Dire Tv - አማርኛ

Dire Tv - አማርኛ This is the official Dire Dawa Administration Mass Media Enterprise (Dire Tv - አማርኛ) page - where you can get all the latest news in Amharic.

You can follow us Here.

‘የሶፍ ኡመር ወግ’ ዛሬ ምሽት 2:30 ይጠብቁ!ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የቀድሞ እና በሥራ ላይ ካሉ አመራሮች ጋር ያደረጉት ውይይት።
20/10/2025

‘የሶፍ ኡመር ወግ’ ዛሬ ምሽት 2:30 ይጠብቁ!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የቀድሞ እና በሥራ ላይ ካሉ አመራሮች ጋር ያደረጉት ውይይት።

 #ዜና | በድሬዳዋ አስተዳደር በማህበረሰቡና በአመራሩ ቅንጅታዊ አሰራር በመዳበሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸው ተገለፀ  | ጥቅምት 09...
19/10/2025

#ዜና | በድሬዳዋ አስተዳደር በማህበረሰቡና በአመራሩ ቅንጅታዊ አሰራር በመዳበሩ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸው ተገለፀ

| ጥቅምት 09 ፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት የተመራ ልዑካን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ተዘዋውሮ ጎብኝቷል።

ልዑኩ ከድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ፈቲያ አደን እንዲሁም ከድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ከሪማ አሊ ጋር በጋራ በመሆን የድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠናን፣ ደረቅ ወደብን፣ በኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የአዲስ አበባ ጅቡቲ ባቡር መስመር ድሬዳዋ ባቡር ጣቢያን፣ የእመርታ ቤተ-መፅሐፍን እንዲሁም "ድሬ መሶብ" የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫን ተመልክቷል።

በጉብኝቱም በድሬዳዋ አስተዳደር በማህበረሰቡና በአመራሩ ቅንጅታዊ አሰራር መዳበር ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸው የተገለፀ ሲሆን፤ ይህም በቀጣይ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ተመላክቷል።

ለልዑክ ቡድኑ በድሬዳዋ ቤተ መንግስት የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበልም ተደርጎለታል።

DGC
ምስል:-ሀየሎም አለበል

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ  | ጥቅምት 09 ፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ ፕሬዚዳንት  ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተቀዳሚ...
19/10/2025

#ዜና | ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ

| ጥቅምት 09 ፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ ባስተላለፉት የሐዘን መግለጫ፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዚዳንት በነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ እረፍት በጥልቅ አዝኛለሁ ብለዋል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በመልካም አበርክቷቸው ሁሌም የሚታወሱ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው ኢትዮጵያውያን መፅናናትን ተመኝተዋል፡፡

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ  | ጥቅምት 09፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋየድሬዳዋ አስተዳደር ከን...
19/10/2025

#ዜና | የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ

| ጥቅምት 09፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የሀዘን መግለጫ መልዕክት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የቀድሞ ፕሬዚዳንት የነበሩት፥ ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በማረፋቸው የተሰማኝን ጥልቅ ኀዘን እገልፃለሁ ብለዋል።

ለመላው ህዝበ ሙስሊም መጽናናትን እመኛለሁ ብለዋል፥ ከንቲባው በሀዘን መግለጫ መልዕክታቸው።

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | ማንቸስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን በአንፊልድ አሸነፈ።  | ጥቅምት 09 ፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋበእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ ማንቸስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን 2 ለ 1 በሆ...
19/10/2025

#ዜና | ማንቸስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን በአንፊልድ አሸነፈ።

| ጥቅምት 09 ፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ ማንቸስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

ለዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ሙሉ ሶስት ነጥብ ያስገኘለትን ጎሎች ብሪያን ምቦሞ እና ሀሪ ማጉዌር ሲያስቆጥሩ ለሊቨርፑል ደግሞ ጋክፖ ሊያስቆጥር ችሏል።

በሊጉ ደካማ አቋም እያሳየ የነበረው ማንቸስተር ዩናይትድ በዛሬው ጨዋታ በአንፊልድ ያሳየው አቋም መነጋገሪያ ርዕስ ፈጥሯል።

በጁሊየት ተድላ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ  | ጥቅምት 09፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመ...
19/10/2025

#ዜና | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ

| ጥቅምት 09፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የሀዘን መግለጫ መልዕክት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በማረፋቸው ኀዘን ተሰምቶኛል ብለዋል።

ሐጂ ዑመር በአመራር ዘመናቸው የተለያዩ ወገኖች ወደ አንድነት እንዲመጡ እና የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሕግ ዕውቅና እንዲኖረው ያደረጉትን አስተዋጽዖ ሁሌም እናስታውሰዋለን ሲሉም ገልጸዋል።

ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላ ኢትዮጵያ ሙስሊሞች መጽናናትን እመኛለሁ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀዘን መግለጫ መልዕክታቸው።

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

  | ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ  | ጥቅምት 09፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ...
19/10/2025

| ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

| ጥቅምት 09፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ኢቢሲ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የፕሬዝደንቱ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡

የድሬዳዋ መገናኛ ብዙሐን ድርጅት በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን ይመኛል።

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | በኃብት ስጦታ አንፃር ስንመለከት ኢትዮጵያ ለሁሉም የሚበቃ ኃብት እንዳላት እናውቃለን - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)  | ጥቅምት 09 ፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ በኃብት...
19/10/2025

#ዜና | በኃብት ስጦታ አንፃር ስንመለከት ኢትዮጵያ ለሁሉም የሚበቃ ኃብት እንዳላት እናውቃለን - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

| ጥቅምት 09 ፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በኃብት ስጦታ አንፃር ስንመለከት ኢትዮጵያ ለሁሉም የሚበቃ ኃብት እንዳላት እናውቃለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በባሌ ዞን ከተለያዩ አመራሮች ጋር ያደረግነው ጉብኝት የመጨረሻ መዳረሻ አስደማሚው የፊንጫ ሀበራ ፏፏቴ ሆኗል ብለዋል።

በግርማ የሚወርደው ፏፏቴ ወደ ሶፍኡመር የዋሻ ሥርዓት የሚደመረውን የወይብ ወንዝ የሚቀላቀል ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮ የሚገኝበት ይኽ አስደናቂ ከባቢ ድንቅ የአዕዋፍ መገኛና በቅርቡ የዋሻ መስህብ የተገኘበት እንዲሁም የራፉ ውብ የዐለት ደን አቅራብያ የሚገኝ ነው ብለዋል።

በቅርቡ በአካባቢው የሚገነባው ማረፊያ ሲጠናቀቅም ለጎብኝዎች የበለጠ ሳቢ እና ምቹ ይሆናል ነው ያሉት በመልዕክታቸው።

ባለፉት ሶስት ቀናት በጉብኝቱ የተሳተፉ የቀድሞ እና በሥራ ላይ ያሉ ኃላፊዎች በጉብኝቱ የተመለከቱት የተፈጥሮ፣ የባሕል እና የሰው ኃብት ከፍ ያለ መነሳሳትን ፈጥሮላቸዋል ሲሉም ገልጸዋል።

የጋራ ሥራችን እነዚህን ኃብቶቻችንን መግለጥ፣ ማሳደግ፣ በኃብቶቹ ላይ በመጨመር ቀጣዩ ትውልድ ችቦውን ተረክቦ እንዲቀጥል መሠረት መጣል ነው ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በርግጥም የተትረፈረፈ ኃብት ምድር ናት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እንሰባሰብ ለማለም እንድፈር የጋራ ነጋችንን በጋራ እንገንባ ሲሉም ገልጸዋል።

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

19/10/2025

በሀረና ክላስተር ከሪራ ፏፏቴ እስከ ቱሉ ዲምቱ ከፍታ የነበረ ጉብኝት

19/10/2025

የሶፍኡመር ሎጅን ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ እየተዘረጋ ያለው የባቡር መሰረተ ልማት የመጀመሪያ ምዕራፍ 2 ኪ.ሜ ግንባታ ተጠናቋል - የኢትየጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ህሊና በላቸው (ኢ/ር)

 #ዜና | ‎የተማሪዎችን ውጤት ለማሳደግ እና  የትምህርት ልማቱን ለማሳካት የሚደረገው የተማሪዎች ቁሳቁስ ድጋፍ ዋነኛው ተግባር ነው ሲል የድሬደዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገለፀ።  | ጥቅም...
19/10/2025

#ዜና | ‎የተማሪዎችን ውጤት ለማሳደግ እና የትምህርት ልማቱን ለማሳካት የሚደረገው የተማሪዎች ቁሳቁስ ድጋፍ ዋነኛው ተግባር ነው ሲል የድሬደዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገለፀ።

| ጥቅምት 09፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

‎የድሬዳዋ ናሽናል ሲሚንቶ አ.ማ በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ በ13 ትምህርት ቤቶች ውስጥ ለሚገኙ 1800 ያህል ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

‎በድጋፍ መርሐግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬደዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልዬ በአስተዳደር ለሚገኙ በገቢያቸው ዝቅተኛ ለሆኑ ቤተሰቦች የተደረገው የትምህርት ቁሳቁሱ ድጋፍ የወላጆችን ወጪ ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋፆ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።

‎ከለውጡ ማግስት በአስተዳደሩ በትምህርት ሴክተር ላይ በተደረገው ማሻሻያ በየጊዜው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እና የምገባ ስርዓትን በመደበኛነት አጠናክሮ ማስቀጠል መቻሉን የጠቀሱት የቢሮ ኃላፊ የትምህርት ልማትን ለማጠናከር የድሬደዋ ናሽናል ሲሚንት አ.ማ ቋሚ አጋር በመሆን ላሳየው ብርቱ አስተዋጽዖም በአስተዳደሩ ስም ምስጋና አቀርባለሁ ሲሉ በመርሐግብር ላይ ተናግረዋል።

‎በጋራ ተያያዝን መተባበር ከቻልን የማይቀረፍ ችግር የለም ያሉት አቶ ሱልጣን አልዬ በአስተዳደሩ እንደ አዲስ የተጀመረው የቅዳሜ እና እሁድ ማጠናከሪያ ትምህርት አንዱ አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል። ተማሪዎች እና ወላጆችም ለውጤት መሻሻል የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

‎በድሬዳዋ አስተዳደር በሚገኙ የልማት ድርጅቶች አማካኝነት በተለያዩ ጊዚያት የሚደረጉ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፎች የማህበረሰን የኑሮ ሸክም በማቃለልና የመረዳዳት ባህልን ከማሳደግ ባሻገር የጣለባቸውን ማሀበራዊ አገልግሎት ለመወጣት የሚያስችል አንዱ ስልት ነው ሲሉ አቶ ሱልጣን ተናግረዋል።

‎የድሬዳዋ ናሽናል ሲሚንት አ.ማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሊዮ ጄሼንግ በበኩላቸው እንደተናገሩት በባለፈው አመት የተደረገውን ድጋፍ በማስቀጠል በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ዘንድሮም ማድረጋችን ተማሪዎች ጥሩ ውጤት እንዲያመጡ እና የነገው ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመፍጠር በቁ የተማረ ኃይል እንዲኖር ለማስቻል ናሽናል ሲሚንት አ.ማ የበኩሉን ድርሻ መወጣቱን አጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።

‎ተማሪዎች ስለ ትምህርት ብቻ ማሰብ እና መትጋት እንዲችሉ በልማት ድርጅቶች የሚደረገው የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ወሳኝ መሆኑን በድጋፍ መርሃግብሩ ላይ ተገልጿል።

‎ሙሉዓለም ሰለሞን
ምስል፦ፋዲል ሬድዋን

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ድሬዳዋ ገቡ  | ጥቅምት 09፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋነገ በድሬዳዋ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች ኮንፍረን...
19/10/2025

#ዜና | የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ድሬዳዋ ገቡ

| ጥቅምት 09፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

ነገ በድሬዳዋ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች ኮንፍረንስ ላይ ለመሳተፍ የፌደራል ጠቅላላ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ድሬዳዋ ገቡ።

የፌደራል ጠቅላላ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ድሬዳዋ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሃርቢ ቡህ እና የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረትን ጨምሮ የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንቶች በድሬዳዋ ከተማ ነገ በሚካሄደው ሀገር አቀፍ የህግ ተርጓሚዎች ኮንፍረንስ ላይ በመሳተፍ የሚመክሩ ሲሆን ከዚህም ባለፈ በድሬዳዋ አስተዳደር ያሉ ፍርድ ቤቶችን የሚገበኙ መሆኑ ተጠቁሟል።

ጉባዔው በድሬዳዋ ለአንድ ቀን የሚቆይ ሲሆን በሐረርና ጅግጅጋ ለሁለት ተከታታይ ቀናቶች እንዲሁ የምክክርና የክልል ፍርድ ቤቶች እንደሚጐበኙ ተገልጿል ።

በአቀባበል ስነ ስርአቱ ላይ የአስተዳደሩ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ከሪማ አሊ ፣ የከንቲባ ፅ/ቤት ኃላፊው አቶ ገበየሁ ጥላሁን ፣ የድሬዳዋ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዋና ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሃመድን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

ስንታየሁ አበራ
ምስል፦ ሀየሎም አለበል

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

👉ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
👉ዩትዩብ ፦
https://www.youtube.com/live/rkHE_fWNmkE?si=TElgNpYHVPxpB77L
👉በቲክታክ ፦
https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Address

Dire Dawa

Opening Hours

Monday 06:00 - 22:00
Tuesday 06:00 - 22:00
Wednesday 06:00 - 22:00
Thursday 06:00 - 22:00
Friday 06:00 - 22:00
Saturday 06:00 - 22:00
Sunday 06:00 - 22:00

Telephone

+251915711939

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Tv - አማርኛ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dire Tv - አማርኛ:

Share