ROCK-Realities Of Community Kembata

ROCK-Realities Of Community Kembata Realities of community kembata will be posted ....

 #ደቡብአፍሪካ የዜጎች ደህንነትን ለማስጠበቅ የተደረገው የዲፕሎማሲ ጥረትበደቡብ አፍሪካ “መጤ ጠል” እንቅስቃሴን ተከትሎ በዜጎቻችን ላይ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ለመከላከል፣ የኢትዮጵያ ከፍ...
30/05/2026

#ደቡብአፍሪካ
የዜጎች ደህንነትን ለማስጠበቅ የተደረገው የዲፕሎማሲ ጥረት
በደቡብ አፍሪካ “መጤ ጠል” እንቅስቃሴን ተከትሎ በዜጎቻችን ላይ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ለመከላከል፣ የኢትዮጵያ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ልዑካን ቡድን ከደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በፕሪቶሪያ (ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ/ም) ውይይት አድርጎ የሚከተሉት ዋና ዋና መግባባቶች ላይ ደርሷል፡

👉ሕጋዊ ሰነድ ላላቸውም ለሌላቸውም ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የደህንነት ዋስትና የመስጠት ኃላፊነት በደቡብ አፍሪካ መንግሥት ላይ መሆኑ ተሰምሮበታል።

👉ማንኛውም ሕገ-ወጥነት በሕገ-ወጥ መንገድ ሊፈታ እንደማይገባና በሀገሪቱ ያሉ ዜጎች በደቡብ አፍሪካ ሕግና ዓለም አቀፍ ስምምነቶች መሠረት እንዲስተናገዱ ስምምነት ላይ ተደርሷል።

👉ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ጨምሮ በወንጀል ሰንሰለቶች ላይ የተቀናጀና የማያዳግም እርምጃ ለመውሰድ ሁለቱ አገራት ተስማምተዋል።

የልዑካን ቡድኑ መልዕክት ለዜጎች፦

ዜጎች ራሳቸውን ከወንጀል ነክ ድርጊቶች እንዲያርቁ እና ችግሮችን ከመሸፋፈን እንዲቆጠቡ፤

ከተበታተነ አሠራር በመውጣት ሀብትን አስተባብሮ ወደ ኩባንያና ትላልቅ ኢንቨስትመንቶች በማደግ፣ በትውልድ ሀገርና በደቡብ አፍሪካ በመሥራት ውጥረቶችን መቀነስ እንደሚቻል ጥሪ ቀርቧል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በኤምባሲውና በሌሎች ተቋማት በኩል አስፈላጊውን ትብብርና ቅንጅት ማድረጉን ይቀጥላል።

Ethiopian embassy SouthAfrica

ወደ ደቡብ አፍሪካ የመጣው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን የዜጎችን ደህንነት ጥበቃ በሚመለከት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተወያይቶ የጋራ መግባባት ላይ ደርሷል  (ፕሪቶሪያ ግንቦት 22 ቀን 2018...
30/05/2026

ወደ ደቡብ አፍሪካ የመጣው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን የዜጎችን ደህንነት ጥበቃ በሚመለከት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተወያይቶ የጋራ መግባባት ላይ ደርሷል
(ፕሪቶሪያ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ/ም)
******************************
በደቡበ አፍሪካ የተጀመረው “መጤ ጠል” እንቅስቃሴ ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ የአፍሪካ አገራት ስደተኞችን ባነጣጠረ መልኩ የማዋከቡ ተግባር፣ የዜጎችን ኃብት እና ንብረት እስከ መዝረፍ እንዲሁም ሥራ እስከ መከልከል ደረጃ ደርሷል፡፡ እንቅስቃሴውን የሚመራበት “ሕገ-ወጥ ስደተኞች ይውጡልን” ሰልፍ በተደጋጋሚ በአገሪቱ አብዛኛው ከተሞች ሲያደርጉ መቆየታቸው እና እ.ኤ.አ. ጁን 30 ቀን 2026 ድረስ አገሪቱን ለቅቃችሁ ወጡ የሚል የማስጠንቀቂያ ገደብ ማስተላለፋቸውን ይታወቃል፡፡ ይህንንም ተከትሎ በዜጎቻችን ላይ የከፋ አደጋና ጉዳት እንዳይደርስ መከላከልን ታሳቢ በማድረግ መንግሥት ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ልዑካን ቡድን ወደ ደቡብ አፍሪካ ልኳል፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካን ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ የውጭ ግንኙነትና ትብብር ዲፓርትመንት፣ የድንበር አስተዳደር ባለሥልጣን፣ የደቡብ አፍሪካ የፖሊስ አገልግሎት እንዲሁም ከሀገር ውስጥ ጉዳዮች ዲፓርትመንት ተወካዮች ጋር ገንቢ ምክክር እና ውይይት አድርጓል፡፡

በውይይቱ ወቅት ሁለቱ አካላት ማንኛውም ሕገ-ወጥነት በሕገ-ወጥነት መንገድ ሊፈታ እንደማይችልና እንደማይገባ ነገር ግን ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ጨምሮ ሌሎች የሕግ ጥሰቶች እና ወንጀሎች ከመሠረታቸው መቆም እንዳለባቸው ተማምነው ለዚህም በጋራ ለመሥራት ተግባብተዋል፡፡ በሌላ በኩል በደቡብ አፍሪካ ላሉ ስደተኛ ኢትዮጵያዊያን ዜጎቻችን ሕጋዊ ሰነድ ላላቸውም ለሌላቸውም የደኀንነት ዋስትና የመስጠት ኃላፊነት እንዳለበት ተሰምሯል፡፡ ነገር ግን ሕገ-ወጥ በሆነ መልኩ በደቡብ አፍሪካ ያሉ ዜጎች የሀገሪቱ ሕግና ደቡብ አፍሪካ ፈራሚ በሆነችባቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች መሠረት መስተናገድ እንዲችሉ ተግባብተዋል፡፡ በዚህም ሂደት የኢትዮጵያ መንግስት በኤምባሲው እንዲሁም በሌሎች ተቋማት በኩል አስፈላጊውን ትብብርና ቅንጅት እንደሚያደርግ ተስማምተዋል፡፡

በተያያዥነት በተለያየ መንገድ በወንጀልና ሕገ-ወጥ ሥራዎች ውስጥ የተጠመዱ ስደተኛ ዜጎች በምንም ሁኔታና ደረጃ ቢሆኑ ከህግ ማምለጥ የማይችሉ መሆኑ ታውቆ የተቀናጀ የሕግ እርምጃ መውሰድ ጉዳይ ላይ በተለይም ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የሚሳተፉ እና ዜጎችን ለእንግልት የሚዳርጉ የወንጀል ሰንሰለቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መውሰድ እንደሚያስፈልግ ሁለቱ አገራት ተወካዮች በውይይታቸው ተስማምተዋል፡፡

በአጠቃላይ የልዑካን ቡድኑ ደቡብ አፍሪካ ያለውን ስደተኛ ዜጎች ሁኔታ አንጻር ከመቼውም ጊዜ በላይ መደራጀትና መቀናጀት፣ የአገሪቱን ሕግና ዓለም-አቀፍ ሕግጋትን በማወቅ ያሉ እድሎችን በሕጉ መሠረት መጠቀም አስፈላጊ መሆኑ ተሰምሮበታል፡፡ ነገር ግን ማንም ሰው ራሱን ከወንጀል ነክ ጉዳዮች እንዲያርቅና የሚከሰቱ ችግሮችንና ወንጀሎችን መሸፋፈን ሳያስፈልግ የሕግ ተጠያቂነትን በመፍጠር ለማሕበረሰባችን የተረጋጋ ኑሮና የሥራ ከባቢ መፍጠር ጠቃሚና ትክክል መሆኑን በልዑካን ቡድኑ በኩል በአጽንዖት ተገልጿል፡፡ በሌላ በኩል ዜጎች በተናጥል ከመንቀሳቀስ ይልቅ ኃብት በማሰባሰብና በማቀናጀት ወደ ኩባኒያና ትላልቅ ኢንቪስትመንት በማሳደግ በትውልድ አገር ኢትዮጵያ እና በደቡብ አፍሪካም መሥራት ቢችሉ የጋራ ተጠቃሚነት በመፍጠር የሚታዩ ውጥረቶችን መቀነስ እንደሚቻል ጠቁሟል፡፡
@ Ministry of Foreign Affairs of EthiopiaPPOA Englis

የቅድሚያ ጥንቃቄ መልዕክት በደቡብ አፍሪካ በሊምፖፖ ግዛት ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ የፀረ-ስደተኛ ተቃውሞ የሚመሩ ግለሰቦች በሊምፖፖ  ግዛት ሰኔ 8 / 2026 (08 June 2026) ከ...
28/05/2026

የቅድሚያ ጥንቃቄ መልዕክት

በደቡብ አፍሪካ በሊምፖፖ ግዛት ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

የፀረ-ስደተኛ ተቃውሞ የሚመሩ ግለሰቦች በሊምፖፖ ግዛት ሰኔ 8 / 2026 (08 June 2026) ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ በሊምፖፖ፣ ፖሎክዋኔ (Jack Botes Park) የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ ቅድሚያ ዝግጀት መድረግ መጀመራቸውን የደረሱን መረጃዎች አሳይተዋል።

ሰለሆነም በተጠቀሰው ቦታ እና አከባቢው የምትገኙ ውድ ኢትዮጵያውያን ጥንቃቄ እንድታደርጉ ለማሳሰብ እንወዳለን።

በትላንትናው ዕለት የፍትህ፣ የወንጀል መከላከል እና የጸጥታ ሚኒስትሮች በአገሪቱ ውስጥ በኢሚግሬሽን እና በሕገ-ወጥ የውጭ ዜጎች ላይ እየጨመረ የመጣውን ተቃውሞ ለመወያየት አስቸኳይ ስብሰባ ጠ...
28/05/2026

በትላንትናው ዕለት የፍትህ፣ የወንጀል መከላከል እና የጸጥታ ሚኒስትሮች በአገሪቱ ውስጥ በኢሚግሬሽን እና በሕገ-ወጥ የውጭ ዜጎች ላይ እየጨመረ የመጣውን ተቃውሞ ለመወያየት አስቸኳይ ስብሰባ ጠርተዋል። ስብሰባው የሚካሄደው በዩኒየን ህንፃዎች ነው። ፎቶ፡ Nkosikhona Malinga-Mnisi /EWN
የደቡብ አፍሪካ የጸጥታ ክላስተር ሚኒስትሮች የደቡብ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ (SADC) አገሮች የኢሚግሬሽን ሕጎችን በማስከበር ረገድ የሚያደርጉትን ጥረት እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ይህ ጥሪ በፕሪቶሪያ በመንግስት፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች እና በሕገ-ወጥ ስደት ላይ ተቃውሞዎችን በሚመሩ ቡድኖች መካከል የተደረገውን አስቸኳይ ስብሰባ ተከትሎ ነው።

ከስብሰባው በኋላ የመከላከያ ሚኒስትር አንጂ ሞትሼክጋ የደቡብ አፍሪካ ባለስልጣናት አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ከጎረቤት አገሮች ሲወጡ ምንም አይነት ምርመራ ሳይደረግላቸው እንዲመለከቱ ይገደዳሉ ብለዋል።

We just returned from an unforgettable 3 day camping expedition exploring the roaring majesty of Ajora Falls, the beauti...
28/05/2026

We just returned from an unforgettable 3 day camping expedition exploring the roaring majesty of Ajora Falls, the beautiful Saro Bira landscape, and the breathtaking views from the top of Mount Hambaricho. 🏕️⛰️

Beyond the stunning scenery, what truly made us feel at home was the incredible hospitality and guiding support from the Hambaricho Eco Tourism Office along with the absolutely delicious authentic local food prepared by the wonderful local moms. ❤️

Kembata Zone is a must visit destination for anyone looking to experience authentic culture and untouched nature. Do yourself a favor plan a longer visit and experience this warmth firsthand.

Don’t just add this place to your bucket list, make it a priority.
We believe Everyone needs to experience the warmth of Kembata!

We always feel at home whenever we visit .

A huge thank you 🙏 to everyone who chose Guzo Adwa Hiking and joined us on this incredible trip. See you soon on another adventure! 🏔️

📞 Booking & Information
+251942545470,+251929176542

የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ ዘራፊዎችን አሰርኩ ብሎል Bloemfontein, South Africa 🇿🇦😭😭በደቡብ አፍሪካ በብሉምፎንቴን፣ ሮክላንድስ አካባቢ አንድ የአልኮል መጠጥ መሸጫ ሱቅን ሲዘርፉ ...
25/05/2026

የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ ዘራፊዎችን አሰርኩ ብሎል

Bloemfontein, South Africa 🇿🇦😭😭በደቡብ አፍሪካ በብሉምፎንቴን፣ ሮክላንድስ አካባቢ አንድ የአልኮል መጠጥ መሸጫ ሱቅን ሲዘርፉ የተገኙ ወደ 100 የሚጠጉ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተሰማ።

ፖሊስም በቦታው ላይ በሚደረገው ምርመራ ህገ-ወጥ ድርጊቱን ሲፈጽሙ የነበሩትን በርካታ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋል የቻለ ሲሆን፣ ምርመራውን መቀጠሉን ተዘግቧል።

በደቡብ አፍሪካ ለምትኖሩ ስደተኞች በሙሉ፦የጥንቃቄ መልዕክት⁉በአሁኑ ወቅት በደቡብ አፍሪካ በተለያዩ አካባቢዎች በኦፕሬሽን ዱዱላ ወይም በተለያዩ ማርች to ማርች ብቻ ሳይሆን በሕጋዊ የመንግሥ...
25/05/2026

በደቡብ አፍሪካ ለምትኖሩ ስደተኞች በሙሉ፦የጥንቃቄ መልዕክት⁉
በአሁኑ ወቅት በደቡብ አፍሪካ በተለያዩ አካባቢዎች በኦፕሬሽን ዱዱላ ወይም በተለያዩ ማርች to ማርች ብቻ ሳይሆን በሕጋዊ የመንግሥት አካላት/በፖሊስ እና በሆም አፌርስ/Home Affairs/ ጭምር የተቀናጀ ትልቅ የፍተሻ ኦፕሬሽን ተጀምሯል በመሆኑም ራሳችንንና ንብረታችንን ከማንኛውም እንግልት ለመጠበቅ የሚከተሉትን ነጥቦች በጥብቅ እንድንተገብርና እንድንጠነቀቅ ለማሳሰብ እንወዳለን፦

1. አሰላም/Asylum እና የሀገሪቱ ID ያላቸው ሰዎች ጥንቃቄ
ከአሰላም ውጭ የዚህን ሀገር ID የያዛችሁ ወገኖች ፦ ሰነድ በሚጠየቅበት ወቅት የ-ID መነሻችሁ/የ4 ዓመትም ይሁን ከዚያ በላይ በጥብቅ እየተመረመረ ነው።"፦አንተ ስደተኛ ሆነህ እንዴት ID ይኖረሃል⁈" የሚሉ ጥያቄዎች እየተበራከቱ ሲሆን ጉዳዩ እስኪጣራ ድረስ የመታሰር ዕድሉ ከፍተኛ ነው።

ከአሰላም ውጭ ሌላ የሀገሪቱን ID የያዛችሁ ሰዎች፣ሰነዶቻችሁን በድፍረት ከማሳየትና ራስን ለአላስፈላጊ ጥርጣሬ ከመዳረግ ተቆጠቡ።

2. "ለምን መጣህ?" ለሚለው ጥያቄ የምንሰጠው ምላሽ
በቁጥጥር ስር ስንውል ወይም ስንጠየቅ "ለስራ ነው የመጣሁት" ከማለት ፍጹም ተቆጠቡ፥ሁላችንም ወደዚህ ሀገር የመጣነው በፖለቲካ/በጸጥታ ምክንያት ጥገኝነት/Refugee ለመጠየቅ እንጂ የስራ ቪዛ ኖሮን አይደለም።

"በሀገሬ ባለው ችግር ምክንያት ተሰደጄ በጥገኝነት/Refugee ላይ የምገኝ ስደተኛ ነኝ፥እዚህም የቀን እንጀራዬን ለማግኘት ትንሽ ተቀጥሬ እየሰራሁ ነው" በማለት ሕጋዊ ይዘት ያለውን ትክክለኛ ምላሽ መስጠት ይበጃል፣በምንም ተአምር ትንሽም ሆነ ትልቅ ንብረት የእኔ ነው አትበሉ።

3. መንጃ ፈቃድ እና ውድ መኪና ያላቸው ወገኖች
መንጃ ፈቃድ አውጥታችሁ ውድ መኪና ይዛችሁ የምትንቀሳቀሱ ወገኖች ራሳችሁን አታጉሉ፣ ትህትና እና ጥንቃቄ አድርጉ።
"ስደተኛ ሆነህ እንዴት መንጃ ፈቃድ አገኘህ? መኪናውስ ከየት መጣ?" የሚሉ ጥያቄዎች እና ክትትሎች እየበዙ በመሆኑ ራስን ከተንኮል መጠበቅ ያስፈልጋል።

4. ሰኔ 30/June 30 የሚባለው ወሬ እና መፍትሔው
ሰኔ 30/June 30 ስለሚባለው ነገር በመንግሥት በኩል ምንም ዓይነት የሰልፍ ዕውቅና አልተሰጠም በመሆኑም አላስፈላጊ ስጋት ውስጥ ከመግባት፥አስቀድሞ ከቤት አከራዮች/House Owners ጋር በመነጋገርና በመስማማት፣በዕለቱ ከቤት ሳይወጡ ጊዜውን በሰላም ማሳለፍ ከሁሉ የተሻለ አማራጭ ነው።

ከጸጥታ አካላት ጋር በሚኖር ፍተሻ ወቅት በፍጹም አለመከራከር፥በሰላምና በትህትና መነጋገር ነገሮችን ያቃልላል።
በአካባቢያችሁ አዲስ የፍተሻ እንቅስቃሴ ሲኖር ለወዳጅ ዘመዶቻችሁ በአስቸኳይ መረጃ በመስጠት ተደጋገፉ።

#ጥንቃቄ ያሻል ህይወት አንደ ከአለፈች አለፈች ነው ስለዚህ በዚህ አለም ለይ አንድ ሰው አንድ ዕድል ነው የመኖር ዕድል ያለው።

@ጥንቃቄ ያስፈልጋል
pls

ደርባን ላይ 99.5 % ዛቻ እና ማስፈራራት እየደረሰበት ፓለው ስደተኛ ህጋዊ ነው ይህ ህጋዊ ስደተኛ ደግሞ እንደ ደቡብ አፍሪካዊያን የመስራት እና የመኖር መብት አለው
25/05/2026

ደርባን ላይ 99.5 % ዛቻ እና ማስፈራራት እየደረሰበት ፓለው ስደተኛ ህጋዊ ነው

ይህ ህጋዊ ስደተኛ ደግሞ እንደ ደቡብ አፍሪካዊያን የመስራት እና የመኖር መብት አለው

22/05/2026

ታላላቆቹ የደቡብ አፍሪካ ሰዎች
እውነቱን እያወጡ ነው ...ከፖን አፍሪካ እያስወጣችሁን ነው በሚል በንዴት ህዝባቸውን እየወቀሱ ነው

Thabo Mbeki በዛሬው ንግግሩ ውስጥ የደቡብ አፍሪካ ነጻነት ትግል የአፍሪካ አገራት የጋራ ትግል እንደነበር አስታውሰዋል።

እንደገለፁት፣ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ለANC ታጋዮች መጠለያ፣ ስልጠና እና የፖለቲካ ድጋፍ ሰጥተዋል፤ ስለዚህ ዛሬ በውጭ ዜጎች ላይ ጥላቻ መፍጠር ከአፍሪካ አንድነት መንፈስ ጋር አይጣጣምም ብለዋል።

በተጨማሪም፣ የኢሚግሬሽን ችግሮች በህጋዊ መንገድ እንጂ በጥላቻ ወይም በግፍ መፍታት እንደማይገባ አሳስበዋል።

ከምባታ: - ከተፈጥሮ ልግስናና ከሕዝብ የሥራ ወኔ የተሸመነ የጽናት ምድር!ከምባታ ሲባል ልብ ውስጥ የሚቀረጽ የልምላሜና የጽናት ምስል ነው። ይህች ምድር በካርታ ላይ የምትገኝ መልክዓ-ምድር ...
21/05/2026

ከምባታ: - ከተፈጥሮ ልግስናና ከሕዝብ የሥራ ወኔ የተሸመነ የጽናት ምድር!

ከምባታ ሲባል ልብ ውስጥ የሚቀረጽ የልምላሜና የጽናት ምስል ነው። ይህች ምድር በካርታ ላይ የምትገኝ መልክዓ-ምድር ብቻ ሳትሆን በተፈጥሮ ለጋስነትና በሰው ልጆች ታታሪነት የተገነባች የሕይወት ቅኔ ናት። ማለዳ ላይ በአረንጓዴው የእንሰት ማሳ ውስጥ የጠል ጠብታዎች በቅጠሎቹ ላይ በፀሐይ ሲያንጸባርቁ፤ ያ የከምባታ ህዝብ የዘመናት ትጋትና የላብ ክብር ውጤት ነው። በአየር ንብረቷ ውስጥ ሰርጎ የሚገባው የቅመም መዓዛና የገበሬው የሥራ ወኔ ተዋህዶ ምድሪቱ የኢትዮጵያ የስጦታ መድረክ መሆኗን በየደቂቃው ያረጋግጣል።

የዚህቺ ምድር ነፍስ የሚገኘው በሕዝቧ ልባዊ ደግነትና በመካከላቸው ባለው የማይናወጥ የአንድነት ቃል-ኪዳን ነው። በአደባባዮችዋ ላይ የሚታየው የሽምግልና ሥርዓት የሰው ልጅ ፈጣሪን በመፍራትና በሞራል ልዕልና እንዴት ሰላምን ማስፈን እንደሚችል የሚያስተምር ድንቅ የሕይወት ፍልስፍና ነው። በዚያ አደባባይ ክህደትና ውሸት ቦታ የላቸውም፤ ይልቁንም እውነትና ፍትሕ በሽማግሌዎች የዕድሜ ልክ ተሞክሮ ተቀርጸው እንደ ወርቅ ያበራሉ። አንዱ ሲቸገር ሌላው የሚቆምለት፣ እንግዳው እንደ ቤተሰብ የሚወደድበት ይህ ትውፊት ከምባታን ለማንኛውም የክፍፍል ውሽንፍር የማትበገር ጽኑ ግንብ ያደርጋታል።

ሲመሽ ደግሞ የከምባታ ውበት ሌላ መልክ ይላበሳል። በኮረብቶቹ ግርጌ የሚታዩት መብራቶች እንደ ከዋክብት ሲፈነጥቁ ከየቤቱ የሚወጣው የቡና ሽታ ከሰዎች ሳቅና ጨዋታ ጋር ይዋሃዳል። በሞቃት ማዕድ ዙሪያ የቆየው የጀግንነት ታሪክ ይነገራል፣ የነገው የብልጽግና ተስፋ ይለመለማል። ይህ የትውልድ ቅብብሎሽ የከምባታን ወጣቶች ንቁና የፈጠራ ተስፋ ያላቸው ያደርጋቸዋል። ይህ ሁሉ የባህልና የሥራ ስብጥር ከምባታን የሰላምና የብልጽግና ተምሳሌት አድርጓታል።

ዛዲግ አብርሃ
የአፍሌክስ ፕሬዝደንት

Address

Durame

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ROCK-Realities Of Community Kembata posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share