ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት, Media, Durame.

የነዳጅ ግብይት ከ50 በመቶ በታች በዲጂታል በፈፀሙ 20 ማደያዎች ላይ ክስ ተመሰረተ፤ዱራሜ፣ ሐምሌ/2017 ዓ.ምየማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠው...
02/08/2025

የነዳጅ ግብይት ከ50 በመቶ በታች በዲጂታል በፈፀሙ 20 ማደያዎች ላይ ክስ ተመሰረተ፤

ዱራሜ፣ ሐምሌ/2017 ዓ.ም

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠው በክልሉ የነዳጅ ግብይትን በህጋዊ መንገድ በማይፈፅሙ አካላት ላይ በሚወሰድ ህጋዊ እርምጃ ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ዳንኤል ዳምጠው እንደገለፁት፤ ተቋሙ የነዳጅ ግብይትን በህጋዊ መንገድ ብቻ እንዲከናወኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይቶች በማድረግ በህገ-ወጦች ላይም ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን አውስተዋል።

የፌዴራል ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በመጋቢት ወር ባደረገው ኢንስፔክሽን መሰረት 22 ባለማደያዎች ከ50 በመቶ በታች ግብይት በመፈፀማቸው ከስህተታቸው እንዲማሩ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን ኃላፊው ገልፀዋል።

ይሁን እንጂ ባለስልጣኑ በግንቦት ወር በድጋሚ ባደረገው ማጣራት 20 ማደያዎች ከ 50 በመቶ በታች የነዳጅ ግብይት በዲጂታል መፈፀማቸውን በመግለፅ በአዋጁ መሰረት ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ማሳሰቡን አቶ ዳንኤል ጠቁመዋል።

በመሆኑም በክልሉ የነዳጅ ግብይት ከ50 በመቶ በታች በዲጂታል ግብይት በፈፀሙ 20 ማደያዎች ላይ በፌደራል በወጣው አዋጅ ቁጥር 1363/2017 አንቀፅ 25 ንዑስ አንቀፅ 10 መሰረት ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ክስ መመስረቱን አብራርተዋል።

የነዳጅ ግብይት በዲጂታል ሽያጭ በማይፈፅሙ አካላት ላይ በአዋጁ መሰረት ከ2 ዓመት ያልበለጠ እስራትና የ300 ሺህ ብር ቅጣት እንደሚያስቀጣ ቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል።

አቶ ዳንኤል በህጋዊ መንገድ ግብይታቸውን የሚፈፅሙ አካላት እራሳቸውን ከህገ-ወጥ አሰራር በመጠበቅ ማህበረሰቡን እንዲያገለግሉ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን ክስ የተመሰረተባቸው ባለማደያዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።

የዳምቦያ ወረዳ አጠቃላይ አመራር አካላት የሐምበርች 777 ተጨማሪ ፕሮጄክት ስራዎችን አፈጻጸም ጉብኝት በማድረግ ብር 54,777 ድጋፍ ያደረጉ ስሆን በቦታው ተገኝተው ሠራተኞችን አሸሜ ብለዋል...
02/08/2025

የዳምቦያ ወረዳ አጠቃላይ አመራር አካላት የሐምበርች 777 ተጨማሪ ፕሮጄክት ስራዎችን አፈጻጸም ጉብኝት በማድረግ ብር 54,777 ድጋፍ ያደረጉ ስሆን በቦታው ተገኝተው ሠራተኞችን አሸሜ ብለዋል፣

ድጋፉን የተረከቡት የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተክሌ ስዩም እንደገለጹት የሐምበርች 777 ተጨማሪ ፕሮጄክት ስኬት የአመራር አንድነት ውጤት መሆኑን ገልጸው የአመራሩ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት መፈጠር በህዝባችን ውስጥ አንድነትና ተነሳሽነት በመፍጠሩ ፕሮጄክቱ እንዲሳካ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያሉ የዞኑ ተወላጆችና ልማቱን የሚደግፉ አካላት ድጋፋቸውን እያበረከቱ መሆኑን ገልጸው የዳምቦያ ወረዳ አጠቃላይ አመራር ላደረገው ድጋፍ ምስጋናየውን አቅርበው በሁሉም ተግባራችን ትብብርና አንድነታችን ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ስሉ አሳስበዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ በፍቅር ታምራት፣ የዳምቦያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙንዳዬ ግርማሞ፣ የዳምቦያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ምስጋና ደስታ እና የወረዳው አስተባባሪ አካላትን ጨምሮ የወረዳው ጠቅላላ አመራር ተገኝተዋል።

#እናመሰግናለን!!
!

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

የከምባታ ዞን ፍትህ መምሪያ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የፍትህ ጽ/ቤት መዋቅሮች ጋር በመሆን ለሐምበርቾ 777 ተጨማሪ ፕሮጄክት ብር 77,777 ድጋፍ በማድረግ እና የ2017 በጀት ዓመት የ...
02/08/2025

የከምባታ ዞን ፍትህ መምሪያ ከወረዳና ከከተማ አስተዳደር የፍትህ ጽ/ቤት መዋቅሮች ጋር በመሆን ለሐምበርቾ 777 ተጨማሪ ፕሮጄክት ብር 77,777 ድጋፍ በማድረግ እና የ2017 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ግምገማና የ2018 ዕቅድ ምክክር መድረክ በተራራው ላይ እያካሄደ ይገኛል፣

ድጋፉን የተረከቡት የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተክሌ ስዩም እንደገለጹት የፍትህ ተቋም ለዜጎች ፍትህን ለማረጋገጥ ከሚሰራው ስራ ጎን ለጎን ለሐምበርቾ 777 ተጨማሪ ፕሮጄክት ስራዎች ላደረጉት ድጋፊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

አቶ ተክሌ ስዩም አክለውም የሐምበርቾ 777 ተጨማሪ ፕሮጄክት በዞኑ ተወላጆችና በልማት ወዳድ በሆኑ አካላት ብርቱ አንድነትና ትብብር ለትውልድ የሚሸጋገር ፕሮጄክት እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ይህ የህዝባችን አንድነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል።

ድጋፉን ያስረከቡት የከምባታ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ አባይነህ ወርቁ በበኩላቸው የሐምበርቾ 777 ተጨማሪ ፕሮጄክት የከምባታ ህዝቦች መገለጫ በሆነው ታሪካዊ ተራራ ላይ እየተሰራ ያለ ፕሮጄክት ስሆን ለብዙዎች የስራ ዕድል የፈጠራ በቀጣይም የገቢ ምንጭ የመሆኑ ዕድል ሰፊ በመሆኑ በዞኑ ውስጥ ያሉ የፍትህ መምሪያና ጽ/ቤቶች በቦታው ተገኝተው አሸም ለማለት ድጋፋቸውን ማበርከታቸውን ገልጸዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ በፍቅር ታምራት፣ የከምባታ ህዝቦች ልማት ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ሎምቤቦና ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ዘውዱ አለሙ፣ የከምባታ ዞን መንገድና ትራንስፖርት መምሪያ ኃላፊና የተጨማሪ ፕሮጄክት አስተባባሪ አቶ ዳዊት አሹሮ፣ የዞን ፍትህ መምሪያ አቃቤያን፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊዎችና አቃቤ አካላት ተገኝተዋል።

 በ IN gender health ፕሮግራም የማዕከላዊ ኢትዮጽያ፣ የሲዳማ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ ኦርዶሎ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 10,777 ብር...
01/08/2025



በ IN gender health ፕሮግራም የማዕከላዊ ኢትዮጽያ፣ የሲዳማ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ ኦርዶሎ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 10,777 ብር አበርክተዋል።

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

#እናመሰግናለን!
!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

የ2017 የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ውጥናችን 100% በመሳካቱ እንኳን ደስ አላችሁ/ደስ አለን መልዕክት የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተ...
31/07/2025

የ2017 የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ውጥናችን 100% በመሳካቱ እንኳን ደስ አላችሁ/ደስ አለን መልዕክት የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተክሌ ስዩም አስተላልፈዋል፣

ችግኝ መትከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ጥቅም በመረዳት ህብረተሰባችን በአደረጃጀት በአንድነት በመውጣት በተዘጋጁ ማዕከላት በመገኘት መርሀ ግብሩ እንዲሳካ አስተዋጽኦ ላባረከቱ ለአመራር አካላት፣ ለባለሙያዎች፣ መንግስታዊ ለልሆኑ ድርጅቶችና ለአርሶ አደር አካላትና ለአጠቃላይ የህብረተሰብ ክፍሎች አቶ ተክሌ ስዩም ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርባዋል።

በዛሬው ዕለት ያካሄድነው የችግኝ ተካላ መርሀ ግብር ስኬት የሚያሳየው በአስተሳሰብና በተግባር አንድ በመሆንና በመተባበር ከሰራን በሁሉም ዘርፍ ያቀድናቸውን ዕቅዶች በቀላሉ በማሳካት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚንችል በመሆኑ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ሆኖ በሀገራዊና በዞናዊ ጉዳዮች አንድነቱን በዕውቀት፣ በብስለትና በጽናት በማረጋገጥ በትብብርና በቅንጅት መስራት ውጤታማ ያደርገናል ስሉ በመልዕክታቸው አክለው አሳስበዋል።

በዋቸሞ ዩንቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ በአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸውን አራት ሺ ችግኞች ተተክለዋል!24/11/2017 ዓ.ም."ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም....
31/07/2025

በዋቸሞ ዩንቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ በአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸውን አራት ሺ ችግኞች ተተክለዋል!

24/11/2017 ዓ.ም.

"ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም. "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል እንደ ሀገር የተያዘውን በአንድ ጀንበር 700 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል ዘመቻ እውን ለማድረግ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ ዛሬ ሐምሌ 24 ቀን 2017 ዓ.ም. ከጧቱ 3:00 ጀምሮ በግቢው ውስጥ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

የዛሬውን ጨምሮ በክረምቱ መርሃ ግብር በአጠቃላይ 1500 የአቦካዶ፣1000 የውበት እና 1500 የጥላ በድምሩ 4000(አራት ሺ) ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣በምክትል ፕሬዝደንት ማዕረግ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ ቺፍ ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ዘውዴ ክፍሌን ጨምሮ መምህራን፣ እንዲሁም የአስተዳደር ሠራተኞች ተገኝተው አሻራቸውን አሳርፈዋል።

#ዘገባው የዱራሜ ካምፓስ የህዝብ ግንኙነት እና ዓለም ዓቀፍ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ነው።

https://www.facebook.com/100064918110886/posts/1156878596486067/?app=fbl

 የዱራሜ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአስተዳደር ሠራተኞችና መምህራን ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 200,777 ብር አበርክተዋል። #እናመሰግናለን! !ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒ...
31/07/2025


የዱራሜ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአስተዳደር ሠራተኞችና መምህራን ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 200,777 ብር አበርክተዋል።

#እናመሰግናለን!
!

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀግብር በከምባታ ዞን ባሉ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች በተመረጡ ማዕከላት እየተካሄደ ነው!
31/07/2025

የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀግብር በከምባታ ዞን ባሉ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች በተመረጡ ማዕከላት እየተካሄደ ነው!

'በመትከል ማንሰራራት' በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ዞናዊ መርሀግብር በከምባታ ዞን በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ለንጉቴ ቀበሌ ዱዲዬ ተፋሰስ ማዕከል ተካሂዷል።ሐምሌ ...
31/07/2025

'በመትከል ማንሰራራት' በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ዞናዊ መርሀግብር በከምባታ ዞን በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ለንጉቴ ቀበሌ ዱዲዬ ተፋሰስ ማዕከል ተካሂዷል።

ሐምሌ 24/2017 ዓ/ም

በመርሀግብሩም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቴክኒኪና ሙያ ትምህርት ስልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰፈ ደቼና የክልል ግብርና ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎችቸ፣ የክልሉ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ አክመል አህመዲን የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሼቱ፣ የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተክሌ ስዩም፣ የከምባታ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተሾማ ሄራሞና የዞኑ አስተባባሪ አካላት፣ የዞኑ ግብርና መምሪያ አመራሮችና ባለሙያዎች፣ የከምባታ ዞን ደንና አካባቢ ጥበቃና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊና ባለሙያዎች፣ የዞኑ መምሪያዎችና ጽ/ቤቶች ኃላፊዎች እንዲሁም ባለሙያዎች፣ የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ አስተባባሪ አካላትና አመራሮች የአካባቢው ህብረተሰብ ተገኝተዋል።

በ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 80.3 በመቶ የሚሆኑት ወደ 7ኛ ክፍል ማሳለፍ መቻሉን የከምባታ ዞን ትምህርት መምሪያ ገለፀ።ውጤቱ እንደ ክልልም ተማሪዎችን በማሳለፍ ዞኑን ...
30/07/2025

በ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 80.3 በመቶ የሚሆኑት ወደ 7ኛ ክፍል ማሳለፍ መቻሉን የከምባታ ዞን ትምህርት መምሪያ ገለፀ።

ውጤቱ እንደ ክልልም ተማሪዎችን በማሳለፍ ዞኑን የመጀመሪያ እንዲሆን ያስቻለ መሆኑን የከምባታ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግርማ ጊቻሞ አብራርተዋል።

ይህ ውጤት እንዲመዘገብ የድርሻቸውን ለተወጡ አካላት ሁሉ በትምህርቱ ማህበረሰብ ስም ኃላፊው ምስጋና አቅርበዋል።

Address

Durame

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category