Mesrak SPORT / ምስራቅ ስፖርት

Mesrak SPORT / ምስራቅ ስፖርት welcome to the OFFICIAL Mesrak Sport | ምስራቅ ስፖርት is one of GSMN
ሀገራዊ ስፖርት በልዩነት!

ዜና | ማንቸስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን በአንፊልድ አሸነፈ።MS ጥቅምት 09 ፥2018 ዓ.ም |በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ ማንቸስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸ...
19/10/2025

ዜና | ማንቸስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን በአንፊልድ አሸነፈ።

MS ጥቅምት 09 ፥2018 ዓ.ም |

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ ማንቸስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

ለዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ሙሉ ሶስት ነጥብ ያስገኘለትን ጎሎች ብሪያን ምቦሞ እና ሀሪ ማጉዌር ሲያስቆጥሩ ለሊቨርፑል ደግሞ ጋክፖ ሊያስቆጥር ችሏል።

ምስራቅ ስፖርት

19/10/2025

ለጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ ክብር ታስቦ የኢትዮጵያ ፖስታ ቤት ድርጅት ያሳተመው ቴምብር ፤ በ 1960 ዓ.ም

Stamp issued in honor of the heroic athlete Shambel Abebe Bikila; 1968



youtube.com/

19/10/2025
ቅዱስ ጊዮርጊስ የ19ኛው የአዲስ አበባ ከተማ የህዳሴ ዋንጫ ሻምፒዮና ሆነ፤19ኛው የአዲስ አበባ ከተማ የህዳሴ ዋንጫ በአዲስ አበባ ስታድዮም ፍፃሜውን ያገኝ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 2 ...
12/10/2025

ቅዱስ ጊዮርጊስ የ19ኛው የአዲስ አበባ ከተማ የህዳሴ ዋንጫ ሻምፒዮና ሆነ፤

19ኛው የአዲስ አበባ ከተማ የህዳሴ ዋንጫ በአዲስ አበባ ስታድዮም ፍፃሜውን ያገኝ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 2 ለ1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሻምፒዮና መሆን ችሏል።

ሽልማቱን ክቡር መኪዩ መሐመድ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ በላይ ደጀን እና የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ሰጥተዋል።

ቅዱስ ጊዮርጊስ ሻምፒዮና መሆኑን ተከትሎ የዋንጫ እና የወርቅ ሜዳልያ ሲበረከትለት መቻል የብር ሜዳልያ ሽልማት ተሸላሚ በመሆን የአዲስ አበባ ከተማ የህዳሴ ዋንጫ ፍፃሜውን አግኝቷል። ( MOCS )

ጥቅምት 02፣ 2018ዓ.ም

ምስራቅ ስፖርት

በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ስፓርታዊ እንቅስቃሴን  ባህል ፣ የአኗኗር ዘይቤ ፣ ጤናን መጠበቂያ ፣ ማህበራዊ ግንኙነትን ማጎልበቻ መንገድ እያደረጉት ይገኛል ።በየእለቱ በተለይም በእረፍት ቀናት ህ...
12/10/2025

በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ስፓርታዊ እንቅስቃሴን ባህል ፣ የአኗኗር ዘይቤ ፣ ጤናን መጠበቂያ ፣ ማህበራዊ ግንኙነትን ማጎልበቻ መንገድ እያደረጉት ይገኛል ።

በየእለቱ በተለይም በእረፍት ቀናት ህፃናት ፣ወጣቶች ፣አረጋዉያን በተናጠል እና በጋራ የተለያዩ ስፓርታዊ እንቅስቃሴዎችን በመኖሪያ አካባቢ እና ከትራፊክ እንቅስቃሴ ዝግ በሆኑ መንገዶች ሲያከናዉኑ መመልከት የተለመደ ሆኗል ።

ማዕከላቱ ጤናን ለመጠበቅ ፣ ተተኪ ስፓርተኞችን ለማፍራት የሚያግዙ በመሆናቸዉ ህብረተሰባችንም ወደ ማዕከላቱ በመሄድ ስፓርታዊ እንቅስቃሴዎች የማድረግ ልምምዱን ይበልጡን ማሳደግ ይገባዋል ። ( MOCS )

ድሬዳዋ ከተማ እግር ኳስ ክለብ የድሬ ካፕ ሻምፒዮን ሆነ። የድሬደዋ ከተማ ዋንጫ በድሬ ከነማ ቡድን አሸናፊነት ተጠናቋል ።በ5 ክለቦች መካከል ሲያካሂዱት የቆየው የድሬ ካፕ ዋንጫ ድሬደዋ ከተ...
12/10/2025

ድሬዳዋ ከተማ እግር ኳስ ክለብ የድሬ ካፕ ሻምፒዮን ሆነ።

የድሬደዋ ከተማ ዋንጫ በድሬ ከነማ ቡድን አሸናፊነት ተጠናቋል ።

በ5 ክለቦች መካከል ሲያካሂዱት የቆየው የድሬ ካፕ ዋንጫ ድሬደዋ ከተማን በ10 ነጥብ ሻምፒዮን በመሆን ፍፃሜው አግኝቷል። በ8 ነጥብ 2ኛ ደረጃን ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርሲቲ በ7 ነጥብ ጂቡቲ ሪፐብሊካን 3ኛ ደረጃ ይዞ አጠናቋል ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር በክብር እንግድነት ተገኝተው ለአሸናፊው ዋንጫ እና ልዩ ሽልማት አበርክተዋል ። የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ እና የንግድ ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሀርቢ ቡህ ፤ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ሽልማቶች ተበርክቷል ።

ጥቅምት 02 ፥2018 ዓ.ም | ድሬ

ምስራቅ ስፖርት

ዜና l በድሬዳዋ የሮጉራ ሉጂ መታሰቢያ የብስክሌት ውድድር ተፈፀመበአንጋፋው ብስክሌተኛ ጀማል ሮጉራ እና ቤተሰቦቹ አዘጋጅነት በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ ምድር ባቡር ኮሪደር ልማት ጉዳና በተካሄደ...
12/10/2025

ዜና l በድሬዳዋ የሮጉራ ሉጂ መታሰቢያ የብስክሌት ውድድር ተፈፀመ

በአንጋፋው ብስክሌተኛ ጀማል ሮጉራ እና ቤተሰቦቹ አዘጋጅነት በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ ምድር ባቡር ኮሪደር ልማት ጉዳና በተካሄደው የሲኞር ሮጉራ ሉጂ መታሰቢያ የብስክሌት የግል ውድድር እጅግ አጓጊ እና ደማቅ ሆኖ ተጠናቋል።

በዚህ የመታሰቢያ ውድድር ላይ የዓለም አቀፋ ብስክሌተኛ አሊሶን ጃክሶን በእንግድነት ተገኝታለች። በርካታ ተመልካች በተከታተለው ጨዋታ በመለስተኛ ኮርስ እና በከፍተኛ ኮርስ የግል የበላይነት ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ በመውጣት ለአሸነፉ ተወዳዳሪዎች ከ5000 ብር እስከ 3000 ብር ተሸልመዋል።

በውድድሩ በከፍተኛ ኮርስ የድሬዳዋ ከነማው ተወዳዳሪ ኦብሳ በግሩም አጨራረስ ብቃቱ አሸንፏል። በመጨረሻም በውድድሩ አስተዋጽኦ ላደረጉ የምስጋና የምስክር ወረቀት እና ለአሸናፊዎች የገንዘብ ሽልማቱን ከዕለቱ የክብር እንግዶች ተበርክቶላቸዋል ።

ምስራቅ ስፖርት

10/10/2025

MS ዜና l በድሬዳዋ የሮጉራ ሉጂ መታሰቢያ የብስክሌት ውድድር እሁድ በከዚራ ዙሪያ እንደሚካሄድ ተገለፀ ።

አንጋፋው ብስክሌተኛ ጀማል ሮጉራ እና ቤተሰቦቹ አዘጋጅነት የሮጉራ መታሰቢያ የብስክሌት ውድድር እሁድ በምድር ባቡር ኮሪደር ልማት መንገድ እንደሚካሄድ ተገልጿል ። በዚህ ውድድር ላይ በአለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂዋ ተጫዋች አሊሶን ጃክሶን እንደምትገኝ አዘጋጆቹ ተናግረዋል ።

የዓለም አቀፋ ብስክሌተኛ አሊሶን ጃክሶን ለስራ ጉብኝት ድሬዳዋ ነገ ትገባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ ከኦሎምፒክ እስከ አውሮፓ የብስክሌት ሻምፒዮና ተወዳዳሪ ዝነኛዋ ሴት ብስክሌተኛ አሊሶን ጃክሶን በድሬዳዋ የፊታችን እሁድ በከዚራ ምድር ባቡር ኮሪደር ልማት መንገድ በሚካሄደው የሮጉራ ሉጂ መታሰቢያ የብስክሌት ክለቦች እና የታዳጊዎች ጨዋታዎችን በእንግድነት እንደምትገኝ ኘሮፈሽናል ተጫዋቹ ኪያ ጀማል ገልጿል ።

ታዋቂዋ ብስክሌተኛ አሊሶን ጃክሶን ከዓለም ቱር እስከ ፓሪስ Roubaix ጨዋታውን አሸንፋለች ። የካናዳ ሻምፒዩና ነች ፤ የቮላታ በስፔን ደረጃ አሸናፊዋ አሊሶን ሁለት ጊዜ ኦሎምፒክ ብስክሌት ውድድር ተሳትፋለች ።

የምስራቁን ብስክሌት ታዳጊ ወጣቶች ለማፍራት ታዋቂ ሴት ብስክሌተኛዋ በድሬዳዋ ብስክሌት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተጠቁሟል ።

የፊታችን እሁድ በአንጋፋው ብስክሌተኛ ጀማል ሮጉራ እና ቤተሰቡ የቀድሞ የድሬዳዋ ብስክሌት ባለታሪክ በአባቱ ስም ሮጉራ ሉጂ የመታሰቢያ የክለብና ታዳጊዎች ብስክሌት ውድድር ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል::

ታዋቂው ብስክሌተኛ ጀማል ሮጉራ እና ቤተሰቡቹ የስፖርት ቤተሰብ ውድድሩን በስፍራው ተገኝተው እንዲከታተሉ ጥሪ አድርገዋል፡፡

መስከረም 30/2018
Mesrak Sport ምስራቅ ስፖርት

09/10/2025

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት እና የካፍ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ ኢሳያስ ጅራ የፊፋ የፀረ-ዘረኝነት እና ፀረ-አግላይነት ኮሚቴ አባል ሆነው ለቀጣዮቹ አራት ዓመታት እንዲሰሩ በፊፋ ተመርጠዋል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በክቡር ፕሬዝዳንታችን ሹመት የተሰማውን ደስታ እየገለጸ መልካም የሥራ ዘመን ይመኛል።

EFF President and CAF Executive Committee member Isayas Jira has been appointed by FIFA as a member of the FIFA Anti-Racism and Anti-Discrimination Committee for the 2025–2029 term.

The Ethiopian Football Federation expresses its delight over the appointment of our esteemed President and wishes him a successful and impactful term of service.

ዜና | የድሬዳዋ ዋንጫ የእግር ኳስ ውድድር ነገ በሚካሄዱ ሁለት ጨዋታዎች ይቀጥላል።የድሬ ካፕ ውድድር ነገ አርብ መስከረም 30 ቀን 2018 በድሬዳዋ አለም አቀፍ ስታድየም ሁለት ጨዋታ ይካሄ...
09/10/2025

ዜና | የድሬዳዋ ዋንጫ የእግር ኳስ ውድድር ነገ በሚካሄዱ ሁለት ጨዋታዎች ይቀጥላል።

የድሬ ካፕ ውድድር ነገ አርብ መስከረም 30 ቀን 2018 በድሬዳዋ አለም አቀፍ ስታድየም ሁለት ጨዋታ ይካሄዳል ።

የጨዋታ ኘሮግራም ፦

ጅቡቲ ሪፐብሊካን ከ ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲ 10፡00 ይጫወታሉ ፤ ድሬ ምርጥ ከ ጅቡቲ ቴሌኮም 12፡00 ይገናኛሉ።

ድሬዳዋ ከተማ በ3 ጨዋታ በ7 ነጥብ ውድድሩን እየመራ ይገኛል። ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ደግሞ በ2 ጨዋታዎች 5 ነጥብ በመሰብሰብ 2ኛ ላይ ተቀምጧል ፤

ጅቡቲ ሪፐብሊካን በ2 ጨዎታዎች በ3 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ይዟል። ጅቡቲ ቴሌኮም በ2 ጨዋታ በ2 ነጥብ 4ኛ ደረጃ ይገኛሉ። ( DFF )

መስከረም 29፥2018 ዓ.ም | ድሬ

Mesrak Sport ምስራቅ ስፖርት

3ኛው የፓን አፍሪካኒዝም የተማሪዎች እግር ኳስ ውድድር በድሬዳዋ ስታዲዮም የመክፈቻ ስነ-ስርዓት ተካሄደ።ክቡር መኪዩ መሐመድ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ...
09/10/2025

3ኛው የፓን አፍሪካኒዝም የተማሪዎች እግር ኳስ ውድድር በድሬዳዋ ስታዲዮም የመክፈቻ ስነ-ስርዓት ተካሄደ።

ክቡር መኪዩ መሐመድ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በውድድሩ መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የማህበረሰብን ተሳትፎ ለማረጋገጥ እና ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ትክክለኛው ቦታ ትምህርት ቤት መሆኑን በመልዕክታቸው አስተላልፈዋል።

የአገራችን ስፖርት ፖሊሲ የስፖርት ልማትን በሶስት ቦታዎች ማለትም በመኖሪያ አካባቢ፣ በመሥሪያ ቦታዎች እና በትምህርት ተቋማት እንደሚከናወን ያመላከቱት ሚኒስትር ዴኤታው ለስፖርት ልማት ትምህርት ቤትን ተመራጭ መሆኑን አፅዕኖት ሰጥተዋል።

በስፖርት ፖሊሲ እንደተመላከተው ስፖርትን በትምህርት ተቋማት ውስጥ ለማስፋፋት ከተቀመጡ ስለቶች መካከል ተማሪዎች በስፖርት ውስጥ እንዲሳተፉ ምቹ ሁኔታ መፍጠር፣ በትምህርት ቤቶች ውስጥ የስፖርት ትጥቅና መሣሪያዎች እንዲሟሉ ማድረግ፣ በትምህርት ተቋማት የስፖርት ክበባትን ማቋቋም ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ሚኒስትር ዴኤታው አክለዋል።

ይህ ውድድር የህዳሴ ግድብ በተመረቀበት፣ ጋዝ እንደ ሀገር ለመጀመሪያ ጊዜ ማምረት በተቻለበት እንዲሁም የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ መሠረተ- ድንጋይ የተቀመጠበት ጊዜ መካሄዱ ለየት ያደርገዋል ብለዋል።

ክቡር አቶ ሱልጣን አልይ የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ በበኩላቸው ትምህርት ቤት የተማሪዎች መፍለቂያ በመሆኑ በትምህርት ተቋማት ስፖርታዊ ስልጠናዎችንና ውድድሮችን ማካሄድ አስፈላጊነትን በመግለፅ በትምህርት ተቋማት ተተኪ ስፖርተኞችን ማፍራት ቀዳሚ ተግባር እንደሆነ ገልፀዋል።

3ኛው የፓን አፍሪካኒዝም የተማሪዎች እግር ኳስ ውድድር ከውድድርም ባሻገር ተማሪዎች የዕርስ በዕርስ ትውውቅ የሚያደርጉበት፣ የልምድ ልውውጥ የሚካሄዱበት እንዲሁም ወንድማማችንነትን የሚያንፀባርቁበት እና ተተኪ ስፖርተኞች የሚፈሩበት እንደሆነም አክለዋል።

በ3ኛው የፓን አፍሪካኒዝም የተማሪዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ ኦሮሚያ ፣ ድሬዳዋ፣ አዲስ አበባ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ሀረሪ ክልልና ከተማ አስተዳደሮች ትምህርት ቤት የተውጣጡ ተማሪዎች እየተሳተፋ ይገኛል።

በመክፈቻ መርሃ ግብሩ ክቡር መኪዩ መሐመድ፣ ክቡር አቶ ሱልጣን አልይ የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር ካሊድ መሐመድን ጨምሮ የፌዴራልና የአስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በድምቀት ተጀምሯል።

ውድድሩም ከመስከረም 29 ቀን 2018 እስከ ጥቅምት 3 ቀን 2018 በድሬዳዋ የሚካሄድ ሲሆን በመክፈቻ ጨዋታ በወንዶች ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የጉጉባ ት/ቤት የሶማሌ ክልል ጅጅጋ ት/ቤትን 1ለ0 አሸንፏል።

መስከረም 29፣ 2018ዓ.ም ድሬ

Mesrak Sport ምስራቅ ስፖርት

Address

Dire Dawa
6068@2024

Telephone

+251915750424

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mesrak SPORT / ምስራቅ ስፖርት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Mesrak SPORT / ምስራቅ ስፖርት:

Share

Category