አቋራጭ ቡድኑ ምክሩን የለገሰ ሲሆን፣ የቡድን ስራ ላይ ትኩረት እንዲያደርጉም አሳስቧል። አትሌቶቹም በዓለም አገር አቋራጭ ንጉሱ አትሌት ቀነኒሳ ገለፃ ፣ልምድና ተሞክሮ መደሰታቸውን ገልፀዋል።

ምንጭ፦ ኢአፌ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
👉በቴሌግራም ፦
https://t.me/+6C5aVWGZeL4wOWM0

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | ድሬዳዋ የሀገርን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት የሚያስጠብቁ ጀግኖች ወታደሮችን በየዘመናት ስታፈራ የቆየች ናት - አቶ ሀርቢ ቡህ  | ታህሳስ 01 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋከድሬዳዋ ...
10/12/2025

#ዜና | ድሬዳዋ የሀገርን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት የሚያስጠብቁ ጀግኖች ወታደሮችን በየዘመናት ስታፈራ የቆየች ናት - አቶ ሀርቢ ቡህ

| ታህሳስ 01 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

ከድሬዳዋ አስተዳደር ለሀገር መከላከያ ሰራዊት አባልነት የምልመላ መስፈርትን ያሟሉ ምልምል ወታደሮች የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ሽኝት ተደርጎላቸዋል።

በሽኝት ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ ለተመልማዮቹ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ ድሬዳዋ የሀገርን ዳር ድንበርና ሉዓላዊነት የሚያስጠብቁ ጀግኖች ወታደሮችን በየዘመናት ስታፈራ የቆየች መሆኗን ገልፀው የአሁኑ ትዉልድ ወጣቶችም ለሀገር አንድነት እና ነፃነት መጠበቅ በጀግንነት የሚፋለም ጀግና የሀገር ወታደር እና ጄኔራሎች እንደምትሆኑ አልጠራጠርም ብለዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር የፍትህ፣ፀጥታና ህግ ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ አብዱሰላም አህመድ በበኩላቸዉ ምልምሎቹ የሀገሪቱ ቀጣይ ሰላም እና ሉዓላዊነት ህልውና በጫንቃቸው ላይ መሆኑን በመገንዘብ በሀገር ፍቅር እና ለሰንደቃቸው ክብር በስነምግባር ሊሰሩ እንደሚገባቸው አስገንዝበው መልካም የስልጠና ጊዜ እንዲሆንላቸዉ ተመኝተዋል።

በሽኝት ስነስርዓቱ ላይ የብልፅግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ ልዩ ረዳት አቶ ዮናስ ጥግነህን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ ሌሎች አመራሮችም ተገኝተዋል።

ሰለሞን አዲሱ
ምስል፦ሰላም ሰይፉ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
👉በቴሌግራም ፦
https://t.me/+6C5aVWGZeL4wOWM0

በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Address

Dire Dawa

Opening Hours

Monday 06:00 - 22:00
Tuesday 06:00 - 22:00
Wednesday 06:00 - 22:00
Thursday 06:00 - 22:00
Friday 06:00 - 22:00
Saturday 06:00 - 22:00
Sunday 06:00 - 22:00

Telephone

+251915711939

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Tv - አማርኛ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dire Tv - አማርኛ:

Share