Harari Mass Media Agency

Harari Mass Media Agency Harari Mass Media Agency is a public media operating in Harar, Ethiopia.
ገፃችንን በመከተል ትኩስ ዜና እና መረጃዎችን ያገኛሉ።

በክልሉ የተሠሩ የልማት ሥራዎች የከተማይቱን ገፅታ የቀየሩ ናቸው :- የሐረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ኮሚኒቲ  አባላት **********የሐረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ኮሚኒቲ አባላት በክልሉ የሚገኙ የልማት ስራ...
23/07/2025

በክልሉ የተሠሩ የልማት ሥራዎች የከተማይቱን ገፅታ የቀየሩ ናቸው :- የሐረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ኮሚኒቲ አባላት
**********
የሐረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ኮሚኒቲ አባላት በክልሉ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተወጣጡ የሐረሪ ብሄራዊ ጉባኤ ኮሚኒቲ አባላት በክልሉ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

በዚህም የአለማቀፍ ቅርስ የሆነው የጀጎል ዉስጥ ለዉስጥ መንገዶችን ፣ አዉ አብዳል ኢንስቲትዩት ት/ቤትን ፣ ኑር ኘላዛን ,እና ኢኮ ፓርክን ጎብኝተዋል ።

የሐረሪ ብሄራዊ ጉባኤ አባላት በክልሉ የተሠሩ የልማት ሥራዎች የከተማይቱን ገፅታ የቀየሩ ናቸው ሲሉ ተናግረዋል ።

በተለይም ከለውጡ መንግስት ወዲህ የተገነቡ አበረታች ግንባታዎች የርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ኦርዲን በድሪ ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን ገልፀው ለዚህም ምስጋና አቅርበዋል ።

የተሠሩ የተለያዩ የልማት ስራዎች ህብረተሰቡ ከራሱ በላይ ሊጠብቃቸዉ እንደሚገባና ለቀጣይ ለልማት ስራዎች ከክልሉ ጎን እንደሚቆሙ ገልፀዋል ።

ዘጋቢ፦ ኢስማኢል አብዱላሂ
16/11/2017

23/07/2025
ክልሉን የሚመጥን ዘመኑን የዋጀ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖር በትኩረት መስራት ይጠበቃል :- ኮምሽነር ረምዚ ሱልጣን ********የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ል...
23/07/2025

ክልሉን የሚመጥን ዘመኑን የዋጀ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖር በትኩረት መስራት ይጠበቃል :- ኮምሽነር ረምዚ ሱልጣን
********

የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ከክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር ክልል አቀፍ የመንገድ ደህንነት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሀግብር ተካሂዷል።

መርሀግብሩ በዋነኝነት የትራፊክ ደህንነት ዙሪያ የአሽከርካሪዎችን ግንዛቤ ማሳደግ ፣ የመንገድ ደህንነትን ማስጠበቅ፣ ህጎች ሳይሸራረፉ ተፈጻሚ እንዲሆኑ ማስቻል ያለመ መድረክ መሆኑ ተገልጿል።

በተጨማሪም ከዘመኑ ጋር የተጣጣመ የትራንስፖርት ስርአት መፍጠር ወሳኝ በመሆኑ በክልሉ ተግባራዊ ለማድረግ ታሳቢ ማድረግን ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮምሽነር ረምዚ ሱልጣን በክልሉ የተቀናጀ የትራፊክ መንገድ ደህንነት በየአመቱ ሲሰራ መቆቱን ገልጸው የሐረር ከተማን የሚመጥን የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖር የበለጠ በቅንጅት መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።

በተጨማሪም በዘርፉ ያሉ መልካም ስራዎች ቢኖሩም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተበራከተ የመጣውን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ መንገድ ትራንስፖርትን ጨምሮ ከማሰልጠኛ ተቋማት ጋር የግንዛቤ መፍጠር ስራዎች መጠናከር እንዳለባቸው አስታውቀዋል።

ይህንንም ከማስቀረት አኳያ የተሳለጠ ዘመናዊና ደረጃውን የጠበቀ ህግን የተከተለ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።

ኮሚሽነር ረምዚ አክለውም ክልሉ በተለያዩ የልማት መስኮች ያስመዘገበውን ስኬት በትራንስፖርቱም ዘርፍ መድገም ይጠበቅብናል ነው ያሉት።

ጤናማ የትራንስፖርት ፍሰት እንዲኖርና በአካልም ሆነ በንብረት ላይ የሚደርስን አደጋ ለመቀነስ በቅንጅት መስራት ይጠበቃል ሲሉ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ያለ እድሜያቸው የሚያሽከረክሩና የመንጃ ፍቃድ ሳይኖራቸው የሚያሽከረክሩ አሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግ መሆኑን ተመላክቷል ።

በቀጣይም የወንጀል መከላከልና ትራፊክ ክፍተቶች ጋር በተገናኘ ስር ነቀል ለውጦች እንደሚካሄዱ ገልጸዋል።

የሐረሪ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ኢንጅነር ፈትሂ እንደገለጹት ህጎችን ከማክበርና ከማስከበር የመንገድ ትራንስፖርት ባለሙያዎች ከትራፊክ ፖሊስ ጋር በመሆን በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በክልሉ የትራፊክ አገልግሎት ጋር በተገናኘ ችግር የሚስተዋሉባቸውን አካባቢዎች በመለየት ችግሩን መቅረፍ ይገባል ብለዋል ።

በቀጣይም የዘርፉን ችግር ከመቅረፍ አንጻር ከአጋር አካላት ጋር የንቅናቄና የግንዛቤ መፍጠር ስራዎች በስፋት እንደሚሰሩ ተመላክቷል።

እንዲሁም በቴክኖሎጂ የታገዘ የራዳር ክትትል ስራ እንደሚሰራም ተመላክቷል።

በመድረኩ በቀጣይ ቀናት የሚሰሩ ስራዎች ዙሪያ ሰነድ ቀርቦ በትራፊክ ፖሊሶችና የመንገድ ደህንነት ባለሙያዎች ጋር ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል ።

ዘጋቢ ፦ሲሳይ ዘርይሁን
16/11/2017

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

23/07/2025

በኢፌድሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ የተመራ ልኡክ በክልሉ በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ የሚገኘውን የካንሰር ማእከልን ጉብኝት።

የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ከአፈርና ውሀ ጥበቃው ባሻገር ለበርካታ ዜጎች የስራ እድልን እንደፈጠረ ተገለፀ ። **********በኢትዮጲያ ለአየር ንብረት ለውጡ የማይበገር ኢኮኖሚን በመፍጠር...
23/07/2025

የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ከአፈርና ውሀ ጥበቃው ባሻገር ለበርካታ ዜጎች የስራ እድልን እንደፈጠረ ተገለፀ ።
**********

በኢትዮጲያ ለአየር ንብረት ለውጡ የማይበገር ኢኮኖሚን በመፍጠር በከፍተኛ ህዝባዊ ተሳትፎ ላለፉት አመታት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ሲካሄድ ቆይቷል።

በዘንድሮ መርሀ ግብርም እንደ ሀገር ከ7.5 ቢሊየን በላይ ፤ በሀረሪ ክልል ደግሞ ሁለት ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ታቅዶ ባሳለፍነው ቅዳሜ በይፋ መጀመሩ ይታወሳል ።

ይህ መርሀ ግብር እንደሀገር ከተጀመረ ወዲህ ተፈጥሮን ምህዋሯ ከፍ በማድረግ የውሀና አፈር ሀብት ልማትና ጥበቃን ማሳደግ ያስቻለ መሆኑን በሀረሪ ግብርና ልማት ቢሮ የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ አራርሶ አደም ገልጸዋል።

በመርሀ ግብሩ ባለፉት አመታት የምግብ ዋስትና ማረጋገጥና ሌሎች አላማዎችን በመያዝ ውጤታማ ለውጥ ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።

የተዘጋጁት ችግኞች 70 በመቶዎቹ ለምግብነት የሚውሉ ሲሆን 30 በመቶው ደግሞ ለአፈርና ውሀ ጥበቃው ለደን ሽፋን የሚውሉ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ጠቁመው ለምግብነት የሚውሉት ለክልሉ አየር ተስማሚ የሆኑ ተክሎች ላይ ያተኮረነው ብለዋል።

መርሀ ግብሩ ከአፈርና ውሀ ጥበቃው ባሻገርም ለበርካታ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል መፍጠሩንም አቶ አራርሶ ይናገራሉ።

በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የዝናብ መቆራረጥ እየተስተዋለ በመሆኑ ዝናብ በሚዘንብባቸው ወቅቶች ችግኝ የመትከል ተግባራት ይከናወናልም ብለዋል።

የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ ለሀገር ኢኮኖሚ፣ ለማህበረሰብ ጤናና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታን በመገንዘብ ባሏቸው ትርፍ መሬቶች ችግኞችን እንዲተክሉ ተናግረው ቢሮው በቂ የመሬት ዝግጅት ላደረጉ ሁሉ ችግኝ ለማቅረብ ዝግጁ መሆኑን አስታውቀዋል።

ዘጋቢ :- ቤተልሄም ደሴ
16.11.17

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ : https://www.youtube.com/

ቴሌግራም: https://t.me/hararimassmediaagency

የሐረሪ ክልል ም/ቤት ቋሚ ኮምቴ የመንግስትን ሃብት በአግባቡ ለማስወገድና የመንግስት እቃዎች ግዥን ጥራት ለማረጋገጥ እየተሰራ ያለው ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስታወቀ። ********...
23/07/2025

የሐረሪ ክልል ም/ቤት ቋሚ ኮምቴ የመንግስትን ሃብት በአግባቡ ለማስወገድና የመንግስት እቃዎች ግዥን ጥራት ለማረጋገጥ እየተሰራ ያለው ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስታወቀ።
********************************

የሀረሪ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ ጽ/ቤት የ2017 የስራ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 እቅድ ገምግሟል።

የክልሉ ግዥና ንብረት ማስወገድ ጽ/ቤት የ2017 የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2018 የስራ እቅድ በጽ/ቤቱ ኃላፊ በአቶ አብዱልባሲጥ አቡበከር ቀርቧል።

በ 2017 የመንግስት መስሪያ ቤቶች ግዥ ፍላጎት ፍላጎት ለማሟላት እየሰራ መሆኑን ተናግረው ከአገልግሎት ውጭ የሆኑ እቃዎች በማስወገድ ከ22ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡን ገልፀዋል።

ሁሉም የመንግስት መስሪያቤቶች ለእቃ ግዥ የሚፈልጓቸውን መስፈርቶች በወቅቱ እንዲያቀርቡ ሲያረጋግጡ መቆየታቸውንም ተናግረዋል።

የግዥ ስርዓቱ በኤሌክትሮኒካዊ መንገድ መካሄዱንና የሰራተኛውን ቁጥር ለመጨመር አስፈጻሚ ሃይሉ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል።

ግዥዎች ና ንብረት ማስወገድ ስርአቱ ግልፅነትና ተጠያቂነት እንዲኖር ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን ተናግሯል።

በ2017 ለ54 የመንግስት መስሪያቤቶች መሳሪያ ግዥ መካሄዱን ገልጸው ንብረት ለማስወገድ በምወጣ ጨረታ ላይ በሀገር አቀፍ እና በክልል ደረጃ ተጫራቾች መወዳደር የምችሉ መሆኑን ገልፀዋል።

በተያዘው የጊዜ ገደብ ውስጥ ዕቃቸው ጥራት በሌላቸውና በማያቀርቡ ተጫራቾች ላይ ዕርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁመዋል።

አቶ አብዱልባሲጥ በቀጣይም የ2018 በጀት አመት እቅድን አቅርበው የ2018 በጀት አመት ከአገልግሎት ውጪ የሆኑ የመንግስት ንብረቶችን ማስወገድ፣ የጽዳት እቃዎች አቅርቦትና በወቅቱ አቅርቦትን ማረጋገጥ፣ የግዥ ስርዓቱን ዲጂታል ማድረግ እና የንብረት ማስወገድ ላይ ትኩረት አድርጎ ይሰራል ብለዋል።

የቋሚ ኮሚቴ አባላትና ሰብሳቢዎችም የ2017 የስራ አፈጻጸምና እቅድ ሪፖርት እና የስራ እቅድን ካዳመጡ በኋላ አስተያየታቸውንና ጥያቄዎቻቸውን አንስተዋል።

በዚህም መሰረት የማይሰሩ የመንግስት መሳሪያዎችን በአግባቡ ከማንሳት፣ የመንግስት እቃዎች ግዥ ላይ የተሰማሩ አቅራቢዎች ውል አክብረው ጥራት ያለው መሳሪያ እንዲያቀርቡ እና የመንግስትን ገቢ ለማሳደግ መሰራት እንዳለበት አንስተዋ

በመጨረሻም የሀረሪ ክልል ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፋቲያ ሳኒ ባስቀመጡት አቅጣጫ በሁሉም የመንግስት ሴክተር መስሪያ ቤቶች የተገዙ ዕቃዎችን በወቅቱና በጥራት የማቅረብ፣የክትትልና ቁጥጥር ስራዎችን መጠናከር አለበት ብለዋል።

ወይዘሮ ፋቲያ አክለውም የአይሲቲ አጠቃቀምን በማጠናከር ሁሉም የመንግስት ሴክተሮች የግዥ መስፈርቶቻቸውን በወቅቱ እንዲያቀርቡ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

ዘገባ፡ሙያዲን ሙክታር
16/11/17

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ : https://www.youtube.com/

ቴሌግራም: https://t.me/hararimassmediaagency

የሀረሪ ብሄራዊ ጉባኤ የመራጮች የጋራ መድረክ በዛሬው እለት ተካሄደ። ********የሀረሪ ጉባኤ መራጮች ለአባላቱ የጉባኤው ሕግ ማዕቀፍ ዙሪያ ንግግር ያደረጉት የጉባኤው የሕግ ጉዳይ ዳይሬክተ...
23/07/2025

የሀረሪ ብሄራዊ ጉባኤ የመራጮች የጋራ መድረክ በዛሬው እለት ተካሄደ።
********
የሀረሪ ጉባኤ መራጮች ለአባላቱ የጉባኤው ሕግ ማዕቀፍ ዙሪያ ንግግር ያደረጉት የጉባኤው የሕግ ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ በክሪ መሀመድ ሲሆኑ በሕግ ማዕቀፍ በኩል ያለውን የብሔረሰቡ ራስን በራስ የማስተዳደር ባህሉንና ሉዓላዊነትቱን እንዲሁም ባህሉን ማሳደግና መጠበቅን በሚመለከት ለአባላቱ ሰፋ ያለ ግንዛቤ ሰጥተዋል፡፡

እንደዚሁም ወጣቶች ሁሉን አቀፍ ማሕበራት መተዳደሪያ ደንብ ረቂቅ አዋጅን በሚመለከት ንግግር ያደረጉት የጉባኤ የመራጮች ጉዳይ ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ አሚራ አሊ ሲሆኑ ሀገር ተረካቢ ወጣቶች አቅም ያላቸው ትውልድ መሆናቸውን በመግለፅ የወጣቶች መደራጀት እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ጉባኤው በቀጣይ ትኩረት በመስጠት ተግባራዊ እንደሚያደርግም ገልፀዋል፡፡

ከአስር የሀገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ የጉባኤው መራጭ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን ያቀረቡ ሲሆን ለቀረቡት ጥያቄዎችና አስተያየቶች የሀረሪ ጉባኤ አፈ ጉባኤ አቶ ሙሒየዲን አህመድ ና የጉባኤው ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ አሚና አብዱልከሪም ሰፋ ያለ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ዘጋቢ ፡- ኢስማኢል አብዱላሂ
16/11/17

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ : https://www.youtube.com/

ቴሌግራም: https://t.me/hararimassmediaagency

የኢፌድሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር በክልላችን ተገኝታችሁ ላደረጋቹት የበጎ ፈቃድ እገዛ ምስጋናዬን አቀርባለው፦ አቶ ኦርዲን በድሪ *******የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ...
23/07/2025

የኢፌድሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር በክልላችን ተገኝታችሁ ላደረጋቹት የበጎ ፈቃድ እገዛ ምስጋናዬን አቀርባለው፦ አቶ ኦርዲን በድሪ
*******
የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ የኢፌድሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ሚንስትር ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላ እና ለልኡካን ቡድናቸው ምስጋናን አቀረቡ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት የምስጋና መልእክት የኢፌድሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ሚንስትር ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላ የተመራ ልኡካን ቡድን በሐረሪ ክልል ተገኝተው የበጎፈቃድ ስራዎችን በማከናወናቸው ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል።

በዚህም ሚንስትር መስሪያቤቱና ተጠሪ ተቋማት በአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳት፣ በትምህርት መሳሪያዎች ድጋፍ እና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላደረጉት እገዛ ከልብ እናመሰግናለን ሲሉም አስፍረዋል።

16/11/2017

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

የክልሉን ህብረተሰብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ስራዎች ተገናክረው መቀጠል እንዳለባቸው  የሀረሪ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ  አስታወቀ ።*************************የሐረ...
23/07/2025

የክልሉን ህብረተሰብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ስራዎች ተገናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የሀረሪ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ ።
*************************

የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና አባላት የክልሉን የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የ2017 እቅድ አፈጻጸምና የ2018 እቅድን ገምግመዋል።

የአፈጻጸምና እቅድ ሪፖርቱን ለምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አባላት ያቀረቡት የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ሀላፊው አቶ መሀመድ ያህያ የክልሉን የፋይናንስ አቅም ማሳደግና ግልጽ የፋይናንስ አሰራር እንዲኖር ሰፊ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አብራርተዋል።

ሙስናና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ የደንበኞችን እርካታ ወደ 90 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ለቋሚ ኮሚቴ አባላቱ አብራርተዋል ።

የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን በቴክኖሎጂ በመታገዝ 80 በመቶ አፈጻጸም ደረጃ መድረሱን ገልጸዋል። በክልሉ የፋይናንስ አሰራርን በማዘመን 48 በሚሆኑ የክልሉ ተቋማት ላይ ክትትልና ድጋፍ መደረጉን ገልጸው ግልጽ የሆነ የፋይናንስ አስራር እንዲኖር ማስቻሉን አንስተዋል።

የመንግስት ተቋማት የግዢና ፋይናንስ አሰራርን በተመለከተ በኤሌክትሮኒክስ እንዲተገበር መደረጉንና በዚህም በክልልና በፌደራል ደረጃ ከ5 ቢሊየን ብር በላይ መሠብሰብ መቻሉን ገልጸዋል ።

የሴክተር ተቋማት የኦዲት ግኝትን እና ክትትልን በተመለከተ የመንግስት ሐብት እንዳይመዘበር ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት።

ቢሮ ሀላፊው በመቀጠልም የ2018 እቅድን ያቀረቡ ሲሆን በመንግሥት የተያዘው በጀት ለታለመለት አላማ እንዲውል በትኩረት ይሰራል ብለዋል ።

የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አባላት በቀረበው ሪፖርት ላይ ሀሳብና አስተያየታቸውን ሰጥታዋል። የወረዳዎች የፋይናንስ አሰራርና ክትትል ምን ይመስላል ? የውስጥ ኦዲትን ለማጠናከር እየተሰራ ያለው ስራ ምን ይመስላል? የክልሉን የፋይናንስ ስርአት ለማሳደግ ምን እየተሰራ ይገኛል የሚሉ ጥያቄዎችን አንስተዋል።

በተጨማሪም በወቅቱ ኦዲት ሪፖርታቸውን ያላቀረቡ ሴክተሮች ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ምን ይመስላል? የመንግስት ንብረትን ኪሳራን ለመከላከል የሚሰሩ ስራዎችስ ምን ይመስላሉ የሚሉ ጥያቄዎች ይገኙበታል።

ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ሀላፊ አቶ መሀመድ ያህያ የተነሱ ሀሳቦችን እንደግብአት በመውሰድ የነበሩ ጥሩ ጎኖችን በማስቀጠል ክፍተቶችን በቀጣይ በጀት አመት ለመቅረፍ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

በመጨረሻም በክልሉ ምክርቤት ቋሚ ኮሚቴ የበጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ፈቲያ ሳኒ ባስቀመጡት አቅጣጫ ግልጽ የሆነ የፋይናንስ አሰራርን መዘርጋት ፣ የክልሉን ገቢ ማሳደግ፣ የኦዲት ግኝትን መከታተል፣ የሰራተኞችን ግንዛቤ ማሳደግና ሴቶችን ማብቃት ስራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

የፋይናንስ ተጠቃሚነትን ማሳደግ፣ የተቋማት በጀት ለታለመለት አላማ እንዲውል በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባም አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

ዘጋቢ ሙየዲን ሙክታር
16/11/17

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ : https://www.youtube.com/

ቴሌግራም: https://t.me/hararimassmediaagency

የበጎ ፈቃድ ተግባር ማህበራዊ ችግሮችን በመቅረፍ የመደጋገፍ ባህል ይበልጥ  ያጠናክራል፦ አቶ ኦርዲን በድሪ *******የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክ...
23/07/2025

የበጎ ፈቃድ ተግባር ማህበራዊ ችግሮችን በመቅረፍ የመደጋገፍ ባህል ይበልጥ ያጠናክራል፦ አቶ ኦርዲን በድሪ
*******
የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን የአቅመ ደካማ ቤት እድሳት መርሀ ግብር አስጀምረዋል።

የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን የ 12 የአቅመ ደካማ ዜጎች የመኖሪያ ቤት እድሳትን በማስጀመር ለ 500 አቅመ ደካማ ቤተሰብ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል ።

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በወቅቱ እንደገለጹት በጎ ፍቃደኝነት ለሰው ልጅ የተሰጠ መልካም ተግባር መሆኑን ገልፀው ብሄር ፣ ቋንቋ ዘር ሳይለይበት ለሁሉም ሰው በቅንነትና በመልካምነት የማገልገል ተግባር ነው ሲሉ ገልጸዋል ።

በጎ ፍቃደኝነትን የእለተ እለት ተግባር በማድረግና እርስ በእርስ በመደጋገፍ፣ በመተጋገዝና በአብሮነት መቆም ዋነኛው ተግባር ሊሆን ይገባልም ብለዋል።

የበጎ ፈቃድ ተግባር ማህበራዊ ችግሮችን በመቅረፍ የመደጋገፍ ባህል ይበልጥ የሚጎለብትበት መሆኑንም ገልጸው አጠናክሮ ማስቀጠልም ይገባል ብለዋል።

የአረንጓዴ አሻራ መርሀ-ግብር የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም በአለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅናና ተጨባጭ ለውጥ ያስገኘ መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ አክለዋል ።

አቶ ኦርዲን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና ተጠሪ ተቋማት በክልሉ በመገኘት ላከናወኑት በጎ ተግባርም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የበጎ ፍቃድ ተግባራትን ለማጠናከር የበኩላችንን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ደግሞ የኢፌድሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር በለጠ ሞላ ገልጸዋል።

የበጎ ፍቃደኝነት ተግባር የሁልግዜም ተግባር መሆን እንዳለበት ያመላከቱት ሚኒስትሩ ሁሉም በዚህ መልካም ተግባር ላይ በመሳተፍ ሀገራዊ ሀላፊነቱን እንዲወጣም ጠይቀዋል ።

ሀረር ከተማን ዘመናዊ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎችን ለማገዝና ከተማዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ እየተከናወነ የሚገኘውን ተግባር እንደሚደግፉም አረጋግጠዋል።

በቀጣይም በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የበጎ ፍቃድ ተግባራትን ለማጠናከር የበኩላችንን ሚና ለመወጣት ዝግጁ ነን ሲሉም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል ።

በመርሀ-ግብሩ ላይ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ የተካሄደ ሲሆን የሲሲቲቪ የደህንነት ካሜራ በፖሊስ ኮሚሽን በመገኘት ምልከታ አካሂደዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በክልሉ የአቅመ ደካሞች ቤት ለመገንባት የሚያስችል የመሠረተ ድንጋይ አስቀምጠዋል ።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ኡመርን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ ተቋማት ተገኝተዋል።

ዘጋቢ፦ ፍቃዱ በላይ
16/11/17

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

23/07/2025

በኢፌድሪ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር በለጠ ሞላ የተመራ ልኡክ በሀረሪ ክልል የተሰሩ የልማት ስራዋችን ሲጎበኙ

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ ተጠሪ ተቋማት የአቅመ ደካማ ወገኖች የመኖሪያ ቤቶች እድሳትን አስጀመሩ*********የየሀረሪ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እና ...
23/07/2025

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ ተጠሪ ተቋማት የአቅመ ደካማ ወገኖች የመኖሪያ ቤቶች እድሳትን አስጀመሩ
*********

የየሀረሪ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እና ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ ተጠሪ ተቋማት በጋራ በመሆን የአቅመ ደካማ ወገኖች የመኖሪያ ቤቶች እድሳትን አስጀመሩ ።

በመርሀ ግብሩ በክልሉ በከተማና ገጠር ወረዳዎች ስር የሚገኙ የአቅመ ደካማ ዜጎችን የመኖሪያ ቤቶች እድሳትን አስጀምረዋል ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ ተጠሪ ተቋማትና የሀረሪ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ኡመርን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችም ተገኝተዋል ።

ዘጋቢ፦ ፍቃዱ በላይ
16/11/17

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

Address

Harar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Mass Media Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harari Mass Media Agency:

Share