Gashaw Getnet

Gashaw Getnet አንቺ የወላዲተ አምላክ የአሥራት አገር
ኢትዮጵያ ሆይ ተነሺ!!!

የሉም ጠፍተዋል ሲሉን ኑረን፣  አለን በእግዚአብሔር ሁሉን ችለን፤ አለን በእግዚአብሔር ሁሉን አልፈን! እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረ...
07/01/2026

የሉም ጠፍተዋል ሲሉን ኑረን፣
አለን በእግዚአብሔር ሁሉን ችለን፤
አለን በእግዚአብሔር ሁሉን አልፈን!

እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!

መልካም በዓል!

04/01/2026

እባክህ ቀና ብለን የምንሔድበትን ደጉን ጊዜ አምጣልን መድኃኔዓለም አባቴ!!

"" ሰሞኑን ስለተፈጠረው ነገር ገሚሱ ሲደነቅ ገሚሱ ደግሞ ሲያጣጥል እመለከታለሁ እኛ ክርስቲያኖች ተዓምር ፈላጊ ተአምር ናፋቂ አይደለንም ለእኛም ተአምር አዲስ ነገር አይደለም መጽሀፎቻችን ሁ...
02/01/2026

"" ሰሞኑን ስለተፈጠረው ነገር ገሚሱ ሲደነቅ ገሚሱ ደግሞ ሲያጣጥል እመለከታለሁ እኛ ክርስቲያኖች ተዓምር ፈላጊ ተአምር ናፋቂ አይደለንም ለእኛም ተአምር አዲስ ነገር አይደለም መጽሀፎቻችን ሁሉ ለማመን በሚከብዱ በተአምር የተሞሉ ናቸው ። ሌላው ደግሞ ይህን ክፍተት በመጠቀም ኢ - አማንያን የሆኑ ቤተ ክርስቲያንን የሚነቅፉ ንግግሮች ሲያደርጉ እመለከታለሁ የፓስተር ላ ብ የተጠረገበት ሶፍት ያድናል ብለህ ተቀብለህ ፀበልን የምታጣጥልበት ሞራል አይኖርህም ።

እንዲሁም ሌሎች ስማቹህን ባልጠራውም ታውቃላቹህ የምትከተሉት የምታምኑበት መጽሀፍ ላይ አንድ ተአምር ተፈልጎ እንኳን አይገኝም በማይመለከታቹህ ነገር አትግቡ ፀበሉንም ተአምሩንም ለእኛ ተውልን።

Inbox አለም ሁሉይስማው፡ በቆላድባ ከተማ የታየው አስደናቂ ተአምር!ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓ.ም : ምስራቅ ደንቢያበዛሬው ዕለት በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ቆላድባ ከተማ የከተማው እንብርት"...
01/01/2026

Inbox አለም ሁሉይስማው፡ በቆላድባ ከተማ የታየው አስደናቂ ተአምር!

ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓ.ም : ምስራቅ ደንቢያ
በዛሬው ዕለት በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ቆላድባ ከተማ የከተማው እንብርት" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ፣ በአንድ ግዙፍ ዋርካ ዛፍ ላይ የቅድስት ኪዳነ ምህረት ድንቅ ተአምራዊ ምስል መታየቱ ተሰማ።

ክስተቱን ለየት የሚያደርገውና የብዙዎችን ትኩረት የሳበው ቀደም ብሎ የነበረው ሁኔታ ነው። በከተማው እየተከናወነ ባለው የኮሪደር ልማት ምክንያት፣ በአስፓልቱ ዳር የሚገኘው ይህ ዋርካ እንዲቆረጥ ታቅዶ ነበር።

ሆኖም ግን፦

* በቀን ስራው ተጀምሮ ዋርካውን ለመቁረጥ ሙከራ ቢደረግም፣ ለመቁረጫነት የሚያገለግሉ ቁሳቁሶች በተደጋጋሚ እየተሰበሩ ስራውን ማከናወን አልተቻለም።

* ሰራተኞቹ "ነገሩ አልሆን አለ" በማለት ትተውት በሄዱበት ጥቂት ሰዓታት ሳይሞላ፣ አመሻሽ ላይ በዋርካው አካል ላይ የኪዳነ ምህረት ድንቅ ምስል ተገልጦ ታይቷል።

በአሁኑ ሰዓት የከተማው ህዝብና ከአካባቢው የመጡ ምዕመናን በቦታው ተገኝተው ይህንን ድንቅ ተአምር እየተመለከቱ ይገኛሉ።

ይህ የእግዚአብሔር ስራ እንጂ የሰው አይደለም" በሚል ምስክርነታቸውን እየሰጡ ነው።

"ዛፉ ሊቆረጥ ሲል መሳሪያው አልሰራ ማለቱ የነገሩን ድንቅነት ያሳያል፤ አሁን ደግሞ ይኸው እናታችን ተገለጠች" የሚሉ የቆላድባ ከተማ ነዋሪዎች በርክተዋል

ጎንደር በቆላድባ የታየው ተአምር ቀጥሏል — ፀበል ፈለቀ!

"የእግዚአብሔር ድንቅ ስራ በቆላድባ ከተማ ተገለጠ!"

ትላንት ማታ በጎንደር በምስራቅ ደንቢያ ወረዳ ቆላድባ ከተማ በዋርካው ላይ የታየው የቅድስት ኪዳነ ምህረት ተአምራዊ ምስል መላውን ዓለም ሲያስደንቅ መቆየቱ ይታወሳል። አሁን ደግሞ ሌላ እጅግ የሚያስገርም ተጨማሪ ተአምር ተከስቷል!

የእናታችን የኪዳነ ምህረት ምስል በታየበት በዚያው ስፍራ፣ በአሁኑ ሰዓት አስደናቂ ፀበል ፈንድቶ ወጥቷል! * ህዝቡ እየተፈወሰ ነው፦ በቦታው የሚገኘው ህዝብ በፀበሉ እየተጠመቀ ይገኛል፤ እግዚአብሔር በቸርነቱ ድውያንን እየፈወሰ፣ የታመሙትን እየዳሰሰ መሆኑ እየተነገረ ነው።

* በስፍራው ያለው ምዕመን በደስታ እልልታና በምስጋና ድምፅ አካባቢውን ሞልቶታል። "ዛፉን እንዳይቆረጥ መሳሪያ የሰበረች እናታችን፣ ዛሬ ደግሞ ለልጆቿ ፈውስን አፈለቀች" በማለት ህዝቡ ምስክርነቱን እየሰጠ ነው።

* በዋርካው ላይ የቅድስት ኪዳነ ምህረት ምስል በግልጽ ታየ።
* ዛሬ ደግሞ ለብዙዎች መዳኛ የሚሆን ፀበል ፈንድቶ ወጣ!
እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው! ቸርነቱና ምህረቱ ለሁላችንም ይሁን።

ተአምሩ_ቀጥሏል፡ በቆላድባ የፈውስ ዝናብ እየዘነበ ነው!

"እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው!"
ትላንት በምስራቅ ደንቢያ ቆላድባ በዋርካው ላይ በታየው ድንቅ ምስል የጀመረው ተአምር፣ ዛሬ ወደ ላቀ የፈውስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። ከአለቱ ስር ፈልቆ የወጣው ፀበል ለብዙዎች መዳኛ እየሆነ ይገኛል!

* በፀበሉ እየተጠመቁ ያሉ በርካታ ወገኖች ከደዌያቸው እየተፈወሱ መሆኑ እየተሰማ ነው።

* ስፍራው በምስጋና፣ በእልልታና በዝማሬ ተሞልቷል። ህዝቡም ከየአቅጣጫው እየመጣ የበረከቱ ተካፋይ እየሆነ ነው።

* የእናታችን ቃል ኪዳን፦ "መሳሪያውን ያስቆመች እናታችን ዛሬ ደግሞ በፀበሏ ቁስላችንን እየጠገነች ነው" በሚል ምዕመናን ምስክርነታቸውን እየሰጡ ነው።

ለመቁረጥ የመጣው መጥረቢያ ተሰበረ፤ ለመፈወስ የመጣው ፀበል ግን ፈለቀ!"

Inbox የአይኑ ብርሃን ተመለሰ! በቆላድባ ተአምሩ ቀጥሏል!

በጎንደር ምስራቅ ደንቢያ ቆላድባ የታየው የኪዳነ ምህረት ድንቅ ተአምር ዛሬም በፈውስ ቀጥሏል፦

እርሷ ምስራቅ ነች ልጇም የጽድቅ ጸሐይ ነውበ325 ዓ.ም በጉባኤ ኒቂያ በነበረው የሲኖዶስ ውይይት ላይ በአደባባይ ተከራክረው ከሐዲያንን ካሳፈሩ 318 ሊቃውንት አንዱ የቆጵሮሱ ሊቀ ጳጳስ ቅዱ...
30/12/2025

እርሷ ምስራቅ ነች ልጇም የጽድቅ ጸሐይ ነው

በ325 ዓ.ም በጉባኤ ኒቂያ በነበረው የሲኖዶስ ውይይት ላይ በአደባባይ ተከራክረው ከሐዲያንን ካሳፈሩ 318 ሊቃውንት አንዱ የቆጵሮሱ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ነበረ።

የጌታችንን የመድኅኒታችንን መለኮታዊ ባህርይ ለሚጠራጠሩ አርዮሳውያንና በተዋሕዶ ሰው ሆኖ መክበሩን ለሚክዱ ቅዱስ ኤጲፋኒዮስ ስለ ተዋሕዶ ምሥጢርና ቅድስት ድንግል ማርያም የመለኮት እናት ስለመሆኗ ሲያስተምር “ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውና አምላክ በተዋሕዶ የከበረ ነው፡፡ በአምላክነቱ መለኮታዊ ባሕርይ ቢኖረውም እንደ ሰውነቱ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ያለ ወንድ ዘር ተፀንሶ በድንግልና ተወልዷል። ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ በትንቢቱ 7፣14 እንደጻፈው “እግዚአብሔር ምልክት ይሰጠናል ድንግል በድንግልና ጸንሳ በድንግልና ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች፡፡ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ እርሱም ድንቅ መካር ኃያል የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል።” በመሆኑም እመቤታችን የአምላክ እናት የእግዚአብሔር እናት ትባላለች ።

ቅዱስ ዮሐንስም በዘመኑ ለተነሱት ከሃዲያን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዘላለማዊ ድንግልና እውነታውን አስረግጦ አስተምሮአል። የክህደት ትምህርት የሚያስተምሩትም በማቴ1÷25 "ዮሴፍም የበኩር ልጇን እስከ ምትወልድ አላወቃትም” ተብሎ ስለተጻፈ ድንግል ማርያም ጌታን ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር በትዳር ኖራለች ብለው ለተነሱበት የተሳሳተ ሃሳብ ሲመልስ፣ እስከ የሚለው ሃረግ ወይም ቃል "ዮሴፍ የበኩር ልጇን እስከምትወልድ አላወቃትም ማለት አንድም ወንድ እንደማታውቅ አንድም እስከ የሚለው ፍጻሜ የሌለው እስከ ነው፡፡ በመሆኑም ጌታን እስከምትወልድ የምትወልደው መድኃኔዓለምን እንደሆነ አላወቀም፡፡ የድኅነት ምክንያት ሆና እንደተመረጠች አያውቅም ነበር፡፡

በሉቃስ ወንጌል ላይም ማርያም ነገርን ሁሉ በልቧ ትጠብቀው ስለነበር ከቅዱሳን የከበረች ከመላዕክትም የበለጠች እንደነበር አያውቅም ነበር። በሌላው ጌታን በፀነሰች ጊዜ ገጽዋ ይለዋወጥ ነበር ይህንንም ሲያይ ዮሴፍ ጻድቅም ስለነበር ሳይገልጣት ተዋት። አበው እንዳስተማሩን እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ፣ በተዋሕዶ ሰው ሆኖ ዓለምን ያዳነበት ጥበቡ ይበልጣልና። ድንግል ማርያም ጌታን ከመፅነሷ በፊት በፀነሰች ጊዜ ከፀነሰችም በኋላ ድንግል ናት። እንዲሁም ከመውለዷ በፊት በወለደችም ጊዜ ከወለደችም በኋላ ድንግል ናት። ይህንንም እግዚአብሔር ስለገለጸለት ከአበይት ነቢያት መካከል አንዱ ቅዱስ ሕዝቅኤል በምዕራፍ 44÷1-4 “ወደ ምስራቅ ወደሚመለከተው በር አመጣኝ ይህ በርም ዝግ ነበር፣ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ለዘላለም ዝግ ሆኖ ይኖራል።” አለኝ ይላል፡፡

ምስራቅ ያላት ድንግል ማርያምን ነው ፀሐይ ከምስራቅ እንዲወጣ ጨለማውንም ዓለም ብርሃን እንዲያደርግ፤ ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስም ከአማናዊት ምስራቅ ከድንግል ማርያም ተልወዶ በኅጢያት ለጨለመው ዓለም የጽድቅ ብርሃን ሆኖ ተገልጧልና፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞንም በመኃልዬ መኃልይ 4÷12 "እህቴ ሙሽራዬ ሆይ የተዘጋ ገነት የታተመ ፈሳሽ ነሽ" በማለት ስለዘላለማዊ ድንግልናዋ ጽፏል። በቅዱስ ጳውሎስም በገላትያ 4÷4 እንደጻፈው የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ያለ ዘርአ ብእሲ ወይም ያለ ወንድ ዘር ከቅድስት ድንግል ማርያም ከአምላክ እናት የተወለደውን አንድያ ልጁን ላከልን፣ እርሱም የእኛን ባህርይም ባህርይ አድርጎ ተወለደ። ልጆችም ስለሆንን እግዚአብሔር አባ አባት ብለን የምንጠራበት የልጅነት መንፈስ ሰጠን፡፡ እመቤታችንም በሕቱም ድንግልና ይህን ጌታ ወለደችልን፡፡ ገዳማውያንም ይህችን እናት ዘወትር አማልጅን ይሏታል፡፡ ገዳማቸውን እደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

28/12/2025

ስለ ጦርነት አስከፊነት አንድ
የሰርቢያኖች ድንቅ አባባል አለ...
ጦርነት ሲጀምር፦ ፓለቲከኞች ጥይት ያቀብላሉ፤ ባለሀብቶች ምግብ ይሰጣሉ፤ ድሆች ግን ልጆቻቸውን ይለግሳሉ።
ጦርነቱም ሲያበቃ፦ ፓለቲከኞች ቀሪ ጥይቱን ይሰበስባሉ፤ ባለጸጎችም ከጦርነቱ በተረፈው ሀብታቸው ማደግ ይጀምራሉ፤ ድሆች ግን ልጆቻቸውን በመቃብር ስፍራ ይፈልጋሉ።
ሠላም ለሁላችን🙏

ገብርኤል ያረዳው ማን አለ!የቅዱስ ገብርኤልን ረዳትነት ለመናገር በንግስ በዓሉ ላይ ለምስክርነት የተገኙት የእስልምና እምነት ተከታይ አባትእግዚአብሔር ይመስገን !!!
28/12/2025

ገብርኤል ያረዳው ማን አለ!

የቅዱስ ገብርኤልን ረዳትነት ለመናገር በንግስ በዓሉ ላይ ለምስክርነት የተገኙት የእስልምና እምነት ተከታይ አባት

እግዚአብሔር ይመስገን !!!

እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል ዋዜማ አደረሳችሁ፤ አደረሰን 🙏ንጉሥ ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን አቃጥሎ ሕዝቡን ማርኮ ወደ ባቢሎን ሲወስድ የይሁዳው ንጉስ የኢዮአቄም ሦስት ልጆችም...
27/12/2025

እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል ዋዜማ አደረሳችሁ፤ አደረሰን 🙏

ንጉሥ ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን አቃጥሎ ሕዝቡን ማርኮ ወደ ባቢሎን ሲወስድ የይሁዳው ንጉስ የኢዮአቄም ሦስት ልጆችም ተማርከው ወርደዋል፡፡

ንጉሡ ከምርኮ ወጣቶች ለቤተ መንግስት ሲመርጥ ሦስቱ ቅዱሳንና ነቢዩ ዳንኤል ተመርጠው የምቾት ሕይወት ተዘጋጅቶላቸው ነበር፡፡ ነገር ግን በምግብና በአምልኮ ከአሕዛብ ጋር ከመተባበር ይልቅ በጾምና ጸሎት ጥሬ ባቄላ መብላት ምርጫቸው ሆነ፡፡ ሠለስቱ ደቂቅ አናንያ፣ አዛርያና ሚሳኤል፡፡ በቤተ መንግስት ውስጥ ቢኖሩም ለእነርሱ ከእግዚአብሔር ፍቅር የተሻለ አልነበረምና በጥሬ ተወስነው ኖሩ፡፡ ሁሉን ቻይ አምላካቸውም እግዚአብሔር ጸጋውን አብዝቶላቸውም በባቢሎን ምድር በውበትም ሆነ በጥበብ የሚደርስባቸው አልተገኘም፡፡ ንጉሡም በባቢሎንና በአውራጃዋ ላይ ሾማቸው፡፡ ስማቸውንም በአማልክቱ ስም ሲድራቅ፣ ሚሳቅና አብድናጎ በሚል ቀየረላቸው፡፡

ንጉሡ ስለወደዳቸው አሕዛብ ቀንተውባቸዋልና የክፋት አዋጅ አሳወጁ፡፡ ናቡከደነጾር ላቆመው 60 ክንድ ቁመት ያለውን የወርቅ ምስል አንሰግድም በማለታቸውም ከእቶን እሳት ተጣሉ፡፡ ከጉድጉዋዱ ወደ ላይ 49 ክንድ የሚነደው ነበልባልም አላስፈራቸውም፡፡ ሦስቱ እግዚአብሔር የመረጣቸው ጠቢባን ሕጻናት አናንያ፣ አዛርያ፣ ሚሳኤል በንጉሡ ፊት ቆመው “ንጉሥ ሆይ እኛ የምናመልከው አምላክ በሰማይ አለ፡፡ ከሚነድደው ከእቶኑ እሳት ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፡፡ ንጉሥ ሆይ! ይህም ባይሆን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድ ዕወቅ” ባሉ ጊዜ ወደ እቶን እሳት ተጣሉ፡፡ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤልም ደርሶ አዳናቸው፡፡ ይህም በዓል በየዓመቱ ታህሣስ 19 ቀን በድምቀት ይከነራል። ቅዱሳን አናንያ፣ አዛርያና ሚሳኤል ያረፉት ከክርስቶስ ልደት በፊት በ500 ዓመተ ዓለም ነው፡፡

ቅዱስ ገብርኤል ከእሳት ባወጣቸው ቀንም
"ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ::
ስቡሕኒ ውዕቱ ወልዑልኒ ውዕቱ ለዓለም::"
የሚለውን ምስጋና ፈጣሪ ገልጾላቸው በእሳቱ ውስጥ ሆነው አመስግነዋል፡፡ ድርሰታቸው 2 ወገን ሲሆን ባለ ስድስት አንቀጹ ምስጋናቸው ከ600 ዓመት በሁዋላ ክርስቶስ እንደሚወለድ የሚያሳይ ሲሆን 33 አንቀጾች ያሉት ምስጋናቸው ደግሞ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ለ33 ዓመታት እንደሚመላለስ በምስጢር የሚያመለካት ነው፡፡ ሠለስቱ ደቂቅ ካረፉ ከ900 ዓመታት በሁዋላ በ400 ዓ.ም አካባቢ ታላቁ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ቤተ ክርስቲያን አንጾላቸው ነበርና አጽማቸውን እንዲያመጣለት ወዳጁን ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን ጠርቶም "አባ! አጽመ ቅዱሳንን ባቢሎን ወርደህ አምጣልኝ?" አለው፡፡ ቅዱሱ ሐጺር ዮሐንስም በደመና ተጭኖ ባቢሎን ገባ፡፡ በቅዱሳኑ መቃብር ፊትም ሰግዶ ሲያለቅስ ሠለስቱ ደቂቅ "ወዳጃችን! ምን ሆንክ?" አሉት፡፡

እርሱም “ወደ ግብጽ እንሒድ:: አባ ቴዎፍሎስ ይፈልጋቹሃል” አላቸው:: ሠለስቱ ደቂቅም “ለቅዱሱ ቴዎፍሎስ እግዚአብሔር ዋጋህን ይክፈልህ፤ አጽማችን ግን እስከ ዓለም ፍጻሜ ባቢሎንን አይለቅም፤ ለክብርህ ግን እንመጣለን፡፡” አሉት፡፡ “ለምልክትም ይሆን ዘንድ መብራት ሳታበራ በሌሊት ጠብቀን በለው” ሲሉም ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን ባርከው ሸኙት፡፡ ሐጺርም መጥቶ መልአክቱን አደረሰ፡፡ በቅዳሴ ቤታቸው ዕለትም ቅዱሳን ቴዎፍሎስ፣ ቄርሎስ፣ ዮሐንስ ሐጺርና ሌሎችም ከምዕመናን ጋር በጨለማ ሳሉ ቤተ ክርስቲያኑ ቦግ ብሎ በራ፡፡ እጅግ የሚደነቅ ብርሃንም ከበባቸው፤ በብርሃኑ መካከል ሠለስቱ ደቂቅ ሲያልፉ በጐ መዓዛ ሸተተ፡፡ ሕዝቡም በደስታና በዝማሬ የቅዱሳኑን ቅዳሴ ቤት አክብሯል፡፡

ገዳማውያንም ቅዱሳኑ አባቶች እንዲያማልዷቸው ይጠይቃሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፤ የቅዱስ ገብርኤል በረከት አይለየን።

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

ድጉ የድሬ ሰው'' ለቁልቢ ገብርዔል የንግስ በዓል ወደ ድሬዳዋ  የመጡ እንግዶች  በከንቲባ ከድር ጁሃር ጋር በመሆን የድሬዳዋ ህዝብ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
27/12/2025

ድጉ የድሬ ሰው'' ለቁልቢ ገብርዔል የንግስ በዓል ወደ ድሬዳዋ የመጡ እንግዶች በከንቲባ ከድር ጁሃር ጋር በመሆን የድሬዳዋ ህዝብ አቀባበል አድርጎላቸዋል።

ለቅንጦት ወይም ለድሎት አይደለም ገንዘቡ ለእለት ጉርስ ነው  በግል ፀብ ወይም በማህበር ጥላቻ ተነሳስቶ  እገሌ የሰጠውን እርዳታ  አንቀበልም ማለት በረሀብ አለንጋ እየተገረፉ ያሉት ወገኖቻች...
26/12/2025

ለቅንጦት ወይም ለድሎት አይደለም ገንዘቡ ለእለት ጉርስ ነው በግል ፀብ ወይም በማህበር ጥላቻ ተነሳስቶ እገሌ የሰጠውን እርዳታ አንቀበልም ማለት በረሀብ አለንጋ እየተገረፉ ያሉት ወገኖቻችንን ላይ መቀለድ ነው። አልቀበልም ካልክ ከኪስህ ለእርዳታ የቀረበውን 15 ሚሊዮን ብር አውጥተህ እንድትሰጥ እንጠይቃለን በአንተና በማህበራቹህ ምክንያት ወገኖቻችንን እርዳታ መነፈግ የለባቸውም።

25/12/2025

እርዳታ አንፈልግም የሚል መግለጫ አየሁና አበሳጬኝ! ኢትዮጵያ ኧራሷ ከኢጣሊ ሳይቀር እርዳታ በማትንቅበት ሁኔታ ላይ እያለን የሀገሩን ልጆች አትረዳም ተብሎ መከልከል ምን ያክል ስሜት
የሚነካ ነውር ነገር ነው🙄🙄!

Address

Gond

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gashaw Getnet posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gashaw Getnet:

Share