Dansha Town Communication affairs office

Dansha Town Communication affairs office በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን የፌስ ቡክ ገፅ

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የተቋማት ዳሰሳ ግብረ መልስ እና የ90 ቀን እቅድ የውይይት መድረክ ተካሂዷል ዳንሻ:- ሀምሌ 11/2017 ዓ.ም)በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳ...
18/07/2025

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የተቋማት ዳሰሳ ግብረ መልስ እና የ90 ቀን እቅድ የውይይት መድረክ ተካሂዷል

ዳንሻ:- ሀምሌ 11/2017 ዓ.ም)በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የተቋማት የሱፐርቪዥን ግብረ መልስ እና የ90 ቀን እቅድ የውይይት መድረክ ተካሄደ ።

በመድረኩ የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዱልዋሀብ ማሞ፣የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ማሩ፣የወረዳው ሰራ አስፈፃሚዎች ፣የጽህፈት ቤት ኃላፊዎች እና ተወካዮች ተገኝተዋል ።

በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የስቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት የሪፎርምና ክትትል ቡድን መሪ በአቶ መከተ ፈንታ፣በዋና ኮምሽነር መ/ር አላቸው ብርሀኑና በአቶ ሁሴን አህመድ በተቋማት የተደረገው ዳሰሳ ለተሳተፊዎች በጥንካሬና በድክመት የተገኘው ውጤት ገለፃ አድርገዋል ።

በነበረው ዳሰሳ ከንቲባ ጽ/ቤት፣የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት ፣ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት እንዲሁም መንገድና ትራንስፖርት ጽ/ቤቶች ከ1-3 ደረጃ ይዘዋል ።

በተቋማት ከታዩ ክፍተቶች የበጀት አለመኖርና የቁሳቁስ እጥረት፣የሰራተኞች አለመሟላት፣ልዩ ልዩ ሙያዊ ስልጠናዎችና የተሞክሮ ልውውጥ አለመኖር ፣መርህ በመከተል ስራን ቆጥሮ ከመስራት ውሱንነት መኖር ፤ኃላፊነት አለመወጣትና ትኩረት አድርጎ አለመስራት፣የእቅድና ሪፖርት መዛነፍ በተወሰኑ ተቋማት በክፍተት ታይቷል።

አቶ ሀብታሙ ማሩ በውይይት መድረኩ ተቋማት ያላቸው ጠንካራ ጎን በማጠናከርና ክፍቶችን በማስተካከል፤የአመራርና የሙያተኛ አቅም በማሳደግ ተረባርበን የተሻለ ተቋም መገንባት ይጠበቅብናል ብለዋል።

በክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣የልማትና የፀጥታ ስራዎች፣የመልካም አስተዳደር እና የህዝብ ግንኙነት ስራዎችን በተቀናጀ መልኩ ለመፈፀም የሚያስችል የ3 ወር እቅድ በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ ሀብታሙ ማሩ ለአለመራሮች አቅርበዋል ።

18/07/2025

"ደም መለገስን ባህል በማድረግ በደም እጦት ምክናያት የሚሞቱ ወገኖችን መታደግ አለብን"

መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር)
የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ

በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የተቋማት የሱፐርቪዥን ግብረ መልስ እና የ90 ቀን እቅድ የውይይት መድረክ እየተካሄደ  ይገኛል ።
18/07/2025

በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የተቋማት የሱፐርቪዥን ግብረ መልስ እና የ90 ቀን እቅድ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል ።

18/07/2025

ታላቁ የህዳሴ ግድብ የመደመር ትውልድ አሻራ የወል እውነት ማሳያ፦ ሌላ የምስራች ተጨማሪ ድል!

ብልጽግና አካታችነትንና ፍትሃዊነትን መርህ አድርጎ ለሁንተናዊ ተምሳሌትነት እየተጋ ሀገራዊ ልዕልናን እያበሰረ ቀጥሏል። ወንድማማችነት/እህትማማችነት ጎረቤትን ባሰቀደመ ድፕሎማሲ የጋራ ተጠቃሚነትን ማዕከል አድርጎ ይሰራል።

በአረንጓዴ አሻራ የተፈጥሮ ሚዛንን በማስጠበቅ ተምሳሌት የሆነችዋ ኢትዮጵያ በፍትሃዊነት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን በስኬት በማጠናቀቅ እጅን በአፍ የሚያስጭን እምርታዎችን እያስመዘገበች ነው። ብሔራዊ ክብርን ያሰጠበቀ፣ የትውልድ ቅብብሎሽና የትጋት ውጤት የሆነው ታላቁ የህዳሴ ግድብ ተጨማሪም ብስራትን በማስቀጠል የልዕልናችንን መንገድ አመላክቷል። ይህ መደመር የትውልድ ኩራት የሆነው ታላቅ የስኬት አሻራ ብዝሃነታቻችንን ያደመቀ አንድነታችንን ያፀና በወል ሀገር የወል እውነትን ያዳበረ ድል ነው። ህዳሴ የብሔራዊነት ትርክት ማጠንጠኛ አንድ ሆነን ብዙ፣ በብዝሃነትም አንድነትን ያፀናንበት ዘመንን የዋጀ የአርበኝነት መገለጫ ነው። መደመር በፍታሃዊነትና በጋራ ተጠቃሚነት ሀገራዊ ልዕልናን እየገነባ ለነገ ምንዳን የሚያሻግር የከፍታ መንገድ ነው።

ኢትዮጵያ የአፍሪካውያን የድል ምልክት የሆነውን አድዋን በደማቸው እንዳስመዘገቡት ሁሉ የመደመር ትውልድ በላቡ የፃፈው የአርበኝነት ማሳያ የሆነው ታላቁ የህዳሴ ግድብም ከእራስ አልፎ ለወንድም አፍሪካዊያንም ኩራት ነው። በተለይም በተፋሰስ ሀገራት ላይ ምንም አይነት ጉዳት ሳያደርስና ይልቁንም ተጨማሪ አቅም በመሆን በዝናብ አጠር ጊዜም ጭምር ውሃው ፍሰቱን ጠብቆ እንድሄድ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል። የጎርፍና ለሌሎች የአየር መዛባቶችንም በመቀነስ፣ የሀይል አማራጭ በመሆን ለጎረቤት ሀገራት ጭምር ጉልህ አበርክቶት አለው።

ይህ ትውልድ የአባቶቹን በደም የከበረች ሀገር በላቡ መስዋዕትነት እያፀና አዳዲስ አሻራዎችን በማኖር ትናንትን፣ ዛሬን እና ነገን አስተሳስሮ ለሁለንተናዊ ብልጽግና እየተጋ ይገኛል። ብሔራዊ ኩራት የወል አሻራ ማሳያ የሆነው ህዳሴ ወንድማማችነትና እህትማማችን በማፅናት ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን በማብሰር የጋራ ከፍታን የሚረጋግጥ ነው። ህዳሴ ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ዕድልና የምስራችም ነው። ለኢትዮጵያዊያን ደሞ የትጋታቸው ውጤት የህብረታቸው የድል ማብሰሪያ ነው። ለተፋሰስ ሀገራት የጎርፍ ስጋትን በመቀነስ በጋራ የመልማትን፣ በድርቅ አለመጠቃትና ውሃው አመቱን ሙሉ ያለማቋረጥና ብክነት ፍሰቱን እንዲጠብቅ ያደረጋል።

ብልጽግና በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም እንደማይደራደረው ሁሉ በፍትሃዊነትና በጋራ ተጠቃሚነት ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን መገንባት መርሁ ነው። ሁለንተናዊ ተምሳሌት በመሆን ከእራስ ባሻገር በማሰብ የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ላይ ይገኛል። ይህ የተፈጥሮ ሚዛንን በማስጠበቅ ተጨማሪ ውሃን ማገኘት የሚያስችል ለጎረቤት ሃገራት ዓቅም የሚሆን የትጋት ውጤት ነው በጥቅሉ አባይ ለኢትዮጵያ ኩራትና ድል ለተፋሰስ ሀገራት ደሞ የምስራች መሆን ችሏል።

ህዝባችሁን በስራ መካስ አለባችሁ :- አቶ ገ/ሄር ደሴዳንሻ፦ሀምሌ 7/2017 ዓ.ም)በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የዳንሻ ከተማና የጠገዴ ወረዳ የ...
14/07/2025

ህዝባችሁን በስራ መካስ አለባችሁ :- አቶ ገ/ሄር ደሴ

ዳንሻ፦ሀምሌ 7/2017 ዓ.ም)በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የዳንሻ ከተማና የጠገዴ ወረዳ የቆላማው ክላስተር የፖሊስ አባላት ግምገማ መድረክ ተካሂዷል ።

በመድረኩ በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገብረእግዚአብሔር ደሴ፣ዋና ኢንስፔክተር አሸብር ሲሳይ፣የወረዳ አመራሮች እና የፖሊስ አባላት ተገኝተዋል።

በቁርጠኝነት የምትሰሩ ታማኝ ፖሊሶች እንዳላችሁ ሁሉ፤ አንዳንድ አባላት ህዝብና መንግስት የጣለባችሁ ኃላፊነት አልተወጣችሁም ቀጣይ ህዝባችሁን በስራ መካስ አለባችሁ ሲሉ የዞኑ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገብረእግዚአብሔር ደሴ ተናግረዋል ።

በግምገማ መድረኩ ህዝባችን በአንዳንድ የፖሊስ አባላት በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውዝ በመሳተፍ፣በጥቅማ ጥቅም በመደለል፣ኃላፊነት በአግባቡ ባለመወጣት፣ በሙስናና ብልሹ አሰራሮች ህዝባችን መማረሩ ተነስቷል ።
በተለያዩ ህገ ወጥ ተግባራት የተጠረጠሩ የፖሊስ አባላት
በግምገማ በመድረኩ የታረሙ ሲሆን ፤
በተደጋጋሚ ወንጀሎች የተጠረጠሩ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ እና ተጣርቶ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው በሚመለከታቸው አካላት በማጠቃለያ ተነስቷል ።

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የዳንሻ ከተማና የጠገዴ የቆላማው ክላስተር  የፖሊስ አባላት የግምገማ መድረክ እየተካሄደ  ይገኛል...
14/07/2025

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የዳንሻ ከተማና የጠገዴ የቆላማው ክላስተር የፖሊስ አባላት የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል ።

12/07/2025
12/07/2025
"የተገኘውን ነጻነት በህግ አግባብ የማረጋገጥና የማስጨረስ የዚህ ትውልድ ኃላፊነት ነው" ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱበአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን "ለመጭው ትውልድ ነጻነትን እንጂ ተ...
12/07/2025

"የተገኘውን ነጻነት በህግ አግባብ የማረጋገጥና የማስጨረስ የዚህ ትውልድ ኃላፊነት ነው" ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ

በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን "ለመጭው ትውልድ ነጻነትን እንጂ ተሻጋሪ እዳን አናወርስም!" በሚል መሪ ቃል 9ኛ ዓመት የድል በዓል በሰቲት ሁመራ ከተማ ተከብሯል።

ሐምሌ 5 የመላው የአማራ ሕዝብና ፍትህ ወዳድ ኢትዮጵያውያን የተባበረ ክንድ የተገለጠባት እለት ናት ያሉት የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ እንዲሁም የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ፦ እለቱ የፈጣሪ ተዓምር የተገለጠበትና የጨቋኞች ስርዓት ላይመለስ ያከተመበት ቅዱስ ዕለት ነው ብለዋል።

ነገሩ "ንጉስ በሰራዊት ብዛት አይድንም" ነውና አፋኝ ቡድኑ በጎንደር ከተማ በመግባት ከቤቴ ለማስወጣትና ለመግደል ቢሞክርም በፈጣሪ ሀይል በፅኑ ተጋድሎና በጎንደር አማራ ሕዝብ እምቢተኝነት ሳይሳካላቸው ቀርቷል ሲሉም አስታውሰዋል።

በጎንደር መናገሻ ከተማ በሁሉም አቅጣጫ የተፈጠረውን ሲሰማ አዛውንት፣ወጣትና ሕጻናት ሳይቀር በእምቢተኝነት አፋኙን ቡድን በመውረር ተጋድሎውን አስመስክሯል። ትግሉን በማቀጣጠልም መላው የአማራ ሕዝብ በወቅቱ ውድ የሕይወት መሰዋዕትነት ከፍሏል ብለዋል።

ትግሉ የመላው ሕዝብ ትግል መሆኑን የገለጹት ኮሎኔሉ፦ የኦረሞ ሕዝብ ደም ደሜ ነው በማለት በወቅቱ የነበረውን የጨቋኝ ስርዓት ሲቃውም እንደነበርም ገልጸዋል።

ሐምሌ 5 ብዙ አስደሳችን እና ተምራዊ ሁነቶች የታዩበት እለት መሆኑን አንስተው የለውጡ መንግስት እንዲመጣ ምክንያት ነበርም ብለዋል።

ነጻነታችን በማወጅ በእራሳችን ቋንቋ፣ወግ እና ባሕል ያለማንም ከልካይ በነጻነት እየኖርን ነው። ይህም የሐም 5 አንዱ ቱርፋት መሆኑን ገልጸዋል።

ጥያቄው የእውነትና የፍትህ ጥያቄ በመሆኑ በመጨረሻም እውነት አሽንፎ በተባበረ ክንድ ነጻ ወጥተናል ብለዋል።

ትግሉ የጋራ ትግል የጋራ ውጤት የተገኘበች የነጻነት ቀን ነው። የተገኘውን ነጻነት በህግ አግባብ የማረጋገጥና የማስጨረስ የዚህ ትውልድ ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል።

ክቡር የትግራ ሕዝብ ሆይ ጸባችን ከጨቋኙ ስርዓት እንጂ ከሕዝቡ አለመሆኑን በመረዳት የነጻነት በዓላችን ስናከብርም ደስ ብሎናልና ደስ ይበላችሁ ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም መጭው ዘመን የሰላም እንዲሆን የተመኙት ኮሎኔሉ፦ ለመላው የአማራ ሕዝብ እና ፍትሕ ወዳድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ እንኳን ለነጻነት ቀናችን በሰላም አደረሳችሁ ሲሉ ደስታቸውን ገልጸዋል።

መረጃው የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ኮሙኒኬሽን ነው።

Address

Gondar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dansha Town Communication affairs office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share