ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት, Media, Durame.

'በመትከል መንሰራራት' በሚል መሪ ቃል በከምባታ ዞን  በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች  የ2017 ዓ/ም  የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በነገው ዕለት ይካሄዳል፣...
09/07/2025

'በመትከል መንሰራራት' በሚል መሪ ቃል በከምባታ ዞን በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የ2017 ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በነገው ዕለት ይካሄዳል፣

የ2017 ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በነገው ዕለት ማለትም በ03/11/2017 ዓ/ም በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደር የዞኑ አሰተባበሪ አካለት በተገኙበት የሚካሄድ ስሆን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ያሉበትን ደረጃ በዞኑ አስተባባሪ አካላትና የዞን አመራሮች እንዲሁም የወረዳዎች አስተባባሪ አካላትና አመራሮች በተገኙበት የሀደሮ ጡንጦ ዙርያ ወረዳን ጨምሮ በሌሎችም ወረዳዎች የመስክ ምልካታ ተደርጓል፣

በዕለቱም በዞኑ ከ500,000 ባላይ ዘርፈ ብዙ ጠቃሜታ ያላቸው ችግኞች ህብረተቡን በማሰተፍ ለመትከል መታቀዱን ያገኘናቸው መረጃዎች አመላክተዋል።

የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የቡታጅራ ክላስተር ሴቶች ክንፍ ህብረት አስታወቀ፤ዱራሜ፦ ሐምሌ 02/2017 ዓ ምየቡታጅራ ክላስ...
09/07/2025

የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የቡታጅራ ክላስተር ሴቶች ክንፍ ህብረት አስታወቀ፤

ዱራሜ፦ ሐምሌ 02/2017 ዓ ም

የቡታጅራ ክላስተር ሴቶች ክንፍ አባላት የ2017 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የንቅናቄ መድረክ አካሄዱ።

በንቅናቄ መድረኩ የክንፉ አመረሮችና አባላት ተገኝተዋል።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቀመሪያ ረሻድ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል ።

የሴቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በፓርቲው በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ለውጦች እየታዩ መምጣታቸውን አብራርተዋል ።

የሴቶችን ውሳኔ ሰጪነትን ለማሳደግ በህብረቱ ጥሩ ጅምር ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም ሴቶች በራስ አቅም በመፍጠር ይበልጥ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚጠበቅ ወ/ሮ ቀመሪያ አስታውቀዋል ።

በ2017 በጀት ዓመት በህብረቱ የተገኙ ጠንካራ ጎኖችን ይበልጥ በማጎልበት በጉድለቶች ላይ ደግሞ የህብረቱ አባላትና አመራር አካላት በቀጣዩ በጀት ዓመት አሁን ካለው በተሻለ ለውጥ እንዲመጣ በጋራ መትጋት ይጠበቃል ሲሉም አሳስበዋል።

በኮንፈረንሱ በክብር እንግድነት የተገኙት የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ም/ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ማናዬ ዳንኤል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ብልጽግና ፓርቲ በሰፊው ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰዋል ።

በተለይም ሴቶችን በተለያዩ ዘርፎች ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ከንቅናቄ ጀምሮ የአሰራርና አደረጃጀቶች ላይ ሰፊ ሰራ ተሰርቷል ብለዋል ።

ሴቶች በሰላም ግንባታ ፣በበጎ ተግባራትና ሴት ተኮር በሆኑ ጉዳዮች ላይ የነቃ ተሳትፎን እያደረጉ መሆኑን ያብራሩት ወ/ሮ ማናዬ በዚህም በየደረጃው የህብረቱ አባላት መሳተፋቸውን አብራርተዋል ።

የህብረቱ አባላት በክልሉ በተለያዩ ጊዜያት የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋና ችግር ለተጋለጡ ወገኖች ከ2 ሚሊየን ብር በላይ የበጎ ተግባር ስራዎችን በማከናወን የወገን አለኝታነታቸውን በተግባር እየተወጡ ይገኛሉ፣ ይህንንም አጠናክሮ ለማስቀጠል በቀጣይ ራሳችንን አሸንፈን ብቁ ለመሆን ከአባላቱ ብዙ መስራት እንደሚጠበቅ አሳስበዋል ።

በኮንፈረንሱ የ2017 ዓ ም የተከናወኑ ተግባራትና በክላስተሩ የሴቶች ክንፍ የህብረቱ ሰብሳቢ በወ/ሮ እናትአለም ሀ/ማሪያም እንዲሁም የ2018 ዓ ም የክላስተሩ የሴቶች ክንፍ ህብርት ጠቋሚ ዕቅድ በሴቶች ክንፍ የህብረቱ ምክትል ሰብሳቢ በወ/ሮ መነን ወልዴ ቀርቦ በተሳታፊ አካላት ውይይት ተካሂዶበታል ።
የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ጅምር ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በአፅንኦት ተገልጿል ።

በሌላ በኩል በህብረቱ እየተከናወኑ ያሉ የበጎ ተግባር ስራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲያስችል ውይይት የተደረገ ሲሆን የደም ልገሳና በህብረቱ አባላት ለድጋፍ የሚውል አልባሳትን የማሰባሰብ ስራ እየተከነ ይገኛል ።

በመጨረሻም በማከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የቡታጅራ ክላስተር ሴቶች ክንፍ ህብረት ከኮንስትራክሽን ባለስልጣን ጋር በመተባበር ለክላስተሩ ሴት ሠራተኞች የሴቶችን አቅም በሊደርሺፕ ማብቃትና በማህበራዊ ሚዲያና የሚዲያ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እንደሚቀርብ ከወጣው መርሃ ግብር ለማወቅ ተችሏል ።
Central Ethiopia Region - Prosperity Party - ብልፅግና

09/07/2025
 አቶ እሸቱ ሉቃስ  ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 1,777 ብር አበርክተዋል። ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ...
09/07/2025



አቶ እሸቱ ሉቃስ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 1,777 ብር አበርክተዋል።

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

   ሜላት ከበደ ከስዊድን  ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 10,000 ብር አበርክተዋል። #እናመሰግናለን !የሀምበሪቾ 777 ደረጃዎች እና በተራራው ኢኮ ቱሪዝም ስፍራን ለማልማት ...
09/07/2025



ሜላት ከበደ ከስዊድን ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 10,000 ብር አበርክተዋል።

#እናመሰግናለን !

የሀምበሪቾ 777 ደረጃዎች እና በተራራው ኢኮ ቱሪዝም ስፍራን ለማልማት ገቢ ለማሰባሰብ የተከፈቱ የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች :

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
• ዳሽን ባንክ - 5351738171021

 የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር መንገዶች ባለስልጣን ዱራሜ ዲስትሪክት ኃላፊ  አቶ ሀይሌ አበራ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 3,777 ብር አበርክተዋል። ሁላችንም ከታች በተ...
09/07/2025



የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር መንገዶች ባለስልጣን ዱራሜ ዲስትሪክት ኃላፊ አቶ ሀይሌ አበራ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 3,777 ብር አበርክተዋል።

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋምና በምግብ እራስን ለመቻል የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፦ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር) ዱራሜ፣ ሐምሌ 1/2017 ዓ.ምበማዕከላዊ ኢትዮጵ...
08/07/2025

የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋምና በምግብ እራስን ለመቻል የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፦ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር)

ዱራሜ፣ ሐምሌ 1/2017 ዓ.ም

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2017 የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ እና የገጠር ኮሪደር የማስጀመር መርሐ ግብር ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር) እንደገለጹት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋምና በምግብ እራስን ለመቻል የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

በአለም አቀፍ ደረጃ እየተስተዋለ ያለው ኢተገማች የአየር ንብረት ለውጥ የደኖች መመናመን እና የዓፈር ለምነት መቀነስ፣ የተባይና የበሽታ ክስተት መስፋፋት እያስከተለ መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

የምርታማነት መቀነስ እና የድህነት መስፋፋት ፣የሙቀት መጨመር የበረሀነት መስፋፋት፣የምንጮች መድረቅ፣የግድቦች በደለል መሞላት፣የመሬት ናዳ መከሰት በተለያዩ ወቅቶች እየተከሰቱ ያሉ ችግሮች መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ከ2011ዓም ጀምሮ ላለፉት ተከታታይ ስድስት ዓመታት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ሲካሔድ መቆየቱን ርዕሰ መስተዳድሩ በንግግራቸው ጠቅሰዋል።

በሀገሪቱ የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ስራ ፈርጀ ብዙ ውጤት እያስመዘገበ ነው ሲሉም ጠቁመዋል።

በወጣቶች ስብዕና ግንባታ ለይ በትኩረት በመሰራት በርካታ በጎ ወጣቶችን ከመፍጠሩም ባሻገር በጎ ፈቃድ ስራዎች ባህል በማድረግ የህብረተሰብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢ...
08/07/2025

በወጣቶች ስብዕና ግንባታ ለይ በትኩረት በመሰራት በርካታ በጎ ወጣቶችን ከመፍጠሩም ባሻገር በጎ ፈቃድ ስራዎች ባህል በማድረግ የህብረተሰብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ገለፀ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የ2017 ዓ/ም ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2018 የዕቅድ ዝግጅት ግምገማ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዱራሜ ከተማ ተካሄዷል።

"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መርህ ቃል የ2017 ክልላዊ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትም በይፋ ተበስሯል።

መድረኩን የመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ግዛቸው ዋሌራ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም መስኮች በርካታ ውጤቶችን ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።

በ2017 በጅት አመት በክልሉ በወጣቶች ስብዕና ግንባታ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን መገምገም መቻሉን የገለፁት ክቡር አቶ ግዛቸው ዋሌራ በዚህ ረገድ በተሰሩ ስራዎች በአመለካከት የተሻሉ በተግባር የሚታዩና ተጨባጭ ውጤቶች እየመጡ መሆኑንም ተናግረዋል።

በስብዕና ግንባታ ላይ የተሰሩ ስራዎች በክልሉ ሰላምና ልማት መረጋገጥ ላይ ጉልህ አበርክቶ እንደሚኖራቸው የተናገሩት አቶ ግዛቸው፣ በባለፈው በጀት አመት በተካሄዱ የወጣቶች የውይይት መድረኮች ወጣቶች ለልማትና ለሰላም ያላቸውን ቁርጠኝነት መረዳት የተቻለበት መሆኑን ጠቁመዋል።

አቶ ግዛቸው አክለውም በክልሉ በገጠር የወጣቶች ማዘውተሪያ ስፍራ በዞን ከተሞች በእድሳት ለይ ያሉ ሁለገብ ስታዲየሞች ተጠናቀው አገልግሎት እንዲሰጡ የተጀመሩ ክትትሎችና ስራዎች በልዩ ትኩረት ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል።

የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሾ በዚሁ ወቅት እንደገለፁት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም መስኮች በርካታ ውጤቶችን በማስመዝገብ የክልሉን አብዛኛውን የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ተችሏል።

የወጣቶችን አደረጃጀት የማጠናከር ሥራ፣ በክረምትና በበጋ የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ4 ሚሊየን በላይ የህበረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ ስለመቻሉ የጠቆሙት የቢሮ ኃላፊው የወጣቶች የስብዕና ማዕከላትን በማጠናከር ወጣቶች በሰላም እሴት ግንባታ ላይ ከፍተኛ ሚናቸውን መወጣት የጀመሩበት ስለመሆኑም በአብነት አንስተዋል።

ባለፈው በጀት አመት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በሁሉም አከባቢዎች በስፋት የተጀመረበትና በስፖርት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት የተጠናከረበት፣ በርካታ ክልላዊና ሀገራዊ ስፖርታዊ ወድድሮች ላይ በመሳተፍ ለክልሉ የወርቅ፣ ብርና ነሐስ ሜዳልያዎችን ማምጣት የተቻለበት መሆኑን ያነሱት አቶ ጌታቸው፣ በሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ መድረኮች ክልሉን የሚወክሉ ስፖርተኞች የተመለመሉበት ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

በባለፈው በጀት አመት አፈጻጸም በጉድለት የተለዩትን በቀጣይ በማረም በ2018 በጀት አመት ዕቅድ ጥንካሬዎችንና ጉድለቶችን ለይቶ በማቀድ የህብረተሰብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርብርብ የሚሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የ2018 በጀት አመት ዕቅድ ላይ ከታችኛው መዋቅር ጋር የግብ ስምምነት ተፈራርሟል።

 👏አቶ መሐሩ አናዬ ከአሜሪካ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 40,000 ብር  አበርክተዋል።  #እናመሰግናለን!ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረ...
08/07/2025

👏

አቶ መሐሩ አናዬ ከአሜሪካ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 40,000 ብር አበርክተዋል።

#እናመሰግናለን!

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራና የገጠር ኮሪደር ልማት  ፕሮግራም በይፋ አስጀመሩዱራሜ፦ሀምሌ 1/2017የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የ2017 ዓመ...
08/07/2025

ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራና የገጠር ኮሪደር ልማት ፕሮግራም በይፋ አስጀመሩ

ዱራሜ፦ሀምሌ 1/2017

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የ2017 ዓመተ ምህረት የአረንጓዴ አሻራና ክልላዊ የገጠር ኮሪደር ማብሰሪያ ፕሮግራም በጉራጌ ዞን ጉመር ወረዳ እየተካሄደ ነው።

በማብሰሪያ ፕሮግራሙ ርዕሰ መስተዳደሩና ሌሎች የፌዴራልና የክልል አመራሮች እንዲሁም የወረዳውና የአካባቢው ህዝብ በጉራጌ ዞን ጉመር ወረዳ አበኬ ቀበሌ የተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞች ተክለዋል።

ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው የ2017 የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላን በይፋ ካስጀመሩ በኋላ ክልላዊ የገጠር ኮሪደር ልማትን በይፋ ያስጀምራሉ።

በክልሉ በተያዘው ዓመት በአረንጓዴ አሻራ ልማት ከ500 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በህብረተሰብ ተሳትፎ እንደሚተከሉ ታውቋል።

በአጠቃላይ ክልሉ የያዘውን የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ፕሮግራም ለማሳካት ከአንድ ሚሊዮን በላይ የክልሉ ነዋሪዎች እንደሚሳተፉም ለማወቅ ተችሏል።

 የከምባታ ዞን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢኮኖሚ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ተስፋነሽ ኤልያስ ለሀምበርቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 5,000 ብር  አበርክተዋል።  #እናመሰግና...
08/07/2025



የከምባታ ዞን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢኮኖሚ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ተስፋነሽ ኤልያስ ለሀምበርቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 5,000 ብር አበርክተዋል።

#እናመሰግናለን🙏
!

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351738171021
SWIFT code: DASHETAA

በከምባታ ዞን በተለያዩ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች  የ2018 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር  አካሂደዋል። ግብርን በወቅቱ በታማኝነት መክ...
08/07/2025

በከምባታ ዞን በተለያዩ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች የ2018 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂደዋል።

ግብርን በወቅቱ በታማኝነት መክፈል የሀገር ፍቅር የዜግነት ግዴታ በመሆኑ ሁሉም ግብር ከፋዮች ግዴታቸውን በታማኝነት በመወጣት የህዝብን የመልማት ፍላጎት ለማሟላት ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸውም ተገልጿል።

በመርሃግብሩም በታማኝነትና በወቅቱ ግብራቸውን ለከፈሉ ደረጀ 'ሐ' ግብር ከፋዮች የዕውቅና ስነ-ስርዓትም እየተደረገ መሆኑን ያገኘናቸው መረጃዎች ያመላክታሉ።

Address

Durame

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category