Dire Tv - አማርኛ

Dire Tv - አማርኛ This is the official Dire Dawa Administration Mass Media Enterprise (Dire Tv - አማርኛ) page - where you can get all the latest news in Amharic.

You can follow us Here.

23/08/2025

#ዜና | ከአካባቢ እና ከግል ንፅህና ጋር በተያያዘ ከአስራ ሰባት በላይ የተለያዩ መለኪያዎችን በመጠቀም በገጠርና በከተማ የሚገኙ ተቋማት ላይ በተደረጉ ምዘናዎች ከ65 በመቶ በላይ ውጤት ማስመዝገብ እንደተቻለ የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌ ተናገሩ።

| ነሐሴ 17 ፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በቢሮው የዎሽ እና አካባቢ ጤና አጠባበቅ ኬዝ ቲም የ2017 ዓ.ም እቅድ ክንውን ግምገማ መድረኩን አካሂዷል።

ዳዊት አያሌው

23/08/2025

| ነሐሴ 17 ፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ያደረጉት ጉብኝት

 #ዜና | "እንደ ሀገር በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረውን የገጠር ኮሪደር ልማት ርዕይን በአስተዳደራችን ባሉ የገጠር ክላስተሮች በመተግበር የመጀመሪያ ተሸላሚ...
23/08/2025

#ዜና | "እንደ ሀገር በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረውን የገጠር ኮሪደር ልማት ርዕይን በአስተዳደራችን ባሉ የገጠር ክላስተሮች በመተግበር የመጀመሪያ ተሸላሚ ለመሆን በቁጭት ልንሰራ ይገባል" ፡- ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌ - የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ

| ነሐሴ 17 ፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ ጤና ቢሮ የዎሽ እና አካባቢ ጤና አጠባበቅ ኬዝ ቲም የ2017 ዓ.ም ፅዱና ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ ቀበሌዎች የስራ አፈፃፀም ግምገማ እንዲሁም የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።

በሀገራችን ከሁለት አስርት አመታት በፊት ጀምሮ ሜዳ ላይ ከመጸዳዳት ነጻ ቀበሌዎችን ለመፍጠር ጥረት ሲደረግ ቆይቷል።

ይህ እንቅስቃሴ ከአምስት ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት ሞት ቅነሳ ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው ሲሆን እስካሁን ባለው መረጃ በአስተዳደራችን ገጠር ቀበሌዎች የተገነቡ የተሻሻሉ መፀዳጃ ቤቶች ሽፋን ከ 54 በመቶ በላይ መድረሱን ያሳያል።

በማህበረሰብ መር ጠቅላላ የንፅህና አጠባበቅ /ሳኒቴሽን መርሃግብር (CLTSH) ከተቀሰቀሱት ቀበሌዎች ውስጥ 47 በመቶዎቹ ሜዳ ላይ ከመጸዳዳት ነጻ መሆናቸውን በማረገገጥ እውቅና መስጠት ተችሏል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ፅጌረዳ ክፍሌ በመድረኩ ላይ እንዳሉት በአስተዳደሩ 18 ቀበሌዎች ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ መሆን የቻሉ እንደሆነ አስታውሰው የግል እና የአካባቢን ንፅህና አስጠብቀው ወደ ኋላ መመለስ እንደሌለባቸው አስገንዝበዋል።

ዶ/ር ፅጌረዳ አያይዘውም አዲስ አባወራ ቤት ሲገነባ መፀዳጃን አብሮ በመስራት ፣ የሰው እና የእንስሳት መኖሪያን በመለየት እንዲሁም የቆሻሻ ማቃጠያን ቦታዎችን መለየት እንደሚገባው ጠቁመዋል።

እንደ ሀገር በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረውን የገጠር ኮሪደር ኢኒሽዬቲቭን በአስተዳደራችን ባሉ የገጠር ክላስተሮች በመተግበር የመጀመሪያ ተሸላሚ ለመሆን በቁጭት መስራት ላይ ማተኮር ይኖርብናል ሲሉም ገልፀዋል።

የገጠር ኮሪደር ፅዱ አካባቢን እና አረንጓዴ ስፍራን መፍጠር አንዱ አላማው እንደሆነ አንስተው የገጠር መኖሪያን ፣ ተቋማትችን እንዲሁም መንገዶችን ንፁህ በማድረግ ለቱሪዝም ምቹ ልናደርጋቸው ይገባናል ሲሉ አመላክተዋል።

በሥራው አፈፃፀም በምልከታው ወቅት ከታዩ ጥንካሬዎቹ ውስጥ ጥራት ያላቸዉ መፀዳጃ ቤቶችን የገነቡ የማህበረሰብ ክፍሎች መኖራቸው፣አብዛኛው መፀዳጃ ቤት ደረጃውን የጠበቀ መሆኑ፣አብላጫው የማህበረሰብ ክፍል ላይ የመፀዳጃ ቤት ጥቅም ግንዛቤ ምድር እና መጸዳጃ ቤት ያላቸዉ አባወራዎችና እማወራዎች በአግባቡ መጠቀማቸው እንደሆነ ተነስቷል።

ከተስተዋሉ ተግዳሮቶች መካከልም በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት የመፀዳጃ ቤቶች መፍረስ ፣ የመፀዳጃ ቤቶች መሙላት ፣ አዲስ የሚገነቡ ቤቶችን ተከታትሎ መፀዳጃ ቤት እንዲሰሩ አለማድረግ፣መፀዳጃ ቤት በአግባቡ አለመጠቀም እና የድህረ ክትትል ስራዎች አለመከናወናቸው መሆናቸው በሪፖርቱ ተዳስሰዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያም የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ፊርማ የተከናወነ ሲሆን ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ ለሆኑ ገጠር ቀበሌዎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ በማበረታቻ መልክ ተበርክቶላቸዋል።

ዳዊት አያሌው
ምስል፦ናትናኤል ገ/ዮሐንስ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
በቲክታክ ፦https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

23/08/2025

#ዜና | በድሬዳዋ የቅርጫት ኳስ ስፖርትን ወደነበረበት ለመመለስ የማህበረሰቡ የላቀ ተሳትፎ ያስፈልጋል ሲሉ የድሬዳዋ ቅርጫት ኳስ የቡድን አባላት ተናገሩ።

| ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የድሬዳዋ መገናኛ ብዙሀን ድርጅት የድሬዳዋን አሁናዊ የቅርጫት ኳስ ሁኔታን ተመልክቷል።

ሰለሞን አዲሱ

 #ዜና | ማዕድን በብዝኃዘርፍ የልማት ምልከታችን አንዱ ቁልፍ ዘርፍ ሆኖ ይቀጥላል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)  | ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋማዕድን በብዝኃዘርፍ የል...
23/08/2025

#ዜና | ማዕድን በብዝኃዘርፍ የልማት ምልከታችን አንዱ ቁልፍ ዘርፍ ሆኖ ይቀጥላል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

| ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋ

ማዕድን በብዝኃዘርፍ የልማት ምልከታችን አንዱ ቁልፍ ዘርፍ ሆኖ ይቀጥላል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ማዕድን በብዝኃዘርፍ የልማት ምልከታችን አንዱ ቁልፍ ዘርፍ ሆኖ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም ለዚህ ርዕይ መሳካት ዐቢይ ሚና ያለው መሆኑን እያስመሰከረ ይገኛል ብለዋል።

ዛሬ በአሶሳ ከተማ ያዩት ለውጥ ከአንድ ዓመት በፊት በከተማው ከነበራቸው ቆይታ ጋር ሲነጻጸር ፍጹም ተቃራኒ እንደሆነም ጠቅሰዋል።

ከተማው የተለወጠበት መንገድ ጥሩ ጅማሮ መሆኑን አንስትው፤ የኮሪደር ሥራ ውጤቱ የሚታይ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ከአሶሳ የተወሰኑ መቶ ኪሎ ሜትሮች ርቀት የሚገኘውና በማሽን የታገዘ ዘመናዊ ፋብሪካ የኩርሙክ ወርቅ ፋብሪካ አስደናቂ የሥራ ውጤት መሆኑን አመልክተዋል።

ፋብሪካው በሚቀጥለው አመት በግማሽ አቅሙ ማምረት ይጀምራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህም የክልሉን ሰፊ የወርቅ አቅም እንደሚያሳይ ተናግረዋል።

ከባለፈው አመት ጉብኝት በኋላ የታየው እድገት የሚበረታታ ነው፤ ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ በሚጠናቀቅበት ጊዜ በጎ ተጽዕኖው በመላው ክልሉ እንደሚታይ ነው የገለጹት።

መሰል ፕሮጀክቶች ከሌሎች ፕሮጀክቶች ጋር ተደምረው የሀገራዊ ብልጽግናችን መገንቢያ ጡቦች ናቸው ብለዋል በመልዕክታቸው።

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
በቲክታክ ፦https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

23/08/2025

| ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋ
የለውጡ መንግሥት በተከተለው አዲስ ዕይታና በወሰደው እርምጃ የሀገር አንጡራ ሀብት የሆነው ተቋም ወደ አዲስ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መምጣቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ።

 #ዜና| የመንግሥት ሠራተኛ የደመወዝ ማሻሻያን ተከትሎ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል - ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)  | ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም |...
23/08/2025

#ዜና| የመንግሥት ሠራተኛ የደመወዝ ማሻሻያን ተከትሎ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል - ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)

| ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋ

ለመንግስት ሠራተኛው የተደረገውን የደመወዝ ማሻሻያ ተከትሎ በምርትና አገልግሎቶች ላይ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።

ከመስከረም 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ እንዲደረግ መወሰኑ ይታወቃል።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)፤ በምርትና አገልግሎት ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ በሕጋዊ የንግድ ሥርዓት ውስጥ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

በነፃ ንግድ ሥርዓት ስም በምርት ላይ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ መጨመርም ሆነ ማከማቸት አስተዳደራዊና ህጋዊ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ድርጊት መሆኑን አስገንዝበዋል።

ለመንግሥት ሠራተኞች የተደረገውን የደመወዝ ማሻሻያ ተከትሎ ገቢ የሆነ ኢኮኖሚያዊ መንስኤ የሌለው የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል በማድረግ እርምጃ እንደሚወሰድ አስገንዝበዋል።

የደመወዝ ጭማሪን ሰበብ በማድረግ በምርትና አገልግሎቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ ሁኔታዎችን ካለማጤን የሚመነጭ መሆኑንም ገልጸዋል።

በእስካሁኑ ሂደት የተስተዋለ ነገር የለም ያሉት ሚኒስትሩ፤ ኢ-ምክንያታዊ የምርት ዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር ዝግጅት መደረጉን አብራርተዋል።

በ2017 በጀት ዓመት ወደ ተሟላ ትግበራ በገባው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የዋጋ ንረትን የማረጋጋትና ገበያን የመምራት ስኬቶችን በመቀመር በሁሉም መስክ ዝግጅት መደረጉን አንስተዋል።

የንግዱ ማህበረሰብ ለሕግ ተገዥ በመሆን ሀገሩንና ወገኑን ማገልገል እንደሚጠበቅበትም ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።

ኢዜአ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
በቲክታክ ፦https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | በድሬዳዋ የቅርጫት ኳስ ስፖርትን ወደነበረበት ለመመለስ የማህበረሰቡ የላቀ ተሳትፎ ያስፈልጋል ሲሉ የድሬዳዋ ቅርጫት ኳስ የቡድን አባላት ተናገሩ።   | ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም |...
23/08/2025

#ዜና | በድሬዳዋ የቅርጫት ኳስ ስፖርትን ወደነበረበት ለመመለስ የማህበረሰቡ የላቀ ተሳትፎ ያስፈልጋል ሲሉ የድሬዳዋ ቅርጫት ኳስ የቡድን አባላት ተናገሩ።

| ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የድሬዳዋ መገናኛ ብዙሀን ድርጅት የድሬዳዋን አሁናዊ የቅርጫት ኳስ ሁኔታን ተመልክቷል።

በድሬዳዋ ስፖርት ታሪክ ውስጥ ትልቅ ስም ካላቸው የስፖርት አይነቶች ውስጥ አንዱ የቅርጫት ኳስ ቢሆንም ከ2014 በኋላ ግን ቅርጫት ኳሱ እየተዳከመ እንዳለ ይነገራል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ባደረግነው ቅኝት ጥያቄ ያቀረብንላቸው የቅርጫት ኳስን ከልጅነታቸው ጀምሮ እስከ ተጨዋችነት ከዚያም በአስልጣኝነትና ቡድንን በበላይነት እያንቀሳቀሱት የሚገኙት ኢንስትራክተር ወንድወሰን ፍስሀ ማህበረሰቡ ተሳትፎውን በማሳደግ ቅርጫት ኳሱን ማሳደግ ይኖርበታል ብለዋል።

ኢንስትራክተር ወንድወሰን አክለውም "ስፖርቱን ለማሳደግ ስፖርትን ከልብህ መውደድ አለብህ" ሲሉ አነቃቂ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ስፖርትን ካልወደድከው መስራት የለብህም የሚሉት ኢንስትራክተሩ በቀጣይ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል።

በተለያዩ ክለቦች የተጨወተውና አሁን ላይ በቡድኑ ውስጥ የሚገኘው ወጣት ተጫዋች አዩብ ኡስማን በበኩሉ ለቅርጫት ኳስ እድገቱ እንቅፋት ከሆኑት ነገሮች አንዱ የሜዳ ጉዳይ እንደሆነ በመግለፅ ሁሉም አካል ይህን ሊያስብበት እንደሚገባ ተናግሯል።

ሌላኛው ተጨዋች እስክንድር ናደው በበኩሉ በቡድኑ ውስጥ ከአመራርነት በዘለለ በፋይናንስ ደረጃ አስተዋፅኦ እያደረጉ የሚገኙትን ኢንስትራክተር ወንድወሰንን በማመስገን ባለሀብቶች ወደ ስፖርቱ መምጣት አለባቸው ብሏል።

ሰለሞን አዲሱ
ምስል፦እስራኤል ሙሉ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
በቲክታክ ፦https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | በድሬዳዋ አስተዳደር የወረዳ አስተዳደር ምክር ቤቶች 4ኛ የስራ ዘመን ፥4ኛ አመት 51ኛ  መደበኛ ጉባኤያቸውን አካሄዱ።  | ነሐሴ 17 ፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋበድሬዳዋ አስተዳደ...
23/08/2025

#ዜና | በድሬዳዋ አስተዳደር የወረዳ አስተዳደር ምክር ቤቶች 4ኛ የስራ ዘመን ፥4ኛ አመት 51ኛ መደበኛ ጉባኤያቸውን አካሄዱ።

| ነሐሴ 17 ፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የወረዳ ዐ1፣06፣07 እና 09 አስተዳደር ምክር ቤቶች 4ኛ የስራ ዘመን 4ኛ አመት 51ኛ መደበኛ ጉባኤያቸውን አካሂደዋል።

በጉባኤውም የ01 እና 06 ወረዳዎች ምክር ቤቶች 4ኛ የስራ ዘመን 4ኛ አመት 51ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ የለቱን አጀንዳ ማፅደቅ ፤ ቃለ ጉባኤ ማጽደቅ ፤ የአስፈፃሚ አካላት የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀምና የ2018 ዓ.ም በጀት አመት እቅድ እና የ2018 በጀት ቀርቦ ጸድቋል።

የ 2017 በጀት አመት በወረዳዎቹ ምክር ቤት የተከናወኑ ስራዎች ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በተመሳሳይ መልኩ የወረዳ 07 እና 09 ምክር ቤቶችም 4ተኛ የሥራ ዘመን 4ተኛ አመት 51ኛ መደበኛ ጉባኤያቸውን
አካሒደዋል።

እንደሌሎቹ ወረዳዎች ሁሉ በ07 እና 09 ወረዳዎች ምክር ቤቶች ጉባኤ ላይ የ2017 የስራ አፈጸም ቀርቦ ከተገመገመ በኋላ የ2018 የስራ እቅድ አቅጣጫ ላይ ውይይት አካሒደዋል።

የወረዳ ምክር ቤቶቹ ጉባኤ ላይ በወረዳዎቹ የተለያዩ ሹመቶችን አፅድቀዋል ።

ነጃት ተገኔ
አማረች አለሙ
ምስል፡ - ፋዲል ሬድዋን

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
በቲክታክ ፦https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት ከማህበራዊና ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው ባሻገር የማህበረሰብን ትስስር የሚያጠናክሩ መሆናቸዉ ተገለፀ ።  | ነሐሴ 17 ፥2017 ዓ.ም| ድሬዳዋየድሬደዋ ...
23/08/2025

#ዜና | የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት ከማህበራዊና ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው ባሻገር የማህበረሰብን ትስስር የሚያጠናክሩ መሆናቸዉ ተገለፀ ።

| ነሐሴ 17 ፥2017 ዓ.ም| ድሬዳዋ

የድሬደዋ አስተዳደር ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ እና የድሬዳዋ አስተዳደር የገቢዎች ባለሥልጣን የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ ተግባራትን አስጀምረዋል።

በመርሃግብሩም በክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎች መካከልየችግኝ ተከላ በአሊ ቢራ ፓርክ ፣ የደም ልገሳ ፣ የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶች የአፍርሶ ግንባታ ስራ በወረዳ 06 እንዲሁም በወረዳ 08 መኖሪያ ቤት ስራን አስጀምሯል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሙሉካ መሀመድ በወቅቱ እንደገለፁት የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት ከማህበራዊና ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ዉጪ የማህበረሰብን ትስስር የሚፈጥሩ መሆናቸዉ ገልፀዉ በተለይ ለድሬዳዋ ሞቃታማ ከተማ የአየር ንብረት ለዉጥን ለመከላከል ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ነዉ ብለዋል ።

አክለዉም እንደዚህ አይነት በጎ ስራዎች በክረምት በጎ ፍቃድ ብቻ ተሰርተዉ ማብቃት ሳይሆን ሁሉም ማህበረሰብ በየኔነት ስሜት በሌላዉም ጊዜ መረዳት የሚገባቸዉን መርዳት ይገባናል ሲሉ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል ።

የድሬደዋ አስተዳደር የገቢዎች ባለስልጣን ዳይሬክተር አቶ አብዱሰላም መሀመድ በበኩላቸው እንደ ሀገር የተጀመሩትን በጎ ተግባራት በማስቀጠል የሀገራችን እድገት ላይ አሻራችን ለማሳራፍ ስራዎችን በይፋ ጀምረናል" ብለዋል ።

በመርሀግብሩ ሲሳተፉና ደም ሲለግሱ ያገኘናቸዉ ለጋሾች ደም መለገስ በደም እጥረት በችግር ዉስጥ የሚገኙትን የማህበረሰብ ክፍሎች ህይወት ማትረፍ ነዉ ይህንም በጎ ተግባራ በመፈፀማቸዉ ደስተኛ መሆናቸዉን ገልፀዋል።

በአጠቃላይ በዘንድሮ በክረምት በጎፈቃድ ሁለቱ ተቋማት 5000 ሺ ችግኞችን ለመትከል ፣ ወደ 100 ዩኒት ደም ለመለገስ ፣ 500 በላይ ለአቅመደካሞች የምግብ ፍጆታ እና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እንዲሁም ከ10 በላይ የአቅመ ደካማ ቤቶች ግንባታ በእቅድ ተይዘው ወደ ስራ ተገብቷል ።

ሰላም ይኄይስ
ምስል : ምንተስኖት ደረጀ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
በቲክታክ ፦https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ወረዳ ምክር ቤቶች 4ኛ አመት 4ኛ የስራ ዘመን 51ኛ  መደበኛ ጉባኤያቸውን ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም ያካሂዳሉ።   | ነሐሴ 16፥2017 ዓ.ም | ድሬ...
22/08/2025

#ዜና | የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ወረዳ ምክር ቤቶች 4ኛ አመት 4ኛ የስራ ዘመን 51ኛ መደበኛ ጉባኤያቸውን ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም ያካሂዳሉ።

| ነሐሴ 16፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ወረዳ ምክር ቤቶች ፎረም ስብሳቢ አቶ አሜ ኡስማን ጉባኤውን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የከተማ ወረዳ ምክር ቤቶች ፎረም ሰብሳቢ አቶ አሜ ኡስማን በሰጡት መግለጫ የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ወረዳ ምክር ቤቶች 4ኛ አመት 4ኛ የስራ ዘመን 51ኛ መደበኛ ጉባኤያቸውን ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም ያካሂዳሉ።

በጉባኤውም የምክር ቤቶቹ 4ኛ የስራ ዘመን 4ኛ አመት 50ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ ማጽደቅን ጨምሮ የአስፈፃሚ አካላት የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀምና የ2018 ዓ.ም በጀት አመት እቅድ እና የ2018 በጀት ማጽደቅ፣
የወረዳ ምክር ቤቶች የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም እና የ2018 እቅድ መመልከትና የወረዳ ማህበራዊ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም እና የ2018 እቅድ በጉባኤዎቹ ቀርቦ እንደሚገመገምና እንደሚፀድቅ ገልፀዋል።

ከዚህም በተጓዳኝ በጉባኤዎቹ የተለያዩ ሹመቶች ቀርበው እንደሚፀድቁ የገለፁት የፎረሙ ሰብሳቢ የድሬዳዋ ዘጠኙ የከተማ ወረዳ ምክር ቤቶች አባላት ቅዳሜ ነሐሴ 17፥2017 ዓ.ም በሚካሄደው 51ኛው መደበኛ ጉባኤ ላይ በመገኘት የተሰጣቸውን የህዝብ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም መልእክት አስተላልፈዋል።

ምንጭ፦ የምክር ቤቱ የትስስር ገፅ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
በቲክታክ ፦https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 #ዜና | የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ልማትና የኮንስትራክሽን ቢሮ በክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ መርሐ ግብር በሶስት ወረዳዎች የኢኮኖሚ አቅማቸው አናሳ የሆኑ ነዋሪዎችን ቤቶች የመገንባት ሥራ...
22/08/2025

#ዜና | የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ልማትና የኮንስትራክሽን ቢሮ በክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ መርሐ ግብር በሶስት ወረዳዎች የኢኮኖሚ አቅማቸው አናሳ የሆኑ ነዋሪዎችን ቤቶች የመገንባት ሥራ አስጀመረ።

| ነሐሴ 16፥2017 ዓ.ም | ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ የክረምት የበጎፍቃድ አገልግሎት አካል የሆነው የቤት እድሳት መርሀ ግብር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በ06፣07 እና በ09 ወረዳዎች በይፋ ጀምሯል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአስተዳደሩ የኮንስትራክሽንና ከተማ ልማት ቢሮ ሀላፊ ኢ/ር ኡመር ዱአሌ እንደገለፁት ቢሯቸው በሀገሪቱ በሁለንተናዊ መስኮች ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ከማሳካት አንፃር በኮንትራክሽን ሴክተር ተልዕኮውን ለማሳካት ከሚያደርገው ተግባር በተጓዳኝ በማህበራዊ መስኮች ሰው ተኮር ተግባራት ላይ በመሳተፍ የመተጋገዝና የመረዳዳት እሴትን ለማጎልበት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልፀዋል።

ኃላፊው አክለውም በዚህም ቢሮው ለስምንት የኢኮኖሚ አቅማቸው አነስተኛ ለሆኑ በከተማና በገጠር ክላስተር በቀለአድ ለሚገኙ ነዋሪዎች ቤቶችን እንደሚገነባ ገልፀው በአጭር ጊዜ አጠናቆ እንንደሚያስረክብም አስታዉቀዋል ።

በቤቶቹ እድሳትና ግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይም የአስተዳደሩ የኮንስትራክሽን ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች የወረዳዎች አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

ሣራ አብዱረሂም
ምስል፦ከቢሮው ገፅ

ተጨማሪ ፥ወቅታዊ ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፦

ፌስቡክ፡-
ለአማርኛ ፦https://www.facebook.com/diretvamharic
ለአፋን ኦሮሞ ፦https://www.facebook.com/share/1B8KihEAkt/
ለአፍ-ሶማሊ ፦https://www.facebook.com/share/199s1kp4Sr/
በቲክታክ ፦https://vm.tiktok.com/ZMSwgmLny/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Address

Dire Dawa

Opening Hours

Monday 06:00 - 22:00
Tuesday 06:00 - 22:00
Wednesday 06:00 - 22:00
Thursday 06:00 - 22:00
Friday 06:00 - 22:00
Saturday 06:00 - 22:00
Sunday 06:00 - 22:00

Telephone

+251915711939

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Tv - አማርኛ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dire Tv - አማርኛ:

Share