18/09/2025
#የኢትዮጵያን ታሪክ ብቻ ሳይሆን የአለምን ታሪክ በቅጡ ለመረዳትና ለማጥናት #ግዕዝን መማር የግድ ይላል።‼️
#ግዕዝን ማጥናት/መማር ለምን አስፈለገ⁉️
#ኢትዮጵያዊያን እንዲገቡ የማይፈቀደው ''The britsh libraray Ethiopic Geez book''‼️
#ሀገራችን የሰው ልጅ መገኛ ናት ካልን የፊደል፣ የአሀዝ፣ የስነጽሁፍ፣ የሰነጥበብ መገኛ ናት ለማለት ያሰደፈራል፡፡ አንዳንድ መዛግብት እንደሚያስረዱት የግእዝ መገኛ ከአዳም፣ ኖህ፣ ካም አንዲሁም ከሴም እንደሆነ እና አዳምም ኢትዮጵያዊ እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡ አዳም የተፈጠረዉ ማእከላዊ ምደር ላይ ነዉ ሰለዚህ ማእከላዊ ምድረ ወይንም የምድር ወገብ የሚያልፈው በኢትዮጵያ ነዉ ስለዚህ አዳም ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ የግእዝ ቋንቋ ከ700 አመተ አለም በፊት ለስነፅሁፍ ሙያ ውሏል፡፡ የሚገረመው ነገር ከአሜረካ ሀርቫረድ ዩኒቨርስቲ፣ ከጀረመን ሀምበረግ ከጣሊያን ካረሚና እና በእንግሊዝ፣ በጀረመን በዩኒቨርስቲዎች በስፍት ይሰጣል፡፡
ለምን የግእዝን ቋንቋ ለማወቅ ፈለጉ❓❗
ምን ይጠቅማቸዋል❓❗
#የተወሳሰበዉን የአለማት ምስጢር ለማወቅ የኢትዮጵያን የሆነዉን ሀብት መፀሀፍ ሄኖክን በአጭበርባሪዉ በጀምስ ብሩስ የተሰረቀውን በግእዝ የተፃፍዉን የዚህን መፀሀፍ ምስጢር ለመፍታት ከአለም የተወጣጡ የሀይማኖት መሪወች፣ ተመራማሪወች ከኢትዮጵያውያን አባቶች ዉጭ ሚስጥሩን ለመፍታት በአወሮፓ ሁሌም ጥናት እና ምርምረ ስብሰባ እንደሚያደርጉ ታዉቃላችሁ? ለምን? ብዙ መልሶች አሉት፡፡
#የኛ የኢትዮጵያን ንብረት የሆኑት ነገር ግን በተለያዩ አጋጣሚ ወደ ዉጭ ሀገረ ተሰርቀው የተወሰዱ መፃህፍት እንዳሉ ይታመናል ከእነዚህም የተወሰኑትን እንመልከት፡፡👇
1-እንግሊዝ...2804
2-ፈረንሳይ...854
3-ጀርመን ...511
4-እስራኤል...386
5-ቫቲካን...286
6-አሜሪካ ...401
7-ጣሊያን...108
8-ቤልጀም..71
9-ሲውዘረላንድ...38
10-ኦስትርያ..37
11-ሲዊዲን..12
12-ሆላንድ..4
13-ካናዳ....3
#በአጠቃላይ 5,515 መፃሂፈት በላይ ከብዙ የአለማት ሀገራት በብዛት መፃሂፍቶቻችን የተወሰዱት እንግሊዝ ሲሆን 2,804 የብራና መፃሂፍቶች ይገኛሉ፡፡ ከነዚህም መካከል የፍልስፍና፣ የዜማ፣ የቅዱሳን ህይወት፣ ህክምና፣ የጥበብ......የመሳስሉት ይገኛሉ፡፡ የሚገርመው ነገር ማንም ሀበሻ ወደ ''The britsh libraray Ethiopic Geez book'' ከዚህ ሙዚየም ገብተው መጎብኘት አይችልም፡፡ ይህ እንዴት የማል? ግን የኢትዮጵያውያን የከፈታ ዘመን ይመጣል በተስፋ እንጠብቃለን፡፡