ወሎ ኢስላማዊ ሚድያ ኔትዎርክ/Wello Islamic Media Network WIMN

  • Home
  • Ethiopia
  • Haik
  • ወሎ ኢስላማዊ ሚድያ ኔትዎርክ/Wello Islamic Media Network WIMN

ወሎ ኢስላማዊ ሚድያ ኔትዎርክ/Wello Islamic Media Network WIMN ኢስላማዊና አዳድስ
መረጃዎችን ለመላው ሙስሊም ማድረስ በአለም ዙሪያ ያሉ መረጃዎችን ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ ማድረስ

ደቡብ ወሎ ዞን ወታደራዊ አመራሮችን የአዋጊነት ስልጠና መስጠቱን በFB ገፁ አንብቤያለሁ።ነገር ግን ዱላ ይዞ አይደለም ሰው ከብት መጠበቅ የሚቀርበትን ሁኔታ መፍጠር ግድ ይለናል። ውጭ አገር ...
25/04/2025

ደቡብ ወሎ ዞን ወታደራዊ አመራሮችን የአዋጊነት ስልጠና መስጠቱን በFB ገፁ አንብቤያለሁ።ነገር ግን ዱላ ይዞ አይደለም ሰው ከብት መጠበቅ የሚቀርበትን ሁኔታ መፍጠር ግድ ይለናል። ውጭ አገር ላይ ያለውን ቴክኖሎጅ ሳየው ኢትዮጵያ ታሳዝነኛለች።ከተማ ላይ ዱላ ይዞ ፖሊስ ሰው ሲጠብቅ ጎዳና ለጎዳና ግዳጅ ሲወጣ በጣም አዝኛለሁ።ለካስ መሪዎቻችን ወጣ ብለው አገር አያዩም ነበር ማለት ነው። መሳሪያና ሙሉ የውጊያ ትጥቅ ታጥቀህ ከተማ ላይ ፓትሮል ማድረግ ያሳፍራል።ውጩ አለምኮ በጣም አድጓል።እነ ዱባይ ላይ ፖሊስ ያየሁት ከወር ኋላ ነው።መሳሪያማ በጭራሽ አይቸ አላውቅም።ከመጣሁ ብዙ ቦታዎችን አይቻለሁ ወታደር አይቸ አላውቀም።ትራፊክ የሚባል ነገር ምንም የለም።ሁሉም ነገር በቴክኖሎጅ ነው።ወንጀል ሰርተህ 15 ደቂቃ አትቆይም ስትያዝ።በእርግጥ ዶክተር አብይ እድል ከሰጠነው የኢማራትን ቴክኖሎጅ አገራችን ላይ ያሳየን ይሆናል።የተጀመሩ ስራዎች ኮሊደር ልማቶች ሁሉ የሚያመላክቱት የውጩን አለማት የስልጣኔ ደረጃ ወደ አገራችንም እየገባ መሆኑን ነው። በቅርቡ በአላህ ፈቃድ መሳሪያና ዱላ የያዘ ፖሊስ የማናይባት ኢትዮጵያን እናያለን። ሰው እየጠበቅንኮ ልማት ማልማት አይቻልም። መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከአፈሙዝና ዱላ መውጣት አለበት።

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ، أَنَّ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ : " خَيْرُ يَوْمٍ طَلَعَتْ عَلَيْهِ الش...
25/04/2025

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ، أَنَّ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ : " خَيْرُ يَوْمٍ طَلَعَتْ عَلَيْهِ الشَّمْسُ يَوْمُ الْجُمُعَةِ ؛ فِيهِ خُلِقَ آدَمُ، وَفِيهِ أُدْخِلَ الْجَنَّةَ، وَفِيهِ أُخْرِجَ مِنْهَا، وَلَا تَقُومُ السَّاعَةُ إِلَّا فِي يَوْمِ الْجُمُعَةِ ". (مسلم)
ፀሐይ ከወጣችባቸው ቀኖች ሁሉ በላጩ የጁሙዓ ቀን ነው።
በጁሙዓ ቀን👉አደም ዓለይሂ ሰላም የተፈጠረበት
👉አደም ዓለይሂ ሰላም ጀነት የገባበት
👉አደም ዐለይሂ ሰላም ከጀነት የወጣበት
👉 የትንሳኤም ቀን በጁሙዓ ቀን እንጅ አትቆምም!!!

21/04/2025
የአህባሾችን ጉድ ተመልከቱ በወሀብያ ላይ ቁርአን እንደቀሩ ይናገራሉአዎ ለዚያምኮ ወረቀት ጫሪ ያሲን ከራሪ ያሉት ሐጅ ወሌ ረሀሂመሁሏህ እነዚህ ድንጋይ ጣይ ጠንቋዮች
19/04/2025

የአህባሾችን ጉድ ተመልከቱ በወሀብያ ላይ ቁርአን እንደቀሩ ይናገራሉ
አዎ ለዚያምኮ ወረቀት ጫሪ ያሲን ከራሪ ያሉት ሐጅ ወሌ ረሀሂመሁሏህ እነዚህ ድንጋይ ጣይ ጠንቋዮች

ወርጣየ ላይ የተዋቀረው  ፀረ-ሠላም ኮሚቴ=====================017 ሰግለንና 027 ቀበሌዎች ላይ የተዋቀረው የሠላም ኮሚቴ የተባለው አደረጃጀት በህዝብ ላይ ችግር ሲፈጥር የነበረ...
18/04/2025

ወርጣየ ላይ የተዋቀረው ፀረ-ሠላም ኮሚቴ
=====================
017 ሰግለንና 027 ቀበሌዎች ላይ የተዋቀረው የሠላም ኮሚቴ የተባለው አደረጃጀት በህዝብ ላይ ችግር ሲፈጥር የነበረና ማህበረሰቡን ለግጭት ሲዳርግ የነበረ ፀረ-ሰላም ነው።ሲጀመረ ይህ ቡድን የተዋቀረው ሊኤከ አሊ በተባለው የቀድሞው የተሁለደሬ ወረዳ አስተዳደር ፀጥታ ሐላፊ የነበረና ሌሎች ካቢኔዎች በመሆን ከሁለት አመት በፊት የተመሰረተ ሲሆን መስራቾቹ በቀሌው ላይ ሰላም እንዳይፈጠር ህዝብ ከህዝብ አየተጋጨ አንድነት እንዳይኖርና ሌሎች ፅንፈኛ ሐይሎችን ወደ ቀበሌው ለማስገባት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠረ ታልሞ የተዋቀረ ነው።
አወቃቀሩን ስንመለከት አህባሽ የሚባለው ቡድን ዋና ዋና አቀንቃኝና ሙስሊሞችን ለማጥቃት ይመቻሉ የተባሉ ሰዎች ተመርጠው ነው የኮሚቴ መዋቅሩ የተሰራው።ከላይ እንደከቨረ የተጠቀሙት የሰላም ኮሚቴ የሚል ሽፋን ከጡት በኋላ የተሰጠው ተልዕኮ ግን ከዚህ በተቃራኒ ነበር።
የሠላም ኮሚቴ ተብየው ምን ሲሰራ ነበር የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም መቸም!
1/ ወሀብያ ሱፍያ እያለ ልዩነቶችን በማስፋት ከቅሬና አበጋር እንድሁም ከቃድዎች በመሆን ከቅሬ እያፈናቀለ በጋራ ሰርቶ በጋራ አምርቶና በጋራ አገርን ማለማት እንዳይቻል አድርጓል።ፌንጥ ያስባላቸው ሰዎች ዝርዝር በአጠቃላይ በሁለቱም ቀበሌ ከ130 በላይ ናቸው።
2/ በሆነ ሰበብ እየፈጠሩ 10ሽ፣30ሽ እየቀጡ በአጠቃላይ 1.5ሚ ብር ያላነሰ ሰብስበው ጫት ቅመውበታል።መረጃዎቹ እጃችን ላይ አሉ።
3/ ወጣቶች አካባቢያቸውን ለመጠበቅ አደረጃጀት ሰርተው ሲንቀሳቀሱ የሠላም ኮሚቴ ተብየው ግን ከጎናቸው መሆን ሲገባው አስተንክር የተባለ ቦታ ከባሪጎና መርኮታ አንድሁም በዚያ ዙሪያ ያሉ አበጋሮችን ቃድዎችንና ቅሬ መሪዎችን በማሰባሰብ ከኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ ጋር እየተመካከሩ አደረጃጀት እየሰሩና ሰልጣኞችነ እየመለመሉ ነበር።ነጭ ነጩን አገር የሚያውቀውን ወርጣየ ወርዳችሁ አንዱን ገበሬ ብትጠይቁት ከስር መሰረቱ የሚነግራችሁን በጠራራ ፀሐይ የተሰራ እውነት ነው የምነግራችሁ።
4/ ሸህ ሙሀመድ ነጅብ የደቡብ ወሎ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት መስጅድና አውቃፍ ዘርፍ ተጠሪ የሆኑት በወንድማቸው አማካኝነት ተፈጠረ በተባለው ሰው የማጥፋት ወንጀል ከሞተባቸው ቤተሰቦች ጋር ዳግሞ ሌላ ችግር እንዳይፈጠር ለማስታረቅ የተያዘውን ፕሮግራም ያደናቀፈው ይሄው የሠላም ኮሚቴ ነኝ ባዩ ፀረ-ሠላም ቡድን ነው። ሰግለን የወዳው ሚሊሻ ጽ/ቤት ሐላፊና ምድብተኛ ካቢኔው ፋንታሁን ባሉበትየሠላም ኮሚቴውን ህገ-ወጥ ተግባር አጋለጨ ነበር።የሸህ ነጅብንና የቤተሰባቸውን እርቅ ያደናቀፈው የሠላም ኮሚቴ መሆኑን ሳቀርብ አምነው አሁንም አይታረቁም ምን ታመጣላችሁ ብለውኛል።እስከ አሁንም እርቅ እንዳይፈፀም ተደርጓል።ለምን ከተባለ እርቅ የሚያስፈልገው ሰላም ለመፍጠር ነው።ኮሚቴው የተዋቀረበት አላማ ደግሞ ግድያና ግጭትን በመፍጠርና በማባባስ ፅንፈኞችን ወደ ቀበሌው ማስገባት ነው።
5/ ይህ የሠላም ኮሚቴ ተብየ የተሰጠውን ተልዕኮ በሚገባ በመወጣት ቀጠናውን ሠላም በማሳጣት በህዝብ ላይ ኪሳራ በማሳደር ተሳክቶለታል።ነገር ግን ይህን ሁሉ ካደረገም በኋላ ዛሬም የሰላም ኮሚቴ የሚል አካል ተሁለደሬ ውስጥ አለ። ነገር ግን የወርጣየ ህዝብ በሚገባ ያለውን ችግር ጠንቅቆ ያውቃል።
በመጨረሻም ለተሁለደሬ ወረዳ አመራሮች ያለኝ ምክረ ሐሳብ የሰላም ኮሚቴውን በማፍረስ በአድስ መልክ ወጣቶችን የሐይማኖት ተወካዮችን የቅሬ መሪዎችን ምሁራኖችንና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችን ያካተተ ኮሚቴ ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ማለትም ከወጣቶች፣ከመንግስት ሰራተኛ፣ ከሰለፊያዎችም ከአህባሾችም እኩል ቁጥር ያላቸው በማድረግ ቢዋቀር እና በደንብ ስልጠና ተሰጥቷቸው መተዳደሪያ ደንብ ወጥቶላቸው እንድሰሩ ቢደረግ
ልዩነቶችን በማጥበብ፣ የጋራ ጉዳዮችን በደንብ ለይተውና አደረጃጀታቸውነ አስፍተው ወርጣየ ላይ የሰላም ግንባታውን ፍትህ አኩልነት፣ ከአድሎ የፀዳ እንድሁም ቢሮክራሲ የሌለበት አሰራር በመዘርጋት የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን በማህበሰቡ ርብርብ የሚሰሩበትን ሁኔታ መፍጠርና የተማረና የሰለጠነ ከሱስ የፀዳ ትውልድ መፍጠር በሚቻልበት ሁኔታ ቢሰራ የሚለውን ሐሳብ እያቀረብኩ በማድረግ መልዕክቱን ተደራሽ አድርጉ።
2/

Address

Haik
017

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ወሎ ኢስላማዊ ሚድያ ኔትዎርክ/Wello Islamic Media Network WIMN posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ወሎ ኢስላማዊ ሚድያ ኔትዎርክ/Wello Islamic Media Network WIMN:

Share