Dansha Town Communication affairs office

Dansha Town Communication affairs office በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን የፌስ ቡክ ገፅ

10/09/2025
የሴቶችና ህፃናት፣ጎዶልያስ እና የዳንሻ ሲሲ ማህበር ከማህበረሰቡ በማሰባሰብ 173 ለሚሆኑ ወገኖች ከ928 ሺ ብር በላይ ለአዲስ አመት በአል መዋያ ድጋፍ  አደረገ ዳንሻ ጻጉሜ 05/2017ዓ....
10/09/2025

የሴቶችና ህፃናት፣ጎዶልያስ እና የዳንሻ ሲሲ ማህበር ከማህበረሰቡ በማሰባሰብ 173 ለሚሆኑ ወገኖች ከ928 ሺ ብር በላይ ለአዲስ አመት በአል መዋያ ድጋፍ አደረገ

ዳንሻ ጻጉሜ 05/2017ዓ.ም)በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የሴቶችና ህፃናት ጽ/ቤት፣ የዳንሻ ከተማ ወጣቶች በጎ አድራጎት ማህበር (ጎዶልያስ) እና የዳንሻ ሲሲ ማህበር ከማህበረሰቡ በማሰባሰብ ከ 173 በላይ ለሚሆኑ ወገኖች ለአዲስ አመት በአል መዋያ የሚሆን ከ 928ሺ ብር በላይ የሚገመት በአይነት እና በገንዘብ ድጋፍ አደረጉ።

ድጋፉ በውጭ አገራት የሚኖሩ ዲያስፖራ ወገኖች፣ መንግስታዊ እና የግል ተቋማት ፣ከባለሀብቶች እና ከከተማው ማህበረሰብ የተሰባሰበ ሲሆን ለእያንዳንዱ አባወራ( እማወራ) ሙሉ ልብስ፣ 30ኪ.ግ እህል እና ብር 1,500 እንዲሁም 2 እርድ ከብቶችና 3 ፍየሎች አቅም ለሌላቸው አረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ድጋፍ አድርገዋል ።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በአካቢው ለሚገኙ የፀጥታ አባላት ለአዲስ ዓመት የበዓል እርድ ስጦታ አበረከተዳንሻ:-ጿግሜ 05/2017 ዓ.ም)በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ...
10/09/2025

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በአካቢው ለሚገኙ የፀጥታ አባላት ለአዲስ ዓመት የበዓል እርድ ስጦታ አበረከተ

ዳንሻ:-ጿግሜ 05/2017 ዓ.ም)በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ ከተማ አስተዳደር በአካቢው ለሚገኙ የፀጥታ አባላት ለአዲስ ዓመት የበዓል እርድ ስጦታ አበረከተ።

149 ሺ ብር በላይ ወጭ በማድረግ 9 ፍየል እና 1 ላም የተበረከተ ሲሆን በወረዳው ለሚገኙ የመከላከያ አባላት፣በግዳጅ ላይ ለሚገኙ የፖሊስና የሰላም አስከባሪ አባላት ፣ ለሠላም አስከባሪና ሚሊሾች የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች እና የሀገር ሽማግሌዎች ቦታው ድረስ በመሄድ ስጦታውን አበርክተዋል።

የአዲስ አመት የበአል ግብይት ቁጥጥር እያደረገ መሆኑ የንግድና ገበያ ልማት ጽህፈት ቤት ገለፀ  ዳንሻ:-ጿግሜ 05/2017 ዓ.ም)በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ ከተ...
10/09/2025

የአዲስ አመት የበአል ግብይት ቁጥጥር እያደረገ መሆኑ የንግድና ገበያ ልማት ጽህፈት ቤት ገለፀ

ዳንሻ:-ጿግሜ 05/2017 ዓ.ም)በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን የዳንሻ ከተማ አስተዳደር የንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት የሚውሉ የምግብ ግብአቶች እና የእርድ እንስሳት ግብይት እየተቆጣጠረ መሆኑ ገልጿል ።

የዳንሻ ከተማ አስተዳደር የንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ነጋ ደጀን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት በማስተላለፍ በከተማችን ለአዲስ አመት የሚውሉ የምግብ ግብአቶች እና የእርድ እንስሳት ግብይት ተመጣጣኝ እንደነበር ተናግረዋል ።

በዳንሻ የመንግስት ሰራተኛ የሸማቾች ህ.ስ.ማ ከ5ሺ 810 ሊትር በላይ የምግብ ዘይት እንዲቀርብ በማድረግ እና ለማህበረሰቡ በማሰራጨት የገበያ ማረጋጋት ስራ መሰራቱ ኃላፊው አክለው ገልፀዋል ።

የአዲስ አመት በአል በሰላም እንዲጠናቀቅ  አስፈላጊውን ዝግጅት መደረጉ ዋና ሳጅን ሀፍታሙ ይርጋ ገለፁ ዳንሻ:-ጻጉሜ 05/2017 ዓ.ም)በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳን...
10/09/2025

የአዲስ አመት በአል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጅት መደረጉ ዋና ሳጅን ሀፍታሙ ይርጋ ገለፁ

ዳንሻ:-ጻጉሜ 05/2017 ዓ.ም)በአማራ ክልል በወልቃይት ጠገዴ ስቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ ከተማ አስተዳደር የአዲስ አመት በአል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጅት መደረጉ የዳንሻ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ ዋና ሳጅን ሀፍታሙ ይርጋ ገለፀዋል ።

"ለ2018 ዓ.ም አዲስ አመት የእንኳን አደረሳችሁ!!" መልእክት በማስተላለፍ "የአዲስ አመት በአል በሰላም እንዲጠናቀቅ የተቀናጀ የፀጥታ ኃይል ስምሪት የፀጥታ ዝግጅት መጠናቀቁ በመግለፅ የአዲስ አመት በአል እስኪያልፍ የተሽከርካሪ ጫና ለመቀነስ የሞተር ሳይክልና የባጃጅ ተሽከርካሪ መከልከላቸውን አክለው ገልፀዋል።

ማህበረሰባችን እንደሁልጊዜው ከፀጥታ አካላት ጎን በመሆን በአሉ በሰላም እንዲከበር የበኩሉ እንዲወጣ አሳስበዋል ።

10/09/2025
የመልካም ምኞት መግለጫ እንኳን ከአሮጌው ዘመን 2017ዓ/ም ወደ አዲሱ ዓመት 2018 ዓ/ም  በሰላም አሸጋግረን !አዲሱ ዓመት 2018ዓ/ም:-🌼የሰላም🌻የደሰታ❤የፍቅር🌼የይቅርታ🌼የጤና ይሁንላች...
10/09/2025

የመልካም ምኞት መግለጫ
እንኳን ከአሮጌው ዘመን 2017ዓ/ም ወደ አዲሱ ዓመት 2018 ዓ/ም በሰላም አሸጋግረን !
አዲሱ ዓመት 2018ዓ/ም:-
🌼የሰላም
🌻የደሰታ
❤የፍቅር
🌼የይቅርታ
🌼የጤና ይሁንላችሁ ይሁንልን!
🌼አዲሱ ዓመት 2018ዓ/ም
🌻ከትችት ወጥተን በተግባር የምንደጋገፍበት!
🌼ጥቃቅን ልዩነትን በጋራ የምንቀርፍበት
🌼ምርታማ የምንሆንበት ዓመት
🌼አካባቢያችን ብሎም አገራችን የሰላም ተምሳሌት የምትሆንበት ዘመን እንዲሆንል
❤ማንነታችን የምናፀናበት
🌼አገራቀፍ አብሮነት ተሻግረን አለማቀፍ አብሮነትን የምናረጋግጥበት ዘመን
🌼የሁሉም ማህበረስብ ተጠቃሚነት የምናረጋግጥበት ዘመን
✈️ የ2042ዓ/ም ረዥሙ ርዕያችን የመጀመሪያው ዓመት በውጤት የምንቋጭበት ዓመት ያድርግልን! እያለ የዳንንሻ ከተማ አስተዳደር ህዝብና መንግስት መልካም ምኞቱን ይገልፃል!
🌼🌼እንቁጣጣሽ🌼🌼
🌼🌼 2018 ዓ/ም🌼🌼
5/13/2017
የዳንሻ ከተማ አሰተዳደር

09/09/2025

Big shout out to my newest top fans! Getachew Abrha, Meresa Abrha, ብርጭቆ የጠገዴዋ, Mamay Gidey, Amare Werku, Enyew Fentahun, Kì Ăbïnhó Dejen, Nega Dejen, Gizatey Dagnew, Tshu Fey Man, Daniel Fentahun, Fantahun Adugna Mekonen, Goitom Alemaw, Mekete Fenta Kebede, Ephrem Ashagre, Frnus Abohey

09/09/2025

ሰባቱ የጉባ ብስራቶች

በሚቀጥሉት አምስት እና ስድስት ዓመታት የሚተገበሩ ሰባቱ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ምንድን ናቸው።

እነዚህ ፕሮጀክቶች ከ30 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚፈልጉ ናቸው።

•~•~•
🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊
•~•~•

"የጎርጎራ ቃልኪዳናችን፤ ለዘላቂ ሰላም እና ለሁለንተናዊ ብልጽግናችን"
•~•~•
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የፓርቲያችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ትዊተር :- twitter.com/AppAmhara?s=09
ዩቲዩብ :- youtube.com/channel/UCxQ5MOnm-YH514Qdta0Kysg
ቴሌግራም:- t.me/amharaapp
ቲክቶክ፡- tiktok.com/

Address

ዳንሻ
Gondar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dansha Town Communication affairs office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share