
09/07/2025
'በመትከል መንሰራራት' በሚል መሪ ቃል በከምባታ ዞን በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የ2017 ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በነገው ዕለት ይካሄዳል፣
የ2017 ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በነገው ዕለት ማለትም በ03/11/2017 ዓ/ም በሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደር የዞኑ አሰተባበሪ አካለት በተገኙበት የሚካሄድ ስሆን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ያሉበትን ደረጃ በዞኑ አስተባባሪ አካላትና የዞን አመራሮች እንዲሁም የወረዳዎች አስተባባሪ አካላትና አመራሮች በተገኙበት የሀደሮ ጡንጦ ዙርያ ወረዳን ጨምሮ በሌሎችም ወረዳዎች የመስክ ምልካታ ተደርጓል፣
በዕለቱም በዞኑ ከ500,000 ባላይ ዘርፈ ብዙ ጠቃሜታ ያላቸው ችግኞች ህብረተቡን በማሰተፍ ለመትከል መታቀዱን ያገኘናቸው መረጃዎች አመላክተዋል።