Harari Mass Media Agency

Harari Mass Media Agency Harari Mass Media Agency is a public media operating in Harar, Ethiopia.
ገፃችንን በመከተል ትኩስ ዜና እና መረጃዎችን ያገኛሉ።

19/09/2025

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በዛሬው ዕለት በአቦከር ወረዳ በ540 ሚሊዮን ብር የሚገነባውን የሀረር ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ላይ ያስተላለፉት መልዕክት።

19/09/2025

ሀረሪ ክልል ወደ ምስራቋ ኮከብነት በምታደርገው ጉዞ ከዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ጎን ለጎን በትምህርት ዘርፋም ከፍተኛ ለውጥ እና አበረታች ውጤቶች ተመዝግቧል፦ አቶ ኦርዲን በድሪ

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር

19/09/2025

የ2017 የማንሰራራት ጅማሮ አዳዲስ ብስራቶችንና ድሎችን ይዘን ወደ 2018 አመት የተሻገርንበት እና ኢትዮጵያ በልጆቿ የተባበረ ክንድ ወደ ላቀ ምዕራፍ የተሻገረችበት ነው፦ አቶ ኦርዲን በድሪ

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሁለት አመራሮች ሹመት ሰጡ *****ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ከመስከረም 9 ቀን ጀምሮ ለሁለት አመራሮች ሹመት ሰጥተዋል። በዚህም መሰረ...
19/09/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሁለት አመራሮች ሹመት ሰጡ
*****
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ከመስከረም 9 ቀን ጀምሮ ለሁለት አመራሮች ሹመት ሰጥተዋል።

በዚህም መሰረት፡-

1ኛ. እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) - የብሔራዊ ባንክ ገዥ

2ኛ. ወ/ሮ እናታለም መለስ - በሚኒስትር ማዕረግ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ አድርገው መሾማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡



9/1/2018

ኢትዮጵያ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለማስተናገድ ጥሪ አቀረበች*******ኢትዮጵያ የ2029 ወይም 2031 የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናን ለማዘጋጀት ለዓለም አትሌቲክስ ፌደሬሽን ጥሪ አቅርባለ...
19/09/2025

ኢትዮጵያ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለማስተናገድ ጥሪ አቀረበች
*******
ኢትዮጵያ የ2029 ወይም 2031 የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናን ለማዘጋጀት ለዓለም አትሌቲክስ ፌደሬሽን ጥሪ አቅርባለች።

በዛሬው እለት በቶኪዮ በተዘጋጀው የኦብዘርቨር መርሃግብር ላይ ከመንግስትና ከፌዴሬሽኑ የተወጣጡ አመራሮች የተካፈሉ ሲሆን ሻምፒዮናውን ለማዘጋጀት ጥያቄ ማቅረቧን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን በድረ ገፁ አስነብቧል።

መንግስት ለአትሌቲክሱ ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት አስፈላጊውን ግብአቶች በሟሟላት፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ ችግሮችን በመቅረፍ እና በቂ ስታዲየሞች በመገንባት የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለማስተናገድ የሚያስችል አቅም መፈጠሩን በስፍራው የሚገኙትና ከኮሚቴው አንዱ የሆኑት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው ክቡር አቶ መክዩ መሐመድ ተናግረዋል

የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን በበኩላቸው አሁን ላይ በኢትዮጵያ እየተገነቡ የሚገኙት የስፖርት ፋሲሊቲዎችና ማዘውተሪያ፣ ሆቴሎች፣ የአየርና የየብስ ትራንስፖርት እና ሌሎች ለሻምፒዮናው የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በተሻለ መልኩ ኢትዮጵያ ላይ ይገኛል ብለዋል።

በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ እየተሳተፉ ያሉት የፌዴሬሽኑ አመራሮች በቶኪዮ ዓለም አቀፍ ስቴዲየም በመዘዋወር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ልምድ ልውውጥ ማድረጋቸውን የፌደሬሽኑ መረጃ ያመላክታል

9/1/2018

ሞዴል ት/ቤቱ የሀረርን ስም የሚያስጠሩ በርካታ የሀረር “አምባሳደሮችን” እንዲያፈራ ድጋፍ ይደረጋል :- አቶ ኦርዲን በድሪ  ******የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በማህ...
19/09/2025

ሞዴል ት/ቤቱ የሀረርን ስም የሚያስጠሩ በርካታ የሀረር “አምባሳደሮችን” እንዲያፈራ ድጋፍ ይደረጋል :- አቶ ኦርዲን በድሪ
******

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት በክልሉ የሚገነባ ሀረር ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋር አስጀምረናል ብለዋል።

ሞዴል ትምህርት ቤቱ ውጤታማና ተስጥኦ ያላቸውን ተማሪዎች ከማብቃት በተጨማሪ ትምህርት ቤቱ ለሚገነባበት የቀላድ አምባ አካባቢ እድገት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል ።

ሞዴል ትምህርቱ በታቀደለት ጊዜና የጥራት ደረጃ ተጠናቆ የሀረርን ስም የሚያስጠሩ በርካታ የሀረር “አምባሳደሮችን” እንዲያፈራ አስፈላጊው ድጋፍና እገዛ የሚደረግ መሆኑንም ገልፀዋል።

9/1/2018

19/09/2025
የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውጤታማ ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ**********************የሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከኦሮሚያ የህግ ስልጠና ...
19/09/2025

የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውጤታማ ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
**********************

የሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከኦሮሚያ የህግ ስልጠና እና ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።

የመግባቢያ ስምምነቱን የተፈራረሙት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ማሂር አብዱሰመድ እና የኢኒስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሱልጣን አብዶ ናቸዉ።

የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ማሂር አብዱሰመድ የመግባቢያ ስምምነቱን በተፈራረሙበት ወቅት እንደገለጹት በየደረጃዉ የሚገኙ የክልሉ ፍርድ ቤቶች የሚሰጡትን አገልግሎት ጥራትና ዉጤታማነት ከጊዜ ወደ ጊዜ ለማሻሻል የሚያስችሉ ተግባራትን እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዉ ይህን አጠናክሮ ለማስቀጠል ከስልጠናና ምርምር ተቋማት ጋር በጋራ መስራታቸዉ የሚኖረዉ ፋይዳ የጎላ ነዉ ብለዋል።

አቶ ማሂር አያይዘዉ እንደገለጹት የተደረገዉ ስምምነት የክልሉ ፍርድ ቤቶች ዳኞች እና ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ፣ ክህሎታቸዉን ለማዳበር እና ሙያዊ ስነ ምግባርን ተላብሰው እንዲሰሩ ለማድረግ የሚያግዙ የአጭር እና ረዥም ጊዜ ስልጠናዎች ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል።

በተጨማሪም የሚስተዋሉ የአሰራር ክፍተቶችን ለመለየት የሚያስችሉ የጥናትና ምርምር ስራዎችን በቀጣይ ከኢኒስቲትዩቱ ጋር በትብብር ለመስራት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

የኦሮሚያ የህግ ስልጠና እና ጥናትና ምርምር ኢኒስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሱልጣን አብዶ በበኩላቸዉ ከሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋር በመስራታቸዉ ደስተኛ መሆናቸዉን ገልጸዋል።

ኢኒስቲትዩቱ የፍትህ አካላትን በተለይም ፍርድ ቤቶችን ለማጠናከር የሚያስችሉ የተለያዩ የስልጠና እና ጥናትና ምርምር ስራዎች ላይ የሚሰራ መሆኑን ገልፀው ከክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋር ዉጤታማ ተግባራትን በቀጣይ የሚያከናዉኑ መሆኑን ጠቁመዋል።

በስምምነት ፊርማ ስነ ስርአቱ ላይ የሐረሪ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ወ/ሮ አሻ አሚኔ እና ሌሎች የኢኒስቲትዩቱ ስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

09/01/18

የሐረሪ ክልል ለትምህርቱ ጥራት እና ውጤት እየሰራ ያለውን አበረታች ተግባራ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ ገለፁ። *******የኢፌዴሪ...
19/09/2025

የሐረሪ ክልል ለትምህርቱ ጥራት እና ውጤት እየሰራ ያለውን አበረታች ተግባራ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ ገለፁ።
*******

የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ በወቅቱ እንደገለፁት ከለውጡ በፊት የነበረውን የትምህርት ስብራት በመቀየር በአቋራጭ የሚገኝ የትምህርት ደረጃ ማስቀረት መቻሉን ጠቁመዋል ።

በዚህም ባለፉት አመታት የተጣራ በእውቀት የተመዘኑ ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በጥራት እየገቡ እንደሚገኝ ጠቁመው በዚህም የሐረሪ ክልል እያስመዘገበ የሚገኘው ውጤት አበረታች መሆኑን ተናግረዋል።

ይህንንም ውጤት በቀጣይ አመት በተሻለ አፈፃፀም መድገም እና ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።

የ 2018 አመት የ12 ክፍል መልቀቂያ ፈተና በመላው ሀገሪቱ ሙሉ በመሉ ከወረቀት ነፃ (ኦላይን )እንደሚደረግ ጠቁመዋል ።

በአመቱ በትምህርቱ ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ወረዳዎች ፣ ትምህርት ቤቶች ፣ ተማሪዎች ፣ በየደረጃ ማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ።

ዘጋቢ :- ገዛኸኝ አራጌ
9/1/18

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እና የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ሮ ብርሀኑ ነጋ  በ540 ሚሊዮን ብር የሚገነባ የሐረር ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ...
19/09/2025

የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እና የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ሮ ብርሀኑ ነጋ በ540 ሚሊዮን ብር የሚገነባ የሐረር ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ አስጀመሩ ።
*************

በሐረሪ ክልል አቦከር ወረዳ በ540 ሚሊዮን ብር የሚገነባ የሐረር ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን የሐረሪ ክልል ርዐሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እና የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ሮ ብርሀኑ ነጋ አስጀምረዋል።

የሐረሪ ክልል ርዐሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በወቅቱ እንደገለፁት በክልሉ ለትምህርቱ ዘርፍ ቅድሚያ ተሰጥቶት ዘርፈ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል ።

በተለይም በክልሉ አቦከር ወረዳ ቀላዳባ አካባቢ በሚፈለገው ደረጃ በልማቱ ብዙም እንቅስቃሴ ያልነበረበት እና በአሁኑ ሰአት በአካባቢው በርካታ መሰረተ ልማቶች እየተስፋፉ ፣የኮሪደር ልማት ስራዎች እየተከናወኑ እና ሌሎችም ለኢኮኖሚው መነቃቃት የሚያግዙ የልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አብራርተዋል ።

በተለይም ዛሬ የተጀመረው የትምህርት ቤት ግንባታ አበርክቶው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል ።

የትምህርት ቤቱ ግንባታ በትምህርት በኩል ያለውን ኢ ፍትሀዊነት ለማስቀረት የሚያግዝ መሆኑ ተጠቁሟል ።

ሀሉም ማህበረሰብ ለትምህርት የደረሰ ህፃናትን ወደ ትምህርት ቤት መላክ እንደሚገባ አሳስበዋል ።

የብልፅግና ጉዞ ማረጋገጥ የሚቻለው ብቁና ብቃት ያለው በቂ የሰው ሀይል ማምረት ሲቻል መሆኑን አረጋግጠዋል ።

የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ሮ ብርሀኑ ነጋ በበኩላቸው ባለፉት 7 የለውጥ አመታት በትምህርቱ ዘርፍ መሰረታዊ ለውጥ መከናወኑን ገልፀዋል ።

በዚህም የተማሪዎችን ከክፍል ወደክፍል መሸጋገር ብቻ እሳቤ በመቀየር በእውቀት ላይ የተመሰረተ በሁሉም ዘርፍ ብቁ እና ተወዳዳሪ ትውልድ ለማፍራት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል ።

በኑሮ ደረጃ የተከፋፈለውን የትምህርት ስርአት በመቀየር ፍትሀዊ የትምህርት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል ።

በተመሳሳይ የትምህርት ጥራትን በከተማም በገጠር ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን አክለዋል ።

በዚህም ከባለፈው አመት ጀምሮ 50 ሞዴል ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት ታቅዶ እስካሁን ድረስ 36ቱን መገንባት መቻሉን ጠቁመው የተቀሩትን በቀሪ አመታት እንደሚጠናቁ ገልፀዋል ።

በዛሬ እለት የተጀመረው የሐረር ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በ540ሚሊዮን የሚገነባ እና በአንድ አመት ውስጥ ተጠናቆ ወደ ስራ እንደሚገባ ተጠቁመዋል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጌቱ ነገዎ በበኩላቸው ዛሬ የተጀመረው ትምህርት ቤት ሀገርን ወደ ከፍተኛ የብልፅግና ጉዞ የሚያሻግሩ ልጆች የሚፈራበት እንደሚሆን እምነታቸውን ገልፀዋል።

ለዚህም ትምህርት ቤት ግንባታ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

ዘጋቢ :- ገዛኸኝ አራጌ
9/1/18

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ሀረሪ ክልል ገቡ*******የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ሀረሪ ክልል ገብተዋል ። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከ...
18/09/2025

የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ሀረሪ ክልል ገቡ
*******
የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ሀረሪ ክልል ገብተዋል ።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከድሬደዋ አለም አቀፍ ኤርፖርት ሲገቡ የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ጌቱ ነገዎ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።

የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ሀረሪ ክልል የገቡት የ2017 ዓ.ም የትምህርት ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ መሆኑን የክልሉ ት/ት ቢሮ መረጃ ያመለክታል።

8/01/2017

የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን በማሻሻል ለህብረተሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የሀረሪ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ አስታወቀ ። ******የሀ...
18/09/2025

የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን በማሻሻል ለህብረተሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የሀረሪ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ አስታወቀ ።
******
የሀረሪ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ያስገነባው ህንፃ ለሥራ ምቹ፣ ፅዱ፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች አስፈላጊ መሠረተ ልማት በማሟላት የቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓቱን በማሻሻል ቴክኖሎጂን ያማከለ አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን እርካታ ለመጨመር እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል።

እንደ ሀገር መንግስት የያዘውን የተቋም ግንባታን ተግባራዊ በማድረግ ምቹ የስራ ሁኔታ በመፍጠር አገልግሎት አሰጣጥ በማሻሻል የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ የተፈጠረ ምቹ ሁኔታ መሆኑን ተገልጿል ።

ቢሮው የአሁናዊና የቀጣይ ጊዜ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ምቹ ቀልጣፋና የህብረተሰብን አዳጊ ፍላጎት በሚመልስ መልኩ ደረጃና ጥራት የተገነባ መሆኑን ቢሮው አመላክቷል።

ህንፃው በቂ የሆነ የመኪና ማቆሚያ ፣ ዘመናዊ የሰራተኞች አዳራሽ፣ ተገልጋዮች ወደ ተቋሙ ሲመጡ አገልግሎት እስኪያገኙ ምቹ ማረፊያዎች እንዲሁም ወቅቱን እና ከተማን ገፅታ በሚገነባ መልኩ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ አስታውቋል::

8/1/2018

Address

Red Cross Street
Harar
1331

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Mass Media Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harari Mass Media Agency:

Share