Durame times

Durame times We stand together

28/05/2026

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Teshome Yohannes, Ansh Kebede, Abî Ye Em Lig, Aliyu Musa

28/05/2026

ግንቦት 24 ሥራ ዝግ ነው‼️

ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ/ም በፌዴራል እና ክልል መንግሥታዊ ተቋማት እንዲሁም የግል ተቋማት ሥራ ዝግ ሆኖ ይውላል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚካሄደውን የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል።

ቦርዱ፦ ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ እንዲያከነውኑ ፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት እንደማያስገድድ አሳውቋል።

የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ አረበታቷል

24/05/2026

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Tofik Gamiel, Ayele Alemayehu, Mhiretu Selamu, Angalko Dobay, Tamirat Melese, Jon Heri, ደሱ ተፈራ, Abush Abu, Shimelis Shibiru, Ashenafi Gintamo, Ibrahim Nasir, Tegegn Tesema, Kebede Kelecho, Tg Ya Tadu Lij, Teketel Abato, Abenezer Melese, Asfew Kerlos, Solomon Ako, Tsegeye Debso, Ede Edilu, Messi Gebre Haileselesase, Betig Alex, Wegu Wegu, Abinet Mitiku, Kebede Ahmed, Rediet Man, Elys Muktr, Yosef Dawit, Tsedeke Dubela, Hambaricho Kembata

02/05/2026

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Tinsu Buenamo, Zeleke Aeyanw, Tamiru Bekele, Masfen Qalebso, Aserasagn Abara, Michael Yonas, Tsega Desta, Tadele Shamebo Edamo, Erg Tfs Msk, Fanose Kelebo, Fitsum Worku, Ergicho Adane, ደርቤ.ደንኤል ሄሪሞ, Tigist Gute, Mirkat Tesema, Bini Benjamin, Fasika Anabo Easter, Mano Abara, ሜር ሜር, Digafu Mathewos, እሼቱ ደስለኝ, Hana Teka, Negsti Berhnu, Abi Alemu, Tamirat Daneli, Teketel Tesfaye, Abush Assefa, Temesigen Tadese, Minase Desalegn, Hopy Tadee, Abel Ermias, Deginet Desta, Štařş Kinĝdøm, Habitamu Bunare, Emu Gela, Asde Elias

14/03/2026

Big shout out to my newest top fans! Tigabu Ermias, Yoseph Yoseph

19/12/2025

ምንም ጉዳት የለዉም !

የፋርስ ባሕረ ሰላጤን ወደ ቀይ የቀየረው
የደም ዝናብ ወሳኝ መረጃዎች !

በኢራን ሆርሙዝ ደሴት ላይ ታህሳስ 17 ቀን 2025 5:10 ፒኤም GMT የዘነበዉ “የደም ዝናብ” የኢራን ደሴት የባህር ዳርቻ ውሃ በአንድ ሌሊት ወደ ቀይ ባህር ቀይሮታል።

በሆርሙዝ ደሴት ላይ የነበረው አስገራሚ ትዕይንት በቪዲዮ ተቀርፆ በማህበራዊ ሚዲያ ከተሰራው በኋላ የበርካቶች መነጋገሪያ እየሆነ ይገኛል ።

ይህን አስደናቂ የተፈጥሮ ክስተት ተከትሎ አንዳንዶቹ ከመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች ጋር በማነፃፀር ቁጣ ነዉ ያሉት ሳይንስ በበኩሉ
በደሴቲቱ ከፍተኛ የብረት ኦክሳይድ ክምችት ምክንያት ነው ያለውን ጉዳይ ከሁለት ወገን መረጃ እንዲኖረን በትንታኔ ለማየት ወድደናል ።

ከሺህ ዓመቱ መባቻ ጀምሮ በርካታ የኢራን ሳይንቲስቶች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ስለሚከሰቱ ድርቅ እና የኢራን የውሃ አጠቃቀም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ሲያስጠነቅቁ ቢቆዩም በዚህ በአሜሪካ የሚመራዉ አለም የማዕቀብ ናዳ አማራጭ ስላሳጣት ሀገሪቱ በምግብ ራስን መቻል አለባት በሚል በተለይም ከፍተኛ ዉሐ የሚፈልገውን ሀባብ አይነት ምርቶች በባለሀብቶች እና ሹመኞች በስፋት ስለሚመረት ለመግለጽ የሚቸግር ችግር ዉስጥ ከቷታል ።

ይህን ተከትሎ ላለፉት ስድስት አመታት በምድሪቱ ዝነብ ነጥፎ በአሁኑ ሰዓት ኢራን በግማሽ ምዕተ ዓመት ውስጥ በአገሪቱ ውስጥ ከተከሰተው እጅግ የከፋ ድርቅ ጋር የሚነፃፀር ከባድ ሁኔታ ላይ ትገኛለች ።

በኦፊሴላዊ ግምቶች መሠረት፣ በአገሪቱ ውስጥ ያለው የዝናብ መጠን ከረጅም ጊዜ አማካይ ጋር ሲነጻጸር በዚህ ዓመት በ89 በመቶ ገደማ ቀንሷል።

ባለፈው ወር የውሃው መጠን በጣም ዝቅተኛ ስለነበር 10 ሚሊዮን ነዋሪዎች የሚኖሩባት ዋና ከተማዋ ከአካባቢው ለቅቆ መውጣት ሊያስፈልጋት እንደሚችል ስጋት መኖሩን መንግስታቸው ገልጿል ።

በዚህ ሁኔታ ዉስጥ ባለችበት ነዉ 100ሚሜ አካባቢ ዝናብ በአንድ ሌሊት በሆርሙዝ ደሴት የዘነበው ።

ከባድ ዝናብ በደሴቲቱ ቀይ የባህር ዳርቻ ዳርቻ የውሃ እና የአሸዋ ቀለም እንዲለወጥ ምክንያት ሆኗል።

ወደቀይነት መቀየሩን ከሃይማኖታዊ ትንቢቶች ጋር ከማያያዛችን በፊት ለመሆኑ ደሴቷ ምን አይነት ናት የሚለውን ማወቅ ያሻል ።

ሆርሙዝን ደሴት በአስደናቂ ነገሮች የተሞላች ናት ።

ብዙውን ጊዜ በቀለማት ያሸበረቀ መልክዓ ምድሯ "የቀስተ ደመና ደሴት" ተብሎ የሚጠራው የሆርሙዝ ደሴት ዓመቱን ሙሉ ተወዳጅ መዳረሻ ነው። ቱሪስቶች ደማቅ አፈርዋን፣ ሻካራ የባህር ዳርቻዋን እና ታሪካዊ ምልክቶችን ለማየት ይጎበኛሉ።

ደሴቲቱ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በጂኦሎጂካል እንቅስቃሴ የተቀረጹ ቢጫ፣ ብርቱካናማ እና ሌሎች የተፈጥሮ ጥላዎችንም ታሳያለች። ሆርሙዝ ለሳይንቲስቶችም ሆነ ለተጓዦች ትኩረት የሚስብ ቦታ ሆኖ ቀጥሏል፣ ይህም በአየር ሁኔታ እና በምድር ጂኦሎጂ መካከል ስላለው ግንኙነት ግንዛቤ ይሰጣል።

እንግዲህ ዝናቡና በዓለም ዙሪያ ያሉ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን ትኩረት የሳበው ተፈጥሯዊው ክስተት በዚህች ደሴት ነዉ ።

አንዳንዶቹ ከመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች ጋር በማነፃፀር አስተያየት እየሰጡ ይገኛሉ ።

አንድ አስደናቂ የተፈጥሮ ክስተት የኢራንን የሆርሙዝ ደሴት ወደ ዓለም አቀፍ የውይይት መድረክ ቀይሮታል ።

አንድ ታዋቂ ዩቱዩቨር “የመጨረሻ ዘመን” ምልክት ሊሆን እንደሚችል ጠቁሟል፣ ሌላኛው ደግሞ “ማለቂያ የሌለው ሀዘን” እንደሚያበቃ ፍንጭ እንደሆነ አክሏል። ሌላው ደግሞ “መጽሐፍ ቅዱሳዊ ይመስላል” ብሏል።

ከዚህ አስደናቂ ክስተት በስተጀርባ ያለው ሳይንሳዊ ማብራሪያ በደሴቲቱ ልዩ

18/12/2025

የሺንሽቾ ከተማ ጊዜያዊ ሽግግር ምክር ቤት አቶ መለሰ ገቡሬን የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አድርጎ ሾመ።

በከምባታ ዞን የብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የመንግሥት ረዳት ተጠሪ በሆኑት በአቶ በፍቅር ታምራት አቅራቢነት አቶ መለሰ ገቡሬ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው ተሹመዋል።

የሺንሽቾ ከተማ ጊዜያዊ አማካሪ ሽግግር ምክር ቤት እያካሄደ ባለው 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው እንዲሾሙ በሙሉ ድምጽ አፅድቋል።

አቶ መለሰ ገቡሬ በሺንሽቾ ከተማ ጊዜያዊ አማካሪ ሽግግር ምክር ቤት ፊት ቀርበው ቃለ መሐላ ፈፅመዋል።

19/11/2025

የብዝኃነት መርከቧ - ኢትዮጵያ
++++++++++++++++

| የተለያየ ቋንቋ መናገር ከመግባባት አይገድባቸውም። የቆዳ ቀለም ውበታቸው ነው። የሰፈሩት የቦታ ርቀት 'ኢትዮጵያውያን' ከመባል አያርቃቸውም። የየግል እምነታቸውን ይዘው፤ የሁሉንም በጋራ አክብረው በፍቅር ይኖራሉ።

አንድ ለመሆን አንድ አይነት እንሁን አይሉም። አንድነታቸውንም አይከፍለውም። የልዩነት ምንጭም አልሆነም።

ይህ ጸጋ በፈጣሪ የተሰጡት መሆኑን ተረድተው በጋራ ስለሀገር ያስባሉ። ብዙ ቋንቋ፣ ብዙ ባህል፣ ብዙ ሃይማኖት ሌላም ብዙ ብዙ ማንነት አላቸው። አንዱ ያለው አንዱ የለውም። አንዱ የአንዱን ሲያይ ይደሰታል። ለማየት ይጓጓል። ለመማር ይናፍቃል።

ሁሉም ብዙኅነትን ያከበሩ የአንዲት ሀገር የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው። ኢትዮጵያ አምጣ የወለደቻቸው፣ ልጆቼ የምትላቸው፤ እነሱም እናቴ የሚሏት ድንቅ ልጆች ናቸው።

ከመርከቧ ላይወርዱ ተማምለው የተሳፈሩ ተጓዦች። ላይነጣጠሉ የተገመዱ ልዩነት የማይለያቸው ህዝቦች።

በየዓመቱ በአንድ የሚያገናቸውን ከተማ መርጠው ብሔር ብሔረሰቦች በአንድ ተገናኝተው በጋራ የጋራ ባህላቸውን ይጋራሉ። ይተዋወቃሉ። ይመክራሉ።

የህዝቡን አንድነት የማይወዱ በአንድነት መቆሙ የከነከናቸው የፖለቲካ ነጋዴዎች በብሔር፣ በቋንቋ፣ በሰፈር ልዩነቱን ሊያሰፉት ቢጥሩም ህዝቡ ግን ኢትዮጵያዊነት አንድነቱን አጽንቶ ቆይቷል።

አንዳቸው የሌላቸው የጉድለት ሙላት፤ አንዳቸው የሌላቸው የድክመት ብርታት ሆነውና አንዳቸው በሌላቸው የችግር ቀን ደርሰው ዘመናትን ዘልቀዋል፡፡

ከዚህም በላይ በጋራ ቆመውና የጋራ ጠላቶቻቸውን በጋራ መክተው አጽንተዋት ኖረዋል፤ እየኖሩም ናቸው፤ ወደፊትም የሚኖሩባት ትልቅ ሀገር ናት፡፡ ኢትዮጵያ።

''ኢትዮጵያ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ብሔር ብሔረሰቦች የራሳቸውን ማንነት፣ ባህላቸውንና ታሪካቸውን ይዘው የተሳፈሩባት፤ ለሁሉም የምትበቃ ትልቅ መርከብ ናት ይላሉ'' የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ ።

እንደ አቶ አረጋ ገለጻ፤ ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገር፤ ትልቅም መርከብ ናት፡፡ ይህች መርከብ ደግሞ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የየራሳቸውን ማንነት፣ ባህላቸውን እና ታሪካቸውን ይዘው የተሳፈሩባት፤ ለሁሉም የምትበቃ ናት፡፡

ኢትዮጵያ የምትባል ትልቅ ሀገር ከተፈጠረችበት ጊዜ ጀምሮ ብሔር ብሔረሰቦች ተዋደውና ተከባብረው ኖረውባታል፡፡ አሁንም እየኖሩ ናቸው ።

አቶ አረጋ እንደሚያብራሩት፤ ለሁሉም የወል ቤት የሆነችው ኢትዮጵያ በተለያዩ ሥርዓቶች የተለያዩ የፖለቲካ አስተሳሰቦች በፖለቲካ ልሂቃን አማካኝነት መጥተው ብዙ ውጣ ውረድ እንድታሳልፍ ቢያስገድዷትም፤ በእነዚህ ውጣ ውረዶች ሁሉ ጸንታ በመቆም አሸናፊ ሆናለች፡፡

ጠላቶቿ ብዙ ጊዜ ትወድቃለች፣ ትበተናለች፣ ትደክማለች ብለው በክፉ ሀሳብ ሲጠብቋትም፤ ክፉ ቀኖችን ሁሉ በአምላኳ ፈቃድ፣ በሕዝቦቿ አንድነትና ጥረት ተሻግራ ብልጽግናዋን የምታረጋግጥበትን ጉዞ ጀምራለች፡፡

ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታትም የቀደመውን የልዩነት ትርክት አስተካክላ እውነተኛ ኅብረብሔራዊ አንድነትን እየገነባች ትገኛለች፡፡

ልዩ ልዩ ባህል፣ ታሪክና ማንነት ያላቸው ህዝቦቿም በጋራ ሊሰሩና ሊያለሙ እንደሚችሉ በማመን የዘመናት ታሪኳን የሚቀይሩ ስራዎችን ሰርተው አሳይተዋል። አሁንም እየሰሩ ነው ።

ዋና አስተዳዳሪው ጨምረው እንደተናገሩት፤ የከምባታ ዞንና ህዝብም የዚች መርከብ አካልም፣ ባለቤትም እንደመሆኑ፤ በመርከቧ ልክ ትኩረት አግኝቶ እየተጓዘ ይገኛል፡፡

የሀንበርቾ ተራራን አይነት ከፍ ያለ አቅም ያላቸው የዞኑን የቱሪዝም መስህቦችን ለይቶ በማልማት በኩል የተከናወኑና እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችም ለዚህ ማሳያዎች ስለመሆናቸው ጠቁመዋል፡፡

20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ምክንያት በማድረግ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተለያዩ አከባቢዎች ምልከታ እያደረገ ያለው የጋዜጠኞች ቡድን ወደ ከምባታ ዞን ገብቷል፡፡ በዓሉም በዚሁ ዞን በድምቀት የሚከበር ይሆናል ።

በወንድወሰን ሽመልስ
+++++++++++++++++++++

19/11/2025

Address

Durame

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Durame times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share