Durame times

Durame times We stand together

19/12/2025

ምንም ጉዳት የለዉም !

የፋርስ ባሕረ ሰላጤን ወደ ቀይ የቀየረው
የደም ዝናብ ወሳኝ መረጃዎች !

በኢራን ሆርሙዝ ደሴት ላይ ታህሳስ 17 ቀን 2025 5:10 ፒኤም GMT የዘነበዉ “የደም ዝናብ” የኢራን ደሴት የባህር ዳርቻ ውሃ በአንድ ሌሊት ወደ ቀይ ባህር ቀይሮታል።

በሆርሙዝ ደሴት ላይ የነበረው አስገራሚ ትዕይንት በቪዲዮ ተቀርፆ በማህበራዊ ሚዲያ ከተሰራው በኋላ የበርካቶች መነጋገሪያ እየሆነ ይገኛል ።

ይህን አስደናቂ የተፈጥሮ ክስተት ተከትሎ አንዳንዶቹ ከመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች ጋር በማነፃፀር ቁጣ ነዉ ያሉት ሳይንስ በበኩሉ
በደሴቲቱ ከፍተኛ የብረት ኦክሳይድ ክምችት ምክንያት ነው ያለውን ጉዳይ ከሁለት ወገን መረጃ እንዲኖረን በትንታኔ ለማየት ወድደናል ።

ከሺህ ዓመቱ መባቻ ጀምሮ በርካታ የኢራን ሳይንቲስቶች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ስለሚከሰቱ ድርቅ እና የኢራን የውሃ አጠቃቀም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ሲያስጠነቅቁ ቢቆዩም በዚህ በአሜሪካ የሚመራዉ አለም የማዕቀብ ናዳ አማራጭ ስላሳጣት ሀገሪቱ በምግብ ራስን መቻል አለባት በሚል በተለይም ከፍተኛ ዉሐ የሚፈልገውን ሀባብ አይነት ምርቶች በባለሀብቶች እና ሹመኞች በስፋት ስለሚመረት ለመግለጽ የሚቸግር ችግር ዉስጥ ከቷታል ።

ይህን ተከትሎ ላለፉት ስድስት አመታት በምድሪቱ ዝነብ ነጥፎ በአሁኑ ሰዓት ኢራን በግማሽ ምዕተ ዓመት ውስጥ በአገሪቱ ውስጥ ከተከሰተው እጅግ የከፋ ድርቅ ጋር የሚነፃፀር ከባድ ሁኔታ ላይ ትገኛለች ።

በኦፊሴላዊ ግምቶች መሠረት፣ በአገሪቱ ውስጥ ያለው የዝናብ መጠን ከረጅም ጊዜ አማካይ ጋር ሲነጻጸር በዚህ ዓመት በ89 በመቶ ገደማ ቀንሷል።

ባለፈው ወር የውሃው መጠን በጣም ዝቅተኛ ስለነበር 10 ሚሊዮን ነዋሪዎች የሚኖሩባት ዋና ከተማዋ ከአካባቢው ለቅቆ መውጣት ሊያስፈልጋት እንደሚችል ስጋት መኖሩን መንግስታቸው ገልጿል ።

በዚህ ሁኔታ ዉስጥ ባለችበት ነዉ 100ሚሜ አካባቢ ዝናብ በአንድ ሌሊት በሆርሙዝ ደሴት የዘነበው ።

ከባድ ዝናብ በደሴቲቱ ቀይ የባህር ዳርቻ ዳርቻ የውሃ እና የአሸዋ ቀለም እንዲለወጥ ምክንያት ሆኗል።

ወደቀይነት መቀየሩን ከሃይማኖታዊ ትንቢቶች ጋር ከማያያዛችን በፊት ለመሆኑ ደሴቷ ምን አይነት ናት የሚለውን ማወቅ ያሻል ።

ሆርሙዝን ደሴት በአስደናቂ ነገሮች የተሞላች ናት ።

ብዙውን ጊዜ በቀለማት ያሸበረቀ መልክዓ ምድሯ "የቀስተ ደመና ደሴት" ተብሎ የሚጠራው የሆርሙዝ ደሴት ዓመቱን ሙሉ ተወዳጅ መዳረሻ ነው። ቱሪስቶች ደማቅ አፈርዋን፣ ሻካራ የባህር ዳርቻዋን እና ታሪካዊ ምልክቶችን ለማየት ይጎበኛሉ።

ደሴቲቱ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በጂኦሎጂካል እንቅስቃሴ የተቀረጹ ቢጫ፣ ብርቱካናማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ጥላዎችንም ታሳያለች። ሆርሙዝ ለሳይንቲስቶችም ሆነ ለተጓዦች ትኩረት የሚስብ ቦታ ሆኖ ቀጥሏል፣ ይህም በአየር ሁኔታ እና በምድር ጂኦሎጂ መካከል ስላለው ግንኙነት ግንዛቤ ይሰጣል።

እንግዲህ ዝናቡና በዓለም ዙሪያ ያሉ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን ትኩረት የሳበው ተፈጥሯዊው ክስተት በዚህች ደሴት ነዉ ።

አንዳንዶቹ ከመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች ጋር በማነፃፀር አስተያየት እየሰጡ ይገኛሉ ።

አንድ አስደናቂ የተፈጥሮ ክስተት የኢራንን የሆርሙዝ ደሴት ወደ ዓለም አቀፍ የውይይት መድረክ ቀይሮታል ።

አንድ ታዋቂ ዩቱዩቨር “የመጨረሻ ዘመን” ምልክት ሊሆን እንደሚችል ጠቁሟል፣ ሌላኛው ደግሞ “ማለቂያ የሌለው ሀዘን” እንደሚያበቃ ፍንጭ እንደሆነ አክሏል። ሌላው ደግሞ “መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይመስላል” ብሏል።

ከዚህ አስደናቂ ክስተት በስተጀርባ ያለው ሳይንሳዊ ማብራሪያ በደሴቲቱ ልዩ

18/12/2025

የሺንሽቾ ከተማ ጊዜያዊ ሽግግር ምክር ቤት አቶ መለሰ ገቡሬን የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አድርጎ ሾመ።

በከምባታ ዞን የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የመንግሥት ረዳት ተጠሪ በሆኑት በአቶ በፍቅር ታምራት አቅራቢነት አቶ መለሰ ገቡሬ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው ተሹመዋል።

የሺንሽቾ ከተማ ጊዜያዊ አማካሪ ሽግግር ምክር ቤት እያካሄደ ባለው 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው እንዲሾሙ በሙሉ ድምጽ አፅድቋል።

አቶ መለሰ ገቡሬ በሺንሽቾ ከተማ ጊዜያዊ አማካሪ ሽግግር ምክር ቤት ፊት ቀርበው ቃለ መሐላ ፈፅመዋል።

19/11/2025

የብዝኃነት መርከቧ - ኢትዮጵያ
++++++++++++++++

| የተለያየ ቋንቋ መናገር ከመግባባት አይገድባቸውም። የቆዳ ቀለም ውበታቸው ነው። የሰፈሩት የቦታ ርቀት 'ኢትዮጵያውያን' ከመባል አያርቃቸውም። የየግል እምነታቸውን ይዘው፤ የሁሉንም በጋራ አክብረው በፍቅር ይኖራሉ።

አንድ ለመሆን አንድ አይነት እንሁን አይሉም። አንድነታቸውንም አይከፍለውም። የልዩነት ምንጭም አልሆነም።

ይህ ጸጋ በፈጣሪ የተሰጡት መሆኑን ተረድተው በጋራ ስለሀገር ያስባሉ። ብዙ ቋንቋ፣ ብዙ ባህል፣ ብዙ ሃይማኖት ሌላም ብዙ ብዙ ማንነት አላቸው። አንዱ ያለው አንዱ የለውም። አንዱ የአንዱን ሲያይ ይደሰታል። ለማየት ይጓጓል። ለመማር ይናፍቃል።

ሁሉም ብዙኅነትን ያከበሩ የአንዲት ሀገር የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው። ኢትዮጵያ አምጣ የወለደቻቸው፣ ልጆቼ የምትላቸው፤ እነሱም እናቴ የሚሏት ድንቅ ልጆች ናቸው።

ከመርከቧ ላይወርዱ ተማምለው የተሳፈሩ ተጓዦች። ላይነጣጠሉ የተገመዱ ልዩነት የማይለያቸው ህዝቦች።

በየዓመቱ በአንድ የሚያገናቸውን ከተማ መርጠው ብሔር ብሔረሰቦች በአንድ ተገናኝተው በጋራ የጋራ ባህላቸውን ይጋራሉ። ይተዋወቃሉ። ይመክራሉ።

የህዝቡን አንድነት የማይወዱ በአንድነት መቆሙ የከነከናቸው የፖለቲካ ነጋዴዎች በብሔር፣ በቋንቋ፣ በሰፈር ልዩነቱን ሊያሰፉት ቢጥሩም ህዝቡ ግን ኢትዮጵያዊነት አንድነቱን አጽንቶ ቆይቷል።

አንዳቸው የሌላቸው የጉድለት ሙላት፤ አንዳቸው የሌላቸው የድክመት ብርታት ሆነውና አንዳቸው በሌላቸው የችግር ቀን ደርሰው ዘመናትን ዘልቀዋል፡፡

ከዚህም በላይ በጋራ ቆመውና የጋራ ጠላቶቻቸውን በጋራ መክተው አጽንተዋት ኖረዋል፤ እየኖሩም ናቸው፤ ወደፊትም የሚኖሩባት ትልቅ ሀገር ናት፡፡ ኢትዮጵያ።

''ኢትዮጵያ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ብሔር ብሔረሰቦች የራሳቸውን ማንነት፣ ባህላቸውንና ታሪካቸውን ይዘው የተሳፈሩባት፤ ለሁሉም የምትበቃ ትልቅ መርከብ ናት ይላሉ'' የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ ።

እንደ አቶ አረጋ ገለጻ፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር፤ ትልቅም መርከብ ናት፡፡ ይህች መርከብ ደግሞ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የየራሳቸውን ማንነት፣ ባህላቸውን እና ታሪካቸውን ይዘው የተሳፈሩባት፤ ለሁሉም የምትበቃ ናት፡፡

ኢትዮጵያ የምትባል ትልቅ ሀገር ከተፈጠረችበት ጊዜ ጀምሮ ብሔር ብሔረሰቦች ተዋደውና ተከባብረው ኖረውባታል፡፡ አሁንም እየኖሩ ናቸው ።

አቶ አረጋ እንደሚያብራሩት፤ ለሁሉም የወል ቤት የሆነችው ኢትዮጵያ በተለያዩ ሥርዓቶች የተለያዩ የፖለቲካ አስተሳሰቦች በፖለቲካ ልሂቃን አማካኝነት መጥተው ብዙ ውጣ ውረድ እንድታሳልፍ ቢያስገድዷትም፤ በእነዚህ ውጣ ውረዶች ሁሉ ጸንታ በመቆም አሸናፊ ሆናለች፡፡

ጠላቶቿ ብዙ ጊዜ ትወድቃለች፣ ትበተናለች፣ ትደክማለች ብለው በክፉ ሀሳብ ሲጠብቋትም፤ ክፉ ቀኖችን ሁሉ በአምላኳ ፈቃድ፣ በሕዝቦቿ አንድነትና ጥረት ተሻግራ ብልጽግናዋን የምታረጋግጥበትን ጉዞ ጀምራለች፡፡

ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታትም የቀደመውን የልዩነት ትርክት አስተካክላ እውነተኛ ኅብረብሔራዊ አንድነትን እየገነባች ትገኛለች፡፡

ልዩ ልዩ ባህል፣ ታሪክና ማንነት ያላቸው ህዝቦቿም በጋራ ሊሰሩና ሊያለሙ እንደሚችሉ በማመን የዘመናት ታሪኳን የሚቀይሩ ስራዎችን ሰርተው አሳይተዋል። አሁንም እየሰሩ ነው ።

ዋና አስተዳዳሪው ጨምረው እንደተናገሩት፤ የከምባታ ዞንና ህዝብም የዚች መርከብ አካልም፣ ባለቤትም እንደመሆኑ፤ በመርከቧ ልክ ትኩረት አግኝቶ እየተጓዘ ይገኛል፡፡

የሀንበርቾ ተራራን አይነት ከፍ ያለ አቅም ያላቸው የዞኑን የቱሪዝም መስህቦችን ለይቶ በማልማት በኩል የተከናወኑና እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችም ለዚህ ማሳያዎች ስለመሆናቸው ጠቁመዋል፡፡

20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ምክንያት በማድረግ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተለያዩ አከባቢዎች ምልከታ እያደረገ ያለው የጋዜጠኞች ቡድን ወደ ከምባታ ዞን ገብቷል፡፡ በዓሉም በዚሁ ዞን በድምቀት የሚከበር ይሆናል ።

በወንድወሰን ሽመልስ
+++++++++++++++++++++

19/11/2025
18/11/2025

የዳምቦያ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አዲስና የሽግሽግ ሹመቶችን ሰጥቷል።

አዲስ ሹመት
አቶ ምሥጋና ማቴዎስ የዳምቦያ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

ሽግሽግ
አቶ ማቴዎስ ኃይሌ የብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ሱፐርቪዥን ኃላፊ፣
አቶ አባይነህ መኬቦ የሠላምና ጸጥታ ክላስተር ጽ/ቤት ኃላፊ፣
አቶ ደሳለኝ ዮሐንስ የፋይናንስ ጽ/ቤት ኃላፊ፣
አቶ አሸናፊ አለሙ የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ፣
አቶ ዘሪሁን ከበደ የብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ም/ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

18/11/2025


"""""""""""""""
የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በአዳዲስና በሽግሽግ የተለያዩ ሹመቶችን ሰጠ።

በዚህም መሠረት የካቢኔ አባላት
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~

1. ወ/ሮ ባንቺ ማቴዎስ ➛ የሺንሽቾ ከተማ ጊዜያዊ አማካሪ ሽግግር ም/ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ

2. አቶ ሽመልስ ተስፋዬ ➛ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ዋና ሥራአስኪያጅ

3. አቶ ፍሬህይወት ተፈራ ➛ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ

3. አቶ ሳሙኤል አበበ ➛ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ

4. አቶ ጴጥሮስ ቦንጆሬ ➛ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ

በምክትል ማዕረግ አመራሮች
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
1. አቶ ሮቤል ዋቸሞ ➛ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ም/ሥራ-አስኪያጅ እና የማስፈፀም አቅም ግንባታ አከባቢ ልማት ዘርፍ ኃላፊ

2. አቶ አስፋው ማቴዎስ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ም/ሥራ-አስኪያጅና የኮንስትራክሽን ዘርፍ ኃላፊ

3. አቶ አዳነ ዳንኤል የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ም/ሥራ-አስኪያጅና የመሬት ዘርፍ ኃላፊ

4. አቶ ብሩክ ጴጥሮስ የቄጣላ ቀበሌ ሥራ-አስኪያጅ

#በሽግሽግ ምደባ የተሰጣቸው #የካቢኔ አባላት
~~~~~~~~~~~~~~~~~~
1. አቶ እንዳለ አበራ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ

2. አቶ ሰመረ በላይነህ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ፕላን ጽ/ቤት ኃላፊ

3. አቶ ስጦታ ደገሎ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ

4. አቶ ፋኖስ ዘነበ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ

5. አቶ ተመስገን ሙሉጌታ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ገቢ ጽ/ቤት ኃላፊ

6. አቶ ደስታ አሼቦ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ

#በሽግሽግ ምደባ የተሰጣቸው አባል

1. አቶ አዲሱ ታደሰ የፓርቲ ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ

#በምክትል ኃላፊ ማዕረግ የሽግሽግ ምደባ የተሰጣቸው አመራሮች
~~~~~~~~~~~~~~~
1. አቶ ፍቅረአብ አበራ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ም/ሥራ-አስኪያጅና የካድስተር ዘርፍ ኃላፊ

2. አቶ ታረቀኝ ሻሜቦ የቄጣላ ቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ

3. አቶ ፍፁም ብርሃኑ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ኃላፊ

4. ወ/ሮ አይናለም አቡዬ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ህብረት ሥራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ

5. አቶ አቤኔዘር በለጠ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ም/ሥራ-አስኪያጅ እና የቤቶች ልማትና አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ

7. አቶ ግዛቸው ኃይሌ የሥራና ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

17/11/2025

ዜና ሹመት,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
የሀደሮ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አዳዲስና በሽግሽግ የተለያዩ ሹመቶችን ሰጥቷል

በዚሁ መሠረት አዳዲስ ሹመት የተሰጣቸው
1. አቶ ከበደ ሶረቶ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ
2.አቶ ገብረወልድ ገብረጊዮርጊስ ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ
3.አቶ ተመስገን ተረፈ ደካ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ
4. አቶ ስዩም ቦልጠኖ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ
5.አቶ ጥላሁን አበበ ማዘጋጃ ቤት ኮንስትራክሽን ዘርፍ ኃላፊ
6. አቶ አስማማው ታገሰ ለውጥ ቀበሌ ማዘጋጃ ቤት ሥራአስኪያጅ
7. አቶ ብርሃኑ ድጋሞ ማዘጋጃ ጽ/ቤት የማስፈጸም አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ

በሽግሽግ የአመራር ሹመት የተሰጣቸው

1. አቶ ኢሳያስ ሊሞሬ ወጣቶች ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ
2. አቶ ዳንኤል አሻሞ ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽ/ቤት ኃላፊ
3. አቶ ንጋቱ አስፈው ህብረት ሥራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ
4. ወ/ሮ ሠላማዊት ሃይባኖ ሴቶችና ህፃናት ጽ/ቤት
5. ድንቅነህ ጴጥሮስ ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽ/ቤት ም/ኃላፊ
6. ወ/ሮ ደሳለች ሀብተወልድ ማዘጋጃ ጽ/ቤት ቤቶች ዘርፍ ኃላፊ
7. አቶ አበራ ጨዕምሶ ወጣቶች ስፖርት ጽ/ቤት ስፖርት ዘርፍ ኃላፊ
8. አቶ ብሩክ ታድዎስ ወጣቶች ስፖርት ጽ/ቤት ወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ
9. ወሪ/ት ፋሲካ ተፈሪ ህዳሴ ቀበሌ ማዘጋጃ ሥራአስኪያጅ ሆነው ተሹመዋል።

መረጀው= የሀደሮ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ነው

17/11/2025

==============ዜና_ሹመት============

የዶዮገና ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በአዲስና በሽግሽግ ለአመራሮች ሹመት ሰጥቷል።
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~



1.አቶ አድነው አብርሃም የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ



1.አቶ ታምሬ ፍቅሬ የፓርቲ ጽ/ቤት ሀብት ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ



1.አቶ እንድሪያስ ጴጥሮስ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ
2.አቶ ካሳሁን ምሻሞ የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ
3.አቶ ኤልያስ ገብሬ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ
4.አቶ አሰፋ ሎጵሶ የንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ
5.አቶ ታሪኩ ተስፋዬ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ
6.አቶ ሀብታሙ አለንጎ የትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ
7.አቶ ሳሙኤል ጌታሁን የሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ
8.አቶ ብርሃኑ በቀለ የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ
9.አቶ ያቤፅ ቃሎሬ የሥራ/ዕ/ፈ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ኃላፊ
10.አቶ ሙላቸው ተክሌ የጤና ጽ/ቤት ኃላፊ
11.አቶ ተድላ መለሠ የዶ/መ/ደ/ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ



1.አቶ ሙሉነህ ወ/ማሪያም የተፎካካሪ ፓርቲዎችና ሲቪክ ማህበራት ጽ/ቤት ኃላፊ



1.አቶ አድነው ዱናሞ የሥራ/ዕ/ፈ/ኢ/ል/ም/ኃላፊና ሥራ/ዕ/ፈ/ዘርፍ ኃላፊ
2.አቶ ጥላሁን ሊራንሶ የማዘጋጃ ቤት ም/ኃላፊና የኮንስትራክሽን ዘርፈ ኃላፊ



1.አቶ አሸናፊ ማዳሞ የወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ም/ኃላፊና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ በማድረግ በአዲስ እና በሽግሽግ ሹመት ተሰጥቷል።

ህዳር 08/2018 ዓ/ም
ዶዮገና

17/11/2025

የአንጋጫ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አዳዲስና በሽግሽግ የተለያዩ ሹመቶችን ሰጥቷል

በዚሁ መሠረት አዳዲስ ሹመት የተሰጣቸው
1. አቶ ወንዱ ማቴዎስ የአንጋጫ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽህፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ
2. አቶ ተስፋጽዮን ሰላሙ የአንጋጫ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ

በሽግሽግ የአመራር ሹመት የተሰጣቸው

1. አቶ ደረጀ ከበደ የአንጋጫ ከተማ አስተዳደር ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ
2. አቶ አቢይ አበበ የአንጋጫ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግምባታ ዘርፍ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል ።

17/11/2025

ዜና ሹመት
***********
የዶዮገና ወረዳ ብልጽግና ቅ/ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት አዲስ የአመራር መዋቅር የተቀላቀሉ አመራሮችን ጨምሮ በሽግሽግ በካቢኔና በምክትል ማዕረግ አደራጅቷል።

ህዳር፣8/2018ዓ.ም
በዚህም መሰረት:-
አዲስ ሹመት የተሰጣቸው ካቢኔ አመራሮች

1. አቶ ደርቤ ሰይፉ የዶዮገና ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ኃላፊ
2. አቶ ታምራት ሙጎሮ የዶዮገና ወረዳ ፕላን ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ
3. አቶ ተከተል ገ/ወልድ ደንና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ
4 አቶ ሙሉጌታ አለሙ የዶዮገና ወረዳ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ኃላፊ

#በምክትል ማህረግ
1.አቶ በሬዱ ታደላ የዶዮገና ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት መንግሥት ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ
2.አቶ ፍቅሩ ደሳለኝ ዶዮገና ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት እርሻ ዘርፍ ኃላፊ
3.አቶ ተስፋዬ ሀደሮ ዶዮገና ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት እንስሳትና ዓሳ ሀብት ዘርፍ ም/ኃላፊ
4. አቶ ተካልኝ አበራ ዶዮገና ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ም/ኃላፊ
5. አቶ ምትኩ አቦሴ አመቾ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ
6. አቶ ተሾመ ነጬ ወንጀላ ብርሃነ ሰላም ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ
7.ወ/ሪት ማህሌት አለሙ የዶዮገና ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት መንገድ ዘርፍ ም/ኃላፊ

#ሽግሽግ የተደረጉ ካቢኔ አመራሮች፦

1.አቶ መለሰ ደኔቦ የዶዮገና ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ
2. አቶ ዳዊት አንጆሬ ዶዮገና ወረዳ ገቢ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ
3. አቶ አቢዮት ኃይሌ ዶዮገና ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ኃላፊ
4.ወ/ሮ ብርሃኔ ዋቻሞ የዶዮገና ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ
5.ወ/ሮ ፍሬሕይወት አበራ የዶዮገና ወረዳ ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ
6. አቶ አዲሴ ጴጥሮስ የዶዮገና ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ
7. አቶ ታምራት ዶቦጭ የዶዮገና ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ ሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ
8.አቶ ፈቃዱ ዮሐንስ የዶዮገና ወረዳ ባህልና ቱርዝም ጽ/ቤት ኃላፊ

#ሽግሽግ የተደረጉ ምክትል ኃላፊዎች፦

1.አቶ መለሰ ከበቶ የዶዮገና ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በካቢኔ ማዕረግ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ
2.አቶ ሰላሙ ታገሠ ፐብሊክ ሰርቪስ ምክትል ኃላፊ
3.አቶ ተስፋዬ ተሰማ የዶዮገና ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ልማት ዕቅድ
4.አቶ ታምራት ኢያቆ የዶዮገና ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ወጣቶች ዘርፍ ም/ኃላፊ
5.አቶ ደገፈ ዋጄቦ የዶዮገና ወረዳ ሠራራ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ
5.ገብርኤል ቢንጫሞ የዶዮገና ወረዳ ህብረት ሥራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ
6. ይርጋለም ሞላ የዶዮገና ወረዳ መሬት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ

መልካም የስራ ዘመን

14/11/2025

የኢቢሲን ጨምሮ የተለያዩ የሀገር ውስጥ ቻናሎች ስርጭት በቴክኒክ ችግር ተቋርጧል
********

የሳተላይት አቅራቢ ቴሌ ፖርት በአየር ጠባይ ለውጥ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ቻናሎችን ጨምሮ አብዛኞቹ የሀገር ውስጥ ቻናሎች የ‘SES' ስርጭት ተቋርጧል።

‘SES' በተሰኘው የቴሌ ፖርት ላይ እስራኤል አካባቢ ባጋጠመው የአየር ጠባይ ችግር ምክንያት የኃይል መቋረጥ በመፈጠሩ ነው ቻናሎቹ ለጊዜው የተቋረጡት።

ስርጭቱን ለመመለስ እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል።

Address

Durame

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Durame times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Durame times:

Share