Durame times

Durame times We stand together

29/08/2025

ኢትዮጵያ ታላቁ የሕዳሴ ግድብን ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም. ልታስመርቅ ነው

ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም. የአፍሪካ መሪዎች እና ሌሎች የተጋበዙ እንግዶች በሚገኙበት እንደሚመረቅ በኬንያ የኢትዮጵያ ምክትል አምባሳደር ደመቀ አጥናፉ ተናገሩ።
ከአምስት ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት በአፍሪካ ግዙፉ እንደሆነ የተነገረለት ሕዳሴ ግድብ ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ ግንባታው ሲካሄድ ቆይቷል።
አምባሳደር ደመቀ ሐሙስ ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም. ለቢቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ የሕዳሴ ግድብ ሴፕቴምበር 9 [ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም.] በይፋ ምረቃው እንደሚካሄድ አመልክተዋል።
በአምስት ዓመታት ውስጥ ግንባታው ይጠናቀቃል ተብሎ የነበረው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ ከአስር ዓመታት በላይ ፈጅቶ የኢትዮጵያ መንግሥት በመጪው አዲስ ዓመት መጀመሪያ ላይ በይፋ እንደሚመረቅ አስታውቆ ነበር።
የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የተጀመረው መጋቢት 24/2003 ዓ.ም. ሲሆን አጠቃላይ ግንባታው 14 ዓመታትን ወስዷል። ከግማሽ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን "በጨለማ ነው የሚኖሩት" ያሉት አምባሳደሩ እነዚህ ሕዝቦች የኤሌትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ታልሞ ግድቡ መገንባቱን ተናግረዋል።
እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ ገንዘብ ማዋጣቱን ያመለከቱት አምባሳደሩ "የነበሩ በርካታ መሰናክሎች" ታልፈው ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም. ምረቃው እንሚካሄድ ገልጸዋል።

አምባሳደር ደመቀ ኢትዮጵያ ትርፍ የኤሌትሪክ ኃይል ማምረት በመጀመሯ ለጂቡቲ፣ ሱዳን፣ ኬንያ እና ታንዛኒያ መሸጥ መጀመሯንም አስታውሰዋል።
በዚህም የተነሳ ከጎረቤት አገራት ጋር በኤሌትሪክ ኃይል አቅርቦት መተሳሰር ተችሏል ያሉት በማለት፣ ይህም ወደ በፖለቲካዊ ትስስር አንደሚያመራም ተናግረዋል።
የሕዳሴውን ግድብ ተጠናቅቆ ሲመረቅ ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የምታከብረው "የአባይ ተፋሰስ አገራት እንዲሁም ቀሪው የአፍሪካ አገራት በጋራ የሚያከብሩት ይሆናል" ሲሉም አክለዋል።
በቅርቡ የሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ ይመረቃል መባሉን ተከትሎ ግብፅ "የዓለም አቀፍ ሕግን በጣሰ መልኩ በምሥራቃዊ ናይል ተፋሰስ የሚደረግ የተናጠል እርምጃን" እንደማትቀበል ለበርካታ አፍሪካ አገራት አሳውቃለች።
14 ዓመታትን የፈጀው እና አምስት ቢሊዮን ዶላር ገደማ ወጪን የጠየቀው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ አምስተኛ ዙር ሙሌት ተጠናቆ ምረቃው ጳጉሜ 4 /2017 ዓ.ም. ጥሪ የተደረገላቸው አገራት መሪዎች በተገኙበት እንደሚካሄድ ምክትል አምባሳደር ደመቀ አጥናፉ አረጋግጠዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን ከጅምሩ እንዲሁም የተካሄዱ አምስት ውሃ ሙሌቶችን በጽኑ ያወገዙት የግብፅ ፕሬዝዳንት፣ ከላይኛው የናይል ተፋሰስ አገራት አንዷ ከሆነችው የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ጋር በቅርቡ በሰጡት መግለጫ ላይ ተቃውሟቸውን አሰምተው ነበር።
ፕሬዝዳንት ሲሲ "በድጋሚ ለግብፃውያን ማረጋገጥ የምፈልገው 105 ሚሊዮን ዜጎቻችን እና 10 ሚሊዮን የሚሆኑ በአገራችን ያሉ እንግዶቻችን በሕይወት የሚያቆየው ውሃ እንዲነካ ፈጽሞ እንደማንፈቅድ ነው" ብለዋል።
አምባሳደር ደመቀ የሕዳሴ ግድብን በተመለከተ "በአሁኑ ወቅት ምንም የሚያሰጋ ነገር የለም" ያሉ ሲሆን፣ ግብፅ ታሪካዊ መብት የምትለው "አክትሞለታል" ካሉ በኋላ "ያለው አማራጭ ወደ ትብብር መምጣት ብቻ ነው" ብለዋል።
ግብፅ በአውሮፓውያኑ 1959 የተፈረመው እና የአብዛኛውን የውሃውን ድርሻ የሚሰጣትን የቅኝ ግዛት ስምምነት መሠረት አድርጋ ታሪካዊ ተጠቃሚነቷን በማስጠበቅ የወንዙን ውሃ በበላይነት የመጠቀም ፍላጎት እንዳላት በመጥቀስ ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ ስትቃ

21/08/2025

Big shout out to my newest top fans! Tigabu Ermias, Yoseph Yoseph

19/08/2025

የሠራተኛውን ችግር በደመወዝ ማሻሻያ ብቻ ሳይሆን በሌሎች አማራጮችም ለመፍታት ታስቧል
++++++++++++++++++

| የመንግሥት ሠራተኛው ችግር በደመወዝ ማሻሻያ ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ በቀጣይ የቤት አቅርቦትን እና የጤና መድኅን ሽፋንን ጨምሮ የተለያዩ መፍትሔዎች እንደሚወሰዱ የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አስታወቀ።

የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን መረጃ እንዳመለከተው፤ መንግሥት ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ ወስኗል።

ሆኖም የመንግሥት ሠራተኛው ችግር በደመወዝ ማሻሻያ ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ በቀጣይ የቤት አቅርቦትን እና የጤና መድኅን ሽፋንን ጨምሮ የተለያዩ መፍትሔዎች ይወሰዳሉ ብሏል።

መንግሥት ለዘመናት ሲንከባለል የመጣውን የመንግሥት ሠራተኛ ዝቅተኛ የክፍያ ሁኔታ እና ተያይዞ የመጣውን የኑሮ ጫና በአንድ ጊዜ በሚደረግ የደመወዝ ማሻሻያ ሊቀርፈው እንደማይችል ይገነዘባል ያለው የኮሚሽኑ መግለጫ፤ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ መንግሥት ከእያንዳንዱ የኢትዮጵያ ብልፅግና ምዕራፍ ሁሉም ዜጋ ተጠቃሚ መሆን አለበት ብሎ ደግሞ ያምናል።

ስለሆነም ከሚወሰዱ ሌሎች ማሻሻያዎች በተጨማሪ፣ ከመስከረም 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት መወሰኑን ገልጿል።

እንዲሁም ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ እንደሚደረግ አመልክቶ፤ ይህ የደመወዝ ማስተካከያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት መጠየቁን ገልጿል።

ይሄም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 560 ቢሊዮን ብር እንደሚያደርሰው ተመላክቷል ።

በልጅዓለም ፍቅሬ
++++++++++++++++++++


#ኢትዮጵያ
#ሠራተኛ #ደመወዝ

18/08/2025

ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት የሚጠይቀው የደመወዝ ማሻሻያ፦
*****************************

ከመስከረም 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡ በዚሁ ማሻሻያ መሠረት፦

1. ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4,760 ወደ ብር 6,ዐዐዐ እንዲያድግ
ይደረጋል፡፡
2. የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6,940 ወደ ብር 11,500 ይሻሻላል።
3. ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም
ማሻሻያ ይደረግበታል፡፡
4. ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21,492 ወደ ብር 39,000
እንዲያድግ ይደረጋል፡፡

በዚህ ጉዳይ ላይ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የሰጠውን መግለጫ በኮሜንት መስጫው ውስጥ ያገኙታል፦

18/08/2025

ከመስከረም ጀምሮ ለሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወሰነ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ፤ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው ብሏል፡፡

በዚህም ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት መወሰኑን አስታውቋል፡፡

በማሻሻያው ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4 ሺህ 760 ወደ ብር 6 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ነው ያለው።

ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21 ሺህ 492 ወደ ብር 39 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ብሏል።

የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6 ሺህ 940 ወደ ብር 11 ሺህ 500 የሚሻሻል መሆኑን ገልጿል።

ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ እንደሚደረግበት አስታውቋል።

ይህ የደመወዝ ማስተካከያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ጠይቋል ያለው ኮሚሽኑ፤ ይሄም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል ብሏል።

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሙሉ መግለጫ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፦https://www.fanamc.com/archives/299145

10/08/2025

♥ የቅርስ ስም፡- አጆራ ማንቲያ ፏፏቴ
♥ የቅርሱ ምድብ፡- (I)
♥ የተመዘገበበት መለያ ቁጥር፡- ET-ME-HT-01
♥ የተመዘገበበት ቀን፡- 07/09/2008 ዓ.ም
♥ ቅርሱን የመዘገበዉ ተቋም ፦ከምባታ ዞን ባ/ቱ/መምሪያ
♥ የቅርሱ መገኛ/አድራሻ ክልል፦ ማ/ ኢትዮጵያ
♥ ዞን፦ ከምባታ ዞን
♥ ወረዳ፦ ሀ/ጡ/ዙ
♥ ቀበሌ ……ልዩ ቦታ፡- አጆራ
♥ የጂ.ፒ.ኤስ መረጃ፡- GPS 37N0345094 0794248.
♥ ከፍታ ከባህር ወለል በላይ 1516ሜ
♥ ቅርሱ የሚገኝበት ሁኔታ (ይዘቱና ምሉእነቱ)፡- በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኝ ነው፡
♥ የቅርሱ ባለቤት፦ የከምባታ ማህበረሰብና መንግሥት ነው፡፡
♥ የቅርሱ ሀገራዊ ፋይዳ ፡- ለቱሪዝም ከሚሰጠው ጥቅም አንጻር ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ ጥቅም ይሰጣል፡፡
♥ የቅርሱ ታሪክና ታርካዊ ፋይዳ፦ አጆራ ፏፏቴ በዞኑ ውስጥ ብሎም በክልል ደረጃ ከሚገኙ ግንባር ቀደም ፏፏቴዎች ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዝ ፏፏቴ ነው፡፡ ፏፏቴው ስያሜውን ያገኘው በሀደሮ ጡንጦ ዙሪያ ወረዳ ከሚገኙ ቀበሌያት አንዱ በሆነው በአጆራ ቀበሌ ከሚኖሩት አጆራ ከሚባሉ ጎሳዎች የመጣ መጠሪያ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ይህን ፏፏቴ ለመጎብኘት ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ቱሪስቶች ሲመጡ በጥልቀቱ ፣በመንታነቱ ፣በአረንጓዴ ሸለቆና በግጭት ምክንያት በሚፈጠረው ነጭ ጭስ የሚደመሙበት እንደሆነ ይታወቃል፡፡
♥ ለህብረተሰቡ ያለዉ ማህበራዊ፣ ባህላዊ፣ሐይማኖታዊ እና መንፈሳዊ ፋይዳ፡- ቱሪስቶች ወደ አከባቢው ስመጡ ከአከባቢው አዳድስ ነገሮችን የአከባቢውን ባህል አውቀውና ተምረው የእነሱን መልካም ተሞክሮዎችን ያጋራሉ ይህ ትልቅ ማህባራዊ ማስተጋብርን ይፈጥራል፡፡
♥ የቅርሱ ምጣኔ ሀብታዊ ፋይዳ፦ ለቱሪዝም አገልግሎትለሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር ያለዉ ፋይዳ ከፍተኛ ነው።
♥ የቅርሱ ተደራሽነት፡- የመጀመሪያ ጉዞዎት መስመር ከአዲስ አበባ በሻሸመኔ ከሆነ ከሻሸሜኔ አርባ ምንጭ የሚወስደውን ዋና አስፋልቱን በመያዝ 337 ከ.ሜትር ርቀት እንደተጓዙ የሾኔ ማዞሪያን ሲደርሱ ወደ በስተቀኝ በመታጠፍ ጥቂት ከ.ሜትሮች ከተጓዙ በኋላ የከምባታ ዞን ርዕሰ ከተማ ዱራሜን ያገኛሉ፡፡ በዚህች ከተማ ለጥቂት ጊዜ ማረፍ ቢያስፈልግዎት የተለያዩ ባህላዊና ዘመናዊ ምግቦችንና መጠጦችን እየቀመሱ የከተማዋን ንጹህ አየር እየተነፈሱ እያለ ዓይኖትን በድንገት ወደ ሀምበርቾ ተራራ ስያመትሩ ውብ የሆነ ሰንሰለታማ ተራራ ያስተውላሉ፡፡ የዱራሜ ከተማ ቆይታዎትን አጠናቀው ጉዞዎትን ወደ አጆራ ፏፏቴ ሲያቀኑ 17 ኪ.ሜትር እደተጓዙ የቃጫ ቢራ ወረዳ ርዕሰ ከተማ የሆነችውን ሺንሺቾ ከተማን ያገኛሉ፡፡ ከተማውን አቋርጠው በሚሄዱበት ወቅት በተፈጥሮ የታደለች ምድራዊ ገነት መሆኗን በዓይነ ህሊና እየቃኙ ከዱራሜ ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው ሌሾ ማዞሪያ ይደርሳሉ፡፡ ሌሾ ማዞሪያን ሲደርሱ ከተማዋን በሁለት ከፍለው የሚያልፍ ከአዲስ አበባ ወላይታ ሶዶ የሚያደርስ አውራ መንገድ ይመለከታሉ፡፡ ይህንን ዋና መንገድ መሃል ለመሃል አቋርጠው ከተጓዙ በኋላ በተፈጥሮ ፍራፍሬዎች የታደለችችውን ሀደሮ ከተማና አካባቢውን እየቃኙ ጉዞዎትን ከሀደሮ ሙዱላ በሚወስደው መንገድ የተከማዋን ክልል ለቀው ሳይወጡ ወደ ግራ በመታጠፍ ወደ አጆራ ፏፏቴ የሚወስደውን ጥርጊያ መንገድ በመያዝ 7 ኪ.ሜትር ያህል እንደተጓዙ የአጆራ መንታያው ፏፏቴ ትንግርታዊ አወራረድ ፣የአዕዋፋት ድንቅ ዜማ ፣በፏፏቴው ግጭት የሚፈጠረውን ጭስና በሸለቆው ውስጥ ቁልቁል የሚታየውን የሥነ-ህይወት ገጽታ ያስተውላሉ፡፡
BY ETHIOPIA HOTEL AND ❤🙏

08/08/2025


የከምባታ ዞን ህዝብ ተወካዮች የምክር ቤት እያካሄደ ባለው 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባኤ አቶ ዳዊት ሀንዲኖን የከምባታ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አድርጎ ሾመ።

አቶ ዳዊት ሀንዲኖ በምክር ቤቱ ፊት ቀርቦ ቃለ መሐላ ፈጽመዋል።

08/08/2025
06/08/2025

የከምባታ ዞን ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባኤን ከነሐሴ 01/2017 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚያካሂድ የዞኑ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አስካለ ሰሶ ገለፁ።

ጉባኤው ከነሐሴ 01-03/2017 ዓ/ም በዞኑ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የሚካሄድ መሆኑም ተመልክቷል።

የከምባታ ዞን ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አስካለ ሰሶ እንደገለፁት ምክርቤቱ በጉባኤው በሚከተሉት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃልም ነው ያሉት።

አጀንዳዎቹም

1. የከምባታ ዞን ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 26ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ-ጉባኤ መርምሮ ማጽደቅ፣

2. የከምባታ ዞን አስ/ር ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት አድርጎ ማጽደቅ፣

3. የከምባታ ዞን አስ/ር ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት አድርጎ ማጽደቅ፣

4. የከምባታ ዞን አስ/ር የ2018 በጀት ዓመት የበጀት መከፋፈያ ቀመርና የበጀት ረቂቅ አዋጅ ቀርቦ ተወያይቶ ማጽደቅ፣

5. የከምባታ ዞን ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት 2018 በጀት ዓመቱ ዕቅድ እና የዕቅዱ ማስፈጸሚያ በጀት ቀርቦ ተወያይቶ ማጽደቅ፣

6. የከምባታ ዞን ከ/ፍርድ ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ እና የዕቅዱ ማስፈፀሚያ በጀት ቀርቦ ተወያይቶ ማጽደቅ፣

7. ሹመት

8. ማሳሰቢያ እና

9. መስክ ጉብኝት እንደሚሆን የተከበሩ ወ/ሮ አስካለ ሰሶ ገልፀዋል።

#የከምባታ ዞን ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት!

03/08/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Fasika Fana, Abinet Demisse

Address

Durame

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Durame times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Durame times:

Share