Quara Communication Affairs Office

Quara Communication Affairs Office ትክክለኛ መረጃን ለአገራችንና ለህዝባችን ተጠቃሚነት ስንል ተደራሽ እናደርጋለን!!

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ " ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር " በሚል መሪ ሀሳብ የብልጽግና ፓርቲ  ያለፉት ዓመታት ጉዞና የቀጣይ አመታት የትኩረት መስኮች ላይ ከጠቅላላ የወረዳ አመራሮ...
12/09/2025

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ " ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር " በሚል መሪ ሀሳብ የብልጽግና ፓርቲ ያለፉት ዓመታት ጉዞና የቀጣይ አመታት የትኩረት መስኮች ላይ ከጠቅላላ የወረዳ አመራሮች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

በውይይቱ የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸው እና የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ማሬ ተገኝተው መድረኩን እየመሩት ነው።

መስከረም 2/2018 ዓ.ም
(የቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት)

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ለአቅመ ደካሞች የበዓል መዋያ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ተካሄደ።ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 1/2018 ዓ.ም (ቋራ ኮሙኒኬሽን) በፕሮግራሙ የተከበሩ አቶ አንዳርጋ...
11/09/2025

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ለአቅመ ደካሞች የበዓል መዋያ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ተካሄደ።

ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 1/2018 ዓ.ም (ቋራ ኮሙኒኬሽን) በፕሮግራሙ የተከበሩ አቶ አንዳርጋቸው ማሬ የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ተገኝተው ለአቅመ ደካሞች ማዕድ አጋርተዋል።

አቅመ ደካሞች በበዓል ወቅት ከቤታቸው የሚቀምሱት የሚያጡበት ሁኔታ እንዳይፈጠር በማሰብ ከተለያዩ የበጎ አድራጊ አካላት ገንዘቡን በማሰባሰብ በዛሬው ዕለት ማዕድ ማጋራት መቻሉን የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፐርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ማሬ ገልፃዋል።

በማዕድ ማጋራቱ በችግር ውስጥ ላሉ አቅመ ደካሞች ማዕድ ማጋራት መቻሉንም አንስተዋል።

ማዕድ ማጋራት መተዛዘንን መረዳዳትን መተሳሰብንና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር በመሆኑ ሁሉም ማህበረሰብ ለዚህ የተቀደሰ ሃሳብ በየበዓሉ ወቅት የበኩሉን እርብርብ ማድረግ መቻል እንዳለበት አሳስበዋል።

በዚህ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ሲያስተባብሩ ለነበሩ ወንድሞች ታላቅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሳችሁ
መልካም አዲስ ዓመት

ለሃገር መከለከያ ሰራዊትና ጥቅል በገለጉ ከተማና በዱባባ ከተማ ለሚገኘው ለጥምር ጦሩ የበዓል መዋያ የእርድ እንስሳት ድጋፍ ተደረገ።ጥቅል ድጋፉ 5  በሬና 13 ፍየል ድጋፍ የተደረገ ሲሆን የ...
10/09/2025

ለሃገር መከለከያ ሰራዊትና ጥቅል በገለጉ ከተማና በዱባባ ከተማ ለሚገኘው ለጥምር ጦሩ የበዓል መዋያ የእርድ እንስሳት ድጋፍ ተደረገ።

ጥቅል ድጋፉ 5 በሬና 13 ፍየል ድጋፍ የተደረገ ሲሆን የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንደርጋቸው፣ የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቴ አንደርጋቸው ማሬና ሌሎች የወረዳ አመራሮች ተገኝተው እርክክብ አድርገዋል።

በርክክቡ የመከላከያ ሰራዊት አመራሮች ሌሎች የወረዳው የፀጥታ መዋቅር አመራሮች ተገኝተው ድጋፉን ርክክብ አድርገዋል።

ጳግሜ 5/2917 ዓ.ም
Quara communication

አቶ አንዳርጋቸው ማሬ የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ለ2018 ዓ.ም አዲስ አመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላለፉ።አዲሱ አመት ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ በማ...
10/09/2025

አቶ አንዳርጋቸው ማሬ የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ለ2018 ዓ.ም አዲስ አመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላለፉ።

አዲሱ አመት ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ በማጠናቀቅ የማድረግና የመፈፀም አቅማችንን ያሳየንበት በዓመት መሆኑን ገልፃዋል።

ኢትዮጵያውያን እጅ ለእጅ ተያይዘን የአይቻልምን አስተሳሰብ በይቻላል ቀይረንና ችለንም ለዓለም ያሳየንበት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ለኢትዮጵያውያን ዳግማዊ የአድዋ ድል የሆነና የዓለም ህዝብ መነጋገሪያ አጀንዳ የሆነ የዘመኑ ታላቅ ተጋድሎ ነው ብለዋል፡፡

በሴራ ፖለቲካ ግድባችንን ለማምከን ዘርፈ ብዙ ጥረቶች ቢደረግበትም መሰናክሎቹን በፅናት በመበጣጠስ በራሳችን የሀብት ምንጭ ዓለም መራራ ሀቁን እንዲቀበል፤ ለተገፉትና ፍርድ ለተጓደለባቸው ጭምር በራስ አቅም አንድነትን በማጠናከርና ፈተናዎችን በመቋቋም የትውልድ አደራንና ህልምን እንዴት እውን እንደሚደረግ አስተምረናል ብለዋል፡፡
በመሆኑንም አዲሱ አመት ለኢትዮጵያዊያን ልዩ ያደርገዋል የማድረግና የመፈፀም አቅምን ከፍ በማድረጉ መላ ኢትዮጵያዊያን በኩራት እንዲነሱ አድርጓል ብለዋል።

አዱሱ አመት የጤና፣ የሰላም፣ የአንድነት እና የብልፅግና ያድርግልን ብለዋል።

መልካም አዲስ አመት
"''' እንቁጣጣሽ """
አቶ አንዳርጋቸው ማሬ
የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ

አቶ አስማረ አንዳርጋቸው የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ ለ2018 ዓ.ም አዲስ አመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላለፉ።አዲሱ አመት ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ለህዝባችን የተበሰረት ...
10/09/2025

አቶ አስማረ አንዳርጋቸው የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ ለ2018 ዓ.ም አዲስ አመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላለፉ።

አዲሱ አመት ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ለህዝባችን የተበሰረት ዓመት በመሆኑ አመቱን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ለአሁኑ ትውልድ የአርበኝት አሻራ፤ ለቀጣዩ ትውልድ ደግሞ የጽናትና የአልበገርም ባይነትን ወኔ የምናወርስበት ታሪካዊ ክስተት ነው፡፡ ስለሆነም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የነገን ተሰፋ ያለመለመ ብቻ ሳይሆን ለተጨማሪ ድሎች የሚያነሳሳ ተግባር ነው ሲሉ አስተዳዳሪው አንስተዋል፡፡

በተጨማሪም በሀገሪቱ የተመዘገበው ለውጥ ትላልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስ የሚቻል መሆኑን በተግባር ያሳየንበት ነው ያሉት አቶ አስማረ ከምንም በላይ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቁ ኢትዮጰያ በዓባይ ወንዝ ላይ የመጠቀም ፍትሃዊ መብቷን ማረጋገጥ ችላለች ብለዋል፡፡

በመሆኑ የ2018 አዲስ አመት አዲስ ብስራት አዲስ ተስፋን የሚያጭር አመት መሆኑንም ገልፃዋል።

አስተዳዳሪው አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና፣ የደስታ፣ የአንድነትና የወንድማማችነት ያድርግልን ብለዋል።

መልካም አዲስ አመት
""" #እንቁጣጣሽ """
አቶ አስማረ አንዳርጋቸው
የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ጳግሜ 5 የነገው ቀን " ድጅታል ኢትዮጵያ እውን እናደርጋለን" በሚል መሪ ቃል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።በፕሮግራሙ የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አ...
10/09/2025

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ጳግሜ 5 የነገው ቀን " ድጅታል ኢትዮጵያ እውን እናደርጋለን" በሚል መሪ ቃል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

በፕሮግራሙ የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸው፣ የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ማሬ፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የወረዳው አማራሮችና የሴክተር መስሪያ ቤት የማኔጅመንት አባላት ተገኝተዋል።

በፕሮግራሙ የነገ ሃገር ተረካቢ ተማሪዎችን በመጋበዝ የጥያቄና መልስ ፕሮግራም በማካሄድ በመጨረሻ ለተማሪዎች ሽልማት ማበርከት ተችሏል።

በፕሮግራሙ አስተማሪ ዶክመንታሪ ፊልም በማቅረብ በድጅታል ኢትዮጵያ እንደሃገርና እንደወረዳ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን በሰነድ ማቅረብ ተችሏል።

በምእራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ዻጉሜ 4 ዘላቂ ልማት ከአገራዊ ማንሰራራት በሚል መሪ ቃልና የታላቁ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ስነ ስርአትን በማሰብ ድምቀት መከበሩ ተገለፀ።ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ...
09/09/2025

በምእራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ዻጉሜ 4 ዘላቂ ልማት ከአገራዊ ማንሰራራት በሚል መሪ ቃልና የታላቁ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ስነ ስርአትን በማሰብ ድምቀት መከበሩ ተገለፀ።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በታላቋ ኢትዮጵያ ልጆች ጥሪት፣ ላብ፣ ዕውቀት እና ደም የተገነባ የመቻል ትዕምርት ነው፡፡

ከእንግዲህ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷ ፍትሐዊ ተጠቃሚ እንጅ ተመልካች አይደለችም፤ በአፍሪካ የታላቁ ግድብ ባለቤት እንጅ የረዥሙ ወንዝ ባለቤት የጥቅሙ ግን ተመልካች አይደለችም፡፡

ሕዳሴ የኢትዮጵያ የተሰናሰነ ብዝኃነት ዐቅም የታየበት፣ በየክፍለ ዘመኑ የዓለምን ታሪክና ፖለቲካ የሚቀይር ተምሳሌታዊ ጥረትና ድል ከኢትዮጵያ እንደሚመነጭ ያስመሰከረ ነው፡፡

እነሆ በ21ኛዉ ዘመንም ኢትዮጵያውን ዳግማዊ ዓድዋን አሳክተዋል፡፡

ሕዳሴ የአይችሉም ትርክትን ‘ኢትዮጵያውያን አይቻሉም’ ወደሚል ቀይሯል፡

የቋራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸዉ በበአሉ ተኝተዉ 14 ዓመትን በጉጉት ስንጠብቀዉ የነበረዉ የጋራ ታሪከሰችን መገለጫ የረጅም ጉዜ ህልማችን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ ምርቃት ላይ እንገኛለን በማለት መልካም ምኞታቸዉንና ደስታቸውን ገልፀዋል።

አቶ አስማረ አያይዘዉ እንደገለፀት አገራችን ሁለት ታሪካዊ ድሎችን ማለትም አድዋንና ህዳሴን ተቀዳጅታለች ካሉ በኋላ የዛሬዉ ድርብ በአል ቦንድ ስንገዛ ቦንድ የገዛነዉ እስከ ወለዱ ታስቦ ሲከፈለነንና የህዳሴዉን ፍፃሜ ስናይ ሶስት ደስታዎችን አግኝተናል በማለት አብራርተዋል።

የከተማና መሰረተ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ገብረ ሚካኤል አስተዉል የበአሉን መወያያ ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት በአገር አቀፍ ደረጃ በዛሬዉ እለት እያከበርን ያለነዉ ሁለት በአል ዘላቂ ልማት ለአገራዊ ማንሰራራትና የህዳሴዉ ግድብ የምረቃ ስነ ስርዓት ትልቅ ማንሰራራት ያመጣነባቸዉ እንደ አገርና እንደ ወረዳ በግብርና በማእድን በቱሪዝም በከተማና መሰረተ ልማት በትራንስፖርት በኤሌክትሪክ ኃይልና እና በውሃና ኢነርጂ ዘርፎች ናቸዉ ብለዋል።

የዛሬዉን ቀን እንደ ወረዳ በተለያዩ መስኮች የተሰሩ ስራዎች በዶክመንተሪ ፊልም አማካኝነት ለታዳሚዎች ቀርቦ ዉይይት የተደረገ ሲሆን ዉይይቱን የመሩት አቶ ዘመነ ሲመቸዉ የቋራ ወረዳ ባህልና ቱሩዝም ፅ/ቤት ኃላፊና የገለጉ መሪ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ጋሻዉ ሲሳይ መርተዉታል።

እንደ ወረዳ በችግር ላይም ሁነን ብዙ አመርቂ ለዉጦችን ያመጣን ሲሆን እንደማሳያ የዉሃ መስመር ዝርጋታ የከተማችንን ማስተማር ፕላን ማስጠበቅ የኔትወርክ ማስፋፋት ስራ የነዳጅ ማደያ ተከላ የመብራት ትራንስፎርመር ተከላና ማስፋፋት የመንገድ ጥገናና ግንባታ ለጎርፍ ተጋላጭ የሆኑ ስፍራዎችን ማፋሰስ ስራዎች የማንሰራራት መገለጫዎች ናቸዉ።

የህዳሴ መመረቅ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የፈጠረው ስሜት++++++++++++++++++++👉ደብረታቦር👉መዕከላዊ ኢትዮጵያ👉ደምቢዶሎ👉ባሕርዳር👉 አዲስ አበባ++++++++++++++++Gazette Plu...
09/09/2025

የህዳሴ መመረቅ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የፈጠረው ስሜት
++++++++++++++++++++

👉ደብረታቦር
👉መዕከላዊ ኢትዮጵያ
👉ደምቢዶሎ
👉ባሕርዳር
👉 አዲስ አበባ
++++++++++++++++

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ህዳሴ #ኢትዮጵያ #ዓባይ #ግድብ

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተሰጠ መግለጫ፤ለመላው ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች እንኳን ደስ አላችሁ፤ታላቁ ሕዳሴ  ግድብ ተጠናቆ ለምረቃ መ...
09/09/2025

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተሰጠ መግለጫ፤

ለመላው ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች እንኳን ደስ አላችሁ፤

ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ ለምረቃ መብቃቱ እኛ ኢትዮጵያውያን ፈተና ሳይበግረን ታሪክ ሰሪ መሆናችንን ለዓለም ፍትህ ጠያቂዎች ያስተማርንበት ታላቅ የተጋድሎ ምዕራፍ ነው!

አባቶቻችን በርዕያቸው "እኛ ዛሬ ባንሰራው ልጆቻችን ይሰሩታል!" በማለት የተናገሩትን የትንቢት ቃል ማዕበሉ ሳያናውጠን፣ ሀዲዳችንን ሳንስት፣ የጀመርነው ታሪካዊ ተግባር ሳይስተጓጎል የሚደርሱብንን ፈተናዎች በፅናት ተቋቁመን ህዝባችን ጋር በመሆን ሌት ተቀን ታግለን ለትውልድ የሚሆን ታላቅ ገፀ በረከት በአዲስ ዓመት መባቻ አበርክተናል፡፡ በዚህም በትንንሽ ፈተናዎች ሸብረክ ማለትን ለማያውቀውና ሲፈተኑ የበለጠ እየጠነከሩ መቀጠልን ለትውልድ እያስተማረ ለሚሄደው ህዝባችን እንኳን ደስ ያለን! እንኳን ደስ ያላችሁ!

ኢትዮጵያውያን እጅ ለእጅ ተያይዘን የአይቻልምን አስተሳሰብ በይቻላል ቀይረንና ችለንም ለዓለም ያሳየንበት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ለኢትዮጵያውያን ዳግማዊ የአድዋ ድል የሆነና የዓለም ህዝብ መነጋገሪያ አጀንዳ የሆነ የዘመኑ ታላቅ ተጋድሎ ነው፡፡ በሴራ ፖለቲካ ግድባችንን ለማምከን ዘርፈ ብዙ ጥረቶች ቢደረግበትም መሰናክሎቹን በፅናት በመበጣጠስ በራሳችን የሀብት ምንጭ ዓለም መራራ ሀቁን እንዲቀበል፤ ለተገፉትና ፍርድ ለተጓደለባቸው ጭምር በራስ አቅም አንድነትን በማጠናከርና ፈተናዎችን በመቋቋም የትውልድ አደራንና ህልምን እንዴት እውን እንደሚደረግ አስተምረናል፡፡ ዛሬ በአለም ላይ ያሉ ምሁራንና ሚዲያዎች አጀንዳቸው ይሄ ሆኖ ኢትዮጵያውያን ያሰቡትን ለማሳካት ጊዜ ይወስድባቸው ካልሆነ በስተቀር የሚያቆማቸው አንዳች ሃይል እንደሌለ ሲተነትኑ ታይዋል፡፡

ታላቁ የህዳሴ ግድብ ስራችን በኢትዮጵያዊ በአንድነት፣ መነሳሳት እና ወኔ የተጀመረ ቢሆንም በተለያዩ ፈተናዎች እንዲኮላሽ ለማድረግ በርካታ ሴራዎች ቢሸረቡም በጥብቅ ክትትልና ግምገማ ችግሮቹን ፈትተን ወደ አዲስ ምእራፍ ሲሸጋገር ጠላቶቻችን ያኔ ነበር እውን እንደሚሆን አስበው ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ለማሳረፍ የተረባረቡት፡፡ ከዓለም አቀፍ ጫናው ባሻገር በውስጣችንም መከፋፈል ለመፍጠር ቢወራጩም በፅናት ተቋቁመን አለም አቀፍ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለውጤት በማብቃታችን ታላቅ ኩራት ይሰማናል፡፡

የግድቡ ግንባታ ለአሁኑ ትውልድ የአርበኝት አሻራ፤ ለቀጣዩ ትውልድ ደግሞ የጽናትና የአልበገርም ባይነትን ወኔ የምናወርስበት ታሪካዊ ክስተት ነው፡፡ ስለሆነም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የነገን ተሰፋ ያለመለመ ብቻ ሳይሆን ለተጨማሪ ድሎች የሚያነሳሳ ተግባር ነው፡፡

በተጨማሪም በሀገሪቱ የተመዘገበው ለውጥ ትላልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስ የሚቻል መሆኑን በተግባር ያሳየንበት ነው። ከምንም በላይ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቁ ኢትዮጰያ በዓባይ ወንዝ ላይ የመጠቀም ፍትሃዊ መብቷን ያረጋገጠ ነው፡፡

ይህ ታላቅ ፕሮጀክት ለኢትዮጵያ ያለው ፋይዳ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ በአገር ውስጥ እና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ዕድገትና ብልፅግና ከፍተኛ ሚና መጫወት እንዲችሉ ዕድል ፈጥሯል፡፡ መላው የሀገራችን ብሎም የክልላችን ሕዝብ ባደረገው የፋይናንስ፣ የፐብሊክ ዲፕሎማሲና የአካባቢ ጥበቃ ሥራ ላይ አስተዋፅኦ በማድረጉ የግንባታ ስራውን በስኬት አጠናቀናል፡፡

Amhara Communication

የድርብ ድል የሆነውን ጳግሜ 4 የማሰራራት ቀንን ታላቅ የህዳሴ ግድብ የተመረቀበት ዕለት በመሆኑ ታላቅ ደስታ እየተሰማን እለቱ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።ጳግሜ 4/2017 ዓ.ም Quara c...
09/09/2025

የድርብ ድል የሆነውን ጳግሜ 4 የማሰራራት ቀንን ታላቅ የህዳሴ ግድብ የተመረቀበት ዕለት በመሆኑ ታላቅ ደስታ እየተሰማን እለቱ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

ጳግሜ 4/2017 ዓ.ም
Quara communication

በህዳሴ ግድብ ምረቃ እንኳን ደስ አላችሁህዳሴ የኢትዮጵያውያን የጋራ ድል ነው።
09/09/2025

በህዳሴ ግድብ ምረቃ እንኳን ደስ አላችሁ
ህዳሴ የኢትዮጵያውያን የጋራ ድል ነው።

በምእራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ዻጉሜ 3 የእምርታ ቀን "እመርታ ለዘላቂ ከፍታ" በሚል መሪ ሐሳብ በድምቀት መከበሩ ተገለፀ።በወርሃ ዻጉሜ 2017 ዓ.ም 3ኛዉ ቀን ላይ እንገኛለን በዓሉ ደግ...
08/09/2025

በምእራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ዻጉሜ 3 የእምርታ ቀን "እመርታ ለዘላቂ ከፍታ" በሚል መሪ ሐሳብ በድምቀት መከበሩ ተገለፀ።

በወርሃ ዻጉሜ 2017 ዓ.ም 3ኛዉ ቀን ላይ እንገኛለን በዓሉ ደግሞ የእመርታ ቀን እመርታ ለዘላቂ ከፍታ በሚል መሪ ሃሳብ በአገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ይገኛል።

የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸዉ ማሬ በበአሉ ተገኝተዉ እንደገለጹት የእመርታ ቀንን የምናከብረዉ የጀመርነዉን የከፍታ ጉዞ በማላቅ እና በማጽናት የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ነዉ ካሉ በኋላ የተረጋጋ ማክሮ-ኢኮኖሚ መፍጠር፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ፣ የኢንዱስትሪ ምርቶችን ተወዳዳሪነትና የገበያ ዲጀታላይዜሽንን ማስፋፋት እና የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራዉ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባና እንደ ወረዳችን ተጨባጭ ሁኔታ ችግር ላይም ሁነን ጥቂት የማይባሉ የመሰረተ ልማት ስራዎች ተሰርተዋል ይህ የእምርታ አንዱ መገለጫ ነዉ በማለት አብራርተዋል።

አቶ አንዳርጋቸዉ አክለዉም ሰላም የእመርታ መሰረትና ከዛሬ ወደ ነገ የምንሻገርበት አገራችን ብሎም ወረዳችን የልማት ግንባር ቀደም የምናደርግበት ቁልፍ መሳሪያ ነዉ ብለዋል።

አቶ ማስረሻ አስፋዉ የግብርና ፅ/ቤት ኃላፊ የእምርታችን መገለጫ የሆኑ ዶክመንተሪ ፊልም ለእይታ በቀረቡበት ወቅት እንዳሉት በግብርናው ዘርፍ እንደኛ ወረዳ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ የተፋሰስ ስራዎች የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ግሪን ኤርያ የችግኝ ተከላ ዝግጅት የመስኖ ዉጤቶች የመካናይዜሽን የእርሻ ማሳ ስራዎች የኤክስፖርት ሰብሎችና የመሰረተ ልማት ስራዎች ተሰርተዋል እነዙህ በሙሉ የወረዳችን እመርታዎች ናቸዉ በማለት አብራርተዋል።

የእምርታ ቀን ሲከበር የተላለፉት መልዕክቶች ውስጥ እምርታ ለዘላቂ ከፍታ ምርትና ምርታማነት እድገት ለምግብ ሉአላዊነት እምርታ አረንጓዴ አሻራ ስኬት ለዲፕሎማሲና አገራዊ ገፅታ እምርታ እና ከምርታማነት በላይ እይታ ለአገር ከፍታ ወዘተ መልዕክቶች ከፍ ብለዉ ተሰምተዋል።

በመጨረሻም በአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄና ብዛህይወት ጥበቃ የተተከሉ ችግኞች በሁለት ሳይት ተተክለዉ የፀደቁና አገልግሎት እየሰጡ ያሉ ቦታዎችን እና በቀጠና 6 የተሰራ የውሃ ግምባታን በመጎብኘት የእለቱ ዝግጅት ተጠናቋል።

በውይይቱ የቋራ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸው፣ የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ማሬ ተገኝተዋል።

የፓናል ውይይቱን የቋራ ወረዳ ንግድና ገቢያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጥጋቡ ተላይነህ፣ የቋራ ወረዳ ህብረት ስራ ኮሚሽን ተጠሪ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሸጋው ቢሰጥ መርተውታል።

Address

Quara
Gondar

Telephone

+251918318183

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Quara Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Quara Communication Affairs Office:

Share