አባድር ወረዳ አዜባች ሊግ/Abadir wareda youth league

  • Home
  • Ethiopia
  • Harar
  • አባድር ወረዳ አዜባች ሊግ/Abadir wareda youth league

አባድር ወረዳ አዜባች ሊግ/Abadir wareda youth league Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from አባድር ወረዳ አዜባች ሊግ/Abadir wareda youth league, News & Media Website, Harar.

Permanently closed.
19/08/2025
 ።የወጣቶች ክንፍ ሃለፊ አቶ ሙስጣፋ ኤሊያስ የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ በተለያዩ ሀገራዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳትፎ ከሚያደርግባቸው መንገዶች አንዱ የደም ልገሳ ፕሮግራሞችን ማ...
19/08/2025


የወጣቶች ክንፍ ሃለፊ አቶ ሙስጣፋ ኤሊያስ

የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ በተለያዩ ሀገራዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳትፎ ከሚያደርግባቸው መንገዶች አንዱ የደም ልገሳ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት ነው። ይህ ተግባር የማህበረሰብ አገልግሎትና የበጎ ፈቃደኝነት ባህልን ለማጠናከር ያለመ ነው።

ደም ልገሳ ምንም አይነት ማካካሻ ሳይጠብቁ በራስ ፍላጎት ላይ ተመስርቶ ደምን መለገስ ነዉ። ይህ ልገሳ በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች ህይወት ወሳኝ ነው ያሉት የወጣት ክንፉ ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሊያስ በሐረርም እንደሌሎች ሀገራት ሁሉ ለተለያዩ የህክምና ፍላጎቶች ደም ወሳኝ ነው።

ከእነዚህም መካከል፦ በወሊድ ጊዜ በሚከሰት ከፍተኛ የደም መፍሰስ ምክንያት ለሞት የሚዳረጉ እናቶችን ህይወት ለመታደግ ትልቅ ሚና ይጫወታል።

በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ጉዳት ለደረሰባቸውና ደም ለፈሰሳቸው ሰዎች አፋጣኝ የህክምና እርዳታ ለመስጠት ያገለግላል።

ለከባድ ቀዶ ጥገናዎች፣ ለካንሰር ህሙማን እና እንደ ታላሴሚያና ሲክል ሴል አኒሚያ ላሉ የደም ህመምተኞች ቀጣይነት ያለው የደም አቅርቦት ያስፈልጋቸዋል።ወጣት ክንፉ የጀመረውን በጎ ተግባር አጠናክሮ እንደሚያስቀጥልም አቶ ሙስጠፋ ኢሊያስ ገልፀዋል።

የድህረ እዉነት ዘመንን የዋጀ  ከመደመር እሳቤ የተቀዳ ሁሉንም አቅሞች ያሰባሰበ ኮሙኒኬሽን ለሁለንተናዊ ብልፅግና ስኬት ወሳኝ ነዉ  :-አቶ ዲኒር ዩሱፍ"በሀረሪ ክልል በአባዲር ወረዳ ለህዝብ...
18/06/2025

የድህረ እዉነት ዘመንን የዋጀ ከመደመር እሳቤ የተቀዳ ሁሉንም አቅሞች ያሰባሰበ ኮሙኒኬሽን ለሁለንተናዊ ብልፅግና ስኬት ወሳኝ ነዉ :-አቶ ዲኒር ዩሱፍ

"በሀረሪ ክልል በአባዲር ወረዳ ለህዝብ ግንኙነት አመራሮችና ባለሙያዎች በገዥ ትርክት ግንባታና የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሄደ።

የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዲኒር ዩሱፍ በፓርቲያችን 2ተኛው መደበኛ ጉባኤ አፅንኦት የተሰጣቸው ገዥ ትርክት እና የኮሙኒኬሽን ስራችን ዙሪያ ውጤታማ ተግባራት ለማከናወን ይረዳ ዘንድ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ መዘጋጀቱን በመክፈቻ መልእክት ያስተላለፏት

የህዝብ ግንኙነት አመራሮችና አባላት ማኅበራዊ ሚዲያውን ለገዥ ትርክት ግንባታ፣ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ ለዕውቀት ሽግግር እና የኢትዮጵያን እውነት ለመግለጥ ዘመነ መረብን የሚመጥን ጠንካራ የሚዲያ እና የኮሙኒኬሽን ሥራ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

የሚድያና ኮሙኒኬሽን ተግባራት የየዕለት ተግባር ነው ያሉት ሀላፊው የሚዲያ አጠቃቀማችንም የሀገር እና የህዝቦች አንድነት እና ወድማማችነትን ሊያጎለብቱ የሚገቡ ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል።

የሀረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ምክትል ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሴይፍ ጌታቸው በበኩላቸው ብዝሃነትን ማዕከል ያደረገ አሳባሳቢ ትርክት መገንባት ሁለንተናዊ እድገትና ብልፅግና ወሳኝ ሚና ያለው መሆኑን ገልፀዋል ።

የተዛባውን ትርክት በማከም፣ ልዩነትን በማጥበብና ስብራትን በመጠገን የብሔራዊነት ትርክት በመገንባት ሀገራዊ አንድነትን ማፅናት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

በመድረኩ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊና ምክትል ዘርፍ ኃላፊን ፣ የወረዳ አስተዳዳሪን ጨምሮ የወረዳ ፓርቲ ጽ/ቤት አመራሮች ተገኝተዋል።

15/06/2025
15/06/2025
15/06/2025
በዛሬው እለት ከአባዲር ወረዳ ወጣቶች ክንፍ አባላት ጋር “ሀገሬን እገነባለሁ ሀላፊነቴን እወጣለሁ” በሚል መሪ ቃል  ወጣቶች በሀገር እና ሀገረ መንግስት ግንባታ ውስጥ ያላቸው ሚና ላይ የተኮ...
23/05/2025

በዛሬው እለት ከአባዲር ወረዳ ወጣቶች ክንፍ አባላት ጋር “ሀገሬን እገነባለሁ ሀላፊነቴን እወጣለሁ” በሚል መሪ ቃል ወጣቶች በሀገር እና ሀገረ መንግስት ግንባታ ውስጥ ያላቸው ሚና ላይ የተኮረ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

👉 በዉይይቱ መድረክ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአባዲር ወረዳ አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አዚዛ ኢብራሂም የወጣቶች አደረጃጀት በማጠናከር እና በማቀናጀት ወጣቶች እርስ በእርስ በመደጋገፍ ፣ በመተባበር ቀጣይነት ባለው መልኩ መስራት እንዳለባቸው በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ የገለጽ ሲሆን አክለውም ወጣቱ የውል ትርክትን ለመገንባት የሚዲያ አጠቃቀምና ኮሚኒኬሽን ስራን ለሀገር ግንባታ መጠቀም አንዳለበትም ገልጸዋል።

👉 የውይይት መድረኩን የመሩት ወጣት ጫላ ሙኽታር እንደገለፁት ወጣት የዛሬ ሀገር በለቤትና የነገ ሀገር ተረካቢ እንድመሆኑ መጠን ክልላችን ላይ የተጀመረው ሁለንተናዊ ለውጥ ወጣቱ ግንባር ቀደም በመሆን በጋራ መግባባት በመተባበር እና በሰላም ግንባታ ጥረቶች ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት አሳስቦዋል። የመጣውን ለውጥ ለማስቀጠል ወጣት የሰላም አምባሳደር በመሆን የህዝቦችን አንድነትና ወንድማማችነት በማጠናከር ሁሉም ወጣት ለሀገር ግንባታ ኃላፊነቱን እንዲወጣና የበኩሉን ሚና ሊያበረክት ይገባል ብለዋል።

👉 በመድረኩ የማወያያ ሰነድ በወጣት በሃር መሃመድ ያቀረበ ሲሆን ወጣቱ የሀገር ባለቤት መሆኑን ተረድቶ በሀገር ግንባታ ላይ የድርሻውን ሊወጣና አሻራውን በግምባር ቀደምትነት ሊያሳርፍ ይገባል በማለት አክለዉም ወጣቱ ነጠላ ትርክቶችን በማክሰም ለብሔራዊ መግባባት ረሱን በማዘጋጀት ለገዥ ትርክት የበላይነት መሥራት እንዳለበት ተገልፀዋል።

Address

Harar

Telephone

+251915781257

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አባድር ወረዳ አዜባች ሊግ/Abadir wareda youth league posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to አባድር ወረዳ አዜባች ሊግ/Abadir wareda youth league:

Share