Quara Communication Affairs Office

Quara Communication Affairs Office ትክክለኛ መረጃን ለአገራችንና ለህዝባችን ተጠቃሚነት ስንል ተደራሽ እናደርጋለን!!

የቋራ ወረዳ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ ዓመት 43ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ።ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 29/2018 ዓ.ም (የቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት) በጉባኤው ዝርዝር ...
09/10/2025

የቋራ ወረዳ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ ዓመት 43ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ።

ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 29/2018 ዓ.ም (የቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት) በጉባኤው ዝርዝር አጀንዳዎች እንዳሉ የገለፁት የቋራ ወረዳ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኑርሁሴን ማህመድ የወረዳ መስተዳደሩን የ2018 በጀት አመት ዕቅድ መርምሮ ማፅደቅ፣ የ2017 ለ2018 ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት መርምሮ ማፅደቅ፣ የ2018 በጀት ዓመት የወረዳውን የምክር ቤት በጀት መርምሮ ማፅደቅ፣ ሹመት ማንሳትና ሹመት መስጠት በሚሉ አጀንዳዎች ጉባኤው እንደሚካሄድ አብራርተዋል።

የቋራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸዉ በጉባኤዉ ተገኝተዉ የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት እንደገለፁት የቋራ ወረዳ ምክር ቤት የህዝብ መስታዉት ህዝብና መንግስትን የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት ሲባል ለህዝብ የሚደርሱ ስራዎችን በዚህ ጉባኤ ለማስታዋወቅ እና ተግባራትን ለመገምገም ከፈፃሚ አካላት የሚሾልኩ ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል ተጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በመግለፅ መድረኩ በይፋ የተከፈተ መሆኑን ተናግረዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ የሰላም አስከባሪና የፖሊስ አባላት የአቅም ግንባታ የኃይል ማጠናከሪያ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 28/2018 ዓ.ም (ቋራ ወረዳ የመንግስ...
08/10/2025

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ የሰላም አስከባሪና የፖሊስ አባላት የአቅም ግንባታ የኃይል ማጠናከሪያ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።

ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 28/2018 ዓ.ም (ቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን) በስልጠናው የመክፈቻ ፕሮግራም ንግግር ያደረጉት የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸው የፀጥታ መዋቅሩን አቅም መገንባትና የኃይል ማጠናከሪያ ስልጠና መስጠቱ የሚገጥሙነን የፀጥታ ችግር ፈጥኖ ለመፍታት አስቻይ ሁኔታን ይፈጥራል ብለዋል።

የወረዳውን ሰላም ማረጋገጥ የህዝባችንን እንግልትና ስቃይ እንዲሁም ግድያ የሚያስቀር ወረዳው እንደ ወረዳ መልማት ባለበት ልክ እንዲለማ ለማስቻል የፀጥታ ማዋቅሩን አቅም በመገንባት የመፈፀም አቅሙን በማሳደፍ ሁለንተናዊ የህዝባችንን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል።

የክብር እንግዳ የሆኑት የሃገር መከላከያ ሰራዊት አመራር ኮለኔል ታከለ አለሙ የፀጥታ መዋቅሩ አቅሙን በመገንባት የመፈፀም ሞራሉን ከፍ በማድረግ የአካባቢውን ሰላም ማረጋገጥ አለበት ብለዋል።

ለዚህም ስልጠናውን ያለምንም መንጠባጠብ መውሰድና መፈፀም ያስፈልጋል ብለዋል።

በስልጠና ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ የምዕራብ ጎንደር ዞን ወጣቶችና ስፓርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛት ዝጋለ፣ የዞኑ የትራንስፓርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉአለም ታደሰ፣ የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸው፣ የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ማሬ እና ሌሎች የወረዳና የዞን የፀጥታ አመራሮች ተገኝተዋል።

የቋራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የመስኖ ልማት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ።በምዕራብ ጎንደር ዞን የቋራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን በወረዳው ውጤታማ ስራዎችን ለማከ...
07/10/2025

የቋራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የመስኖ ልማት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ።

በምዕራብ ጎንደር ዞን የቋራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን በወረዳው ውጤታማ ስራዎችን ለማከናወን የንቅናቄ መድረክ በመፍጠር ወደ ትግባር መግባታቸውን የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ማስረሻ አስፋው ገልፃዋል።

አሁን ላይ የንቅናቄ መድረኩን ወደ ተግባር በመቀየር በመስኖ የሽንኩርት ልማትን በዚህ መልኩ የተጀመረ መሆኑ አንስተዋል።

ሌሎች ወደ ተግባር ያልገባችሁ ቀበሌዎች እንዲሁም አርሳአደሮች ወደ ተግባር በመግባት ምርትና ምርታማነትን በመስኖ አስፍቶ መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል።

መስከረም 27/2018 ዓ.ም
የቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት

ከ 900 ሺህ በላይ የሚሆኑ የተለያዩ የጉልበት ሠራተኞችን እንደሚፈልግ የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር ጥሪ አቀረበ፡፡ ገንዳ ውኃ: መስከረም 27/2018 ዓ.ም በአማራ ክልል ሰሊጥ በስፋት ...
07/10/2025

ከ 900 ሺህ በላይ የሚሆኑ የተለያዩ የጉልበት ሠራተኞችን እንደሚፈልግ የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር ጥሪ አቀረበ፡፡

ገንዳ ውኃ: መስከረም 27/2018 ዓ.ም በአማራ ክልል ሰሊጥ በስፋት ከሚመረትባቸው አካባቢዎች መካከል የምዕራብ ጎንደር ዞን ቀዳሚው ነው፡፡

በዞኑ የሰሊጥ ምርት እና የሌሎች ሰብሎች ሥብሠባ ተጀምሯል፡፡

የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዳርጌ ጌጡ በሰጡት መግለጫ ፤በዞኑ የኤክስፖርት እና የኢንዱስትሪ ግብዓትን ጨምሮ የምግብ ነክ ሰብሎችም በስፋት መለማታቸውን ጠቁመዋል።

በተያዘው የመኸር ምርት ዘመን 529 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች ለማልማት ታቅዶ እየተስራ ሲሆን በዚህም ከ12.6 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

በዞኑ የለማውን የሰሊጥ ሰብል በወቅቱ ለመሰብሰብ ከ 900 ሺህ በላይ የጉልበት ሠራተኞች በአፋጣኝ ወደ ምዕራብ ጎንደር ዞን እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ምዕራብ ጎንደር ዞን በቅባት ሰብሎች ከአማራ ክልል አልፎ ለሀገር ትልቅ አስተዋጽኦ ያለው አካባቢ በመሆኑ ርብርብ በማድረግ ሰብሉ በወቅቱ ሊሰበሰብ ይገባል ነው ያሉት ፡፡

በየዓመቱ በስፋት የሚመረተውን ምርት ለመሠብሠብ የጉልበት ሠራተኛ ጥሪ እንደሚቀርብም ገልጸዋል፡፡ የሠራተኛ እጥረትን በሜካናይዜሽን መፍታት ካልተቻለ ችግሩን መቅረፍ እንደማይቻል ነው የተናገሩት፡፡

ወደፊት ችግሩን ለመፍታት የክልሉ እና የፌዴራል መንግሥት ለምዕራብ ጎንደር ዞን ታላላቅ የሜካናይዜሽን ግብዓቶችን ሊሰጡት ይገባል ነው ያሉት፡፡

አርሶ አደሮች እና ባለሃብቶች በሠራተኛ እጥረት ምክንያት ምርታቸው ሊበላሽ እንደሚችል እየገለጹ መኾናቸውንም ገልጸዋል፡፡ በዞኑ ከ900 ሺህ በላይ ሠራተኞችን እንደሚፈልጉም አስታውቀዋል፡፡

በዚህም በዞኑ መተማ፣ቋራ፣ ምዕራብ አርማጭሆ እና በሌሎችም ያሉ አርሶአደር እና ባለሃብቶች በስፋት ያመረቱትን ምርት ለማሠብሠብ ሠራተኞችን በስፋት እየፈለጉ ነው።

በሚፈለገው ልክ ሠራተኛ ወደ አካባቢው ባለመምጣቱ ችግር ላይ ስለመሆናቸው አስተያየታቸውን የሠጡ ባለሃብቶች ገልጸዋል

ምርቱ ጊዜው ሳያልፍ እንዲሠበሠብ እና ወቅቱን ባልጠበቀ ዝናብ እንዳይበላሽ በየአካባቢው ያሉ መሪዎች ሠራተኞችን አስተባብረው እንዲልኩላቸውም ጠይቀዋል፡፡

ሁሉም አካል ሰብሉ እንዲሠበሠብ ተባባሪ መኾን አለበት ነው ያሉት፡፡ ሁሉም እጅ እና ጓንት ኾኖ በመሥራት ሠራተኞች ወደ ምዕራብ ጎንደር ዞን እና ሌሎች ሰሊጥ አምራች ወደ ሆኑ አካባቢዎች እንዲገቡ ማድረግ አለበት ብለዋል፡፡

ሰሊጥ ጊዜ የማይሰጥ ሰብል መኾኑን የተናገሩት አልሚዎቹ በትክክለኛው ጊዜ መሠብሠብ ካልተቻለ ምርቱ እንደሚፈስ እና ድካምን መና እንደሚያስቀር ነው የገለጹት፡፡

ሠራተኞቹ ወደ ምዕራብ ጎንደር ዞን ሲመጡ በየደረጀው ያለ አካላት ከስጋት ነፃ ሆነው በተፈጠረው የሥራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ፡፡

የደረሰውን ሰሊጥ በጊዜ ለመሠብሠብ ሠራተኞች ወደ አካባቢው በስፋት እንዲገቡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ዞኖች በስፋት ሠራተኛ እንዲልኩላቸውም ጠይቀዋል፡፡

ሠራተኞች በስፋት እንዲገቡ የሁሉም ትብብር እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል፡፡

የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰሊጥ እንዳይባክን ርብርብ ማድረግ ይገባል ያሉት አቶ አንዳርጌ፤ባለሃብቶች እና የዞኑ አሥተዳደር የጉልበት ሠራተኞችን ለመቀበል ዝግጅት መጨረሳቸውንም ተናግረዋል፡፡

የምግብ፣ የመጠለያ፣ የውኃ፣ የመድኃኒት እና ሌሎች አቅርቦቶች ዝግጁ መደረጋቸውንም ጠቁመው፤ ሠራተኞች በፍጥነት ወደ ዞኑ እንዲገቡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

📷 West gondar communication/ምዕራብ ጎንደር ዞን ኮሙኒኬሽን

የሁልጊዜ በጎ አድራጊው ወንድማችን አድጎ/አዲር መለሰ ከእስራኤል የበጋ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ምክንያት በማድረግ ረዳት ለሌላቸው ተማሪዎች 100 ደርዘን ደብተርና 15 ፓኮ እስክርቢቶ ድጋፍ ...
07/10/2025

የሁልጊዜ በጎ አድራጊው ወንድማችን አድጎ/አዲር መለሰ ከእስራኤል የበጋ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ምክንያት በማድረግ ረዳት ለሌላቸው ተማሪዎች 100 ደርዘን ደብተርና 15 ፓኮ እስክርቢቶ ድጋፍ አደረገ።

ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 27/2018 ዓ.ም (የቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት) በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ምክንያት በማድረግ በተደጋጋሚ ድጋፍ በማድረግ የሚታወቀው ወንድም አድጎ/አዲር መለሰ ከእስራኤል ረዳትና ለሌላቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳስቁስ 100 ደርዘን ደብተር እና 15 ፓኮ እስክርቢቶ በገንዘቢ ሲተመን 82ሺ 500 መቶ ብር ወጭ በማድረግ ድጋፍ አድርገዋል።

ድጋፉን በተወካያቸው በወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ አብነት ደሴ ለበጋ በጎ ፈቀድ አገልግሎት አሰጣጥ አስተባባሪ ለወረዳው ወጣቶችና ስፓርት ጽ/ቤት ኃላፊ ለአቶ አድማሱ ውቤ ርክክብ አድርገዋል።

ወንድማችን አድጎ/አዲር መለሰ በተከታታይ አመታት ለአቅመ ደካሞች ማዕድ በማጋራት በቅርቡ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለአቅመ ደካሞች ቤት መስሪያ 46ሺ 720 ብር ድጋፍ በማድረግ ለወገን ደራሽ ወገን መሆኑን በጎ አድራጊነታቸውን በተግባር እያረጋገጡ ያሉ ወንድማችን ናቸው።

ይህ ወንድማችን አሁንም ለወገኔ ቀጣይነት ያለው ድጋፌን አደርጋለሁ በማለት 82ሺ 500 ብር ወጭ በማድረግ ለረጅ አልባ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል።

ኦላይን ምዝገባን በማጠናከር ወጣቶችን በተለያዩ የስራ መስክ ማሰማራት እንደሚገባ ተገለፀ።ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 27/2018 ዓ.ም (ቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት) በምዕራብ ጎንደ...
07/10/2025

ኦላይን ምዝገባን በማጠናከር ወጣቶችን በተለያዩ የስራ መስክ ማሰማራት እንደሚገባ ተገለፀ።

ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 27/2018 ዓ.ም (ቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት) በምዕራብ ጎንደር ዞን የቋራ ወረዳ ስራና ስልጠና ጽ/ቤት በ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ዙሪያ ግምገማ ተካሄዷል።

በውይይቱ የምዕራብ ጎንደር ዞን ወጣቶችና ስፓርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛት ዝጋለ፣ የዞኑ ትራንስፓርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉአለም ታደሰ፣ የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸው፣ የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ማሬና ሌሎች የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።

ውይይቱ በወረዳው ስራና ስልጠና ጽ/ቤት በ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ተግባራትና በተቋሙ የአሰራር ሂደት ጋር በተያያዘ ውይይት ተካሄዷል።

ስራና ስልጠና ጽ/ቤት የወጣቶችን የስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች በስፋት ለመፈፀም የኦላይን ምዝገባን በማስፋት ወጣቶችን በተለያዩ የስራ መስክ እንዲሰማሩ ትልቁን ድርሻ መውሰድ መቻል እንዳለበት ተገልፃዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ የታደሰ የጅኦስትራቴጅያዊ ቁመና በሁሉም ኢትዮዽያዉያን የጋራ  ትጋት በሚል መሪ ቃል ከገለጉ ከተማ ጠቅላላ የመንግስት ሰራተኞች ጋር ዉይይት  ተካሄደ።ቋራ/ገለ...
06/10/2025

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ የታደሰ የጅኦስትራቴጅያዊ ቁመና በሁሉም ኢትዮዽያዉያን የጋራ ትጋት በሚል መሪ ቃል ከገለጉ ከተማ ጠቅላላ የመንግስት ሰራተኞች ጋር ዉይይት ተካሄደ።

ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 26/2018 ዓ.ም (ቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት) የቋራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸዉ በክልል እንደ ወረዳም የተከሰተዉ የሰላም እጦት ችግር ለመፍታት ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተው የአገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማረጋገጥ የመንግስት ሰራተኛዉን በመጠቀም እያጋጠመን ያለዉን ችግር ለመቅረፍ የታደሰ የጅኦስትራቴጅዊ ቁመና በመያዝ በሁሉም ኢትዮጵያን የጋራ ትጋት ለመፍጠር የሚካሄድ መድረክ መሆኑን በመክፈቻ ንግግራቸው አንስተዋል።

የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ማሬ የመወያያ ሰነዱን ባቀረቡበት ወቅት እንዳብራሩት የሀገር ብሔራዊ ጥቅምና የጅኦስትራቴጅያዊ ቁመና ምን እምደሚመስል የኢትዮዽያዊ ብሔራዊ ጥቅም ምንነት የብሔራዊ ጥቅም ዋነኛ ፈተናዎች ቁልፍ ሁኔታዎች የብሔራዊ ጥቅምን የሚያረጋግጥ የድፕሎማሲ አቅም መገንባት የመንግሥት ተቋማት ሚና የመሳሰሉ ነጥቦች በዝርዝር እያነሱ አብራርተዋል።

የዉይይቱ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት አገራዊ ለዉጡ እዉን እንዳይሆን የተረዱ አካላት የዉሸት ትርክትን በህዝቡ ላይ የሚጭኑ አካላት በጥቅሉ አገሪቱ እንደ ሀገር እንዳትቀጥል የሚፈልጉ አካላት አሁን ላይ ላለንበት ቀዉስ ግንባር ቀደም ተዋናዮች ናቸዉ ብለዋል።

የዉይይቱ ተሳታፊዎች አክለዉም አገራችን ኢትዮዽያ የረጅም አመታት ታሪክ አይበገሬ አገር ወዳድ ህዝብ ማራኪ የሆነ ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ ብዙ ብሄሮች ብሄረሰቦች፣ ብዙ የህዝብ ቁጥር እና ብዙ የተፈጥሮ ሃብት ያላት አገር በመሆኗ ይህን ሁሉ ፀጋዎች እንዳትጠቀም ባዳና ባንዳዎች እረፍት እየነሷት ነዉ በማለት ገልፀዋል።

የምዕራብ ጎንደር ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛት ዝጋለ ዉይይትን በመሩበት ወቅት እንደተናገሩት የሀገራችንን እድገትና ብልፅግና የማይፈልጉ አገራት በባንዳ ታዝለዉ ገብተዉ እረፍት እየነሱን ያሉት ብለዉ ካነሷቸዉ ነጥቦች ዉስጥ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በመሆኗ ከብዙ አፍሪካ አገራት ጋር የምትዋሰን የዉሃ ፖለቲካ መሪ ማለትም የአባይ ወንዝ መነሻ በመሆኗ የብዙ ተፈጥሮ ሃብት ባለቤት በመሆኗ በስንዴ እርዳታ ተሸፍና እንድትኖር የረጅም ጊዜ ፍላጎታቸዉ በመሆኑ ነዉ በማለት አፅንኦት ሰጥተዉ ተንትነዋል።

አቶ ግዛት በማከልም ባዳን አዝሎ የሚመጣዉ ባንዳ አገራችን የምታነሳዉንና የምታራምደዉን ፖሊሲዎች በተቃራኒ ጎራ በመሰለፍ ህዝብና አገር እንዳይረጋጋ በርትተዉ እየሰሩ መሆኑን አስገንዝበዉ በሁለንተናዊ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ ላይ ትኩረት ሰጥተን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።

የቋራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸዉ ውይይቱን በመሩበት ወቅት እንዳሉት የሀገራዊ ጥንካሬያችንና ድክመታችን የሁላችንም ድምር ዉጤት ነዉ ካሉ በኋላ ዛሬ በዚህ መድረክ የቀረበዉ መወያያ ሰነድ እጅግ አስፈላጊነት እያንዳንዱ ዜጋ የብሔራዊ ጥቅምን ቢረዳ ኑሮ የሰላም መቃወስ ዉስጥ አንገባም ነበር ብለዋል።

ዋና አስተዳዳሪ በመቀጠልም በአገራዊ ጉዳይ ላይ የማይደራደር ዜጋ ማፍራት ለነገ የማይባል ስራ ነዉ አገራችንን ኋላቀር ያደረግናት እኛ ነን የፖለቲካ ባህላችንን በማዘመን በግጭትና ጦርነት የሚፈታ የህዝብ ጥያቄ አለመኖሩንና አሰባሳቢ ትረክቶችን ማዳበርና ማስፋት ያስፈልጋል በማለት በስፋት ገልፀዋል።

አቶ አንዳርጋቸዉ ማሬ የቋራ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ በበኩላቸዉ እንዳብራሩት ለአንድ አገር ቋሚ ወዳጅ ቋሚ ጠላት የለም ብሔራዊ ጥቅም እስከተከበረ ድረስ በሀገራችን ጉዳይ ተመሳሳይ አቋምን በመያዝ ብሔራዊ ጥቅሟን ያስከበረች አገር መመስረት ይገባል ብለዋል።

ቋራ ወረዳ የሰሊጥ ሰብል አሰባሰብ ስራ አሁናዊ ገፅታ በከፊል!!       መስከረም 26/2018 ዓ.ም(ቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት)
06/10/2025

ቋራ ወረዳ የሰሊጥ ሰብል አሰባሰብ ስራ አሁናዊ ገፅታ በከፊል!!

መስከረም 26/2018 ዓ.ም
(ቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት)

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ "የታደሰ የጅኦስትራቴጅያዊ ቁመና በሁሉም ኢትዮጵያዊያን የጋራ ትጋት" በሚል መሪ ቃል ከገለጉ ከተማ የጠቅላላ የመንግስት ሰራተኞች ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው...
06/10/2025

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ "የታደሰ የጅኦስትራቴጅያዊ ቁመና በሁሉም ኢትዮጵያዊያን የጋራ ትጋት" በሚል መሪ ቃል ከገለጉ ከተማ የጠቅላላ የመንግስት ሰራተኞች ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው።

ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 26/2018 ዓ.ም (ቋራ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት) በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸው የታደሰ ጅኦስትራቴጅያዊ ቁመና በሃገራችን የጋራ ትጋት ለመፍጠር እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆነች ሃገር ለመገንባት በተመሳሳይ የጋራ ትርክትን በብሄራዊ ጥቅም ላይ ለመገንባት የጋራ እርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል።

በተለይ የመንግስት ተቋማት ስቪል ሰርቫንት የተሳለጠ አገልግሎትን በመስጠት የህዝባችንን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከስር ከስር በመፍታት ሃገር አሻጋሪ ስራዎችን መስራት ይገባል ብለዋል።

በውይይቱ የምዕራብ ጎንደር ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛት ዝጋለ፣ የዞኑ ትራንስፓርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉአለም ታደሰ የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸው፣ የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ማሬ፣ የብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ፀሃይወርቅ ተስፋየ እና ሌሎች የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ ከሚኒ ካቢኔ አባላትና ከወረዳው የፓሊስ ጽ/ቤት የፀጥታ አመራሮች ጋር ውይይት ተካሄዷል።ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 23/2018 ዓ.ም በው...
03/10/2025

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ በወቅታዊ የፀጥታ ጉዳይ ከሚኒ ካቢኔ አባላትና ከወረዳው የፓሊስ ጽ/ቤት የፀጥታ አመራሮች ጋር ውይይት ተካሄዷል።

ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 23/2018 ዓ.ም በውይይቱ የምዕራብ ጎንደር ዞን ወጣቶችና ስፓርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛት ዝጋለ፣ የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸው፣ የዞኑ ትራንስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉአለም ታደሰ የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ፀሃይወርቅ ተስፋየ እና ሌሎች የወረዳ አመራሮች ተገኝተዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን የቋራ ወረዳ መንገድ ትራንስፖርት ጽ/ቤት " አርቆ ማየት አልቆ መስራት" በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት አመት እቅድ ትውውቅ እና የ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገ...
02/10/2025

በምዕራብ ጎንደር ዞን የቋራ ወረዳ መንገድ ትራንስፖርት ጽ/ቤት " አርቆ ማየት አልቆ መስራት" በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት አመት እቅድ ትውውቅ እና የ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ።

ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 22/2018 ዓ.ም (ቋራ የመንግስት ኮሙኒኬሽን) የምዕራብ ጎንደር ዞን የትራንስፖርት መምሪያ ዋና ኃላፊ አቶ ሙሉዓለም ታደሰ በመድረኩ ላይ ተገኝተዉ ሃሳብ እንደሰጡት በባጃጅ ስምሪት ተግባራት ዙሪያ በአንዳንድ ተሽከርካሪዎች የህዝብ ቅሬታ እየተነሳ መሆኑን አንስተው መርሃ ግብር የሌላቸዉ መኪኖች በወረዳዉ እየሰሩ እንደሚገኙ ገልፃዋል።
በመሆኑም የተሽከርካሪ ጉዳይ በጥብቅ መታየት እንዳለበት እና የከተማው የመነሃሪያ የመብራት ዝርጋታና የፅዳት ጉድለት መስተካከል መቻል እንዳለበትም ጠቅሰዋል።

አቶ ሙሉዓለም አያይዘዉም በቀጣይ ሁሉም የተቋሙ አገልግሎት ሰጭ ባለሙያዎች ህገ ወጥ አስራርን መቆጣጠርና ጥቆማ መስጠት እንዳለበት የመረጃ ልዉውጥና ግንኙነት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትና የተቋሙ እቅድ ተዋረዱን ጠብቆ መታቀድ እንዳለበት በአጠቃላይ ከባለፈዉ አመት አፈፃፀም የተሻለ እንደወረዳ ለዉጥ አስተግባሪ ስራዎች መፈፀም እንዳለባቸዉና ለህዝብ ተደራሽ የሆነ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸዉ አሳስበዋል።

የቋራ ወረዳ መንገድ ትራንስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንድሙ አለባቸዉ እንደተናገሩት የ2018 ዓ.ም በጀት አመት የእቅድ ትዉውቅና የበጀት አመቱ የመጀመሪያ ሩብ አመት አፈፃፀም እንደተቋም ጥሩና አመርቂ ስራዎች የተሰሩ መሆኑን አንስተዉ ጥንካሬያችንን አስቀጥለን በድክመት የታዩትን በቀጣይ የህዝባችንን የልማት ጥያቄ የሚፈቱ ስራዎችን መስራት ይጠብቅብናል ብለዋል።

የመድረኩ ታዳሚዎች የፅህፈት ቤት ባለሙያዎች የድርሻቸዉ እንዲወጡ እንደ ተቋም ያነሷቸዉ ሀሳቦች ለስራቸዉ እንቅፋት የሆኑ ጉዳዮችን አንስተዉ በቀጣይ ስራቸዉ ግን ከባለፈዉ አመት የበለጠ ማነኛዉም ሰራዊት ለተግባራት ግንባር ቀደም ሁነን በመገኘት ለህዝባቸዉ አገለግሎት መስጠት እንዳለባቸዉ ጠቅሰው ከመሰረተ ልማት አኳያ እንደመነሃሪያ መሰል ያልተሟሉ ብዙ ቁሳቁሶችን የዞን መምሪያዉና የወረዳ አመራሮች ድጋፍና ክትትል እንዲያደርጉላቸዉ አሳስበዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የ2017 ለ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የማጠቃለያ ሪፖርት ግምገማና የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎት እቅድ ትዉውቅ መድ...
01/10/2025

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የ2017 ለ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የማጠቃለያ ሪፖርት ግምገማና የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎት እቅድ ትዉውቅ መድረክ ተካሄደ።

ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 21/2018 ዓ.ም (ቋራ የመንግስት ኮሙኒኬሽን) የቋራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ ተገኝተዉ እንደተናገሩት በጎ ፈቃድ ሰጭ ልዩ ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በተለያየ የበጎ ፈቃድ መስክ ተሰማርተዉ ብዙ በጎ ሰዉ ተኮር ስራዎችን ሲያከናዉኑ ለቆዩ የምስጋና አቅርበዉ የዜጎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በክረምት ብቻ ተወስኖ የሚቀር ሳይሆን የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎት በቀጣይ የሚጀመር መሆኑን ገለፀዋል።

የቋራ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት ተወካይ ኃላፊ አቶ አማረ ይላቅ የ2017 ለ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አሰጣጥ የማጠቃለያ ሪፖርት ሲያቀርቡ እንደገለፁት የክረምት ወራት ተግባራትን በተገቢው መንገድ መስራት በመቻሉ ከ38 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስት ወጭን ማስቀረት መቻሉን አብራርተዉ በእነዚህ ተግባራት ላይ ሲሳተፉ የቆዩ አካላት የሽኝት ፕሮግራም የተዘጋጀ መሆኑና በበጎ በፈቃደኝነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱና ተሳትፎ ላሳዩ አመራሮች ለከተማችን ነዋሪዎች ነጋዴዎች ለወጣቶች የማበረታቻ ሽልማት እንደሚደረግ አብራረተዋል።

የቋራ ወረዳ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት የወጣቶች ጉዳይ ማካተት ተወካይ ቡድን መሪ የ2018 ዓ.ም የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎት እቅድ ትዉውቅ በዝርዝር አቅርበዋል።

በቀረበዉ አፈፃፀምና የእቅድ ትዉውቅ ላይ ሰፊ ዉይይት የተደረገበት ሲሆን የቋራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸውና የምዕራብ ጎንደር ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛት ዝጋለ የውይይት መድረኩ መርተዉታል።

አቶ ግዛት በዉይይቱ ወቅት እንተናገሩት የቋራ ወረዳ በችግርም ዉስጥ ሁኖ ከሌሎች ወረዳዎች በተለየ መልኩ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከእቅድ በላይ በማከናወን በተለይ የግል የጤና ተቋማት ለአቅመ ደካሞች የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ ብቸኛዉ ወረዳ ቋራ ነዉ ብለዋል።

አቶ ግዛት አያይዘዉም በክረምት በጎ ፈቃድ የነበሩ አደረጃጀቶችን በበጋ ወራትም በመድገም የወጣቶች የስብእና ማእከል በመገንባት የወጣቶች የስፖርት ማዘዉተሪያ ስፍራዎችን በማስፋፋት በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን ማብዛት እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዉ ተናግረዋል።

የቋራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የዉይይት መድረኩን በመሩበት ወቅት እንደገለፁት ቀጣናችን ብዙ ሃብት ያለን በመሆኑ አደረጃጀት ፈጥረንና አቀናጅተን በመስራት በበጎ ፈቃድ ስራ ላይ ብዙ በጎ ፈቃደኛን በማሰማራት የማይናወጥ ዉጤት ማስመዝገብ ይገባል ብለዉ ከተማችንን ዉብና ፅዱ ለማድረግ የቄራ አገልግሎት ቦታ በመከለል ለቀጣይ ትኩረት የሚሰጠዉ ጉዳይ ነዉ ብለዋል።

የወረዳ አመራሮች የተቋማት ቡድን መሪዎች በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች የሀይማኖት አባቶች የሀገር ሽማግሌዎች የዞን አመራሮች የክረምት በጎ ፈቃድ ሰጭ አካላት የተቋማት ፎካሎች በመድረኩ ታድመዋል።

ለክረምት በጎ ፈቃድ ንቁ ተሳታፊ ለነበሩ ተቋማት ግለሰቦችና ድርጅቶች የምስጋና የምስክር ወረቀት በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

Address

Quara
Gondar

Telephone

+251918318183

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Quara Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Quara Communication Affairs Office:

Share