
21/07/2025
➾ ‹‹ቂርቆስ›› ማለት የስሙ ትርጓሜ ጣፋጭ ሽቶ፤ ጥዑም መአዛ፤ ያማረ ሽቶ ማለት ነው።😍
ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ አባቱ ቆዝሚስ ፣ እናቱ ኢየሉጣ ይባላሉ። ሀገራቸውም ሮም ነበር።
ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣ ለክርስቶስ ፍቅር ራሳቸው ያስገዙ እናትና ልጅ ክርስቲያኖች ነበሩ
የሦስት ዓመት እድሜ ያለው ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣ በጣኦት አምላኪዎች ተይዘው ተሰቃዩ
ለሃይማኖታቸው መጽናት እንዳለባቸው፣ ከአምላካቸው ውጪ ለጣኦት እንደማይሰግዱ አበርትተው ለሚያሰቃዩዋቸው ተናገሩ
በፈላ ውሃ ሊከቷቸው ሲሉ እናትየው ፈራች፤ በዚህን ጊዜ ቅዱስ ቂርቆስ አበረታት
"እናቴ ሆይ አትፍሪ አናንያ ዓዛርያና ሚሳኤልን ከእሳት ነበልባል ያዳናቸው እግዚአብሔር እኛንም ከዚህ የፈላ ውሃ ያድነናል" እያለ አጠነከራት
ያመኑትን የማይከዳው አምላካችን መልአኩን ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ አዳናቸው
ዛሬም እኛ በአምላካችን አምነን በክርስትናችን ፀንተን በእምነት ብንኖር እግዚአብሔር አይተወንም።
✞ የቅዱሳኑ በረከት ይደርብን።😍❤🙏