Mesrak SPORT / ምስራቅ ስፖርት

Mesrak SPORT / ምስራቅ ስፖርት welcome to the OFFICIAL Mesrak Sport | ምስራቅ ስፖርት is one of GSMN
ሀገራዊ ስፖርት በልዩነት!

ማንቼን ሰኞ ሰኞ እያጫወቱ ሰንጠረዡ ይህን መስሏል። እውነት ለመናገር የዋንጫውን ነገር ለሲቲ ብንተወው ይሻላል። መከረኛው 2ኛን ማንም አይነካበትም። የማንቼ ትግል ከፍ ሲል ለዋንጫው ዝቅ ሲል...
14/12/2025

ማንቼን ሰኞ ሰኞ እያጫወቱ ሰንጠረዡ ይህን መስሏል። እውነት ለመናገር የዋንጫውን ነገር ለሲቲ ብንተወው ይሻላል። መከረኛው 2ኛን ማንም አይነካበትም። የማንቼ ትግል ከፍ ሲል ለዋንጫው ዝቅ ሲል ለቻንፒየንስ ሊግ ቦታ ነው። ማንቼ ጥገናዊ ለውጡን አልጨረሰም። ሲጨርስ ወየውላችሁ‼

ይቺን ስለ እሱ እናውራ‼️ ከስኬቷ ጀርባ ስላለው ስለ ዝምተኛው ባለሙያ፥ ስለ አሰልጣኟ፥ ስላልተዘመረለት ባለቤቷ፥ ስለ ልጆቿ አባት፥ ስለ እሱ እናውራ የባንክ አውቶቢስ፥ የስፖርተኞቹ ሰርቪስ ...
14/12/2025

ይቺን ስለ እሱ እናውራ‼️

ከስኬቷ ጀርባ ስላለው ስለ ዝምተኛው ባለሙያ፥ ስለ አሰልጣኟ፥ ስላልተዘመረለት ባለቤቷ፥ ስለ ልጆቿ አባት፥ ስለ እሱ እናውራ

የባንክ አውቶቢስ፥ የስፖርተኞቹ ሰርቪስ የፍቅር በር ከፈተላቸው

ከ27 አመት በፊት እሷ የንግድ የባንክ ሯጭ፥ እሱ ደግሞ የክለቡ የ C ቡድን ተጫዋች ሆነው ተዋወቁ፥ መሰረት ደፋር እና ቴዎድሮስ ሀይሉ

በአንዱ ቀን ከልምምድ በኋላ የኳሱና የአትሌቲክሱ ቡድን አባላት ምሳ ለመመገብ በአንድ አውቶቢስ ወደ ክለቡ ሲመለሱ መሰረት እሱ ካለበት አጠገብ ተቀመጠች፤ በፈገግታ ተቀበላት፤ ከጎኑ ወንበር የተጋራችው ግራ ጎኑ ትሆናለች ብሎ ግን አላሰበም

ገና በመጀመሪያ ቀን ትውውቃቸው ውሃ ሰጣት፤ ውሃ አጣጩ እንደምትሆን ግን አልገመተም፤ ተግባቡ፤ ደጋግመውም ተገናኙ፤ ጓደኛሞች ሆኑ

ታሳዝነዋለች...

በቻለው አቅም ያግዛታል፤ ከክለቡ ምግብ ቀንሶ በቱታው ኪስ ደብቆ ይዞላት ይሄዳል፤ ሳንድዊች እየሰራ ያቀብላታል

መሰረት ያኔ የ250 ብር ወርሃዊ ደሞዝተኛ ነበረች፤ የአትሌቲክስ ፍቅርና ችሎታ ብቻ እንጂ ኢኮኖሚያዊ አቅም የሌላት ምስኪን፥ ከደሞዟ ቀንሳ ለቤተሰቧ የምትሰጥ ተስፈኛ አትሌት፥ ባቄላ እየሸጠች እናቷን የምትረዳ ልባም ወጣት፥ እናም ያዝንላታል

ይንከባከባታል....

ሰውነቷ እንዲጠነክር የላም ወተት ተከራይቶላት አቅመኛ እንድትሆን ያግዛታል

በሌላኛው ቀን ደግሞ ከራሱ ቀንሶ በሶ እየበጠበጠ ጃንሜዳ ይዞላት ይሄዳል፤ ከልምምድ በኋላ ሁለቱ ስፖርተኞች አረፍ ብለው በሷቸውን እየተጎነጩ ይመካከራሉ

ባለው አቅም ሁሉ ያግዛታል...

መሰረት ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ እድል ያገኘች ጊዜ ለኤምባሲ የምትከፍለው ብር አጠራት፤ እያለቀሰች አማከረችው፤ ሳቋን እንጂ እንባዋን ማየት የማይፈልገው ቴዲ ሁለቴ ማሰብ ሳይፈልግ እናቱ በስጦታ ያበረከቱለትን የአንገት ሃብል ሸጠውና ብሩን ሰጣት፤ ጉጉቷ ተሳክቶ ሄደች፤ በድል ተመለሰች

ከአንገቱ የማይጠፋው ሃብል አለመኖሩን የተረዱት እናቱ 'ልጄ ዱርዬ ሆነ፥ ሱስ ጀመረ፥ ቁማር ውስጥ ገባ' ብለው ከቤት አባረሩት፤ ይባስ ብሎ ከባንክ እግር ኳስ ተጫዋችነቱም ተቀነሰ፤ ወጣቱ ቴዲ ግን ቅድሚያ ለመሲ አለ

ያበረታታል፥ ደጀን ይሆንላታል...

ሙሉ ትኩረቱን ለእሷ አድርጎ የአትሌቲክስ አሰልጣኝነት ኮርስ ወስዶ መሰረት- መሰረት እንዲኖራት እየጣረ ለስኬቷ መልፋቱን ቀጠለ፤ በኦሊምፒክ ሁለት ወርቅና አንድ ብር ስታጠልቅ፥ በአለም ሻምፒዮና ሁለት ወርቅ አንድ ብርና ሁለት ነሀስ ለሃገሯ ስታመጣ፥ በአለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አራት ወርቅ አንድ ብርና አንድ ነሀስ ስታገኝ በጥቅሉ በሩጫ ህይወቷ 183 ውድድር አድርጋ 161 ስታሸንፍ በእያንዳንዱ ዱካዋ የእሱ አሻራ ታትሞበታል፤ ስትበደል ቀዳሚ ተሟጋቿ፥ ስትደክም ከፊት ያለ አበርቺዋ፥ ስትገፋ ድምፅዋ ሆኖ ሁለት አስርት አመታትን ተሻግሯል፤ ክብረወሰን ስትሰብርና የአለም ኮከብ አትሌት ተብላ የንግስና ዘውድ ስትጭን ቀዳሚ ደስታ ተጋሪዋ፥ በሴራ ስትገለል እንባ አባሽ አጋሯ ሆኖ ከርሟል

የመሰረት ባል ቴዲ አሁንም ወጣት አትሌቶችን እያሰለጠነ ለኦሊምፒክና ለአለም ሻምፒዮና እያበቃ ይገኛል፤ ታላላቅ አትሌቶችን አሰልጥኗል፤ አሁን የእነ መዲና ኢሳ፣ ሳሙኤል ፍሬው፣ ፋንታዬ በላይነህና ሌሎች በርካታ አትሌቶች አሰልጣኝ ነው

አሁንም ይሳሳላታል..

የመሲና የቴዲ በአውቶቢስ ጉዞ ከጎን በመቀመጥ የጀመረው ትውውቅ በ2004 ወደ ትዳር አድጎ ሶስት ልጆችን አፍርተው ሁለት ተጨማሪ ልጆችን አሳድገው እዚህ ደርሰዋል፤ ልክ እንደ ድሮው አሁንም ያዝንላታል፥ ይንከባከባታል፥ ያግዛታል፥ ያበረታታል፥ መከታ ይሆንላታል፥ ዛሬም ይሳሳላታል፥ መሰረትም እንደዛው

ስለ እሱ ነው ያወራነው፤ ስለ ውሃ አጠጪው፥ ስለ ወተት ተከራዩ፥ ስለ በሶ አቅራቢው፥ ስለ ሃብል ሻጩ፥ ስለ አሰልጣኙ፥ ስለ ባልና አባቱ፥ ስለ መሰረት- መሰረት፥ አዎ ስለ ቴዎድሮስ ሀይሉ

የወቅቱ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ጀግናዋ አትሌት መሰረት ደፋር ዛሬ ዕሮብ ህዳር 10 የልደት ቀኗ ነው፤ ስለ እሷ ብዙ ተብሏል፤ ሀገርን በአለም አደባባይ ከፍ አድርጋ፥ ሰንደቋን በኩራት አሰቅላ፥ መዝሙሯን አዘምራ ኢትዮጵያን አስጠርታለች፤ እናም ለኢትዮጵያ እንኳን ተወለድሽላት፤ ከትናንት ጅማሬዋ እስከ አሁኑ ክብሯ አብሯት ላለው ሁሌ ከአፏ ለማይጠፋው ከመጋረጃ ጀርባ ለተደበቀው ለባለቤቷ ቴዎድሮስ ሀይሉ ደግሞ እንዲህ እንላለን፤ ለመሰረት- መሰረት ስለሆንክ እናመሰግናለን፥ ላንተም እንኳን ተወለደችልህ! ( በታምሩ ዓለሙ የተዘጋጀ )

ምስራቅ ስፖርት

ኢትዮጵያ በብስክሌት ከአፍሪካ በቀዳሚነት አጠናቀቀች2 ወርቅ - 2 ብር - 2 ነሀስበ4ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታ የኢትዮጵያ ወጣት ቡድን ተጨማሪ ሜዳልያ አግኝቷል፡፡በብስክሌት ወንዶች የጎዳና...
14/12/2025

ኢትዮጵያ በብስክሌት ከአፍሪካ በቀዳሚነት አጠናቀቀች

2 ወርቅ - 2 ብር - 2 ነሀስ

በ4ኛው የአፍሪካ ወጣቶች ጨዋታ የኢትዮጵያ ወጣት ቡድን ተጨማሪ ሜዳልያ አግኝቷል፡፡

በብስክሌት ወንዶች የጎዳና ላይ ውድድር ለገሰ ሰለሞን ለኢትዮጵያ የብር ሜዳልያ አስገኝቷል፡፡

በአጠቃላይ በብስክሌት ስፖርት ኢትዮጵያ ሁለት ወርቅ ሁለት ብርና ሁለት ነሀስ በማግኘት በቀዳሚነት አጠናቃለች፡፡

MS ዜና l በድሬዳዋ ናትናኤል ጥላሁን ከGR ክለብ የግል ብስክሌት ውድድርን አሸነፈ ፤ አሚር ጃፈር ከቶቶ ክለብ 2ኛ ወጥቷል ፡፡ፍሪ የተጣራ የተፈጥሮ ውሃ ከድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን...
16/11/2025

MS ዜና l በድሬዳዋ ናትናኤል ጥላሁን ከGR ክለብ የግል ብስክሌት ውድድርን አሸነፈ ፤ አሚር ጃፈር ከቶቶ ክለብ 2ኛ ወጥቷል ፡፡

ፍሪ የተጣራ የተፈጥሮ ውሃ ከድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ጋር በመተባበር የከፍተኛ ኮርስ እና መለስተኛ ኮርሰ የግል ብስክሌት ውድድር በድሬዳዋ ተካሄደ ።

ዛሬ በድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ፊት ለፊት በተካሄደው 25 ዙር በሸፈነው 39 ተወዳዳሪዎች ባደረጉት ማራኪ ጨዋታ ናትናኤል ጥላሁን ከGR ክለብ በግሩም አጨራረስ አሸናፊ ሆኗል ። የድሬ ቶቶው ተወዳዳሪ አሚር ጃፈር 2ኛ ሲወጣ ሀብቶም ሀይላይ ካሳ ከድሬ ቶቶ ክለብ 3ኛ ደረጃ በመያዝ አሸንፈዋል ።

በመለስተኛ ኮርስ በምድብ B ረመዳን በያን ፤ አብዱልቃድር ታረቀኝ እና ብሩክ በጋሻው ከ1ኛ እስከ 3ኛ በመውጣት አሸንፈዋል።
በዕለቱ በየአምስቱ ዙር ጨዋታ ቮላታ መካሄዱ በተወዳዳሪዎች መካከል አዝናኝና ጠንካራ ፉክክርን አስመልክቷል።

በዚህ ጨዋታ አሸናፊ ተወዳዳሪዎች የተዘጋጀላቸውን የማበረታቻ ገንዘብ ከድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ማሳተፍና ማልማት ዳሬክቶሬት ዳሬክተር ከአቶ ኢብሳ ዱሪ እና ከአዘጋጁ ፍሪ የተጣራ የተፈጥሮ ውሃ ስራ አስኪያጅ ከአቶ ዳዊት ሰለሞን እንዲሁም ከአስተዳደሩ ም/ቤት ተወካይ ከአቶ አህመድ አብዶ እና ከአቶ ዳንኤል ምትኩ የቶቶ ስፖርት ክለብ ም/ኘሬዚዳንት ሽልማቱን አበርክተዋል ።

በቀጣይ ሳምንት ውድድሩ 2ኛ ቀን ጨዋታ ይካሄዳል ።

DYSC l ህዳር 07 ቀን ፣ 2018 l

ምስራቅ ስፖርት Mesrak Sport

ME ዜናl ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት " በሚል መሪ ቃል 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን በማስመልከት በድሬዳዋ የማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት...
16/11/2025

ME ዜናl ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት " በሚል መሪ ቃል 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን በማስመልከት በድሬዳዋ የማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሄደ ።

በድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን አስተባባሪነት በተካሄደው የማስ ስፖርት እንቅስቃሴው የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ፣የአስተዳደር ም/ቤት አፈጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፈቲያ አደን፣ የወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ካሊድ መሐመድ ፣ ከፍተኛ አመራሮች ፣ ወረዳዎች ፣ ስፖርተኞች፣ አሰልጣኞች፣ የኮሚሽኑ ባለሙያዎች እና ህብረተሰቡ ተሳትፈዋል ።

ህዳር 7/2018
Mesrak Sport

የአውሮፓ ሀገራት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎችየአውሮፓ ሀገራት ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ ዛሬ ወሳኝ የማጣሪያ ጨዋታዎችን በተለያዩ ከተሞች ያደርጋሉ።ምድብ ሁለትን በ10 ነጥብ እና በዘጠኝ ንጹሕ...
15/11/2025

የአውሮፓ ሀገራት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች

የአውሮፓ ሀገራት ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ ዛሬ ወሳኝ የማጣሪያ ጨዋታዎችን በተለያዩ ከተሞች ያደርጋሉ።

ምድብ ሁለትን በ10 ነጥብ እና በዘጠኝ ንጹሕ የግብ ክፍያ እየመራች የምትገኘው ስዊዘርላንድ በአንድ ነጥብ ግርጌ ላይ ከተቀመጠችው ስዊድን ጋር ምሽት 4:45 ትጫወታለች።

በሌላ የምድብ ሁለት ጨዋታ ከአራት ጨዋታዎች ሦስት ነጥብ የያዘችው ስሎቫኒያ እና በሰባት ነጥብ እና በአንድ የግብ ዕዳ ከምድቡ በሁለተኛነት ከምትገኘው ኮሶቮ ጋር ምሽት 4:45 ጨዋታቸውን ያደረጋሉ።

በ10 ነጥብ ምድብ ሦስትን የምትመራው ዴንማርክ እስካሁን ያደረገቻቸውን አራት ጨዋታዎች ከተሸነፈችው ቤላሩስ ጋር ትጫወታለች። ጨዋታው ምሽት 4:45 ላይ የሚካሄድ ይኾናል።

በሌላ የምሽት ጨዋታ 2:45 ላይ 10 ነጥብ ብትይዝም በስድስት የግብ ክፍያ በዴንማርክ የተበለጠችው ስኮትላንድ ወደ ግሪክ አምርታ ትገጥማለች።

በምድብ አምስት ጆርጅያ ከስፔን፣ ተርክዬ ከቡልጋሪያ ምሽት 2:00 ላይ ይጫወታሉ። በጨዋታው ስፔን ድል አድርጋ ተርክዬ ነጥብ ከጣለች ስፔን በቀጥታ አላፊ ትኾናለች።

በምድብ ስምንት ቆጵሮስ ከኦስትሪያ ምሽት 2:00፤ ቦሲኒያ ሄርዝጎቪኒያ ከሩማኒያ ምሽት 4:45 ላይ ይጫወታሉ።

ምድብ 10 ላይ ካዛኪስታን ከቤልጀየም ቀን11:00 ላይ የሚጫወቱ ይኾናል። ቤልጀየም ካሸነፈች አላፊ ትኾናለች። በዚሁ ምድብ ሌችስታይን ከዌልስ ምሽት 2:00 ላይ ይጫወታሉ ሲል ቢቢሲ በድረ ገጹ አስነብቧል። (Ameco )

ኅዳር 06/2018 ዓ.ም

Mesrak Sport

ምርጥ ብቃት ላይ የሚገኙ የፊት መስመር ተጫዋቾች ...ለቡድናቸው እና ለሀገራቸው ግቦችን በማስቆጠር ጥሩ ጊዜ እያሳለፉ የሚገኙ ምርጥ የፊት መስመር ተጫዋቾች ናቸው፡፡ኖርዌያዊው ኤርሊንግ ብራው...
15/11/2025

ምርጥ ብቃት ላይ የሚገኙ የፊት መስመር ተጫዋቾች ...

ለቡድናቸው እና ለሀገራቸው ግቦችን በማስቆጠር ጥሩ ጊዜ እያሳለፉ የሚገኙ ምርጥ የፊት መስመር ተጫዋቾች ናቸው፡፡

ኖርዌያዊው ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ፣ እንግሊዛዊው ሃሪ ኬን እና ፈረንሳዊው ኪሊያን ምባፔ፡፡

የ25 ዓመቱ የማንቼስተር ሲቲ የፊት መስመር ተጫዋች ሃላንድ በ2025/26 የውድድር ዓመት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ባደረጋቸው 11 ጨዋታዎች 14 ኳሶችን ከመረብ ጋር በማገናኘት የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃን ይዟል፡፡

በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ደግሞ ለሲቲ ባደረጋቸው 4 ጨዋታዎች ልክ እንደ ወቅቱ ምርጦች ሃሪ ኬን እና ኪሊያን ምባፔ 5 ግብ ማስቆጠር ችሏል፡፡

ለሀገሩ ኖርዌይ ደግሞ በዚህ የውድድር ዓመት እስካሁን ባደረጋቸው ጨዋታዎች 14 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ ሌላው በዚህ የውድድር ዘመን ድንቅ ጊዜ እያሳለፉ ከሚገኙ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው፡፡

የሪያል ማድሪዱ ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ በስፔን ላሊጋ በውድድር ዓመቱ ባደረጋቸው 12 ጨዋታዎች 13 ግብ በማስቆጠር የላሊጋውን ከፍተኛ ግቢ አግቢዎች ደረጃ በመምራት ላይ ይገኛል፡፡

በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ቡድኑ ድል እንዲያደርግ ትልቁን አስተዋፅኦ እያበረከተ የሚገኘው ኪሊያን ምባፔ በ4 ጨዋታ 5 ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡

የ26 ዓመቱ ኪሊያን ምባፔ ለሀገሩ ፈረንሳይ በ2025/26 እስካሁን ባደረጋቸው ጨዋታዎች 5 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

እንግሊዛዊው የ32 ዓመቱ የባየርን ሙኒክ የፊት መስመር ተጫዋች ሃሪ ኬን በዚህ የውድድር ዓመት ስኬታማ ጊዜ እያሳለፈ ሲሆን፤ በውድድር ዓመቱ በጀርመን ቡንደስሊጋ እስካሁን ባደረጋቸው 10 ጨዋታዎች 13 ግብ በማስቆጠር የቡንደስሊጋውን ኮከብ ጎል አስቆጣሪነት እየመራ ነው፡፡

በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ለሙኒክ ባደረጋቸው 4 ጨዋታዎች 5 ግብ በማስቆጠር ድንቅ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል፡፡

በዲኤፍቢ ፖካል 4 እና በሱፐር ካፕ ደግሞ 1 ግብ ማስቆጠር የቻለው ሃሪ ኬን በሁሉም ውድድር ለሙኒክ 3 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል፡፡

ሃሪ ኬን ለሀገሩ እንግሊዝም 6 ግቦችን በማስቆጠር በብሔራዊ ቡድኑ ጥሩ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል፡፡

ምርጥ ብቃታቸውን እያሳዩ የሚገኙት ሦስቱም ተጫዋቾች በሚጫወቱበት ሊግ የኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃውን እየመሩ ይገኛል፡፡

የወቅቱ የፊት መስመር ድንቅ ተጫዋቾች በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ በተመሳሳይ 5 ግቦችን ያስቆጠሩ ሲሆን ማን የተሻለ ሆኖ የውድድር ዓመቱን ያጠናቅቃል የሚለው ይጠበቃል፡፡ ( FBC )

ሕዳር 6፣ 2018

ምስራቅ ስፖርት

MS ዜና l የሴካፋ ከ17ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ውጤት ዩጋንዳ 4 -0 ቡሩንዲን አሸንፈችድሬዳዋ ስታዲዩም 🇧🇮 Burundi 0-4 Uganda 🇺🇬11' 28' Thomas Og...
15/11/2025

MS ዜና l የሴካፋ ከ17ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ውጤት
ዩጋንዳ 4 -0 ቡሩንዲን አሸንፈች

ድሬዳዋ ስታዲዩም

🇧🇮 Burundi 0-4 Uganda 🇺🇬

11' 28' Thomas Ogema
31' 41' Owen Mukisa

TotalEnergies U17 AFCON qualifiers - Group B - MD 1 (GAME 2)

ህዳር 6/2018

Mesrak Sport ምስራቅ ስፖርት

15/11/2025
የታንዛኒያ ብሔራዊ ቡድን በሰፋ ግብ ሱዳንን አሸንፏል፡፡ MS ዜና l ኢትዮጵያ የምታዘጋጀው ከ17 ዓመት በታች የሴካፋ ውድድር ዛሬ በድሬዳዋ ስታዲዩም በመጀመሪያው ጨዋታ  ታንዛኒያ እና ሱዳን...
15/11/2025

የታንዛኒያ ብሔራዊ ቡድን በሰፋ ግብ ሱዳንን አሸንፏል፡፡

MS ዜና l ኢትዮጵያ የምታዘጋጀው ከ17 ዓመት በታች የሴካፋ ውድድር ዛሬ በድሬዳዋ ስታዲዩም በመጀመሪያው ጨዋታ ታንዛኒያ እና ሱዳንን ያገናኘው ጨዋታ ታንዛኒያ በግማሽ ደርዘን ጎል 6 ለ 0 ውጤት አሸንፈው ወጥተዋል፡፡

የሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ

‎⏱️ 2:00 | 🇧🇮 ቡሩንዲ ከ ዩጋንዳ 🇺🇬

በድሬዳዋ አለም አቀፍ ስታዲየም

ምስራቅ ስፖርት

ሶማሊያ እና ደቡብ ሱዳን አቻ ተለያዩ።MS ዜና l ኢትዮጵያ የምታዘጋጀው ከ17 ዓመት በታች የሴካፋ ውድድር በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲዩም  በመጀመሪያው ጨዋታ ሶማሊያ እና ደቡብ ሱዳንን...
15/11/2025

ሶማሊያ እና ደቡብ ሱዳን አቻ ተለያዩ።

MS ዜና l ኢትዮጵያ የምታዘጋጀው ከ17 ዓመት በታች የሴካፋ ውድድር በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲዩም በመጀመሪያው ጨዋታ ሶማሊያ እና ደቡብ ሱዳንን ያገናኘው ጨዋታ በሁለት አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።

ምስራቅ ስፖርት

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ሩዋንዳን አሸነፈ!🇪🇹🇪🇹 ለአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያ ሩዋንዳን ሁለት ለዜሮ አሸንፋለች። ኢትዮጵያ ባስተናገደችው ውድ...
15/11/2025

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ሩዋንዳን አሸነፈ!🇪🇹🇪🇹

ለአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያ ሩዋንዳን ሁለት ለዜሮ አሸንፋለች።

ኢትዮጵያ ባስተናገደችው ውድድር ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በመጀመሪያ አጋማሽ ዳዊት ካሳና ሁዘይፋ ሻፊ ባስቆጠሯቸው ጎሎች አሸንፈዋል ፡፡

ምስራቅ ስፖርት

Address

Dire Dawa
6068@2024

Telephone

+251915750424

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mesrak SPORT / ምስራቅ ስፖርት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Mesrak SPORT / ምስራቅ ስፖርት:

Share

Category