Afar Trade and Market Development bureau

Afar Trade and Market Development bureau Afar Trade and Market Dev't Bureau

26/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሠላም አደረሣችሁ !!! በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

ኢድ ሙባረክ !!!

Hordoftoota Amantaa Musliimaa hundaaf, baga ayyaana Iid-Al-Adahaa waggaa 1447ffaa nagaan geessan. Ayyaanni kun kan nagaa, kan jaalalaa kan milkii isiniif haa ta'u.

Eid Mubarak!!!

26/05/2026

የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር የክቡር ሐጂ አወል ዓርባ የ1447 ሂጅራ የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

የተከበራችሁ የክልላችን ሕዝቦች፣
በመላው አገሪቱ የምትገኙ ውድ ወገኖቼ፣ እንዲሁም በዓለም ዙሪያ የምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፤

በቅድሚያ ለ1447ኛው ሂጅራ የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም፣ በጤና እና በደስታ አደረሳችሁ።
ይህንን ታላቅ በዓል ስናከብር፣ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ እጅግ ውድ እና በዱንያ ላይ ካሉ ቀናት ሁሉ በላጭ የሆኑትን የዙልሒጃህ መጀመሪያ አስር ቀናትን በታላቅ አምልኮ፣ በበጎ ምግባር እና በኸይር ሥራዎች ስናሳልፍ ቆይተን ነው። አላህ (ሱብሐነሁ ወተዓላ) በቅዱስ ቁርኣኑ የእነዚህን ቀናት ታላቅነትና ክብር ሲያስታውሰን እንዲህ ሲል ማልሏል፡-"በማለዳው እምላለሁ፤ በአስሩም ሌሊቶች እምላለሁ።" (ሱረቱ አል-ፈጅር፡ 1-2)
የአላህ መልክተኛም (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በእነዚህ ቀናት የሚሰሩ መልካም ሥራዎች በአላህ ዘንድ ያላቸውን የላቀ ተወዳጅነት በሐዲሳቸው እንዲህ ሲሉ አረጋግጠውልናል፡-
"በነዚህ (በአስሩ የዙልሒጃህ) ቀናት ውስጥ ከሚሰሩ መልካም ሥራዎች ይልቅ አላህ ዘንድ ይበልጥ ተወዳጅ የሆኑ መልካም ሥራዎች የሚሰሩባቸው ሌሎች ቀናት የሉም።" (ሶሒሕ አል-ቡኻሪ)
እነሆ! በዚሁ በተባረከው ወር በ10ኛው ቀን ላይ ሆነን ታላቁን የዒድ አል-አድሃ በዓል እናከብራለን። ይህ ወቅት የእስልምና እምነት አምስተኛው ማዕዘን (ሩክን) የሆነው ታላቁ የሐጅ ሥነ-ሥርዓት በዓለም ዙሪያ ከሚገኙ በሚሊዮኖች ከሚቆጠሩ ሙስሊሞች መካከከል የእኛም ወገኖች ጭምር በተገኙበት በቅዱስ ስፍራ የሚከወንበት የእንድነትና የክብር ወቅት ነው።
የዒድ አል-አድሃ በዓል የነቢዩ ኢብራሂም (ዐለይሂ-ሰላም) የላቀ ታዛዥነትና መስዋዕትነት የሚዘከርበት ከመሆኑም በላይ፣ በዋናነት የእርስ በእርስ መተዛዘንና የወንድማማችነት ማረጋገጫ ነው። የበዓሉ መስዋዕትነት (ዕርድ) ተጨባጭ ትርጉም የሚኖረው ያለው ለሌለው በማካፈል፣ ለሰፊው ማኅበረሰብ፣ ለችግረኞች፣ ለየቲሞችና አቅመ-ደካሞች እጅ በመዘርጋት ጭምር ነው። ቅዱስ ቁርኣን የበዓሉን ስጋ አስመልክቶ ማኅበራዊ ፋይዳውን ሲያስገነዝብ እንዲህ ይላል፡-
"ከእርሷም (ከዕርዱ ስጋ) ብሉ፤ ችግረኛ ለሆነውና ለማይለምነውም (ለደሃው) አብሉ፡፡" (ሱረቱ አል-ሐጅ፡ 36)
ይህ መለኮታዊ እሴት ዛሬ ለሀገራችን እና ለክልላችን አብሮነት፣ ለዘላቂ ሰላም እና ለጋራ ልማታችን መሠረታዊ ምሰሶ ነው። እኛም በኢትዮጵያ እንደ አንድ ሕዝብ ተሳስረን የምናከብረው ይህ በዓል፣ በመካከላችን ያለውን የመረዳዳትና የእህትማማችነት መንፈስ ይበልጥ የሚያጠናክር ነው።

ይህንን ታላቅ በዓል ስናከብር ኢትዮጵያችን በሁለንተናዊ የለውጥ እና የዕድገት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። በመላው ሀገሪቱ እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች፣ በተለይም በአፋር ክልል በየዘርፉ እየታዩ ያሉ የልማት ሥራዎች የሕዝባችንን የነገ ተስፋ ይበልጥ የሚያለመልሙ ናቸው። በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ አገልግሎቶች፣ በመሠረተ ልማት እና በሕዝብ አስተዳደር ዘርፎች የተመዘገቡት ስኬቶች የሪፎርሙ ተጨባጭ መገለጫዎች ናቸው።

በክልላችን በስፋት እየተተገበሩ ያሉት የተዛባውን ትርክት የቀየረው የግብርና አብዮት፤ የንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች፣ የትምህርትና የጤና ተቋማት ግንባታ፣ እንዲሁም የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ የሚያነቃቁ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ለክልላችን ዘላቂ ብልፅግና ጠንካራ መሠረት እየጣሉ ነው። እነዚህ የለውጥ ውጤቶች የሕዝባችንን የሕይወት ጥራት ከማሻሻል ባለፈ፣ የኢትዮጵያን የጋራ ዕድገት እያፋጠኑ ይገኛሉ። መንግሥታችን የሕዝቡን የልማት ጥያቄዎች በቅድሚያ የመመለስ ስትራቴጂካዊ ቁርጠኝነትን በመያዝ የጀመራቸውን ዘላቂ ሥራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል።

በቅርቡ የምናካሂደው ሰባተኛው አገራዊ ምርጫ፣ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታችንን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ወሳኝ ምዕራፍ ነው። ይህ ታላቅ ብሔራዊ ሂደት ከበዓሉ ማግስት ጥቂት ቀናት በኋላ የሚከናወን ሲሆን፣ የእያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነት የላቀ ነው። ምርጫው በሰላማዊ፣ በበሰለ እና በመቻቻል መንፈስ እንዲጠናቀቅ ማድረግ የሁላችንም የጋራ ግዴታ ነው።
እንደ ኢትዮጵያውያን እና እንደ አፋር ሕዝብ ለሀገራችን ሰላምና ሕልውና ቅድሚያ በመስጠት፣ የምርጫውን ሂደት በከፍተኛ የዲሲፕሊን እና የሕግ አክባሪነት መንፈስ እንድናከናውን ጥሪዬን አቀርባለሁ። ምርጫ በሃሳብ የሚፎካከሩበት እንጂ የምንቃረንበት ሳይሆን፣ ሀገርን ለጋራ ተጠቃሚነት የምናጸናበት የዴሞክራሲ መድረክ ነው። በመሆኑም በዓሉን በሰላምና በፍቅር እንደምንከብረው ሁሉ፣ ምርጫውንም በተመሳሳይ የጋራ መግባባትና ለኢትዮጵያ ብልፅግና በሚጠቅም መልኩ እንድናጠናቅቀው እሻለሁ።

በድጋሚ ለሁሉም የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለዒድ አል-አድሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የአላህ ሰላም፣ ምሕረት እና በረከት በክልላችን እና በሀገራችን ብሎም በዓለማችን ሁሉ ይሁን።

አላህ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይጠብቅልን!
ሀጂ አወል ዓርባ ዑንዴ
የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር

EiD MubarakQafar Rakaakayih doolatak Kabxa kee Qadaaga Daddoosih Biirok Naharsi Saqqal Massakaxxale Acmad Qabdulkaadir  ...
26/05/2026

EiD Mubarak

Qafar Rakaakayih doolatak Kabxa kee Qadaaga Daddoosih Biirok Naharsi Saqqal Massakaxxale Acmad Qabdulkaadir

Unkaqino Farmo Tatruse

Unkaq Muslimin Ummattay Afa Baaxoy, Baaxoh Addal Geytimma intá Muslimiin Ummattak Baxsaluk Qafár Ummattak Hijrâ Loowok 1447 Heele Qiid- Al Adha (Qarafa) Qiid Muquk Sin Suguseeh, Nee Sugusem

Qiid Qafár Ummattah Saay Kee Salaam Edde Daabimaah, Bisô Maxco Kee Dadal Arac Edde Giyah, Sittin Kacanu Kee Sittin Assakoxxo Maqar Luk Arac Edde Giyah Yan Qiid Yakkem Qaagita.

Qiid Mubarak ❤️❤️❤️

የአፋር ክልል ንግድ ና ገበያ ልማት ቢሮ ሀላፊ የተክቡሩ አህመድ አብዱልቃድር
የ1447 ሂጅራ የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰለም አደረሰችሁ አደረሰን ። በአሉ የሰላም: የፍቅር : የመተሳሰብ እንድሆንለችሁ እመኛለሁ . አፉ በሉልኝ አውፍ ብያችሃለሁ

21/05/2026
19/05/2026
የአፋር ክልል የንግድ ገባያ ልማት ቢሮ የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት ጋር በገራ በመተባበር  በክልሉ በሚገኙ ከ7 ከተማ መስተዳደር እና ከ6 ወረዳ ለተወጣጡ የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ከ55...
15/05/2026

የአፋር ክልል የንግድ ገባያ ልማት ቢሮ የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት ጋር በገራ በመተባበር በክልሉ በሚገኙ ከ7 ከተማ መስተዳደር እና ከ6 ወረዳ ለተወጣጡ የንግድ ክትትልና ቁጥጥር ከ55 በላይ ዳይሬክቶሮችእና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጣ ግንቦት 6/9/2018

የኢትዮጵያ ሥነ-ልክ ኢንስቲትዩት በአፋር ክልል ለሚገኙ የንግድ ቢሮ ሕጋዊ ሥነ-ልክ ተቆጣጣሪዎች የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና የቴክኒክ እና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ። በሰመራ ከተማ ከግንቦት 5 እስከ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ለአንድ ሳምንት በሚቆይ ስልጠና በመካሄድ ላይ ባለው በዚህ መድረክ፣ ከክልል፣ ከዞንና ከወረዳ የተወከሉ ደይሬክተሮች እና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኝሉ። ሥልጠናው በተለይም በሚዛን አለካክ እና በነዳጅ መቆጣጠሪያ ሜትር አጠቃቀም ላይ ያተኮረ ሲሆን።
በሥልጠናው መክፈቻ ላይ የክልሉ የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አህመድ አብዱልቃድር እንደገለጹት፤ የሸማቹን መብት ማስጠበቅና የንግድ ቁጥጥር ስራዎችን ማከናወን የቢሮው ዋነኛ ኃላፊነት ቢሆንም፣ የመለኪያ መሣሪያዎችን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ የሰለጠነ የሰው ኃይልና የቴክኒክ መሣሪያዎች እጥረት እንቅፋት ሆኖ መቆየቱ እና ፉትሃዊ የንግድ ስርዓት እድሰፍን እና።ኃላፊው አክለውም፣ “ይህ ሥልጠና የተበረከቱልን የማነጻጸሪያ መሣሪያዎች ያሉብንን ክፍተቶች ለመሙላት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው” በማለት ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ምኒስትር እና ለኢንስቲትዩቱ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይም የክልሉን የአስፈጻሚነት አቅም ለማሳደግ መሰል ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

10/05/2026

Address

Dubti
7402

Telephone

+251921548927

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Afar Trade and Market Development bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Afar Trade and Market Development bureau:

Share