Gashaw Getnet

Gashaw Getnet አንቺ የወላዲተ አምላክ የአሥራት አገር
ኢትዮጵያ ሆይ ተነሺ!!!

‎➾ ‹‹ቂርቆስ›› ማለት የስሙ ትርጓሜ ጣፋጭ ሽቶ፤ ጥዑም መአዛ፤ ያማረ ሽቶ ማለት ነው።😍‎‎ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ አባቱ ቆዝሚስ ፣ እናቱ ኢየሉጣ ይባላሉ። ሀገራቸውም ሮም ነበር። ‎‎ቅዱስ ቂ...
21/07/2025

‎➾ ‹‹ቂርቆስ›› ማለት የስሙ ትርጓሜ ጣፋጭ ሽቶ፤ ጥዑም መአዛ፤ ያማረ ሽቶ ማለት ነው።😍

‎ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ አባቱ ቆዝሚስ ፣ እናቱ ኢየሉጣ ይባላሉ። ሀገራቸውም ሮም ነበር።

‎ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣ ለክርስቶስ ፍቅር ራሳቸው ያስገዙ እናትና ልጅ ክርስቲያኖች ነበሩ

‎የሦስት ዓመት እድሜ ያለው ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣ በጣኦት አምላኪዎች ተይዘው ተሰቃዩ

‎ለሃይማኖታቸው መጽናት እንዳለባቸው፣ ከአምላካቸው ውጪ ለጣኦት እንደማይሰግዱ አበርትተው ለሚያሰቃዩዋቸው ተናገሩ

‎በፈላ ውሃ ሊከቷቸው ሲሉ እናትየው ፈራች፤ በዚህን ጊዜ ቅዱስ ቂርቆስ አበረታት
‎"እናቴ ሆይ አትፍሪ አናንያ ዓዛርያና ሚሳኤልን ከእሳት ነበልባል ያዳናቸው እግዚአብሔር እኛንም ከዚህ የፈላ ውሃ ያድነናል" እያለ አጠነከራት

‎ያመኑትን የማይከዳው አምላካችን መልአኩን ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ አዳናቸው

‎ዛሬም እኛ በአምላካችን አምነን በክርስትናችን ፀንተን በእምነት ብንኖር እግዚአብሔር አይተወንም።

‎✞ የቅዱሳኑ በረከት ይደርብን።😍❤🙏

"ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ"             መዝ. 44 (45)፥17እመቤቴ ማርያም ለሊቱን የያቆብ ለሊት አድርጊልን!
21/07/2025

"ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ"
መዝ. 44 (45)፥17

እመቤቴ ማርያም ለሊቱን የያቆብ ለሊት አድርጊልን!

19/07/2025

"በጨንቃችሁ ጊዜ ሁሉ ቅዱስ ሩፋኤል አባቴ አለው ይበላችሁ"።

🥰🙏🥰

18/07/2025

የሞትን ደብዳቤ ወደ ሕይወት የሚቀይረው መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል የእኛንም ሕይወት ይቀይርልን።🙏❤

ሚካኤል›› ማለት መኑ ከመ አምላክ (እግዚአብሔር)፤ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው ማለት ነው፡፡ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት ነው እንደ እግዚ...
18/07/2025

ሚካኤል›› ማለት መኑ ከመ አምላክ (እግዚአብሔር)፤ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው ማለት ነው፡፡

ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ የሚያመለክት ነው እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ ንጹሕ ርህሩህ ኃይል ረቂቅ ማነው መልሱ የለም ነው፡፡

ቅዱስ ሚካኤል የስሙ ዘርፍ ሆነው የሚጨመሩ መጠሪያዎች አሉት እነዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠውን የባለሟልነት ክብር የሚገልጹ ናቸው፡፡

ይኸውም መልአከ ኃይል፣ መጋቤ ብሉይ፣ መልአከ ምክሩ፣…ናቸው፡፡

መልአከ ኃይል የተባለው እግዚአብሔር በሱ አማካይነት ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራት ኃይሉን ስለገለጸ - ዲያብሎስን ከነሠራዊቱ ስላሸነፈ ነው፡፡

መጋቤ ብሉይ የተባለበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእግዚአብሔር እየተላከ ብዙ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራ በመሆኑ ነው፡፡

መልአከ ምክር ወይም የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ የተባለበት ምክንያት እግዚአብሔርን በምክሩ ይረዳዋል ለማለት ሳይሆን እግዚአብሔር የሚሠራውን ሥራ ለወዳጁ ለቅዱስ ሚካኤል ይገልጽለታል በሱም አማካኝነት ይሠራል ለማለት ነው፡፡

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በምልጃው ይጠብቀን🙏

ቅድስት ሆይ ለምኝልን ❤🥰
18/07/2025

ቅድስት ሆይ ለምኝልን ❤🥰

የእመቤቴ ምስጋናዋ እንደ ሰማይ ኮከብ እንደ ባሕር አሸዋ በዝቶልኝ እንደ ልብስ ለብሼው እንደ ምግብ ተመግቤው ጠግቤው›› እያለ  ሲመኝ ይኖር ስለነበር የተመኙትን መስጠት ልማዱ ነውና እግዚአብ...
17/07/2025

የእመቤቴ ምስጋናዋ እንደ ሰማይ ኮከብ እንደ ባሕር አሸዋ በዝቶልኝ እንደ ልብስ ለብሼው እንደ ምግብ ተመግቤው ጠግቤው›› እያለ ሲመኝ ይኖር ስለነበር የተመኙትን መስጠት ልማዱ ነውና እግዚአብሔር የልቡን መሻት ፈጸመለት፡፡ እመቤታችንም ተለገልጻለት እርሷን ለማወደስ በቅቷል፡፡

✍️ከዕለታት በአንዱ ቀን ሰኞ ነግህ በሆነ ጊዜ ተግባሩን አድርሶ ከመካነ ግብሩ ተቀምጦ ሳለ እመቤታችን መጣች፤ የብርሃን ምንጣፍ ተነጠፈ፤ የብርሃን ድባብ ተዘረጋ፡፡

✍️ከዚያም ላይ ሁና ‹‹ሰላም ለከ ኦ ፍቅርየ ኤፍሬም፤ ወዳጄ ኤፍሬም ሰላም ለአንተ ይሁን›› አለችው፤ እርሱም ታጥቆ እጅ ነሥቶ ቆመ፡፡ ‹‹ወድሰኒ›› አለችው፤ ‹‹እፎ እክል ወድሶተኪ ዘኢይክሉ፤ ሰማያውያን ወምድራውያን ምድራውያን ጻድቃን ሰማያውያን መላእክት አንችን ማመስገን የማይቻላቸው ለእኔ እንደምን ይቻለኛል?›› አላት፤

✍️‹‹በከመ አለበወ፤ በመንፈስ ቅዱስ ተናገር›› አለችው። ከዚህ በኋላ ‹‹ባርኪኝ›› አላት፤ ‹‹በረከተ ወልድየ ወአቡሁ ወመንፈስቅዱስ ይኅድር በላዕሌከ፤ የልጄና የአባቱ እና የመንፈስ ቅዱስ በረከት በላይህ ላይ ይደርብህ›› አለችው፤ ተባርኮም ምስጋናዋን ጀምሯል፡፡ በእንደዚህም ሁኔታ የሰባቱን ዕለታት ውዳሴ ማርያም መድረስ ችሏል፡፡ (ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ)

✍️ለአባታችን ቅዱስ ኤፍሬም የተለመነችው እመቤታችን ለእናም ትለመነንአሜን !
መልካም ምሽት !

13/07/2025

እንኳን ለአጋዕዝት አለም ቅድስት ስላሴ አመታዊ
ክብረ በዓል አደረሠን! አደረሳችሁ!

13/07/2025

በመማረር ውስጥ ምንም ጥሩ ነገር አይገኝም..... ኑሮ ይከብዳል ሁሉም ነገር እንዳሰቡት አይሆንም ለመበሳጨት ለማዘን እልፍ አዕላፍ ተራ ምክንያቶች አይጠፉም.... በዚህ ውስጥ ግን ያልሆነው ያልተሳካው ለበጎ ነው ብሎ ማለፍ እና ባለቤቱን ማመስገንን የመሰለ ነገር የለም🙏 "እሰይ ነጋ ላመሰግንህ ነው" የሚለው መዝሙር የስልኬ ጥሪ ከሆነ 7 አመት አልፎታል..... ተበሳጭቼ ራሱ ስልኬ ሲጠራ ወደ ምስጋና እመለሳለሁ🙏 ፈጣሪን ማመስገን የመሠለ ነገር የለም🙏

️የአባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ታሪክ በአጭሩ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሐገራቸው ንሂሳ ግብጽ ነው፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ልጅ አጥተው 30 ዘመን ሲ...
12/07/2025

️የአባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ታሪክ በአጭሩ

አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሐገራቸው ንሂሳ ግብጽ ነው፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡

ልጅ አጥተው 30 ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን ክብሩ ከሰማይ ከፍታ የሚበልጥ ልጅ እንኪ ተቀበይ የሚል ድምጽ ሰማች፡፡

በዚህ መሠረት ቅዱስ አባታችን ጻድቁ አቡዬ ገብረ መንፈስ ቅዱስ መጋቢት 29 ተፀንሰው ታኀሣስ 29 ተወለዱ፡፡

አባታችን ዓይን በገለጡ ጊዜ ከሚታይ ነገር ላይ እንዲያርፍ እርሳቸውም በተወለዱ ጊዜ አፈፍ ብለው ተነስተው «ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ዘዓውፃእከኒ እምጽልመት ውስተ ብረሃን» ብለው አመስግነዋል።

"ከጨለማ ወደ ብርሃን ላወጣኸኝ ለአብ ምስጋና ይገባል ለወልድ ምስጋና ይገባል ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል" ማለት ነው !

በኋላም ምድራዊ መብል መጠጥ ሳይመገቡ ሳይጠጡ ለምስጋና ተግተው መላዕክትን ይመስላሉ፡፡

አባታችን ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በኢትዮጵያ 262 ዓመት ኖረው በ562 ዓመታቸው በተስፋቸው ያመነውን በኪዳናቸው የተማጸነውን ጌታ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ሊምርላቸው ቃልኪዳን ተቀብለው በዕለተ እሁድ ዐርፈዋል፡፡

መላእክት በአክናፈ እሳት ኢየሩሳሌም ወስደው በየማነ ምስዋዕ ቀብረዋቸዋል፡፡

አሁንም በኛ ዘመን በተሰጣቸው ቃልኪዳን ለተማፀነ ሁሉ ብዙ ገድልና ተዓምራትን እየፈፀሙ ይገኛሉ !

አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ይባርኩን ይጠብቁን ! በረከታቸው ይደርብን !

Address

Gond

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gashaw Getnet posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gashaw Getnet:

Share