ገጠመኝ - ትዝብት/Giv

ገጠመኝ - ትዝብት/Giv በህይወት ዘመንዎ መልካም እና መጥፎ የሚሉትን ገጠመኝዎን ያጋ

04/11/2025

ይኼንን ጽሑፍ ቁጭ ብለህ እያነበብህ ያለኸው በዚህ ሰዓት ምሥራቅ አርሲ ገጠር ውስጥ ስላልተገኘህ ብቻ ነው:: በዚህች ቅጽበት በሥጋት ውስጥ ሆነው "ከአሁን አሁን ምን ይመጣብን ይሆን?" እያሉ ያሉ የኦሮሚያ ምእመናን ቁጥራቸው ብዙ ነው:: ከቀናት በፊት የተገደሉትን ተናግረን ሳናበቃ አሁን ደግሞ ሌላ ቦታ አምስት እንደተገደሉ እየሰማን ነው::

ሰሞኑን ከሁለት ሺህ ዓመታት በፊት ሔሮድስ ስላሳደዳት እመቤታችን "ሰቆቃወ ድንግል" እያልን እያዘንን ነው:: ከሰይፍ ልጅዋን ማስጣል ያልቻለች የአርሲዋን እናትስ እንዴት ዝም እንበላት? ይህንን የማያቆም ሞት ዜና ሰምተን ወደ ጉሮሮአችን የሚወርድ ምግብና መጠጥ የምንተኛውም እንቅልፍ የለም:: የእነርሱ ሞት የእኛ ሞት ነው:: የእነርሱ መቁሰል የእኛ ቁስል ነው:: የቦታ ለውጥ እንጂ በእነርሱ የደረሰው በእኛም ሊደርስ ይችላል::

ቤተ ክርስቲያን ምሕላ እንድታውጅ ፣ ለተሠዉት ተገቢውን ክብር እና ጸሎተ ፍትሐት እንድታደርግ እንጠብቃለን:: ቤተ ክርስቲያን በየትኛውም ቦታ የንጹሐን ደም ዳግመኛ እንዳይፈስስ እንደ ራሔል ዕንባዋን የምትረጭበት ጊዜ አሁን ነው::

የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ትኩረት ያልሠጠውን ችግር ሌላ አካል ሊጨነቅበት አይችልም:: ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን በአስተዳደራዊ መዋቅርዋ መንግሥት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ በሙሉ ትኩረት የምትሠራበት ጊዜም አሁን ነው:: ቅዱስ ሲኖዶስ በዚህ ዓይነት ጊዜ የሚያሳየው ምላሽ ከሌለ ሌላ ቀን ቢጣራ የማይሰማውን ቤተ ክርስቲያን አልባ ክርስቲያን በራሱ ላይ ይፈጥራል:: ሐዋርያዊትዋ ቤተ ክርስቲያንም በክህነት የማትመራ የመሆን አደጋ ይገጥማታል:: ክህነት ከሌለ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንም ምሥጢራትም የሉም::

ኦርቶዶክሳውያን ምእመናንም ይህንን ጊዜ ለመካሰስ ፣ አባቶችን ለመሳደብ ፣ አንዱ ሌላውን ለማስጠቆርና ለመናቆር ሳይሆን ለጸሎት ለምሕላና ለሰብአዊ ሥራና መሬት ላይ ቢወርዱ ችግሮችን የሚፈቱ ዘላቂ መፍትሔዎች ላይ በትብብር ለመሥራት ምክንያት ብናደርገው የተሻለ ነገር ማምጣት እንችላለን::

የሌላ እምነት ተከታዮች ሆነው ይህ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያውያን ላይ የተቃጣ ጥቃት ብለው ጉዳዩን በተቋምም በግልም ያወገዙ ሰዎችን እናከብራለን:: "ይበላችሁ" ብለው የተሳለቁትን እና በክፉ ቀን ክፋታቸውን ላሳዩን ደግሞ እውነተኛ ማንነታቸውን ስላሳዩን እያመሰገንን "አቤቱ፥ በኢየሩሳሌም ቀን የኤዶምን ልጆች አስብ፦ “እስከ መሠረትዋ ድረስ አፍርሱ አፍርሱ፡” ያሉአትን" ብለን ለሰማያዊው ዳኛ ሠጥተናቸዋል:: መዝ. 137:7



04/11/2025

💔"በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት መርቲ ወረዳ በሚገኘው ጋዶ ቀበሌ የሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን በትናንትናው ዕለት ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት በኋላ 5 ምእመናን የእርሻ ሥራቸውን አጠናቀው ምሳቸውን እየበሉ ባሉበት ጊዜ በታጠቂዎች በተከፈተባቸው የተኩስ ጥቃት መገደላቸውን ለማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ የደረሰን መረጃ ያሳያል፡፡

በተጨማሪም ከተገደሉት ውጪ ሌሎች 3 ምእመናን ደግሞ ታግተው የተወሰዱ ሲሆን እስከ አሁንም የደረሰቡት እንዲሁም ያሉበት ሁኔታ አይታወቅም ተብሏል፡፡

ይህን የምእመናኑ የግድያ እና የአፈና ተግባር ከሰሞኑ በሀገረ ስብከቱ እንደነበረው ሁሉ ተባብሶ የቀጠለ መሆኑን በመረጃው ተነግሯል፡፡

በተለይም ላለፉት ሁለት ዓመታት የገጠር ቀበሌው እና በውስጡ የሚኖሩ ምእመናን ከስጋት ነጻ ሆነው ኖረው አያውቁም፡፡

የተገደሉት ምእመናን ሥርዓተ ቀብራቸው በአቦምሳ ከተማ በሚገኘው በደብረ ገነት ትንሣኤ ብርሃን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን እንደተፈጸመ በመረጃው ተመላክቷል፡፡

Mahibere Kidusan Broadcast Service - ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት

05/04/2025

Address

Gondar-Ethiopia
Gondar
96

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ገጠመኝ - ትዝብት/Giv posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category