Quara Communication Affairs Office

Quara Communication Affairs Office ትክክለኛ መረጃን ለአገራችንና ለህዝባችን ተጠቃሚነት ስንል ተደራሽ እናደርጋለን!!
(1)

ወልድያ በኮሪደር ልማት እየደመቀች ነው።የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወልድያ ከተማ የተሰራውንና እየለማ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት በምሽት ተዘዋውረው መመልከታቸውን የሚያሳይ ምስል።
09/06/2026

ወልድያ በኮሪደር ልማት እየደመቀች ነው።

የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወልድያ ከተማ የተሰራውንና እየለማ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት በምሽት ተዘዋውረው መመልከታቸውን የሚያሳይ ምስል።

የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች እነማን ናቸው?ሰኔ 1/ 2018 ዓ.ምጤና ይስጥልን! ባለፈው ሳምንት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ተሳታፊዎች እነማን እንደሆኑ ጠይቀናችሁ ነበር፡፡ ለተሳትፏችሁ ...
08/06/2026

የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች እነማን ናቸው?

ሰኔ 1/ 2018 ዓ.ም

ጤና ይስጥልን! ባለፈው ሳምንት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ተሳታፊዎች እነማን እንደሆኑ ጠይቀናችሁ ነበር፡፡ ለተሳትፏችሁ ከልብ እናመሰግናለን፡፡

👉እነሆ አጭር ማብራሪያ

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገራችን ኢትዮጵያ ከሚገኙ እና በውጭ ሀገራት ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የአጀንዳ ሃሳቦችን ማሰባሰቡ የሚታወቅ ነው፡፡ በዚህ የምክክር ሂደት በክልል/ ከተማ አስተዳደር ደረጃ፣ በፌዴራል ደረጃ እንዲሁም በዲያስፖራው ማህበረሰብ ዘንድ የተሰበሰቡ አጀንዳዎች በኮሚሽኑ ተደራጅተው ለመጨረሻው የአጀንዳ ቀረፃ እየተዘጋጁ ነው፡፡

👉ለመሆኑ በእነዚህ አጀንዳዎች ላይ የሚመካከረው ማን ነው?

በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ ተሳትፎን የሚያደርጉ አካላት ኮሚሽኑ አጀንዳ ካሰባሰበባቸው ባለድርሻ አካላት የተመረጡ/ የተወከሉ ሲሆን ይህም በባለድርሻ አካላቱ እውቅና ሲከናወን ቆይቷል፡፡ በዚህ መሰረት በክልሎች/ ከተማ አስተዳደሮች፣ እና በዲያስፖራው ማህበረሰብ ዘንድ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በአጀንዳ ማሰባሰብ ወቅት በሀገራዊ ምክክር ጉባዔው ላይ እነሱን ወክለው የሚመካከሩ ወኪሎቻቸውን እንዲመርጡ ተደርጓል፡፡

በሌላ በኩል በኩሚሽኑ አሰራር ስርዓት መሰረት በክልሎች/ከተማ አስተዳደሮች እና በፌዴራል ተቋማት በሚገኙና ወኪሎቻቸውን በአጀንዳ ማሰባሰብ ወቅት እንዲመርጡ ያልተደረጉ ባለድርሻ አካላት ወኪሎቻቸውን በደብዳቤ ወክለው ለኮሚሽኑ እንዲያሳውቁ ኮሚሽኑ ለባለድርሻ አካላቱ ጥሪ በማስተላለፍ ላይ ይገኛል፡፡

በዚህ መሰረት በአጠቃላይ 4,000 የሚጠጉ ተሳታፊዎች የሚሳተፉበት የሀገራዊ ምክክር ሂደት

👉የየወረዳው የሕብረተሰብ ክፍል ወኪሎችን

👉የክልል/ከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት ወኪሎችን

👉የፌዴራል ባለድርሻ አካላት ወኪሎችን እና

👉የዲያስፖራ ማህበረሰብ ወኪሎችን ያሳትፋል፡፡

ኢትዮጵያ እየመከረች ነው!

የመተማ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም የበጀት ድጋፍ የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ድጋፍ  አደረገ።በመተማ ወረዳ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የስርዓተ ምግብ ፕሮግራም አማካኝነት ...
07/06/2026

የመተማ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም የበጀት ድጋፍ የሴቶች ንጽህና መጠበቂያ ድጋፍ አደረገ።

በመተማ ወረዳ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የስርዓተ ምግብ ፕሮግራም አማካኝነት ለጎዴ ጫማ ማጥበቂያ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት እና ለመንደር 6 አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ለሴቶች የንፅህና መጠበቂያ ድጋፍ ተደርጓል።

በስፍራው የተገኙት የመተማ ወረዳ ት/ት ጽ/ቤት ም/ኃላፊ ወ/ሮ ዘሃራ የሱፍ ሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም የአመጋገብ ሁኔታን ለማሻሻል የሚሰራ መሆኑን ጠቅሰው በትምህርቱ ዘርፍም የአመጋገብ ስርአተ ትምህርት መስጠት፤ የተመጣጠነ ምግብ ዙሪያ እውቀት ማስፋፋት ላይ በአትኩሮት በመስራት በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የዳበረ ግንዛቤና የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝ በማድረግ ረገድ ትምህርት ቤቶችን የተሞከሮ ማእከል ማድረግ አለብን ብለዋል በመጨረሻም በተመረጡ ት/ቤቶች የተሰጡ ግብዓቶች በአግባቡ እንዲጠቀሙ አሳስበዋል።

የወረዳው ሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ገብረሕይወት አየነው በበኩላቸው ስረዓተ-ምግብ ላይ መስራት ሃገርን መገንባት እና ትውልድን ማስቀጠል ሰለሆነ በወሰድናቸው ስልጠናወች እና ግብአቶች ልክ በትኩረት መስራት እንዳለበት በማሳሰብ አጠቃላይ ለቀጣይ ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማጠናከር የፕሮግራሙን ግብ ዳር ማድረስ አለብን ብለዋል፡፡

በድጋፍ ርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የመተማ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ም/ኃላፊ ወ/ሮ ዘሃራ የሱፍ ፣የሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ገብረሕይወት አየነው እና የት/ቤቶቹ ርዕሰ መምህራን ተገኝተዋል።

መተማ ወረዳ ኮሙኒኬሽን
ግንቦት 30/2018 ዓ.ም

‎በሰሜን ጎጃም ዞን ለጥፋት ሀይሎች ተላልፎ ሊሰጥ የነበረ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ዋለ።‎‎በሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን አቸፈር ወረዳ መነሻውን ጭንባ ከተማ አድርጎ ወደ ባህርዳር ከተማ ለጠላ...
07/06/2026

‎በሰሜን ጎጃም ዞን ለጥፋት ሀይሎች ተላልፎ ሊሰጥ የነበረ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ዋለ።

‎በሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን አቸፈር ወረዳ መነሻውን ጭንባ ከተማ አድርጎ ወደ ባህርዳር ከተማ ለጠላት ተላልፎ ሊሰጥ የነበረው 2 ስናይፐር መሳሪያ እና 2 ክላሽንኮቭ መሳሪያ በጀግናው ጥምር ጦር እስከ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውሏል።

ከአማራ ኮሙኒኬሽን

ቋራ ወረዳ ስፓርት ለፍቅር፣ ስፓርት ለሰላም ፣ስፓርት ለጤና በሚል መሪ ቃል የቋራ ወረዳ  አመራሩ ቡድንና  ከህዝባዊ ፖሊስ  ቡድን ጋር የእግር ኳስ ጭዋታ ወድድር ተካሄደ።ገለጉ:- ግንቦት 3...
07/06/2026

ቋራ ወረዳ ስፓርት ለፍቅር፣ ስፓርት ለሰላም ፣ስፓርት ለጤና በሚል መሪ ቃል የቋራ ወረዳ አመራሩ ቡድንና ከህዝባዊ ፖሊስ ቡድን ጋር የእግር ኳስ ጭዋታ ወድድር ተካሄደ።

ገለጉ:- ግንቦት 30/2018 በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ስፓርት ለፍቅር፣ ስፓርት ለሰላም ፣ስፓርት ለጤና በሚል መሪ ቃል የቋራ ወረዳ አመራሩና ህዝባዊ ፖሊስ የእግር ኳስ ጭዋታ ወድድር መካሄዱን የቋራ ወረዳ ባህል ቱሪዝም ስፖርት ጽ/ቤት ገልጿል።

ጨዋታ በአመራሩ አሸናፊነት የተጠናቀቀ ሲሆን በውድድሩ በሁለቱም ቡድኖች ፍፁም የሆነ እስፓርታዊ ጭዋነትን የተላበሰና ሳቢና ማራኪ የሜዳ ላይ እቅስቃሴዎችን የታየበትና ስፓርት ለሠው ልጆች ዘርፍ ብዙ ጥቅሞችን መያዙን ያስገነዘበ ጨዋታ ነዉ።

የቋራ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ሰፓርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አድማሡ ውቤ ስፖርታዊ ዉድድሩን በሚመለከት እንደገለጹት በቀጣይ ሁሉም የህብረተሠብ ክፍል በየትኛውም የስፖርት እንቅስቃሴ በማድረግ በስፖርት አእምሮዉ የዳበረ ማህበረሰብ መፈጠር እዳለበት እና ስፖርታዊ ዉድድሮች ጤናማ የሆነ የስራ እንቅስቃሴ ፋይዳዉ የጎላ እንደሆነ አብራርተዋል።

የ2018 ለ2019 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ4 መቶ ሺህ በላይ ችግኞችን በማፍላት የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቁን የቋራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አስታወቀ።ገለጉ:...
07/06/2026

የ2018 ለ2019 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ4 መቶ ሺህ በላይ ችግኞችን በማፍላት የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቁን የቋራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አስታወቀ።

ገለጉ:- ግንቦት 30/2018 በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ የ2018 ለ2019 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ4 መቶ ሺ በላይ ችግኚችን በማፍላት የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቁን የቋራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አስታዉቋል።

በወረዳዉ የ2018 ለ2019 ዓ.ም የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር 4 መቶ 83 ሺህ 459 የደንና የቆላ ፍራፍሬ ችግኝ መዘጋጀቱን የቋራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማስረሻ አስፋዉ ገልፀዋል።

ኃላፊዉ አያይዘዉ እንደገለጹት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በ24 ቀበሌዎች በ50 ተፋሰስ እንደሚካሄድ ገልፀዉ በ45 የተከላ ሳይት ተከላ እንደሚደረግና 3 መቶ 56 ሺ 74 የመትከያ ጉድጓድ በማዘጋጀት የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁን አብራርተዋል።

አቶ ማስረሻ አክለዉም ለተከላ ከተዘጋጀዉ የደን ችግኝ ዉስጥ አገር በቀል 1 መቶ 55 ሺህ 523 አገር በቀል እንደሆነ ጠቁመዉ በቆላ ፍራፍሬ 277.8 ሄክታር መሬት ልየታ ተደርጓል።

መጨረሻም የ2018 ለ2019 ዓ.ም ለአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የሚመለከታቸዉ አጋር አካላት እና ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የበኩላቸዉን እንዲወጡ እንዲሁም ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

ቋራ ወረዳ ገለጉ ከተማ ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለዉ ዝናብ በንብረት ላይ  ጉዳት አደረሰ።በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ገለጉ ከተማ በትናትናው ዕለት ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለዉ ዝናብ በን...
07/06/2026

ቋራ ወረዳ ገለጉ ከተማ ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለዉ ዝናብ በንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ገለጉ ከተማ በትናትናው ዕለት ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለዉ ዝናብ በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል።

ግንቦት 29/2018 ዓ.ም 9 ሰዓት አካባቢ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለዉ ዝናብ በመንግስት ተቋማት በግለሰብ መኖሪያ ቤቶችና የንግድ ድርጅቶች ላይ የንብረት ዉድመት አስከትሏል።

ሁሌም የክረምት መግቢያ አካባቢ እንደዚህ አይነት የተፈጥሮ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል እና ህብረተሰቡ ከእነዚህ መሰል የተፈጥሮ አደጋዎች እራሱን እንዲጠብቅ መልዕክት የተላለፈ ሲሆን በንብረት ላይ እንጅ በሰዉ ላይ ምንም ጉዳት አልደረሰም።

ቋራ ወረዳ ዱባባ ቀበሌ ከጥቃቅንና አነስተኛ አባላት ጋር በኮንቲነር የነበሩ የደረጃ ሽግግር ዙሪያና በአዲስ የስራ ዕድል ከሚፈጠርላቸው ወጣቶች ጋር ውይይት ተካሄደ።ገለጉ:- ግንቦት 28/201...
05/06/2026

ቋራ ወረዳ ዱባባ ቀበሌ ከጥቃቅንና አነስተኛ አባላት ጋር በኮንቲነር የነበሩ የደረጃ ሽግግር ዙሪያና በአዲስ የስራ ዕድል ከሚፈጠርላቸው ወጣቶች ጋር ውይይት ተካሄደ።

ገለጉ:- ግንቦት 28/2018 ዓ.ም በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ዱባባ ቀበሌ ከጥቃቅንና አነስተኛ አባላት ጋር በኮንቲነር የነበሩ የደረጃ ሽግግር ዙሪያና በአዲስ የስራ ዕድል ከሚፈጠርላቸው ወጣቶች ጋር ውይይት ተካሄደ።

ውይይቱ በጥቃቅንና አነስተኛ ተመልምለው ኮንቲነር የተሰጡ አካላት ከ5 አመትና ከዚያ በላይ ያስቆጠሩ በመሆናቸው የደረጃ ሽግግር በማድረግ ለአዲስ የስራ ዕድል ለሚፈጠርላቸው ወጣቶች እንዲያስረክቡ የሚያስችል ውይይት ነው።

በውይይቱ የቋራ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሲራጅ ሙሀመድ፣ የቋራ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ በዕምነቱ ሲሳይ፣ የዱባባ ንዑስ መዘጋጃ ስራ አስኪያጅ አቶ ፈንታሁን አሰፋ እና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ባለሙያ ተገኝተዋል።

ቋራ ወረዳ የዓለም የአካባቢ ቀን" የአየር ንብረት ለዉጥ ተፅዕኖን መታደግ"/climate Action/በሚል መሪ ቃል  በተለያዩ ኩነቶች በድምቀት ተከበረ።ገለጉ:- ግንቦት 28/2018 በምዕራብ...
05/06/2026

ቋራ ወረዳ የዓለም የአካባቢ ቀን" የአየር ንብረት ለዉጥ ተፅዕኖን መታደግ"/climate Action/በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ኩነቶች በድምቀት ተከበረ።

ገለጉ:- ግንቦት 28/2018 በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ የዓለም የአካባቢ ቀን "የአየር ንብረት ለዉጥ ተፅዕኖን መታደግ"/climate Action/ በሚል መሪ ቃል በፓናል ዉይይትና አካባቢን በማፅዳት በተለያዩ ኩነቶች በድምቀት ተከብሯል።

የዓለም አካባቢ ቀን በየዓመቱ ግንቦት 28 እንደሚከበርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ53ኛ በአገራችን ለ33ኛ እና በክልላችን ለ29ኛ ጊዜ በወረዳ ደረጃም እየተከበረ የሚገኘዉ ህብረተሰቡ በአየር ንብረት ለውጥ እና ተዛማጅ የአካባቢ ጉዳዮች የሚኖራቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ እና አወንታዊ ሚና የሚወጣ ዜጋ በማፍራት ፅዱ እና ምቹ አካባቢን መፍጠር ነዉ ።

የቋራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸዉ የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት አንደገለፁት የአየር ንብረት ለዉጥን ትርጉምና ታሪካዊ አመጣጥንና ያለዉን ፋይዳ በዝርዝር በመጠቆም የአየር ንብረት ለዉጥ ጉዳይ እንደቀላል መታየት እንደለለበት እና አካባቢን ከብክለትና ከደን ጭፍጨፋ ለመታደግ የሁሉም ዜጎች ተሳትፎ ማድረግ እንደሚገባ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የአየር ንብረት ለዉጥ ተፅዕኖ የሚቀንሱ ስራዎችን መስራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ማራኪ ፅዱ እና ንፁህ ካባቢ ለመፍጠርና ራሳችንን ከሰው ሰራሽ በሽታዎች ለመከላከል የቆሻሻ አወጋገድ መመሪያዎችንና ህጎችን በመተግበርና ህጋዊ ተጠያቂነትን በማስፈን ሊሆን እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የበዓሉ መከበር ዋና ዓላማ አካባቢን መጠበቅ ራስን መጠበቅ አካባቢን ማፅዳት ለዘላቂ ህይወት የአየር ንብረት ለዉጥ ተፅዕኖን መታደግ ችግኞችን በመትከልና መንከባከብ አረንጓዴ አካባቢን መፍጠር አካባቢያችን በማፅዳት ፅዱ አካባቢን መፍጠር የሚል ትልቅ ትርጉም እንዳለዉ ተገልጿል።

የቋራ ወረዳ ዋና አስተዳሰሪ አቶ አስማረ አንዳርጋቸዉ፣የወረዳዉ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸዉ ማሬ፣ የወረዳዉ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኑርሁሴን ማህሙድ፣የቋራ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ካሳነሽ ሃብቱ ፣አቶ ማስረሻ አስፋዉ የወረዳዉ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ፣ አቶ ሙሉቀን በለዉ የወረዳዉ አካባቢና ደን ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ፣የተቋማት የስራ ኃላፊዎችና የወረዳዉ የመንግስት ሰራተኞች ተገኝተዋል።

የቋራ ወረዳ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ በወረዳው የሚገኘውን ሆስፒታል፣ የከተማ ፋርማሲና እየተሠሩ ያሉ መሠረተ ልማቶችን ተዘዋውረው የመስክ ምልከታ አደረጉ።ገለጉ:- ግንቦት 28/2018 ምክር ቤቶ...
05/06/2026

የቋራ ወረዳ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ በወረዳው የሚገኘውን ሆስፒታል፣ የከተማ ፋርማሲና እየተሠሩ ያሉ መሠረተ ልማቶችን ተዘዋውረው የመስክ ምልከታ አደረጉ።

ገለጉ:- ግንቦት 28/2018 ምክር ቤቶች በደንብ ቁጥር 12/2003 በተሠጣቸው ተግባርና ሀላፊነት መሠረት አሰፈጻሚውን አካል መከታተልና መቆጣጠር እንዲሁም የተሠሩ ሥራዎችን በመጎብኘት አሰተያየት ይሰጣሉ ይሕን መነሻ በማድረግ በዛሬው እለት የቋራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን፣ የከተማ መድሐኒት ቤትንና በገለጉ መሪ መዘጋጃ ቤት እየተሠሩ የሚገኘውን የውስጥ ለውስጥ የመንገድ ጠረጋና አነስተኛ የድልድይ ስራ በአካል በመገኘት የመሥክ ምልከታ ማድረጋቸውን የቋራ ወረዳ ምክር ቤት ገልፃዋል።

በጉብኝቱ የተገኙት የወረዳው ዋና አፈ - ጉባኤ የተከበሩ አቶ ኑርሑሴን ማሕሙድ እንደገለጹት እንደ ክልል የገጠመን የሠላም ችግር ሣይበግረን በወረዳችን ሕዝብን ሊጠቅሙ የሚችሉ የተለያዩ ስራዎች እየተሠሩ መሆኑን ገልጸው ዛሬ በጉብኝታችን የተመለከትናቸው ስራዎች ትልቅ ማሣያ ስራዎች መሆናቸውን ብለዋል።

ምክር ቤት ጽ/ቤቱና ቋሚ ኮሚቴዎች ደግሞ ጉባኤ ከማድረግ ባሻገር ሕዝብን ሊጠቅሙ የሚችሉ ስራዎችን ያሉበትን ሁኔታ በአካል በመገኘት መገምገም መቻሉ የተቋሙ ትልቁ ተግባርና ቋሚ ኮሚቴዎችም የሕዝብ እንደራሴነታቸውን የሚያረጋግጡበት ተግባር መሆኑንም አንስተዋል።

ሌላኛው በጉብኝቱ ከተገኙ ቋሚ ኮሚቴዎች መሐከል የተከበሩ አቶ ሐሊቡ ገብሩ እንደገለጹት በሆስፒታሉና በከተማ መድሐኒት ቤቱ እየተሠጡ ያሉ አገልግሎቶች የሚበረታቱ መሆኑን ገልጸው ቀጣዩ የክረምት ወራት ስለሚገባ ሕብረተሰቡ በሕክምና መድሐኒት እጥረት ችግር ላይ እንዳይወድቅ ከወዲሁ ግብአት እንዲያሟሉ አሳስበዋል።

የተከበሩ አቶ ጨቅሌ መለሠ እንደገለጹት የገለጉ መሪ መዘጋጃ እያከናወናቸው ያለውን ተግባራት አድንቀው የተከፈቱ መንገዶች ጠጠር እንዲለብሱና አነስተኛ ድልድዩም በፍጥነት ተጠናቀው ለሕዝብ አገልግሉት እንዲውሉ ሐሣባቸውን ገልፃዋል።

በመጨረሻውም በጉብኝቱ የታዩ ጠንካራ ጎኖች እንዲቀጥሉና በክፍተትነት የታዩ ስራዎች ማሥተካከያ እንዲደረግባቸው አሰተያየት በመሥጠት የመሥክ ምልከታው ተጠናቋል።

Address

Quara
Gondar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Quara Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Quara Communication Affairs Office:

Share