ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት, Media, Durame.

የመሳላ በዓልን አስመልክቶ የዳምቦያ ወረዳ ከተለያዩ ቀበሌያት ለተመለመሉ አቅመደካሞች  ማዕድ ማጋራቱን ገለፀ።ዳምቦያ፣ መስከረም 15/2018 ዓመተ ምህረት(የዳምቦያ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን...
26/09/2025

የመሳላ በዓልን አስመልክቶ የዳምቦያ ወረዳ ከተለያዩ ቀበሌያት ለተመለመሉ አቅመደካሞች ማዕድ ማጋራቱን ገለፀ።

ዳምቦያ፣ መስከረም 15/2018 ዓመተ ምህረት(የዳምቦያ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን) በከምባታ ዞን የዳምቦያ ወረዳ የከምባታ መሳላ በዓልን ምክንያት በማድረግ ከተለያዩ ቀበሌያት ለተመለመሉ ለ52 አቅመደካሞች ማዕድ ማጋራቱን የገለፁት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙንዳዬ ግርማሞ ናቸው።

ክቡር ዋና አስተዳዳሪው ጉዳዩን አስመልክተዉ ባስተላለፉት መልዕክት በዚህ መሳላ በዓል ያለዉ ከሌለዉ ጋር ተካፍሎ የሚበላበት፣ የተጣለ የሚታረቅበት፣ የተራራቀ የሚቀራረብበትና የሚተሳሰቡበት እንዲሁም ልጆች የአባቶችን ምርቃት የሚቀበሉበትና በቀጣይ ዓመት ዕቅድ ላይ የሚወያዩበት እንደሆነም አስረድተዋል።

ክቡር አቶ ሙንዳዬ አክለውም ከኢኮኖሚ ችግር አንፃር በዓሉን በባዶ ልያሳልፉ ያሉትን አቅመ ደካሞች በወረዳዉ አስተባባሪነት ከወረዳዉ አመራር፣ ከሀገር ውጭና ሀገር ውስጥ ካሉ በጎ አድራጊ ወገኖች ከተገኘ ሀብት ለ52 አቅመደካሞች የመሳላ በዓል ቅርጫ ስጋ፣ ዘይትና ትራንስፖርት ዛሬ ማከፋፈሉን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪዉ ይህን ደጋግና በጎ አድራጊ ወገኖች ከፍ ያለ ክብር አለን በማለት በዓሉ ለመላው ከሀገር ውጪና ከሀገር ዉስጥ የሚኖሩ የከምባታ እና የዳምቦያ ወረዳ ህዝቦች የሰላም እንዲሆንም ተመኝተዋል።

ከተረጂዎቹ መካከል አንዳንዶች በሰጡት አስተያየት ይህን ቅዱስ ሀሳብ ያመነጨዉን፣ ያስተባበረዉንና ሀብቱን የሰጡዉን አካል ፈጣሪ ከዘመን-ዘመን ያድርሰዉ ብለዋል።

በስብሰባው ላይ ዋና አስተደዳሪ ክቡር አቶ ሙንዳዬ ግርማሞ፣ የዳምቦያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ሽታዬ ገዕኖሮ፣ የዳምቦያ ወረዳ ዋና አፈጉባኤ አቶ ዳንኤል ማሞ፣ የዳምቦያ ወረዳ ሠራተኛና ማህበራዊ ግንኙነት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ተሾመ ዮሐንስና ሌሎችም የዳምቦያ ወረዳ አመራርና የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
በከምባታ ዞን የዳምቦያ ወረዳ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ በተገኙበት የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር ሥነ ሥርዓት በሺንሽቾ  እየተካሄደ ይገኛል።ዱራሜ፣ መስከረም 16/2018 ዓ/ምበመርሃ ግብሩ...
26/09/2025

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ በተገኙበት የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር ሥነ ሥርዓት በሺንሽቾ እየተካሄደ ይገኛል።

ዱራሜ፣ መስከረም 16/2018 ዓ/ም

በመርሃ ግብሩም የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ፣ የከምባታ፣ ሀላባ፣ ጠምባሮ፣ የዳውሮና ኮንታ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታሪኩ ተስፋዬና የከተማ አመራሮችና የሺንሽቾ ቅዲስት ሲላሴ ቤተክርሲቲያን ምዕመናን በተገኙበት መርሐ ግብሩ እየተካሄደ ይገኛል።

እርስ በእርስ የመረዳዳት ባህልን በማጎልበት ለችግር ተጋላጭ የሆኑ ማህበረሰብ አካላትን መርዳት ከሰው ተኮር ተግባራት አንዱ መሆኑ ተገለጸ፣ ዱራሜ፣ መስከረም 16/2018 ዓ/ምየመስቀል በዓልን...
26/09/2025

እርስ በእርስ የመረዳዳት ባህልን በማጎልበት ለችግር ተጋላጭ የሆኑ ማህበረሰብ አካላትን መርዳት ከሰው ተኮር ተግባራት አንዱ መሆኑ ተገለጸ፣

ዱራሜ፣ መስከረም 16/2018 ዓ/ም

የመስቀል በዓልን ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ለ42 አካላት የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ድጋፍ አደርጓል፣

በመርሀግብሩ ላይ የተገኙት የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተክሌ ስዩም እንደገለጹት ካለን አካፍለን/ቀንሰን በኑሮ ችግር ውስጥ ያሉ የህብረተሰብ አካላትን መርዳት ባህል ሆኖ ተጠናክር መቀጠል ያለበት መሆኑን አሳስበዋል።

አቶ ተክሌ ስዩም አክለውም የ2018 የመስቀል በዓልን ስናከብር የፓርቲው እሳቤ የሆነውን ሰው ተኮር ተግባርን በመፈጸም ማዕድ በማጋራትና አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ ተገቢነት እንዳለው ገልጸው የ2018 የመስቀል በዓል የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅርና የስኬት እንዲሆን ተመኝተዋል።

በመርሃግብሩ ላይ የተገኙት የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ብዙነሽ ታዴዎስ በበኩላቸው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች የእርስ በእርስ የመደጋገፍ ስርዓትን እያጎለበቱ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ የድጋፍ መርሃግብር የተሳተፉ ተቋማትና አካላትን ያመሰገኑ ስሆን የ2018 የመስቀል በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ42 ሴቶች የጤፍና የቦቆሎ ዱቄት እና የምግብ ዘይት ድጋፍ መደረጉንም ጭምር ገልጸዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) የመስቀልን በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧልእንኳን...
26/09/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) የመስቀልን በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል

እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ!

እንኳን ለብረሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ! ፤ አደረሰን! እያልኩ ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ ፣

ባለብዙ ቀለም ፣ መስኩ ለምለም፣ ዜጎች ለአዳዲስ ሰኬቶች የሚነሳሱበት የተስፋና የብርሃን ወቅት በሆነዉ ወረሃ መስከረም የሚከበረው የመስቀል በዓል ልዩ ድምቀት ያለዉና በሃይማኖታዊና ማህራዊ እሴቶችና ትሩፋቶች የታጀበ ነዉ።

ተፈጥሮ ምድርን ደማቅና ዉብ አድርጎ በሚያሸበርቅበት፣ የአዲስ ዓመት ማግስት የሚከበረዉ የመስቀል በዓል ሃይማኖታዊ አስተምህሮዉና ማህበራዊ ትዉፊቶቹ ለአዳዲስ ሰኬቶች የሚያነሳሱ ናቸዉ።

በዓሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልም ከሃይማኖታዊ እሴቶቹ ባሻገር ማህበራዊ ትሩፋቶቹ በርካታ ናቸዉ።
ተራርቀዉ የሠነበቱ ቤተሰቦች ፣ ተገናኝተዉ ቤተሰባዊ ፍቅራቸዉን የሚወጡበት፣ሐሴታቸዉን የሚገልፁበት ነዉ።

የተስፋ ብርሃን፣የፅናት፣ የአሸናፊነትና የመስዋዕትነት ምልክት የሆነዉ የመስቀል በዓል የአብሮነት፣ የተስፋና የትጋት እሴቶችን እንድናጠናክር የሚያግዝ ነዉ።

በዓሉ የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበት፣ ለሠላምና ለልማት ግንባታ በአጠቃላይ ለሁለንተናዊ ብልጽግና በጋራ ለመትጋት የምንነሳሰበት እንዲሆን እመኛለሁ ።

መልካም የመስቀል በዓል!

አመሠግናለሁ !

በሁሉም ዘርፍ የሚሰጠውን አገልግሎት በማዘመን ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ከብልሹ አሰራር የጸዳ እና  በእርካታ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን መስራት ይገባል :-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ...
25/09/2025

በሁሉም ዘርፍ የሚሰጠውን አገልግሎት በማዘመን ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ከብልሹ አሰራር የጸዳ እና በእርካታ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን መስራት ይገባል :-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )

ዱራሜ ፣መስከረም 15/2018 ዓ/ም

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ስራ ጀመረ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) እንደገለጹት በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋ፣ከብልሹ አሰራር የጸዳ፣የህብረተሰቡን እርካታ ያረጋገጠ እንዲሁም የአገልጋይነት መንፈስ የተላበሰ እንዲሆን ያስችላል ብለዋል።

በክልሉ ለመጀመሪያ ጊዜ ተገንብቶ ስራ የጀመረው የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአጭር ጊዜ አገልግሎት መለየት፣ ማኑዋል ማዘጋጀት፣ቢሮን መገንባትና ማደስ፣ሰራተኛ መረጣ እና የቴክኖሎጂ አቅርቦት ስራ ማከናወን መቻሉን አብራርተዋል።

በክልሉ በዛሬው እለት ከተመረቀው ፕሮጀክት ልምድ በመውሰድ በወራቤ፣በቡታጅራ፣በወልቂጤ፣በሳጃ፣በዱራሜ፣በቁሊቶ ከተሞች በ2018 ማጠቃለያ ላይ ሰባት መሶብ የአንድ ማዕከላት እንደሚኖሩ ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በ2018 በጀት አመት በሀገሪቱ እና በክልሉ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

ማዕከሉ ተገንብቶ ወደ ተግባር እንዲገባ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አመራሮች ለፌደራል እና ለክልል ተቋማት ርዕሰ መስተዳድሩ ምስጋና አቅርበዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በበኩላቸው የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ የተንዛዛ፣ የግልጸኝነት ጉድለት ያለው ለብልሹ አሰራር የተጋለጠ እንግልት የበዛበት እና ተገልጋይ ተኮር ያለመሆኑ በመንግስት እና በፓርቲ ከግንዛቤ ውስጥ ገብቷል ብለዋል።

በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታየው ክፍተት በህዝብ ዘንድ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ ስለመስተዋሉም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

በሁሉም ዘርፍ የሚስተዋለውን የአገልግሎት አሰጣጥ እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ (ዶ/ር ) አቅጣጫ ማስቀመጣቸውን ተከትሎ በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እውን ማድረግ መቻሉን አቶ አንተነህ ጠቁመዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለዜጎች የተደራጀ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

በክልሉ በዛሬው እለት ተመርቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ክቡር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) ኮሚቴ በማቋቋም ለስራው ልዩ ትኩረት በመስጠታቸው ፕሮጀክቱ ስኬታማ እንዲሆን አስችሎታል ሲሉም አቶ አንተነህ ጠቁመዋል።

ማዕከሉ ዜጎች የተሟላ የዲጂታል አማራጮችን በመጠቀም የፌደራል እና የክልል ተቋማትን አገልግሎት ማግኘት እንደሚያስችላቸው የተናገሩት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ የተገልጋዮችን እንግልት እና ከወረቀት ጋር ተዛማጅ የሆኑ አሰራሮችን የሚያስቀር ነው ብለዋል።

ማዕከሉ በሰባት የፌደራል እና የክልል ተቋማት 20 አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረግ የሚያስችል ስለመሆኑም አቶ አንተነህ በንግግራቸው አመላክተዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የፕሮጀክቶች አስተባባሪ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ብርሀኑ ተስፋዬ እንደገለጹት የክልሉ መንግስት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተገንብቶ ለውጤት እንዲበቃ በማድረጉ ምስጋና አቅርበዋል።

የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩን ተልዕኮ ከማሳካት አንጻር በሀገሪቱ ሰባት ማዕከላት ለምረቃ መብቃታቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን ጨምሮ ስድስት ማዕከላት እየተመረቁ ነው ብለዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሀገሪቱ የአገልግሎት አሰጣጡን ተደራሽነትና ግልጸኝነትን ከማሳደግ አንጻር ወደ አንድ ደረጃ እንደሚያሳድገውም አብራርተዋል።
በህዳሴ ግድብ ግንባታ፣በቱሪዝም መዳረሻ ልማት፣በከተማ እና በገጠር ኮሪደር፣በአረንጓዴ አሻራ፣በሌማት ትሩፋት፣በስንዴ ልማት እንዲሁም የማዕድን ልማት የኢትዮጵያ ማንሰራራት መገለጫዎች ናቸው ሲሉም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል።

በመርሐ ግብሩ ለፕሮጀክቱ ስኬታማነት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
Central Ethiopia Region - Prosperity Party - ብልፅግና

የዱራሜ ከተማ  የመሳላ ገበያ(ቦቦዳ) የቀንድ ከብት ግብይት በምስል፦
25/09/2025

የዱራሜ ከተማ የመሳላ ገበያ(ቦቦዳ) የቀንድ ከብት ግብይት በምስል፦

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ ዱራሜ፣ጨመስከረም 15/2018 ዓ/ምየማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕ...
25/09/2025

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ

ዱራሜ፣ጨመስከረም 15/2018 ዓ/ም

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ

በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ ዲላሞ ኦቶሬ ( ዶ/ር) ፣የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የፕሮጀክቶች አስተባባሪ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ብርሀኑ ተስፋዬ ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በዛሬው እለት ተመርቆ ስራ የጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት 5 የፌደራል እና 2 የክልል ተቋማት 20 አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸውን ስራ ጀምረዋል።

በማዕከሉ ንግድና ገበያ ልማት፣ገቢዎች፣ኢሚግሬሽን፣ንግድ ባንክ፣ፖስታ አገልግሎት ፣ፋይዳ እና ኢትዮ ቴሌኮም በነዚህ ተቋማት 20 አገልግሎት መስጠት ያስችላል ተብሏል።

ተቋሙ ወደፊት ከ60 በላይ አገልግሎት ማስተናገድ የሚችል ስለመሆኑም ተመላክቷል።

በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነ ዲጂታላይዝድ ፣የተገልጋዩን ህብረተሰብ ጊዜ ወጪ ፣ሀብት እና እንግልት የሚቀንስ ሲሆን የአገልግሎት ጥራት የሚያሻሽል ስለመሆኑም ተመላክቷል።
Central Ethiopia Region - Prosperity Party - ብልፅግና

የመደመር መንግስት፡-• የልማት ጉዳይን ቀዳሚ አጀንዳ አድርጎ ይሠራል፤• በኢንተርፕረነርሺፕ ዕሳቤ የሚመራ የኢኮኖሚ ተዋናይ ዐቅም ለራሱ ይፈጥራል፤• የዳበረና በዉድድር የተመሠረተ የገበያ ኢኮ...
24/09/2025

የመደመር መንግስት፡-

• የልማት ጉዳይን ቀዳሚ አጀንዳ አድርጎ ይሠራል፤
• በኢንተርፕረነርሺፕ ዕሳቤ የሚመራ የኢኮኖሚ ተዋናይ ዐቅም ለራሱ ይፈጥራል፤
• የዳበረና በዉድድር የተመሠረተ የገበያ ኢኮኖሚ ሥርዓት ለመገንባት ይጥራል፤
• በሀገር ወዳድነት ስሜት ይሠራል፤
• ለገበያ ምቹ የሆኑ መደላድሎችን ያዘጋጃል፤
• የልማት ስራ የትዉልድ ቅብብሎሽ ሥራ ነው ብሎ በማመን፣ ወረት ለማስተረፍ ይሠራል፣
• የተረጋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ አስተዳደር ለማስፈን ይሠራል፣
• የሚፈጥረው የኢኮኖሚና የሲቪል ሰርቪስ ሥርዓት፣ ለአዳዲስ ሐሳቦች ለንግድ ሸቀጦች፣ ለአገልግሎት ንግድ፣ እንዲሁም ለካፒታል ዝውውር ክፍት ነው፡፡

የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከተረጅነት ወደ ምርታማነት እሳቤ የተዘራ የጤፍ ክላስተር ማሳ የመስክ ምልከታ በሆለገባ ቀበሌ አካሄደዋል፣
24/09/2025

የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከተረጅነት ወደ ምርታማነት እሳቤ የተዘራ የጤፍ ክላስተር ማሳ የመስክ ምልከታ በሆለገባ ቀበሌ አካሄደዋል፣

በከምባታ ዞን የአንጋጫ ኤግል ወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት ቡድን  ለሀምበርቾ ዳግም 777 ልማት ፕሮጀክት 10,777 ብር ድጋፍ አደረገ።ዱራሜ፣ መስከረም 14/2018 ዓ/ምስፖርት ቡድን የገንዘብ ...
24/09/2025

በከምባታ ዞን የአንጋጫ ኤግል ወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት ቡድን ለሀምበርቾ ዳግም 777 ልማት ፕሮጀክት 10,777 ብር ድጋፍ አደረገ።

ዱራሜ፣ መስከረም 14/2018 ዓ/ም

ስፖርት ቡድን የገንዘብ ድጋፍ ከማድረጉም በተጨማሪ በፕሮጀክቱ ስፍራ በመገኘት እየተሠራ ያለውን ሥራ ጎብኝተዋል።

ድጋፉን የተረከቡት የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ ደነቀ ደልከሶ በዞኑ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸውን ጠቅሰው ከዚህም የዞኑ ህዝብ የጥበብ አሻራ ያረፈበት ውብ የተፈጥሮ ስፍራ የሆነው ሀምበርቾ 777 የልማት ፕሮጀክት አንዱ ነው ብለዋል።

ሀምበርቾን ጨምሮ በዞኑ ውስጥ በሁሉም አካባቢ ያሉ የቱሪስት መዳረሻዎችን እሴት ጨምሮ በማልማት ዞኑን ተመራጭ የቱሪስት መዳራሻ ለማድረግ እየተደረገ ባለው ርብርብ የሁሉም ህብረተሰብ ክፍል የነቃ ተሳትፎ እያደረገ እንደሚገኝ ገልፀው በዚህ ድንቅ ፕሮጀክት አሻራቸውን ላስቀመጡ ለአንጋጫ ኤግል ወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት ቡድን ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የከምባታ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ እንግዳ ተሰማ በድጋፉ ርክብክብ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ስፖርት በባህርዩ ዘርፈ ብዙ ጠቃሜታ አለው አንዱና ዋናው ሰዎችን በአንድ መዕቀፍ ይሰበስባል ከስፖርታዊ ተግባራት በሻገር በአገራዊም ሆነ በአከባቢያዊ የልማት ጉዳይ ላይ የጋራ አቋም መያዝ የሚያስችል "Mentality" መገንባት የሚያስችል መደላድል ይፈጥራል ለዚሁ የአንጋጫው ኤግል ወርልድ ትኳንዶ ስፖርት ቡድን በቂ ማሳያ ነው ብለዋል።

ኤግል ወርልደ ትኳንዶ መሠልጠኛ በስፖርታዊ ጨዋነት የተመሰከረለት በአካል የዳበረ በአእምሮ የበለፀገ ዜጋን በማፍራት ሂዳትም የሚጠበቅበትን የትውልድ ኃላፊነት እየተወጣ ያለው ምርጥ የስፖርት ተቋም መሆኑንም አቶ እንግዳ ተሰማ አብራርተዋል።

የመምሪያው ኃላፊ አክለውም ኤግል ወርልድ ቴኳንዶ ይህ ብቻ ሳይሆን በአንጋጫ ከተማ ከወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት ከስፖርታዊ ተግበራት በሸገር በበርከታ የበጎ ፈቃድ አገለግሎት ሥራዎች እና እንዲሁም በተለያዩ ማህበራዊና ልማታዊ ጉዳዮች ላይ በመሳተፍ የዜግነት ሃላፍነት እየተወጣ ያለ የስፖርት ቡድን መሆኑን ገልፀዋል።

በዛሬው ዕለት ደግሞ የዞኑ መንግስት ለዞኑ ህዝብ ዘላቂ ተጠቃሚነትና ለትውልድ አቅዶ ከሚሰራቸው ሥራዎች አንዱ በሆነው ሀምባሪቾ ተራራ ላይ በሚሠራው ደግም 777 የልማት ሥራ ላይ እንደ ዜጋም እንደ አካባቢ ተወላጅም በዚሁ በጎ ተግባር ላይ አሻራ ለማሳረፍ በገንዘብና በሀሳብ ለደረገው ተሳትፎ ምስገናና ዕውቅና ይገባቸዋልም ብለዋል።

ወጣቶች በየአካባቢያችን በከተማና በገጠር በሚደረጉ የልማት፥የሰላም ግንባታ፥የዴሞክራስና ወዘተ ጉዳዮች መሳተፍ እንደተጠበቀ ሆኖ ሌሎችን በዚሁ ልክ እንዲሳተፉ መነሳሳትና መስተባበር ያስፈልጋል ስሉም አቶ እንግዳ ተሰማ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

ድጋፉን ያበረከቱት የአንጋጫ ኤግል ወርልድ ቴኳንዶ ስፖርት ቡድን አባላት በበኩላቸው ሀምበርቾ ልማት ዞናዊ አንድነት የፈጠረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ አሻራቸውን በማስቀመጣቸው ደስተኞች መሆናቸውን ተናግረዋል።

የተግባር አፈጻጸም ውጤታማ እንዲሆን የአመራሩ ቁርጠኝነትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት መስራት ህብረተሰቡን በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚ እንደሚያደርገው ተገለጸ፣ዱራሜ፣ 14/2018 ዓ/ምየከ...
24/09/2025

የተግባር አፈጻጸም ውጤታማ እንዲሆን የአመራሩ ቁርጠኝነትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት መስራት ህብረተሰቡን በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚ እንደሚያደርገው ተገለጸ፣

ዱራሜ፣ 14/2018 ዓ/ም

የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የመንግስትና የፓርቲ የ90 ቀናት መደበኛና የንቅናቄ ተግባራት አፈጻጸም ግምገማ በዱራሜ ከተማ አካሂዷል፣

በመድረኩ ላይ የተገኙት የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተክሌ ስዩም እንደገለጹት የታቀዱ ዕቅዶችን በአመራር ቁርጠኝነት በተቀናጀ መልኩ በመፈጸም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች በተሻለ መልኩ ተጠናክረው መቀጠል ያለባቸው መሆኑን አሳስበዋል።

አቶ ተክሌ ስዩም አክለውም የአመራሩ ስርዓት ውጤታማና በፓርቲው ድስፕሊን የሚመራበትን አሠራር በመዘርጋት የታቀዱ ዕቅዶችን ለመፈጸም በቅንጅት መስራትና ትጋትን በመጨመር የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል።

የውስጠ ፓርቲን ትግል በማጠናከር ጤናማ የስራ አካባቢን በመፍጠር፣ የንቅናቄ ተግባራትን በአደረጃጀት መፈጸም፣ የአፈጻጸም ግምገማን ወቅቱን ጠብቆ ማካሄድ ፣ ለስራ አጥ የስራ ዕድል ለመፍጠር በትኩረት መስራት፣ የትምህርት መማር ማስተማር ስራን አጠናክሮ መቀጠል፣ የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባን በትኩረት መስራት፣ በማህበራዊ ሚዲያ የወንድማማችነትን እሴት የጠበቀ አጠቃቀም ያለውን የሚዲያ ሠራዊት መገንባት ተገቢነት እንዳለው አቶ ተክሌ ስዩም አያይዘው ገልጸዋል።

አደረጃጀቶችን በማጠናከር በቤተሰብና በህብርት ደረጀ ተከታታይ ውይይቶችን ማድረግና ጥራት ያላቸውን መረጃዎችን ማደራጀት፣ የፓርቲ መዋጮን በአሠራሩ መሠረት ተግባራዊ በማድረግ የፓርቲውን የፋይናንስ አቅም ማጎልበት አስፈላጊ መሆኑንና ሌሎችንም ትኩረት መሰጣት ያለባቸውን ዝርዝር ጉዳዮችን አቶ ተክሌ ስዩም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ በፍቅር ታምራት የተግባር ውጤታማነትን ለማምጣት ወቅቱን የጠበቀ የፖለቲካ ሁኔታ እየተገመገመ መመራት እንዳለበት በመግለጽ በተላይም የአመራር ቅንጅት በአስተሳሰብና በተግባር መገለጽ እንዳለበት አሳስበዋል።

የወንድማማችነትን እሴት በማጎልበት ነጠላ ትርክትን ማክሰም ተገቢነት እንዳለው ያሳሰቡት አቶ በፍቅር ታምራት የፖለቲካ ጤንነት የሚጎዱ ነገሮችን ቶሎ በማረም በንቅናቄና በመደበኛ የፓርቲና የመንግስት ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት መሠራት እንዳለበት አሳስበዋል።

አቶ በፍቅር ታምራት አያይዘውም በ90 ቀናት ውስጥ የታቀዱ የገቢ አሰባሰብ፣ ለወጣቱ የስራ ዕድል ፈጠረ፣ የተማሪዎች ምዝገባ ስራዎችና ሌሎችንም የተቋማት ዕቅዶችን አመራሩ ቆጥሮ በትኩረት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።

በመድረኩም የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ደንታሞን ጨምሮ የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች እና የሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የከምባታ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ  ጉዳይ መምሪያ ድጋፍ ለሚሹ ለ90 ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።ዱራሜ፣ መስከረም 14/2018 ዓ/ምድጋፉን ለተማሪዎች ያስረከቡት የከምባታ ዞን ሠ...
24/09/2025

የከምባታ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ድጋፍ ለሚሹ ለ90 ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

ዱራሜ፣ መስከረም 14/2018 ዓ/ም

ድጋፉን ለተማሪዎች ያስረከቡት የከምባታ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ የተከበሩ አቶ አለሙ አሼቦ መምሪያው ከተለያዩ በጎ አድራጎት ድርጅቶች፣ ማህበራትና ግለሰቦች ጋር በመተባበር ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች የተለያዩ ድጋፎችን በማሰባሰብ እየደገፈ መቆየቱን ገልፀዋል።

አንድም ተማሪ ከትምህርት ገበታው መራቅ የለበትም በምል መሪ ሀሳብ ከመምሪያው ሠራተኞች በማሰባሰብ የትምህርት ቁሳቁስ ማሟላት ለማይችሉ ለ90 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉን የገለፁት የተከበሩ አቶ አለሙ አሼቦ ተማሪዎች የተደረገላቸውን ድጋፍ ለታለመለት ዓላማ ብቻ በመጠቀም በትምህርታቸው ጎብዘው ሰብዓዊነትን ተላብሰው እንዲያድጉም ጭምር መክረዋል።

የተከበሩ አቶ አለሙ አሼቦ አያይዛውም በመሳላ በዓል ወቅት የመረዳዳታችንና የመተጋገዝ ባህላችንን የበለጠ በማጠናከር በየአካባቢው ካሉ ድጋፍ የሚሹ ወገኖች ጋር ማዕድ መጋራት ይገባል ስሉም አሳስበዋል።
የከምባታ ዞን መንግስት ኮ/ጉ/መምሪያ

Address

Durame

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category