02/01/2026
በክልሉ የገቢ አሰባሰብ አቅምን በማሳደግ የታዩ ጉድለቶችን ለመሙላት በቅንጅት ይሰራል :- አቶ መሀመድ ያህያ
*********
በሀረሪ ክልል የገቢ አሰባሰብ አቅምን በማሳደግ የታዩ ጉድለቶችን ለመሙላት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ሀላፊ አቶ መሀመድ ያህያ ገለፁ።
በሀረሪ ክልል የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱን ለመምራት የተቋቋመው ኮሚቴ በክልሉ በ5 ወር መሰብሰብ የነበረባቸውና ያልተሰበሰቡ ግብሮችን በአግባቡ መሰብሰብ በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።
በዚህም የገቢ አፈጻጸምን በዝርዝር በማየትና በመገምገም ጉድለቶችን በመለየት በዕቅዱ መሰረት ያልተከናወነበት ችግሮች ላይ መግባባት ላይ ከተደረሰ በኃላ የማስተካከያ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል ።
የኮሚቴው ሰብሳቢ እና የሀረሪ ክልል የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ ያህያ እንደገለፁት ገቢን በመሰብሰብ ረገድ የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ቅንጅት ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
በክልሉ የገቢ አሰባሰብ አቅምን በማሳደግ የታዩ ጉድለቶችን ለመሙላት በትኩረትና በቅንጅት እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
24/ 04/18