30/05/2026
#ደቡብአፍሪካ
የዜጎች ደህንነትን ለማስጠበቅ የተደረገው የዲፕሎማሲ ጥረት
በደቡብ አፍሪካ “መጤ ጠል” እንቅስቃሴን ተከትሎ በዜጎቻችን ላይ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ለመከላከል፣ የኢትዮጵያ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ልዑካን ቡድን ከደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በፕሪቶሪያ (ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ/ም) ውይይት አድርጎ የሚከተሉት ዋና ዋና መግባባቶች ላይ ደርሷል፡
👉ሕጋዊ ሰነድ ላላቸውም ለሌላቸውም ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የደህንነት ዋስትና የመስጠት ኃላፊነት በደቡብ አፍሪካ መንግሥት ላይ መሆኑ ተሰምሮበታል።
👉ማንኛውም ሕገ-ወጥነት በሕገ-ወጥ መንገድ ሊፈታ እንደማይገባና በሀገሪቱ ያሉ ዜጎች በደቡብ አፍሪካ ሕግና ዓለም አቀፍ ስምምነቶች መሠረት እንዲስተናገዱ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
👉ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ጨምሮ በወንጀል ሰንሰለቶች ላይ የተቀናጀና የማያዳግም እርምጃ ለመውሰድ ሁለቱ አገራት ተስማምተዋል።
የልዑካን ቡድኑ መልዕክት ለዜጎች፦
ዜጎች ራሳቸውን ከወንጀል ነክ ድርጊቶች እንዲያርቁ እና ችግሮችን ከመሸፋፈን እንዲቆጠቡ፤
ከተበታተነ አሠራር በመውጣት ሀብትን አስተባብሮ ወደ ኩባንያና ትላልቅ ኢንቨስትመንቶች በማደግ፣ በትውልድ ሀገርና በደቡብ አፍሪካ በመሥራት ውጥረቶችን መቀነስ እንደሚቻል ጥሪ ቀርቧል።
የኢትዮጵያ መንግሥት በኤምባሲውና በሌሎች ተቋማት በኩል አስፈላጊውን ትብብርና ቅንጅት ማድረጉን ይቀጥላል።
Ethiopian embassy SouthAfrica