09/10/2025
የቋራ ወረዳ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 14ኛ ዓመት 43ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ።
ቋራ/ገለጉ:- መስከረም 29/2018 ዓ.ም (የቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት) በጉባኤው ዝርዝር አጀንዳዎች እንዳሉ የገለፁት የቋራ ወረዳ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኑርሁሴን ማህመድ የወረዳ መስተዳደሩን የ2018 በጀት አመት ዕቅድ መርምሮ ማፅደቅ፣ የ2017 ለ2018 ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት መርምሮ ማፅደቅ፣ የ2018 በጀት ዓመት የወረዳውን የምክር ቤት በጀት መርምሮ ማፅደቅ፣ ሹመት ማንሳትና ሹመት መስጠት በሚሉ አጀንዳዎች ጉባኤው እንደሚካሄድ አብራርተዋል።
የቋራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸዉ በጉባኤዉ ተገኝተዉ የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት እንደገለፁት የቋራ ወረዳ ምክር ቤት የህዝብ መስታዉት ህዝብና መንግስትን የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት ሲባል ለህዝብ የሚደርሱ ስራዎችን በዚህ ጉባኤ ለማስታዋወቅ እና ተግባራትን ለመገምገም ከፈፃሚ አካላት የሚሾልኩ ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል ተጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በመግለፅ መድረኩ በይፋ የተከፈተ መሆኑን ተናግረዋል።