Dansha Town Communication affairs office

Dansha Town Communication affairs office በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን የፌስ ቡክ ገፅ

08/10/2025
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ሠቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ለመንግስት መስርያ ቤቶች አ...
07/10/2025

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ሠቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ለመንግስት መስርያ ቤቶች አጠቃላይ በስሩ የሚገኙ የብልጽግና ህብረት፣የብልፅግና ቤተሠብ አባላት ሱፐርቪዥን አደረገ።

ዳንሻ፦መስከረም 27/2018ዓ.ም)በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ለመንግስት መስርያ ቤቶች የብልፅግና ህብረት፣የብልጽግና የቤተሰብ አባላት ሱፐርቢዥን አደረገ።

በሱፐርቪዥን የህብረት ኮሚሽን አመራሮች የአባላት እና የህብረት የእቅድ ዝግጅት፣ የ1ኛ ሩብ አመት የስራ አፈፃፀም ፣ የአባላት ጥራት ፣ የማንነትና የወሠን ስራዎች እንዲሁም ሌሎች አጠቃላይ የፓርቲ ስራዎች ምልከታ ተደርጓል ።

"መፅሐፍ ለታራሚዎች" በሚል መሪ ሀሳብ ምድረ ሐሽማል ኢዩቶፕያ የመፃህፍት መደብር በማህበራዊ ሚድያ በማሰባሰብ 70 መፃሕፍት ለዳንሻ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት አበረከተ መስከረም 23/2018ዓ.ም ...
03/10/2025

"መፅሐፍ ለታራሚዎች" በሚል መሪ ሀሳብ ምድረ ሐሽማል ኢዩቶፕያ የመፃህፍት መደብር በማህበራዊ ሚድያ በማሰባሰብ 70 መፃሕፍት ለዳንሻ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት አበረከተ

መስከረም 23/2018ዓ.ም .ም)በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር "መፅሐፍ ለታራሚዎች" በሚል መሪ ሀሳብ ምድረ ሐሽማል ኢዩቶፕያ የመፃህፍት መደብር በማህበራዊ ሚድያ በማሰባሰብ 70 መፃሕፍት ለታራሚዎች አበርክቷል ።

በወጣት ዳኘው መብራቴ (ምድረ ሐሽማል ኢዩቶፕያ የመፃህፍት መደብር) ከ30ሺ ብር በላይ ግምት ያላቸው የተሰበሰቡት መፅሐፍት በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የፖሊስ ጽ/ቤት የወንጀል መከላከል ኃላፊ የሆኑት ምክትል ኢንፔክተር ወንድም ደሳለይ ተረክበዋል ።

ወጣት ዳኘው መብራቴ የመፅሐፍ ድጋፍ ላደረጉ ሁሉ በማመስገን 'ለንባብ ገደብ የለውም' በማለት በቀጣይም በአካባቢያችን ለሚገኙ ቤተንባብና ትምህርት ቤቶች የሚሆኑ መጽሐፍት የማሰባሰብ ስራ እንደሚቀጥልና ማነኛውም ሰው ድጋፍ ማድረግ እንደሚችል ተናግረዋል።

"አርቆ ማየት አልቆ መስራት በሚል መሪ ቃል" የ2018 ዓ.ም የአሻጋሪ ዘላቂ የልማት እቅድ ትውውቅ መድረክ ከህብረት፣ከቤተሰብ እና ከአባላት ጋር በሁሉም ቀበሌዎች  ተካሄደ።ዳንሻ: መስከረም ...
03/10/2025

"አርቆ ማየት አልቆ መስራት በሚል መሪ ቃል" የ2018 ዓ.ም የአሻጋሪ ዘላቂ የልማት እቅድ ትውውቅ መድረክ
ከህብረት፣ከቤተሰብ እና ከአባላት ጋር በሁሉም ቀበሌዎች ተካሄደ።

ዳንሻ: መስከረም 19/2018ዓ.ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ እስተዳደር "አርቆ ማየት አልቆ መስራት በሚል መሪ ቃል" የ2017 ዓ.ም የፓርቲና የመንግስት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 ዓ.ም የአሻጋሪ ዘላቂ የልማት እቅድ ትውውቅ መድረክ ከህብረት፣ ከቤተሰብ እና ከፓርቲው አባላት ጋር በሁሉም ቀበሌዎች ተካሂዷል።

29/09/2025

የመደመር መንግሥት ነገን የተሻለ ለማድረግ የትናንት፣ የዛሬና የነገ ተደራራቢ ኃላፊነቶቻችንን በአስቸኳይ እንድንወጣ ያደርጋል፡፡ እንዲሁም ተለዋዋጭ በሆነው የዓለም ሁኔታ ውስጥ፣ ጥንካሬያችንን ለማረጋገጥና ከግባችን ለመድረስ እንድንፈጥን ያስችላል፡፡ የመደመር መንግሥት ፍጥነትና ፈጠራን መሠረት ያደረገ ዕሳቤ ነው፡፡

ተማሪ ሹመተይ እርጥቡና ተማሪ መንግስቱ ቸኮለ በክልሉ መንግስት ተሸላሚ ሆኑ  ዳንሻ: መስከረም 19/2018ዓ.ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ እስተዳደር የቢ...
29/09/2025

ተማሪ ሹመተይ እርጥቡና ተማሪ መንግስቱ ቸኮለ በክልሉ መንግስት ተሸላሚ ሆኑ

ዳንሻ: መስከረም 19/2018ዓ.ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ እስተዳደር የቢትወደድ አዳነ መኮነን 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የሆኑ ተማሪ ሹመተይ እርጥቡ 524.1 ነጥብ በማምጣት፤

እንዲሁም ተማሪ መንግስቱ ቸኮለ 507.24 ነጥብ በማምጣት በአማራ ክልል መንግስት ለየአንዳንዳቸው ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ።

"አርቆ ማየት አልቆ መስራት በሚል መሪ ቃል" የ2018 ዓ.ም የአሻጋሪ ዘላቂ የልማት እቅድ ትውውቅ መድረክ ከመንግስት ሰራተኞች ጋር ተካሄደ።ዳንሻ: መስከረም 19/2018ዓ.ም በአማራ ክልል ...
29/09/2025

"አርቆ ማየት አልቆ መስራት በሚል መሪ ቃል" የ2018 ዓ.ም የአሻጋሪ ዘላቂ የልማት እቅድ ትውውቅ መድረክ ከመንግስት ሰራተኞች ጋር ተካሄደ።

ዳንሻ: መስከረም 19/2018ዓ.ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ እስተዳደር "አርቆ ማየት አልቆ መስራት በሚል መሪ ቃል" የ2017 ዓ.ም የፓርቲና የመንግስት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 ዓ.ም የአሻጋሪ ዘላቂ የልማት እቅድ ትውውቅ መድረክ ከመንግስት ሰራተኞች ጋር ተካሂዷል ።

በመድረኩ በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዱልዋሀብ ማሞ፣የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀፍታሙ ማሩ፣ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች እንዲሁም የመንግስት ሰራተኞች ተገኝተዋል።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር እና የፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የ2017ዓ.ም የእቅድ አፈፃፀም የተከናወኑ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች እንዲሁም የ2018 ዓ.ም የጽ/ቤቶች እቅድ የቀረበ ሲሆን ከተሳታፊ የመንግስት ሰራተኞችጋር ውይይት ተደርጓል ።

ፕሮግራሙ በውይይቱ ተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች በሚመለከታቸው አካላት ምላሽና ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን በ2017 በጀት አመት ከፍተኛ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ሴክተር መስርያ ቤቶችና ቀበሌዎች የእውቅና መርሃግብር በማካዴ ፍጻሜውን አግኝቷል።

"አርቆ ማየት አልቆ መስራት በሚል መሪ ቃል" የ2017 ዓ.ም የፓርቲና የመንግስት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 ዓ.ም የአሻጋሪ ዘላቂ የልማት እቅድ ትውውቅ መድረክ ከመንግስት ሰራተኞች ...
29/09/2025

"አርቆ ማየት አልቆ መስራት በሚል መሪ ቃል" የ2017 ዓ.ም የፓርቲና የመንግስት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 ዓ.ም የአሻጋሪ ዘላቂ የልማት እቅድ ትውውቅ መድረክ ከመንግስት ሰራተኞች ጋር እየተካሄደ ይገኛል።

ዳንሻ: መስከረም 19/2018ዓ.ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ እስተዳደር "አርቆ ማየት አልቆ መስራት በሚል መሪ ቃል" የ2017 ዓ.ም የፓርቲና የመንግስት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2018 ዓ.ም የአሻጋሪ ዘላቂ የልማት እቅድ ትውውቅ መድረክ ከመንግስት ሰራተኞች ጋር እየተካሄደ ይገኛል።

የዳንሻ ከተማ የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር ከ 272 ሺ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለ1,005 ተማሪዎች የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ ዳንሻ፦መስከረም 18/2018 ዓ.ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠ...
28/09/2025

የዳንሻ ከተማ የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር ከ 272 ሺ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለ1,005 ተማሪዎች የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

ዳንሻ፦መስከረም 18/2018 ዓ.ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የዳንሻ ከተማ የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር " ማንም ተማሪ በደብተር እጦት ከትምህርት ገበታ መቅረት የለበትም " በማለት ለ 1,005 ተማሪዎች ከ 272,828 ብር ወጪ በማድረግ የመማርያ ደብተርና እስክርቢቶ ድጋፍ አድርገዋል ።

የቁሳቁስ ድጋፍ በተደረገበት ወቅት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መ/ር አብዱልዋሀብ ማሞ እንዳሉት " በማህበሩ ወጣቶች በተጨባጭ የሚታዩ የቤት ጥገናና እድሳት፣የአረጋውያን እና የአቅመ ደካማ አረጋውያን ድጋፍ እና ልዩ የበጎ ፈቃድ ስራዎች እየሰሩ ይገኛሉ ፤

እሄ ደግሞ ሌሎች ወጣቶች እንደ አርአያነት በመውሰድ የማህበሩ አባል በመሆን በጎ ስራዎች መስራት አለብን " ያሉ ሲሆን " ወላጆች የትምሀርት ቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገላቸው እና መላው ተማሪዎቻችን ጠንከር ያለ ክትትል እና ድጋፍ በማድረግ የወጣቶቹ በጎ ተግባር ወደ ፍሬ ለመቀየር ሁላችንም ሀላፊነት ልንወስድ ይገባናል " ሲሉ አሳስበዋል ።

የዳንሻ ከተማ የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር ሊቀ መንበር አቶ አባስ ጌታቸው " የአቅመ ደካማ አረጋውያን ቤት ለማደስ እና ለመስራት ከጎናችን ሆነው ልዩ ልዩ ድጋፍ ሲያደርጉልን የነበሩ እና አሁንም በውጭ ሀገር ለሚገኙ እና በከተማችን ያሉ ወንድምቻችን ለተማሪዎች የትምሀርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለማድረግ ከጎናችን ለሆኑት ሁሉ በማመስገን ፤
የተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ከማሟላት በተጨማሪ የተማሪዎች የትምሀርት ደረጃ ማሻሻል ጠንካራ ክትትል ያስፈልጋል ብለዋል ።

ድጋፋ የዳንሻ ከተማ የወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር፣ የሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ እና ከትምህርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከሀገር ወዳድ ዲያስፖራው፣ ከግለሰቦች እና ከተለያዩ ተቋማት የተሰባሰበ ሲሆን ለ1,005 ተማሪዎች ሙሉ ደብተርና 2 የእስክርቢቶ ድጋፍ ተደርጓል ።

መድረኩ ለማህበሩ ድጋፍ ላደረጉ ግለሰቦችና ተቋማት የእውቅናና የምስጋና ሰርተፍኬት በመስጠት ተጠናቋል ።

በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የመስቀል ደመራ በአል በድምቀት ተከበረ።ዳንሻ፦መስከረም 17/2018ዓ.ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ...
27/09/2025

በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የመስቀል ደመራ በአል በድምቀት ተከበረ።

ዳንሻ፦መስከረም 17/2018ዓ.ም በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የመስቀል ደመራ በአል በከተማዉ አደባባይ ኃይማኖታዊ ስረዓቱን ጠብቆ በድምቀት ተከብሯል።

በሀይማኖታዊ በአሉ ቅዱስ እፀ መስቀሉን አስመልክቶ ቅኔ፣ትምህርት፣መዝሙር እና የፀሎት መርሐ ግብር ተካሂዷል ።

በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የመስቀል ደመራ በአል በፎቶ :-
27/09/2025

በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የመስቀል ደመራ በአል በፎቶ :-

Address

ዳንሻ
Gondar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dansha Town Communication affairs office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share