26/09/2025
የመሳላ በዓልን አስመልክቶ የዳምቦያ ወረዳ ከተለያዩ ቀበሌያት ለተመለመሉ አቅመደካሞች ማዕድ ማጋራቱን ገለፀ።
ዳምቦያ፣ መስከረም 15/2018 ዓመተ ምህረት(የዳምቦያ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን) በከምባታ ዞን የዳምቦያ ወረዳ የከምባታ መሳላ በዓልን ምክንያት በማድረግ ከተለያዩ ቀበሌያት ለተመለመሉ ለ52 አቅመደካሞች ማዕድ ማጋራቱን የገለፁት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙንዳዬ ግርማሞ ናቸው።
ክቡር ዋና አስተዳዳሪው ጉዳዩን አስመልክተዉ ባስተላለፉት መልዕክት በዚህ መሳላ በዓል ያለዉ ከሌለዉ ጋር ተካፍሎ የሚበላበት፣ የተጣለ የሚታረቅበት፣ የተራራቀ የሚቀራረብበትና የሚተሳሰቡበት እንዲሁም ልጆች የአባቶችን ምርቃት የሚቀበሉበትና በቀጣይ ዓመት ዕቅድ ላይ የሚወያዩበት እንደሆነም አስረድተዋል።
ክቡር አቶ ሙንዳዬ አክለውም ከኢኮኖሚ ችግር አንፃር በዓሉን በባዶ ልያሳልፉ ያሉትን አቅመ ደካሞች በወረዳዉ አስተባባሪነት ከወረዳዉ አመራር፣ ከሀገር ውጭና ሀገር ውስጥ ካሉ በጎ አድራጊ ወገኖች ከተገኘ ሀብት ለ52 አቅመደካሞች የመሳላ በዓል ቅርጫ ስጋ፣ ዘይትና ትራንስፖርት ዛሬ ማከፋፈሉን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪዉ ይህን ደጋግና በጎ አድራጊ ወገኖች ከፍ ያለ ክብር አለን በማለት በዓሉ ለመላው ከሀገር ውጪና ከሀገር ዉስጥ የሚኖሩ የከምባታ እና የዳምቦያ ወረዳ ህዝቦች የሰላም እንዲሆንም ተመኝተዋል።
ከተረጂዎቹ መካከል አንዳንዶች በሰጡት አስተያየት ይህን ቅዱስ ሀሳብ ያመነጨዉን፣ ያስተባበረዉንና ሀብቱን የሰጡዉን አካል ፈጣሪ ከዘመን-ዘመን ያድርሰዉ ብለዋል።
በስብሰባው ላይ ዋና አስተደዳሪ ክቡር አቶ ሙንዳዬ ግርማሞ፣ የዳምቦያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ሽታዬ ገዕኖሮ፣ የዳምቦያ ወረዳ ዋና አፈጉባኤ አቶ ዳንኤል ማሞ፣ የዳምቦያ ወረዳ ሠራተኛና ማህበራዊ ግንኙነት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ተሾመ ዮሐንስና ሌሎችም የዳምቦያ ወረዳ አመራርና የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
በከምባታ ዞን የዳምቦያ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት