Harar news

Harar news never ever give up

12/08/2026

Celebrating my 3rd year on Facebook. Thank you for your continuing support. I could never have made it without you. 🙏🤗🎉

19/07/2026

Never g8ve up👍❤

25/06/2026

it taks 0000.00001 seconda❤

19/06/2026

ቴሌብር አካውንት ከፍተን በማስጀመር በስጦታ እንንበሽበሽ!

ቴሌብር ላይ ስንመዘገብ እና default pin ስንቀይር የእንኳን ደህና መጣችሁ 15 ብር ስጦታ፤ ከ100 ብር በታች አየር ሰዓት ስንሞላ 15% ስጦታ ፤ 100 ብር እና ከዛ በላይ አየር ሰዓት ስንሞላ 25% ምርቃት ፤ በቴሌብር ጥቅል ስንሞላ 10% ተጨማሪ የጥቅል መጠን እንዲሁም ቴሌብር ሱፐርአፕ አውርደን ስንጠቀም 100 ሜ.ባ ዳታ ስጦታ ወደስልካችን በቀጥታ ይገባል! በቴሌብር ስንመረቅ እንዲህ ነን!

ቴሌብር ሱፐርአፕን
https://bit.ly/telebirr_SuperApp ጭነን ስንመዘገብ እንዲህ ነን!




 #ኢመደአ ለኢትዮጵያ ባህር ኃይል ከፍተኛ መኮንኖች የሳይበር ደህንነት ስልጠና ሰጠየኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ለኢትዮጵያ ባህር ኃይል ከፍተኛ መኮንኖች የሳይበር ደህን...
04/05/2026

#ኢመደአ ለኢትዮጵያ ባህር ኃይል ከፍተኛ መኮንኖች የሳይበር ደህንነት ስልጠና ሰጠ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ለኢትዮጵያ ባህር ኃይል ከፍተኛ መኮንኖች የሳይበር ደህንነት ንቃተ-ህሊና ማጎልበቻ ስልጠና ሰጥቷል። ይህ ስልጠና በዋነኝነት ትኩረቱን ያደረገው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዙ ወታደራዊ ኦፕሬሽኖች ላይ ሊሰነዘሩ የሚችሉ የሳይበር ጥቃቶችን አስቀድሞ ለመከላከልና የተቋሙን የመረጃ ደህንነት ለማረጋገጥ በሚያስችሉ ስልቶች ላይ ነው። ስልጠናው በዘመናዊው የቴክኖሎጂ ዘመን ለሀገር መከላከያ ዘርፍ አስፈላጊ የሆነውን የዲጂታል እውቀት ለማስጨበጥ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

በስልጠናው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ኮሞዶር ጀማል ቱፊሳ እንደገለጹት፣ ስልጠናው ሁለቱ ተቋማት ከዚህ ቀደም በነበራቸው የመግባቢያ ስምምነት መሠረት የተከናወነ ሲሆን በተለይም በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በመረጃ ልውውጥና በሰው ኃይል ልማት ዙሪያ ተቋማቱ በጋራ ለመሥራት የገቡትን ቃል የሚያሳይ እንደሆነ ተመላክቷል። ስልጠናው የሁለቱን ተቋማት ስትራቴጂካዊ አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረውም ኮሞደሩ ገልጸዋል።

ኮሞደሩ አክለውም የባህር ኃይሉ የሚጠቀማቸው ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች ለሳይበር ጥቃት ተጋላጭ ሊሆኑ እንደሚችሉ በመጠቆም፣ ስልጠናው እነዚህን መሣሪያዎች በጥንቃቄ ለመያዝ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ውጤታማና ስኬታማ ወታደራዊ ኦፕሬሽን ለመፈጸም የቴክኖሎጂ መሠረተ-ልማቶችን ከጠላት ጥቃት መጠበቅ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፣ ስልጠናው የአባላቱን የመከላከል አቅም እንደሚያሳድግ እምነታቸውን ገልጸዋል።

በመጨረሻም ኮሞደሩ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር የዲጂታል ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን በመጥቀስ፣ መሰል የንቃተ-ህሊና ማጎልበቻ መድረኮች በቀጣይነት በተለያዩ የኃይል ክፍሎች ውስጥ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጿል። የባህር ኃይሉ ወደፊትም ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በቅርበትና በአጋርነት እንደሚሠራም አረጋግጠዋል።

ተጨማሪ የሳይበር ደህንነት መረጃዎችን ለማግኘት፡-
• ድረ ገጽ፦ https://www.insa.gov.et
• ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/INSA.ETHIOPIA
• ቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/?_t=8qBKkyp092r&_r=1
• ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com//featured
• ቴሌግራም፦ https://t.me/insagovet
• ትዊተር (X) ፦ https://twitter.com/INSAEthio
• ሊንክድኢን:- https://www.linkedin.com/.../information-network.../
• የሳይበር ጥቃት ጥቆማ ለመስጠት፡- ነጻ የስልክ መስመር 933

The Information Network Security Administration (INSA) was first established in 2007 by the Council of Ministers Regulation No. 130/2007 with the aim of protecting our country's information and information infrastructures from attacks and safeguarding national interests. Our ...

04/05/2026

ሰበር ዜና፦ አዲስ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ጭማሪ ተደረገ

ላይ የ25 ብር ጭማሪ ተደረገ።

አዲስ አበባ | ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዛሬ ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ስራ ላይ የሚውል አዲስ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ማስተካከያ ማድረጉን አስታውቋል።

#ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ መሠረት፣ የዋጋ ማስተካከያው የተደረገው የዓለም የነዳጅ ዋጋ መነሻ በማድረግና በሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀደም ሲል በተላለፈው የዋጋ ግንባታ አፈጻጸም ውሳኔ መሠረት መሆኑ ተገልጿል።

በአዲሱ የዋጋ ማስተካከያ መሠረት ከተማ የሚኖረው የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በሊትር፦**

1. #ቤንዚን፦ 167.50 ብር
2. #ኬሮሲን፦320.66 ብር
3. ነጭ ናፍጣ፦180.46 ብር
4. #ቀለል ያለ ጥቁር #ናፍጣ፦170.62 ብር
5. ከባድ ጥቁር ናፍጣ፦167.37 ብር
6. የአውሮፕላን #ነዳጅ፦319.76 ብር

#መንግስት ይህ የዋጋ ማስተካከያ ከዛሬ ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን የወሰነ ሲሆን፣ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላትም መመሪያው መላኩ ታውቋል።

©️የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር

ውድ ተከታታዮቻችን፣ ይህ የዋጋ ጭማሪ በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎቻችሁና በኑሮ ውድነቱ ላይ ያለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ያላችሁን አስተያየት በኮመንት መስጫው ላይ ያካፍሉን።

  ODUU ARIIFACHIISAA: RUUSIYAAN WARAANA SEENTEE?Pirezidaant Puutiin misaa'elota baalistiikii gosa "Satan II" jedhaman 50...
07/04/2026

ODUU ARIIFACHIISAA: RUUSIYAAN WARAANA SEENTEE?

Pirezidaant Puutiin misaa'elota baalistiikii gosa "Satan II" jedhaman 50 gara Iiraantitti akka ergaman ajaja dabarsaniiru. Puutiin, "Ameerikaan amma dhiiftee yoo baate malee ni baddi," jechuun akeekkachiisa cimaa kennaniiru.

Qabxiilee Ijoo:
✅Meeshaa Waraanaa: Meeshaan "Satan II" jedhamu kun humna guddaa kan qabuu fi fageenya dheeraa rukutuu kan danda'u dha.

✅Akeekkachiisa Puutiin: Ameerikaan dhimma Iiraan keessaa akka harka ishee baastu akeekkachiisaniiru.

✅Haala Ammaa: Kunis wal-dhabdee Ameerikaa fi Iiraan gidduu jiru gara lola addunyaatti geessuu danda'a.

  ብላለችአሜሪካ ማየት የምትችለውን ዒላማ ሁሉ ደብድባ ጨርሳለች። ይሄ ቀረኝ የምትለው የላትም። ቀራት ከተባለ የኢራን ሰላማዊ ህዝብ የሚጠቀምባቸው ድልድዮች፣ የነዳጅ ማውጫዎች/ማጣሪያዎች እና...
07/04/2026

ብላለች

አሜሪካ ማየት የምትችለውን ዒላማ ሁሉ ደብድባ ጨርሳለች። ይሄ ቀረኝ የምትለው የላትም። ቀራት ከተባለ የኢራን ሰላማዊ ህዝብ የሚጠቀምባቸው ድልድዮች፣ የነዳጅ ማውጫዎች/ማጣሪያዎች እና የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ናቸው። ለዛም ነው ዛቻዋ በእነዚህ የሲቪል ተቋማት ላይ የሆነው።

በሌላ በኩል ደግሞ አማሪካ ከነጀለሷ የሚሳይል እና የመከላከያ ስርዓታቸው ተተኳሽ ጨርሰዋል። የቀራቸው ውስን ቁጥር ያላቸው እጅግ አውዳሚ ሚሳይሎቻቸው ናቸው። በሚዝቱት መሰረት አውዳሚ ሚሳይሎቻቸን በኢራን የሲቪል መሰረተ ልማቶች ላይ ለማዝነብ የሚራራ አንጀት ወይም የሚያስብ ጭንቅላት ባይኖራቸውም ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ተላላኪዎች ላይ የምትወስደውን የአፀፋ እርምጃ የሚመክቱበት የአየር መከላከያ ስርዓት ተተኳሽ መጨረሳቸው ወይም መመናመኑ አሳሳቢ ሆኖባቸዋል።

የ45 ቀናት ተኩስ ማቆም ሀሳብ የመጣችሁ እዚህ ጋ ነው:: በኢምሬትና በሳውዲ ወጪ በአሜሪካ፣ በጀርመን እና በሌሎችም የአውሮፓ አገራት በገፍ የታዘዙት የድሮን፣ የሚሳይልና የአየር መከላከያ ስርዓት ተተኳሾች እስኪደርሱ በተኩስ ማቆም ስም የሆርሙዝ ሰርጥን አስከፍተው ኢኮኖሚያቸውን ይደጉማሉ። ጎን ለጎንም ደብዛቸው የጠፉት የኢራን ድሮኖች፣ ሚሳይሎች እና የአየር መከላከያ ስርዓቶች ያሉበት ቦታ በስለላና በሳተላይት ይለያሉ። ጎን ለጎንም በ45ቱ ቀናት ኢዝቦላንና ሀማስን በእግረኛ ጭምር አድቅቀው ኢራንን አጋር አልባ ያደርጓታል፤ በመጨረሻም ፊታቸውን ወደራሷኢራን መልሰው የቀራትን በአዲስ አቅርቦትና ጉልቦት በማወዳደም ያንበረክኳታል።

ለዚህም ነው ኢራን "ዘላቂ የተኩስ አቁም ካልሆነ . . ." የምትለው። "እኛም አውቀናል - ጉድጓድ ምሰናል" ማለት ይሄም አይደል❓😉

እናንተስ ምን ትላላችሁ❓🙂

Address

Harar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harar news posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share