HU FM 91.5 RADIO

HU FM 91.5 RADIO Haramaya University Community Radio Station

"በጥሩ ውጤት በማለፋችን ተደስተናል" አሉ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ት/ቤት የ12 ክፍል ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ትምህርት ቤቱ ካስፈተናቸው ተማሪዎች 48.7 ከመቶ የሚሆ...
15/09/2025

"በጥሩ ውጤት በማለፋችን ተደስተናል" አሉ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ት/ቤት የ12 ክፍል ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች

ትምህርት ቤቱ ካስፈተናቸው ተማሪዎች 48.7 ከመቶ የሚሆኑ የዩኒቨርሲቲ መግቢየ ውጤት ማስመዝገባቸውን ትምህርት ቤቱ አስታውቋል።

የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን የትምህርት ሚኒስቴር በዛሬው ዕለት ይፋ ሲያደርግ ከ500 ነጥብ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ትምህርት ቤት ተማሪዎች በውጤቱ መደሰታቸውን ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ኤፍ ኤም 91.5 ተናግረዋል፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ትምህርት ቤት ተፈታኝ ተማሪ ያሬድ ተስፋዬ 533 ውጤት በማግኘት ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያሳለፈውን ውጤት አስመዝግቧል፡፡

ተማሪ ያሬድ ተስፋዬ አበበ "ከጠበኩት በላይ ወጤት በማግኘቴ ተደስቻለሁ" ሲል ስሜቱን ገልጿል፡፡

በተመሳሳይ የዩኒቨርሲቲው ሞዴል ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ የሆነኘችው ፌኔት መሐመድ ሐሰን 518 ነጥብ ውጤት አስመዝግባለች፡፡

ውጤቱን በተመለከተ "የልፋቴን በማግኘቴ ተደስቻለው" ስትል ደስታዋን ገልጻለች።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ስዩም ሸጋ ሞዴል ትምህርት ቤት ካስፈተናቸው 39 ተማሪዎች መካከል 19 ተማሪዎች ማለፋቸውን ተናግረዋል፡፡

ሶስት ተማሪዎች ከ500 በላይ የሆነ የማለፊያ ውጤት አስመዝግበው ማለፋቸውን የጠቅሱት ርዕሰ መምህሩ ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች "እንኳን ደስ አላችሁ" ብለዋል፡፡

ከዚህም ባሻገር በማካካሻ (ሬሚዲያል) መርሀ ግብር ትምህርታቸውን መከታተል የሚያስችላቸው ውጤት ያገኙ ተማሪዎች መኖራቸውንም ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡

ዘጋቢ፦ ይበልጣል ግዛው
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ኤፍ ኤም 91.5

  Godinoota baha fi lixaa hararghe fulbaana 06-20, 2018 aanooleen hundii isaan rooba ni argatu, irraa caala lafa gammooj...
15/09/2025



Godinoota baha fi lixaa hararghe fulbaana 06-20, 2018 aanooleen hundii isaan rooba ni argatu, irraa caala lafa gammoojjii kan ta'an kan duraan rooba hin argatin amma garuu rooba xiqqaa hangaa guddaa guyyaatti mm 30-100 roobu akka danda'uu ni eegama.

Girmaa Asaffaa: Kolleejii qonnaa fi saayinsii naannoo Yuunivarsiitii Haramaayaa
05/01/2018

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ ትምህርት ቤት ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለሁለተኛ ጊዜ በሙሉ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አስመዘገቡ ትምህርት ቤቱ ዘንድሮ ያስፈተናቸው ተማሪዎች...
15/09/2025

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ ትምህርት ቤት ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለሁለተኛ ጊዜ በሙሉ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አስመዘገቡ

ትምህርት ቤቱ ዘንድሮ ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ ውጤት በማምጣት ማለፋቸውን የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር አቶ አህመድ ደዶ ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ኤፍ ኤም 91.5 ተናግረዋል።

ከተማሪዎቹ ውስጥ አራቱ ከ500 በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ሲሆን የተቀሩት ከ400 በላይ እና 3 ተማሪዎች ብቻ ከ350 በላይ ውጤት ማምጣታቸውንና በዚህም ሁሉም ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባቸውን ውጤት ማግኘታቸውን አቶ አህመድ አብራርተዋል።

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ባቋቋመው ልዩ አዳሪ ያልሆነ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ከምስራቅ ሐረርጌ ወረዳዎች ውስጥ በ8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ እና ለመግቢያ በሚሰጠው ፈተና የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎችን ከ9ኛ ክፍል ጀምሮ የትምህርት ወጪያቸውን ሸፍኖ ዩኒቨርሲቲው ውስጥ በማስተማር ለውጤት እያበቃቸው መሆኑን የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር ተናግረዋል።

በ2017 ዓ.ም በተሰጠው የሀገር አቀፍ ፈተናን ወስደው ሁሉም ተማሪዎች በከፍተኛ ውጤት በማለፋቸው የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ መደሰቱንና ባለፈውም ዓመት ትምህርት ቤቱ ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ማስመዝገባቸውን አቶ አህመድ አስታውሰዋል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ጀማል ዩሱፍ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ያቋቋመው ልዩ አዳሪ ያልሆነ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ባስመዘገቡት ውጤት መደሰታቸውንና ተማሪዎቹን ለውጤት እንዲበቁ አስተዋፅዖ ላበረከቱ መምህራንና ሰራተኞች ምስጋና አቅርበዋል።

በተመሳሳይም የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ አዴሌ ከተማ ያቋቋመውና ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የቅርብ ክትትል የሚያደርግለት አዳሪ ትምህርት ቤት ዘንድሮ ያስፈተናቸውን ተማሪዎች በሙሉ በማሳለፉ መደሰታቸውን የትምህርት ቤቱ የአስተዳደር ቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ጀማል ተናግረዋል።

ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡት ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው ፣ መምህራኖቻቸው ፣ የአካባቢው መስተዳድር አመራሮች እና ለሐረማያ የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በሙሉ ዶክተር ጀማል የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ሬዲዮ ኤፍ ኤም 91.5
መስከረም 05/2018 ዓ.ም

𝐓𝐨 𝟐𝐧𝐝 𝐘𝐞𝐚𝐫 𝐚𝐧𝐝 𝐀𝐛𝐨𝐯𝐞 𝐇𝐚𝐫𝐚𝐦𝐚𝐲𝐚 𝐔𝐧𝐢𝐯𝐞𝐫𝐬𝐢𝐭𝐲 𝐂𝐇𝐌𝐒 𝐔𝐧𝐝𝐞𝐫𝐠𝐫𝐚𝐝𝐮𝐚𝐭𝐞 𝐒𝐭𝐮𝐝𝐞𝐧𝐭𝐬We are happy to inform you that dormitory assignmen...
13/09/2025

𝐓𝐨 𝟐𝐧𝐝 𝐘𝐞𝐚𝐫 𝐚𝐧𝐝 𝐀𝐛𝐨𝐯𝐞 𝐇𝐚𝐫𝐚𝐦𝐚𝐲𝐚 𝐔𝐧𝐢𝐯𝐞𝐫𝐬𝐢𝐭𝐲 𝐂𝐇𝐌𝐒 𝐔𝐧𝐝𝐞𝐫𝐠𝐫𝐚𝐝𝐮𝐚𝐭𝐞 𝐒𝐭𝐮𝐝𝐞𝐧𝐭𝐬

We are happy to inform you that dormitory assignments for the 2018 EC academic year are now finalized. 🏫

✅ All eligible students (2nd year and above) can check their assigned dorm details (block & room number) through the link below:

Use the following ID format
Batch 2014 ID/Year
Batch 2014 T/ID/Year (Transfer)
Batch 2015 ugpbID/Year
Batch 2015 ugpbtID/Year (Transfer)
Batch 2015 ugprnID/Year
Batch 2016 ugprID/Year
Batch 2016 ugprtID/Year (Transfer)

👉 http://dormitoryps.haramaya.edu.et/DormSearch.aspx

📌 Please review your assignment carefully and report any discrepancies to the Student Dormitory Service Office.

📖 Reminder: kindly adhere to the university’s dormitory rules and regulations to ensure a safe and comfortable living environment for everyone.

Best regards,
𝐇𝐚𝐫𝐚𝐦𝐚𝐲𝐚 𝐔𝐧𝐢𝐯𝐞𝐫𝐬𝐢𝐭𝐲
College of Health and Medical Sciences

11/09/2025
 !ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለመላው ኢትጵያውያን እንኳን ለ2018 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡በሀገራችን ቀደምት ከሆኑት አንዱ የሆነው ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ላለ...
10/09/2025

!

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለመላው ኢትጵያውያን እንኳን ለ2018 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡

በሀገራችን ቀደምት ከሆኑት አንዱ የሆነው ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ላለፉት 72 ዓመታት በመማር ማስተማርና ምርምር ስራ ከሀገራችን አልፈው ዓለምን እያገለገሉ ያሉ ባለሙያዎችንና ቴክኖሎጂዎችን በማፍራት ኃላፊነቱን በሚገባ እየተወጣ ይገኛል!

በአዲሱ የ2018 ዓመትም በቂ ዕውቀት የጨበጡና ሀገርና ወገናቸው በሚገባ የሚያገለግሉ ባለሙያዎችን አብቅቶ ለማስመረቅ ፣ ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎችን በማከናወን ዩኒቨርሲቲያችን ውስጥ የሚገኘው እውቀት የማህበረሰባችንንና የሀገራችንን ችግሮች ለማስወግድ የሚያስችሉ ውጤታማ ስራዎችን የምንሰራበት ዘመን ይሆናል።

በእኛ ኢትዮጵያውያኖች አንድነትና ጥረት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ለምረቃ በመብቃቱ ለምንጀምረው አዲስ ዓመት ልዩ ስጦታና ዓመቱን በአዲስ ተስፋ እንድንጀምር ያደረገን በመሆኑ በአዲሱ ዓመትም መሰል ስኬታማ ውጤቶችን ለራሳችንና ለሀገራችን የምናስመዘግብበት ይሆናል፡፡

አዲሱ የ2018 ዓመት ተማሪዎቻችን ዕውቀት የሚቀስሙበት ፣ መምህራንና ሰራተኞች ውጤታማ ስራዎችን የሚፈፅሙበት ፣ ተመራማሪዎቻችን ውጤታማ የምርምር ስራዎችን የሚያከናውኑበት ፣ መላው ኢትዮጵያውያንም ሠርተው የሚለወጡበት ብሩህ ዘመን እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ
ጷጉሜን 05 ቀን 2017 ዓ.ም

 !Yuunivarsiitiin Haramaayaa Lammilee Itiyoophiyaa Maraan baga nagayaan geessan jechuun Hawwii qabu isiniif ibsa. Yuuniv...
10/09/2025

!
Yuunivarsiitiin Haramaayaa Lammilee Itiyoophiyaa Maraan baga nagayaan geessan jechuun Hawwii qabu isiniif ibsa.

Yuunivarsiitiiwwan buleeyyii biyyi keenya qabdu keessaa Yuunivarsiitiin Haramaayaa tokko yoo ta'u waggoottan torbaatamii lamaan(72) darbaniif Adeemsa baruu fi barsiisuun, qorannoo fi qo'annoon biyya keenya irra Darbuun ogeessota fi teeknoolojii biyyoota alaa tajaajilan gumaachuun gahee isaa sirnaan bahachaa jira.

Bara 2018ttis ogeessota gahuumsa fi beekumsa gahaa qabanii fi rakkoo lammiilee isaa furuu fi sirnaan tajaajiluun danda'amu Eebbisiisuu, Qorannoo fi qo'annoon rakkoo hundeen furuu fi dhabamsiisuu danda'an itti hojjannu ta'a.

Tattaaffii fi tokkummaa Itiyoophiyaanotaan Hidhi Guddichi laga Abbayyaa xumuramee Eebbifamuun kennaa bara haaraa jalqabne kana yoo ta'u, Bara haaraa Kanattis Abdii fi cichoominaan injifannoo walfakkaataa Yuunivarsiitii fi biyya keenyaaf bara itti galmeessisnu ta'a.

Barri Haaraan 2018, bara barattootni keenyaa beekumsa fi ogummaa gaarii itti horatan, Barsiisonni fi hojjettoonni keenya hojii bu'a qabeessa fi milkaa'ina qabu hojjatan, qorattoonni keenya qorannoo rakkoo lammilee keenyaa hundeen furuu itti hojjatan, akkasumaas bara Itiyoophiyaanonni hundi hojjatanii itti milkaa'an akka isiniif ta'u Yuunivarsiitiin Haramaayaa hawwii gaarii isiniif hawwa.

Yuunivarsiitii Haramaayaa
Phaagumee 5, bara 2017

 , a source of unshakable pride for Ethiopia and a lasting beacon of hope for its people! Congratulations! The Grand Eth...
09/09/2025

, a source of unshakable pride for Ethiopia and a lasting beacon of hope for its people!
Congratulations!

The Grand Ethiopian Dam (GERD) stands as an immense national achievement far beyond being a proud source of hydroelectric energy. It is a renaissance of hope, a testament to an unshakable national pride and a powerful symbol of the strength and resilience of the Ethiopian people and their institutions. Ethiopia’s successful completion of this massive project has demonstrated to the world that Ethiopians can overcome any setback and accomplish even great things when they stand united around gallant and transformative national goals.

On behalf of the entire Haramaya University community, I extend my heartfelt congratulations to the Ethiopian government and its people on this historic achievement. I also congratulate the country’s diverse institutions that tirelessly contributed to the completion of the massive hydroelectric dam. Your unwavering support for the government’s farsighted mission and vision to transform Ethiopia’s energy landscape has made this colossal achievement possible.

Through their academic excellence, research and meaningful community engagement, the Ethiopian higher learning institutions are expected to contribute to the realization of their country’s grand development aspirations. Haramaya University greets GERD as a catalyst for sustainable development, energy equality and technological advancement. Our university reaffirms its unwavering commitment to supporting and advancing Ethiopia's renaissance through its pillars of teaching, research and community engagement. We will work indefatigably to uphold the vision behind both the GERD and the Green Legacy Initiative. GERD and other great achievements that Ethiopia has made serve us as an enduring inspiration, a beacon of hope for building a country rooted in sustainable development, economic advancement, societal resilience and collective growth. With this spirit, our university will work steadfastly to engage in cutting-edge research, foster change-inspiring innovations and cultivate vision-guided citizens who, with their firm commitment and profound passion, strive to shape the future of their beloved nation in a transformative direction.

Let this milestone inspire us all to dream big and stand together to build a prosperous and proud Ethiopia, a self-reliant and dignified nation.

Congratulations, Ethiopia. The Renaissance is happening. Let us work hard and stand strong to build a future that belongs to us, a future which our country leads with vision, determination and perseverance.

JEMAL YOUSUF (PhD)
PRESIDENT, HARAMAYA UNIVERSITY
09 September 2025

  ! Dhaloonni kun dhaloota dhufuuf wanta boonaan dabarsinu seenaa tokko keenyee jira! Baga waliin gammanne !Tokkummaa fi...
09/09/2025

!

Dhaloonni kun dhaloota dhufuuf wanta boonaan dabarsinu seenaa tokko keenyee jira! Baga waliin gammanne !

Tokkummaa fi tattaffii Itoophiyaanotaan Hidhi haaromsa guddichi Itoophiyaa xumuramee Eebbaaf gahuun ummata Itoophiyaa maraa fi mootummaan baga gammadan jechaa maqaa Hawaasa Yuunivarsiitii Haramaayaa maraan ergaa baga geessanii dabarsina.

Qormaata hedduu darbuun guyyaa arraa Eebbaaf kan gahe hidhi haaromsa keenya Itoophiyaanoonni yeroo waliin tumsinee fi tokko taane roga jireenya hundaan yaadaa fi qalbii hin shoroorkoyne ,tokkummaa fi abdii qabaachuu keenya kan agarsiisuu dha.

Ijaarsi hidha guddicha keenya bu'aa hojii ijaarsa keenyaa qofa osoo hin taane sab-boonnummaa biyyooleessaa fi mallattoo ofitti amanamummaa akkasumaas bu'aa cichoomina walootti.

karoora irraa kaasuun hanga dhuma humna maddisiisuutti lammileen Itoophiyaa hirmaannaa dammaqqaa fi Aarsaan godhan milkaa'ina seenaa kanaaf dhagaa bu'uraa tahee jira.

Argamiinsa Bu'aa cululuqaa seena qabeessa kanaaf hanga wareegama lubbutti kafalani obboleeyyan, dhaabbilee fi qaamoota dhimmi ilaalatu hundaaf gammachuu dhiheessina.

Yuunivarsitiin Haramaayaa misoomaa biyyaa fi jijjiramaaf ejjannoo cimaa qabaachuu dhaabbata barnoota seenaa keessatti mirkaneesse tahuu isaatiin, ijaarsi hidha haaromsaa akka xumuramu deeggarsa gama isaa akkuma godhaa turetti, misooma waara biyyattii kan saffisiisan qorannoo, kalaqaa fi humna nama gahumsa qabu hojii Oomishuu raawwachuun haroomsa Itoophiyaa dhugoomsuuf ejjannoo cimaa qabaachuu ni mirkaneessina.

Milkaa'inni Ijaarsa hidhi haaromsaa, dhaloonni dhufuu sodaa malee akka karoorfatu, tokkummaan hojjetu fi itoophiyaa badhaate akka ijaaruuf kan kakaasee dha.

Baga gammanne! Bu'aan wal gargaaruun hojjechuu biyya keenya bira darbee biyyoota ollaa keenyaas fayyadamoo kan godhu tahuu isaan, hidhata qaxanaa keenya kan cimsuu fi waliin akka fayyadamnu gochuun, fudhatamummaa Itoophiyaan qaxanaa keessatti qabdu kan ol kaasu seenaa barreessinee jira.

Haala mijataa dhaloota dhufuuf dabarsuuf Hawaasni Yuunivarsiitiichi waan danda'u hunda akka godhu irra deebiin waada seenna!

! !

Dr.Jamaal Yuusuf
Pireezidantii Yuunivarsiitii Haramaayaa
Qaammee 04,2017

 ! የዚህ ትውልድ አባለት ለመጪው ትውልድ በኩራት የምናስተላልፈውን አንድ ታሪክ አስቀምጠናል! እንኳን ደስ አለን!በእኛ ኢትዮጵያውያኖች አንድነትና ጥረት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባ...
09/09/2025

!

የዚህ ትውልድ አባለት ለመጪው ትውልድ በኩራት የምናስተላልፈውን አንድ ታሪክ አስቀምጠናል! እንኳን ደስ አለን!

በእኛ ኢትዮጵያውያኖች አንድነትና ጥረት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ለምረቃ በመብቃቱ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እና መንግስት እንኳን ደስ አላችሁ በማለት በመላው በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ስም የእንኳን ደስ አለን መልዕክታችን እናስተላልፋለን።

ብዙ ፈተናዎችን አልፎ ዛሬ ለምረቃ የበቃው ግድባችን ኢትዮጵያውያን ስንተባበር በሁሉም የሕይወት ዘርፎች ያለንን የማይናወጥ መንፈስ፣ አንድነት እና ጽናትን የሚያሳይ ነው። ታላቁ የህዳሴ ግድባችን የግንባታ ስራ ውጤት ብቻ ሳይሆን የብሔራዊ ኩራት እና በራስ የመተማመን ምልክት እንዲሁም የጋራ ቁርጠኝነት ትሩፋት ነው።

ከዕቅድ ጀምሮ እስከ መጨረሻው የኃይል ማመንጨት ስራ ድረስ የኢትዮጵያ ዜጎች የነቃ ተሳትፎና መስዋዕትነት ለዚህ ታሪካዊ ስኬት የማዕዘን ድንጋይ ሆኗል። ለዚህ አንጸባራቂ ውጤት መገኘት የህይወት መስዋዕትነትን ጭምር ከፍለው ታሪክ ለጻፉ ወንድም እህቶቻችን፣ ተቋማት እና ባለድርሻ አካላት በሙሉ ምስጋና እናቀርባለን።

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለሀገር ልማትና ለውጥ ቁርጠኛ መሆኑን በተግባር ያስመሰከረ የትምህርት ተቋም እንደመሆኑ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እንዲጠናቀቅ እንዳደረግነው አስተዋጽዖ ሁሉ የሀገራችን ዘላቂ እድገት የሚያፋጥኑ የምርምር፣ የፈጠራ እና ብቁ የሰው ኃይል የማፍራ ስራን በማከናወን የኢትዮጵያን ህዳሴ ዕውን ለማድረግ ቁርጠኝነታችንን እናረጋግጣለን።

የህዳሴ ግድብ ግንባታ ስኬት መጪው ትውልድ በድፍረት እንዲያልም፣ በጋራ እንዲሰራ እና የበለፀገች ኢትዮጵያን እንዲገነባ ያነሳሳ ነው።

እንኳን ደስ አለን! በመተባበር የመስራታችን ውጤት ከሀገራችን አልፎ ጎረቤት ሀገራትንም ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ ቀጠናዊ ትስስራችን እንዲጠናከርና የጋራ ተጠቃሚ እንድንሆን በማድረግ የኢትዮጵያን በቀጠናው ላይ ያላትን ተቀባይነት ክፍ የሚያደርግ አኩሪ ታሪክ ጽፈናል።

ብሩህ ጊዜ ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ የሚችለውን ሁሉ እንደሚያደርግ በድጋሜ ቃል እንገባለን!

እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!

ዶ/ር ጀማል ዩሱፍ
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት
ጷጉሜን 4/2017 ዓ.ም

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዳይሬክቶሬት የምርጥ ዘር ብዜት ስራ ዛሬ ተጎብኝቷልየሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ጀማል ዩሱፍ እና የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ...
08/09/2025

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዳይሬክቶሬት የምርጥ ዘር ብዜት ስራ ዛሬ ተጎብኝቷል

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ጀማል ዩሱፍ እና የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር አብዲ መሐመድ ኢንተርፕራይዙ የድንች ምርጥ ዘር ብዜት ላይ እያከናወነ ያለውን ስራ እንዲሁም የህግ ኮሌጅ ዲን የሆኑት ዶክተር ሪቻርድ ዊንትዜል እያካሄዱት ያለውን የደን ልማት ስራ ጎብኝተዋል።

ጷጉሜን 03/2017 ዓ.ም

 እንኳን ለ2018 የትምህርት ዘመን በሰላምና በጤና አደረሳችሁ እያልን ነባር ተማሪዎቻችን ወደ ዩኒቨርሲቲያችሁ የምትገቡት መስከረም 12 እና 13/2018 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ አስፈላጊውን ...
08/09/2025



እንኳን ለ2018 የትምህርት ዘመን በሰላምና በጤና አደረሳችሁ እያልን ነባር ተማሪዎቻችን ወደ ዩኒቨርሲቲያችሁ የምትገቡት መስከረም 12 እና 13/2018 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳውቃለን።

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ
ጷጉሜን 3/2017 ዓ.ም

Address

Harar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when HU FM 91.5 RADIO posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to HU FM 91.5 RADIO:

Share

Category