
23/07/2025
በክልሉ የተሠሩ የልማት ሥራዎች የከተማይቱን ገፅታ የቀየሩ ናቸው :- የሐረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ኮሚኒቲ አባላት
**********
የሐረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ኮሚኒቲ አባላት በክልሉ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።
ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተወጣጡ የሐረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ኮሚኒቲ አባላት በክልሉ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በዚህም የአለማቀፍ ቅርስ የሆነው የጀጎል ዉስጥ ለዉስጥ መንገዶችን ፣ አዉ አብዳል ኢንስቲትዩት ት/ቤትን ፣ ኑር ኘላዛን ,እና ኢኮ ፓርክን ጎብኝተዋል ።
የሐረሪ ብሄራዊ ጉባኤ አባላት በክልሉ የተሠሩ የልማት ሥራዎች የከተማይቱን ገፅታ የቀየሩ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል ።
በተለይም ከለውጡ መንግስት ወዲህ የተገነቡ አበረታች ግንባታዎች የርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ኦርዲን በድሪ ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን ገልፀው ለዚህም ምስጋና አቅርበዋል ።
የተሠሩ የተለያዩ የልማት ስራዎች ህብረተሰቡ ከራሱ በላይ ሊጠብቃቸዉ እንደሚገባና ለቀጣይ ለልማት ስራዎች ከክልሉ ጎን እንደሚቆሙ ገልፀዋል ።
ዘጋቢ፦ ኢስማኢል አብዱላሂ
16/11/2017