Quara media

Quara media We deliver accurate and factual information to our society

በጎንደር ትላንት ውጥረት ፈጥሮ የዋለው መከላከያ ተቃውሞ ገጠመው። ጎንደር በዚህ ሰዓት ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም። መንገዶች ተዘግተዋል ፣ በመከላከያ ስም ታጥቆ የመጣው የኦነግ ሸኔ ገዳ...
04/05/2023

በጎንደር ትላንት ውጥረት ፈጥሮ የዋለው መከላከያ ተቃውሞ ገጠመው።

ጎንደር በዚህ ሰዓት ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም። መንገዶች ተዘግተዋል ፣ በመከላከያ ስም ታጥቆ የመጣው የኦነግ ሸኔ ገዳይ ቡድን ከድንበሩ ውጭ ከአማራ ክልል ከተሞች ላይ ባስቸኳይ ለቆ መውጣት አለበት ተብሏል።

®®®አሻራ ሚዲያ

የፕሬስ ነጻነት ችግር በስፋት የሚታይባቸው 10 የአፍሪካ ሀገራት*****     *******አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከደቡባዊ አፍሪካ ሚዲያ ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ባስጠናው ጥናት ኢትዮጵያን ጨ...
04/05/2023

የፕሬስ ነጻነት ችግር በስፋት የሚታይባቸው 10 የአፍሪካ ሀገራት
***** *******
አምነስቲ ኢንተርናሽናል ከደቡባዊ አፍሪካ ሚዲያ ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ባስጠናው ጥናት ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ የፕረስ ነጻነት ችግር ውስጥ ነው ብሏል።በኢትዮጵያ በ2022 ብቻ 29 ጋዜጠኞች ታስረዋል ተብሏል።

©አል ዐይን አማርኛ

03/05/2023

አማራው ላይ የሚደረገው ዘመቻ ከአቶ ግርማ የሺጥላ ሞት ጋር ግንኙነት የለውም። የአቶ ግርማን ሞት አማራው ላይ የጀመሩትን ዘመቻ ማጠናከሪያ ነው ያደረጉት።

#አማራው ላይ ዘመቻ የተጀመረው በጦርነቱ ወቅት ያሳየው ስነልቦና ስላስፈራቸው ነው። ብርሃኑ ጁላ መሃል አገር እየተዝናና ከባድ መሳርያ አዘርፎ አገር ሲያስወጋ የአማራ አርሶ አደር በዱላና መጥረቢያ ጭምር ከሰራዊቱ የተቀማ መሳርያ አስመልሷል።

#ገዥዎቹ ሁለት ልብ ሲሆኑ አገር ቤት ያለው ብቻ ሳይሆን በውጭ ይኖር የነበረው አማራ ወደ ጦር ሜዳ መጥቷል።

#በጦርነቱ ወቅት የአማራውን አቅም የተመለከቱት ገዥዎች አማራ ከጦርነት ማግስት በዚህ ስነ ልቦናው ከተመለሰ አደገኛ ነው ብለው ፈርተዋል። ሰላማዊውን ዜጋ ወደ አዲስ አበባ እንዳይገባ በመከልከል "ፅንፈኛ ፋኖ፣ኤርትራ ያሰለጠነችው" ማለት የጀመሩት በዚህ ፍርሃት ምክንያት ነው።

#አማራው የጠነከረ ስነ ልቦና እንዳለው ቢያውቁም የአማራ ብልፅግና አብሯቸው የሚውል እንኩቶ ጥርቅም እንደሆነ ያውቁታል። አንድ ቀን "ትግል ወዘተ" ብሎ መግለጫ አወጣ። ከዛ በኋላ የት እንዳለ አይታወቅም።

#ገዥዎቹ ዘመቻውን በጦርኑ ስነ ልቦና ሰግተው ቢጀምሩትም የመከላከያ ሰራዊት አባላት በቁርጥ ቀን ማን አብሮት እንደነበር ያውቃል። ምንም እንኳ ዕዙ በአማራ ህዝብ ላይ የጥላቻ ወዝ በጠገቡት የሚመራ ቢሆንም በደንብ ከተሰራበት የመከላከያ ሰራዊቱ አባላት የህዝብን ውለታ ያውቁታል። በዚህ ዘመቻ በርካታ ምልክቶች ታይተዋል።

#አሁንም መታወቅ ያለበት ህዝብ ሲፈጅ የከረመን ኦነግ በዓለም አቀፍ መድረክ እየተደራደረ፣ አገር ያዳነን ኃይል ለመምታት የሚደረገው አካሄድ አገር ከማፍረስ ውጭ አላማውም ውጤቱም አያምርም። ገዥዎቹ አማራውን ከየ አቅጣጫው አዳክመው ርስቶቹን አስረክበው አንገቱን አስደፍተው "ስልጣናችን ቀና ብሎ እንዳያይ እናደርገዋለን" ብለው አስበዋል። የዘመቻው አላማ ይሄ ነው። የሚሆን አይደለም።

shifrew

ወዴት እየሄድን ነው???**ነብሦ ይማር**
28/04/2023

ወዴት እየሄድን ነው???

**ነብሦ ይማር**

26/04/2023

በሀገረ ሱዳን የተፈጠረውን አለመረጋጋት ሸሽተው የሚመጡ የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜጎችን የምእራብ ጎንደር ዞን መተማ ዮኋንስ ከተማ በሰላም እያስተናገደች ነው
** ** **
በጎረቤት ሀገር ሱዳን የእርስ በእርስ ግጭት ምክንያት የተለያዩ ሀገር ዜጎች በመሸሽ በምእራብ ጎንደር ዞን መተማ ዮኋንስ ከተማ በኩል እየገቡ ነው። በተፈጠረው የውስጥ አለመረጋጋት ምንክያት ጦርነቱን ሸሽተው ከካርቱም ወደ ጎረቤት ሀገር ኢትዩጵያ የሱዳን ዜጎችን ጨምሮ የ23 ሀገራት የተለያዪ ሃገራት ዜጎች እንደገቡና ወደ ሚፈልጉት አካባቢ እየሄዱ ይገኛሉ።

በዚህም የምዕራብ ጎንደሯ የፍቅር ከተማ መተማ ዮሃንስ ከተማ እንግዶቿን እያስተናገደች ሲሆን በቀን ከ15-20 የሚሆኑ መኪናዎች ወደ ጎንደር እየሄዱ ይገኛሉ ። በዚህ የጦርነት ስጋት ሺሽትም ህፃናት፣ ሴቶች እና አቅመ ደካሞች ይገኙበታል።

የመተማ ዮሃንስ ከተማ አስተዳደር፣ የዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ የሚመለከታቸው የፀጥታ አካላትም ዜጎች ያለምንም እንግልት ወደ ሚፈልጉት አካባቢ እንዲደርሱ ሰብአዊ ተግባራትን እየተከናወነ እንደሆነ ተገልጿል።

ዘገባው፦ የምዕራብ ጎንደር ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ነው።

23/04/2023
21/04/2023
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች  እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅር እና የጤና እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!!!
20/04/2023

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!

በዓሉ የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅር እና የጤና እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!!!!

የአማራ ክልል ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውል ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል፡፡                         *** *** *** የአማራ ክልል ለታላ...
20/04/2023

የአማራ ክልል ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውል ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል፡፡
*** *** ***
የአማራ ክልል ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የሚውል ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ማድረጉን የአማራ ክልል የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ ማሥተባበሪያ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡

የጽሕፈት ቤት ኀላፊው አቶ ኃይለሚካኤል ካሳሁን እንደገለጹት የአማራ ክልል ለታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ እያደረገው ያለው አስተዋጽኦ ይበል የሚያሠኝ እና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው ብለዋል፡፡

አቶ ኃይለሚካኤል እንዳሉት ድጋፉ የመሠረት ድንጋይ ከተጣለበት ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ መኾኑንም አንስተዋል፡፡

ድጋፉ ከልዩ ልዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች በቦንድ ግዥ፣ በልገሳ፣ በልዩ ልዩ ገቢ ማስገኛ ፕሮግራሞች እና በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ሥራዎች የተደረገ ታሪካዊ ድጋፍ ነው ብለዋል፡፡

የተደረገው ድጋፍ ፡-

👉ከመንግሥት ሠራተኞች 510 ሚሊዮን 429 ሺህ 476 ብር

👉ከባለሃብቱና ከንግዱ ማኅበረሰብ 100 ሚሊዮን 270 ሺህ 876 ብር

👉ከአርሶ አደሮች 236 ሚሊዮን 20 ሺህ 455 ብር

👉ከድርጅቶችና ተቋማት እንዲሁም ከልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ብር 330 ሚሊዮን 732 ሺህ 723 ብር

👉በልገሳ ከተለያዩ የኅብረተስብ ክፍሎች የተሰበሰበ 9 ሚሊዮን 289 ሺህ 665 ብር

👉ከልዩ ልዩ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክቶችና ፕሮግራሞች ብር 31 ሚሊዮን 388 ሺህ 850 ብር ሲሆን

➨በአጠቃላይ 1 ቢሊዮን 218 ሚሊዮን 132 ሺህ 46 ብር መሰብሰብ ተችሏል ነው ያሉት፡፡

የአማራ ክልል ሕዝብ ለግድቡ ግንባታ ገንዘብ ከማዋጣት በተጨማሪ ግድቡ በደለል እንዳይሞላ ለማድረግ በተፈጥሮ ሃብት ልማት ጥበቃ ሥራዎች ላይ ባደረገው ያላሰለሰ ተሳትፎ ከ33 ቢሊዮን 797 ሚሊዮን 786 ሺህ 822 ብር የሚገመት የጉልበት ድጋፍ ማደረጉንም አቶ ኃይለሚካኤል አስረድተዋል፡፡

አሚኮ

ሸኔ በሶደሬ…"…ትናንት ከምሽቱ 3:00 እስከ 4:00 ሰዓት ሲሆን በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ከናዝሬት በቅርብ ርቀት የሚገኘው የሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይ ከ50 በላ...
19/04/2023

ሸኔ በሶደሬ…
"…ትናንት ከምሽቱ 3:00 እስከ 4:00 ሰዓት ሲሆን በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ከናዝሬት በቅርብ ርቀት የሚገኘው የሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይ ከ50 በላይ በሚሆኑ የታጠቁ ኃይሎች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተነግሯል። ታጣቂዎቹ አልከፈት ያላቸውን የቤተ መቅደሱን በር ቦንብ አፈንድተው ሰብረው በመግባት ንዋያተ ቅድሳቱን አውድመዋል። የቤተ ክርስቲያኑን አስተዳዳሪ ቤትም ሰብረው በመግባት በወቅቱ አስተዳዳሪው ባይኖሩም በቤት ዕቃዎች ላይ ጉዳት፣ በካህናቱም ላይ ከፍተኛ ማዋከብ ፈጽመዋል፣ የደብሩንም በመውሰድ እስከአሁን እንዳልለቀቋቸው ተሰምቷል።

Ethiosat. Net

Address

Gonder

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Quara media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Quara media:

Share