Harari Mass Media Agency

Harari Mass Media Agency Harari Mass Media Agency is a public media operating in Harar, Ethiopia.
ገፃችንን በመከተል ትኩስ ዜና እና መረጃዎችን ያገኛሉ።

ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአጭር ጊዜ በዓሉን ለማስተናገድ  ያከናወነው ቅድመ ዝግጅት  የሚደነቅ ነው :- ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ ****የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 20ኛውን የኢትዮጵያ...
14/11/2025

ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአጭር ጊዜ በዓሉን ለማስተናገድ ያከናወነው ቅድመ ዝግጅት የሚደነቅ ነው :- ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ

****
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን ለማስተናገድ በአጭር ግዜ ያከናወነው ቅድመ ዝግጅት የሚደነቅ መሆኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ዛህራ ሁመድ ገልፀዋል።

ምክትል አፈ ጉባኤዋ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአጭር ጊዜ በዓሉን ለማስተናገድ ያከናወነው ቅድመ ዝግጅት የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል።

ቀሪ ስራዎች በቀሩት ጊዜያት እንዲጠናቀቁ አቅጣጫ መቀመጡንና አብዛኛዎቹ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ተናግረው በዓሉን የክልሉን ሁለንተናዊ ገጽታ ለማስተዋወቅ መጠቀም ይገባል ሲሉም ምክትል አፈ ጉባኤዋ አሳስበዋል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ትግሉ መለሰ በበኩላቸው ክልሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተጀመሩ መሰረተ ልማቶችን ለማጠናቀቅ ያደረገው ዝግጅት የሚደነቅ ነው ብለዋል።

በዓሉን በሚመጥን መልኩ የተገነቡ የመንገድ፣ የስቴዲየም፣ የሆቴሎችና የሁነት ማሳያ ፕሮጀክቶችና መሰረተ ልማቶችን በአጭር ጊዜ በጥራት ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል ተሞክሮ የሚወሰድበት ነው ሲሉም ተናግረዋል።

በአሉ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያንፀባርቅ መልኩ እንደሚከበር የገለፁት ደግሞ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ዘሪሁን እሸቱ ናቸው ።

በዓሉን በደመቀ ሁኔታ ለማክበር የተለያዩ ኮሚቴዎች መዋቀራቸውን ገልፀው በመሰረተ ልማት ግንባታ፣ በሰላምና ፀጥታ፣ በሎጂስቲክ እና መስተንግዶ ስራዎች መከናወናቸውንም አብራርተዋል።

ዘጋቢ :- ይድነቃቸው ጌታቸው
05/03/18

ተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

የዘንድሮ የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ስናከብር የከተማውን ልማት ባፋጠነ መልኩ ነው :- ከንቲባ ሳሙኤል ሽጉጤ ****በአሉን አስመልክቶ በሆሳዕና ከተማ የተገነቡ ፕሮጀክቶች የከተማውን ...
14/11/2025

የዘንድሮ የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ስናከብር የከተማውን ልማት ባፋጠነ መልኩ ነው :- ከንቲባ ሳሙኤል ሽጉጤ

****
በአሉን አስመልክቶ በሆሳዕና ከተማ የተገነቡ ፕሮጀክቶች የከተማውን ገፅታና የስራ ባህልን የቀየሩ መሆናቸውን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ ገለፁ።

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ በሰጡት መግለጫ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአሉን ለማስተናግድ ከተመረጠበት ግዜ ጀምሮ በዋናነት የበአል ማክበሪያ ስፍራዎች ላይ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን መሰራታቸውን ተናግረዋል።

በዋናነትም ለዝግጅቱ የተለያዩ ፕሮግራሞች የሚከናወኑበት የስታዲየምና አዳራሽ ግንባታ በአንፊ ቲያትር ደረጃ ግንባታው በፍጥነት ተገንብቶ መጠናቀቁን ገልፀዋል።

ለበአሉ ታዳሚዎችም ደረጃቸውን የጠበቁ የማረፊያ ክፍሎች መዘጋጀታቸውን ጠቁመው ከ1,625 በላይ ለሚሆኑ የባህል ልኡካን ቡድን አባላትም በዋቻሞ ዩንቨርስቲ ለማሳረፍ ዝግጅት መጠናቀቁንም አክለዋል ።

በከተማ አስተዳደሩ 20ኪ.ሜ የሚሸፍን የውስጥ ለውስጥ መንገድ እየተከናወነ እንደሚገኝና ከዚህ ውስጥም 10.3 ኪ.ሜ የሚሆነው በፌደራል መንግስት
እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል ።

የመንገድ ግንባታዎቹም በተያዘላቸው የግዜ ገደብ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ከተማዋን ለማስዋብ እየተከናወኑ ከሚገኙት 35ኪሜ የኮሪደር ልማት ስራ ውስጥ 22.2 ኪ.ሜትሩ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንደተገነባና በቀጣይ ቀናት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆኑም ገልጸዋል ።

በአጠቃላይ በሆሳዕና በ7 ቢልዮን ብር ወጪ የተለያዩ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆናቸውን የተናገሩት ከንቲባው በዚህ ረገድ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚገነቡ የልማት ስራዎች በርካታ ስለመሆናቸውም ተናግረዋል።

ቀኑን አስመልክቶ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶች ክልሉን ዘመናዊ ከማድረግ ባሻገር በርካታ ቱሩፋቶችን ይዘው መምጣታቸውን ገልጸዋል ።

በከተማው እንግዶች በሚመጡባቸው ሶስት አቅጣጫዎች ደማቅ አቀባበል ለማድረግ በቂ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመው ለዚህም መልካም ወጣቶች ተደራጅተው በዝግጅት ላይ እንደሚገኙም አስታውቀዋል።

ዘጋቢ :-ይድነቃቸው ጌታቸው
05/03/18

ተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

14/11/2025

መንግስት ከሚያከናውናቸው ሰውተኮር ስራዎች ውስጥ የትምህርት ቤት የምገባ መርሀግብር አንዱ ነው ፦ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ

14/11/2025

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር ያደረጉት ውይይት።

የሃንጋሪ ምርጥ የዶሮ ዝርያዎችን ለአርብቶ አደሮች ማከፋፈሉን የሀረሪ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።*************************************ቁጥራቸው 3,982 ቴትራ ኢች የሚ...
14/11/2025

የሃንጋሪ ምርጥ የዶሮ ዝርያዎችን ለአርብቶ አደሮች ማከፋፈሉን የሀረሪ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
*************************************

ቁጥራቸው 3,982 ቴትራ ኢች የሚባሉ ምርጥ የዶሮ ዝርያዎች ከሃንጋሪ በማስመጣት ለአርሶና አርብቶ አደሮች እንዲከፋፈል መደረጉን የሀረሪ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የተመረጠው ዶሮ ዝርያ በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ሜድሮክ ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከሀንጋሪ እነዲያስገባ ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረት 3982 ዶሮዎች አስገብቶ በማባዛት ለአርሶና አርብቶ አደሮች እንዲከፋፈል እየተደረገ መሆኑን በሀረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የእንስሳትና የአሳ ሀብት ልማት ዳይሬክተር አቶ ኑሬ መሀመድ ገልፀዋል።

አዲሱ የዶሮ ዝርያ በዓመት ከ250 እስከ 260 እንቁላል የሚጥሉ ሲሆኑ ከ3 እስከ 4
ኪሎ ግራም ስጋ እንደሚኖራቸው አክለው ገልፀዋል።

በክልሉ የዶሮ እርባታና ማከፋፈያ ማዕከል ኃላፊ ወይዘሮ ሰርካለም ዳመራው በዶሮ ልማት ኢኒሼቲቭ የአርሶአደሮችን ህይወት ለማሻሻል 7 የዶሮ መንደር ተቋቁሞ ለአንድ አርሶ አደር 25 የዶሮ ጫጩት በመስጠት ስራው እየተተገበረ መሆኑን ተናግረዋል።

በዘመናዊ ማሽነሪዎች በመጠቀም በፍጥነት በማባዛት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም እየተሰራ ነው ሲሉ አክለው ገልፀዋል።

ከውጭ የገቡ የተመረጡ የዶሮ ዝርያዎች በቂ ምግብ ስለሚያስፈልጋቸው፤ ለዶሮዎቹ በማሽን የተዘጋጀ መኖ መሰጠት እንዳለበት በቢሮው የእንስሳት መኖ ምርት ባለሙያ የሆኑት አቶ መሃመድ አብዲ ተናግረዋል።

የተመረጡ የዶሮ ዝርያዎችን በስፋት በማባዛት የሌማት ትሩፋት ፕሮግራምን ለማስፋት እየተሰራ ስለመሆኑም ተገልጿል።

ዘጋቢ፦አዳም ኢብራሂም
5/3/18

ተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ሰጪነቷን ትቀጥላለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) *******************ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ኢትዮጵያ ለአ...
14/11/2025

ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ሰጪነቷን ትቀጥላለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ ሰጪነት ከአፍሪካ የመሪነት ሚናዋን መጫወት እንደምትቀጥል አስታወቁ።

ኢትዮጵያ COP 32ን ለማስተናገድ ያቀረበችውን ጥያቄ በሙሉ ድምፅ ለደገፈው ለአፍሪካ የተደራዳሪዎች ቡድን ምስጋና አቅርበዋል።

አፍሪካ በብራዚል ቤሌም ከተማ በተካሄደው የ2025ቱ የተመድ የአየር ንብረት ለውጥ ኮንፈረንስ (COP 30) ላይ በአንድ ድምፅ ተናግራለች፤ ዓለምም ሰምቷታል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

ኢቢሲ
05 03 2018

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ የተመራውን ልዑክ በፅ/ቤታቸው ተቀብለው ተወያይተዋል።ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ...
14/11/2025

ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ የተመራውን ልዑክ በፅ/ቤታቸው ተቀብለው ተወያይተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን በተመለከተ ለልዑካን ቡድኑ ገለፃ አድርገዋል።

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በበኩላቸው በሰጡት አስተያየት ከወራት በፊት ወደ ሀረር በመጡበት ወቅት ጅምር የኮሪደር ልማት ስራዎችን መመልከታቸውን በማስታወስ በአሁኑ ጊዜ ከተማዋን የቀየረ የኮሪደር ልማት ማከናወን መቻሉን አድንቀዋል።

በተለይ በከተማዋ የሚገኙ ታሪካዊ ቅርሶች ይዘታቸውን ሳይለቁ መልሰው እንዲለሙ የተደረገበት ሁኔታ አበረታች መሆኑን ገልፀዋል።

ይህም በክልሉ ካለው ሰላም ጋር ተዳምሮ የሀረር ከተማን ለኑሮ የተመቸች አድርጓታል ሲሉ አምባሳደሩ መናገራቸውን ከክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

በቀጣይ የሆቴል ቱሪዝምን ጨምሮ ሀረር ከምትታወቅባቸው መስህቦች አንዱ የሆነውን የሀረር ቡና በማስተዋወቅ የአሜሪካ ኢንቨስተሮች ወደ ክልሉ በመምጣት በዘርፉ እንዲሰማሩ ለማስቻል ይሰራል ብለዋል።

05/03/18

በሀረሪ ክልል አዎንታዊ ሰላም መገንባቱን የክልሉ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ ገለፁ።***********************በሀረሪ ክልል ማህበረሰቡን የሰላሙ ባለቤት ...
14/11/2025

በሀረሪ ክልል አዎንታዊ ሰላም መገንባቱን የክልሉ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ ገለፁ።
***********************

በሀረሪ ክልል ማህበረሰቡን የሰላሙ ባለቤት በማድረግ በተሰራው ስራ በአሁኑ ወቅት በክልሉ አዎንታዊ ሰላም መገንባቱን የክልሉ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሃላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ ገለፁ።

የክልሉን ሰላምን ለማጽናት በተከናወኑ ተግባራት የማህበረሰቡ ንቁ ተሳትፎ የጎላ መሆኑንም ነው ሀላፊው የገለፁት ።

የሀረሪ ክልል ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ሀላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ በተለይ ለሀረሪ ብዙሀን መገናኛ ኤጀንሲ እንዳስታወቁት በክልሉ የጸጥታ መዋቅርን ይበልጥ በማጠናከርና ለሰላም ልዩ ትኩረት በመስጠት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት መቻሉን ገልጸዋል ።

በተለይ ማህበረሰቡን የሰላሙ ባለቤት በማድረግ በተከናወኑ ተግባራት አዎንታዊ ሰላም ማስፈን መቻሉን ጨምረው ገልፀዋል።

የክልሉን ሰላም ለማስፈን በተከናወኑ ተግባራት የማህበረሰቡ ሚና የጎላ መሆኑን ጠቁመው ማህበረሰቡን ከፀጥታ ተቋማት ጋር ያለውን ቅንጅት ይበልጥ በማጠናከር የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራ ሲከናወን መቆየቱንም አንስተዋል።

ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን ከማጠናከርና የክልሉን ሰላም ከማጎልበት አኳያ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የሰላም ቤተሰቦች ተሳትፎአቸው የላቀ እንደነበርም አንስተዋል ።

ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎን ከአጎራባች ክልሎች ጋር በቅርበት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመው በዚህም ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት መቻሉንም ገልጸዋል ።

በክልሉ የሲሲቲቪ የደህንነት ካሜራ የመሰረተ ልማትን ተግባራዊ በማድረግ የክልሉን ደህንነት ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ ይገኛልም ሲሉም ተናግረዋል ።

አሁን የተገኘውን አዎንታዊ ሰላም በቀጣይ ዘላቂ ለማድረግ ከመቼውም ግዜ በላይ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው ማህበረሰቡም ለሰላም ዘብ በመቆም ሀገራዊ ሀላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል ።

ዘጋቢ፦ፍቃዱ በላይ
05/03/18

ተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

የተማሪዎች የምገባ መርሀ-ግብር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ጉልህ ሚና አለው።ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ******************************በሐረሪ ክልል 40ሺ ተማሪዎ...
14/11/2025

የተማሪዎች የምገባ መርሀ-ግብር የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ጉልህ ሚና አለው።ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ
******************************

በሐረሪ ክልል 40ሺ ተማሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በዛሬው እለት በይፋ አስጀምረዋል።

የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በወቅቱ እንደገለፁት የተማሪዎች የምገባ መርሀግብ እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህፃናት ወደትምህርት ቤት እንዲመጡ እንዲሁም እንዳያቋርጡ እና የትምህርት ጥራትን ከማረጋገጥ አንፃር ትልቅ አበርክቶ እንዳለው ገልፀዋል ።

መንግስት ከሚያከናውናቸው ሰውተኮር ስራዎች ውስጥ የትምህርት ቤት የምገባ መርሀግብር አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል ።

የምገባ መርሀግብሩ በክልሉ በገጠርና በከተማ በ67 ትምህርትቤቶች ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቁመው ይህም 40ሺ ተማሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አንስተዋል ።

ተማሪዎች ትምህርታቸውን ያለ ሀሳብ በአግባቡ እንዲከታተሉ ፣የትምህርት ቅበላቸው እንዲጨም ፣ በስነ ልቦና ብቁ እና ጥሩ ውጤት እንዲያስመዘግቡ እንደሚረዳ ጠቁመዋል ።

በተለይም መቀንጨር እና መቀጨጭን በማስቀረት በክህሎ፣ በአመለካከት ፣በእውቀት እና በስነምግባር የተገነባ አምራች ዜጋ ለመፍጠር እንደሚያስች ገልፀዋል ።

ይህ መርሀግብር የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን ለማብቃት የሚሰራ በመሆኑ ሁሉም ህብረተሰብ በየደረጃው ባለው አቅም ማገዝ እና መደገፍ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጌቱ ነገዎ በበኩላቸው በዘንድሮው አመት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ቀደም ተብሎ መጀመሩን ጠቁመው ይህም የተማሪዎችን በስነ ልቦና ዝግጁነት እንደሚጨምር ጠቁመዋል ።

የተማሪዎች ማርፈድ ፣ መጠነ ማቋረጥ እና የትምህርት ክፍለ ጊዜ ብክነትን እንደሚያስቀር አስረድተዋል ።

ይህም በክልል አቀፍ የ6 እና 8ኛ ክፍል ዉጤት ላይ ማየት መቻሉን ገልፀው በዘንድሮው የተሻለ ዉጤቶችን ለማስመዝገብ በትኩረት እንደሚሰራ አክለዋል።

በተለይም መርሀግብሩ ከ600 በላይ ለሆኑ እናቶች የስራ እድል መፍጠሩን ገልፀዋል ።

ዘጋቢ፦ገዛኸኝ አራጌ
05/03/2018

ተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

የዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ በድምቀት ይከበራል :- ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)  **********...
14/11/2025

የዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ በድምቀት ይከበራል :- ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

****************************

የዘንድሮው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ በሆሳዕና ከተማ በድምቀት እንደሚከበር የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል ።

በመግለጫቸውም ዘንድሮ በአሉ ሲከበር ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፍፃሜ ሆኖ በርካታ የተስፋ ብርሃን የታየባቸው ትላልቅ ፕሮጀክቶች ለምረቃ የበቁበትና መሰረት የተጣለባቸው መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀዋል።

በአሉ በክልሉ መከበሩ የህዝቡን አንድነት ከማጠናከር በተጨማሪ የልማት ኢኒሼቲቭ በጥራትና በብዛት በላቀ ደረጃ መሰራት መቻሉን ተናግረዋል።

በቱሪዝም ዘርፉ ደግሞ ክልሉ ያለውን ፀጋ አውጥቶ እንዲጠቀም መልካም እድል የፈጠረና በተጨማሪ ዲጅታል ኢትዮጵያ ተግባራዊ ለማድረግ አበርክቶው የጎላ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዝግጅት ምእራፍ ምቹና በቂ የሆቴል ዝግጅት መደረጉን ፣ የሲንፖዚየም አዳራሽ መጠናቀቁንና ከ35 እስከ 40ሺህ ተመልካቾችን መያዝ የሚችል ስታዲየም መገንባቱንም ርዕሰ መስተዳደሩ ገልፀዋል ።

በአሉን በድምቀት ለማክበርም ዝግጅት መጠናቀቁን በመግለፅ በክልሉ አስተማማኝ የፀጥታ ግንባታ እንደተከናወነም አክለዋል።

ርዕሰ መስተዳደር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በመልእክታቸው ህዝቡ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ በክልሉ ተገኝቶ በበአሉ እንዲሳተፍ ጥሩ አቅርበዋል።

20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት ኅዳር 29/2018 ዓ.ም በሆሳዕና ከተማ ''ዲሞክራሲ መግባባት ለኀብረ ብሄራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል ይከበራል።

ዘጋቢ :- ይድነቃቸው ጌታቸው
05/ 03/18

ተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

በኢትዮጲያ የአሜሪካ አምባሳደር የተመራ ሉኡካን ቡድን የቢሲዲሞ ጠቅላላ ሆስፒታልን ጎበኙ።*******በኢትዮጲያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ የተመራው ሉኡካን ቡድን በቢሲዲሞ ሆስፒታል ...
13/11/2025

በኢትዮጲያ የአሜሪካ አምባሳደር የተመራ ሉኡካን ቡድን የቢሲዲሞ ጠቅላላ ሆስፒታልን ጎበኙ።
*******
በኢትዮጲያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ የተመራው ሉኡካን ቡድን በቢሲዲሞ ሆስፒታል በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።

ጉብኝቱ በዋናነት በሆስፒታሉ በኪዩር ብላይንድነስ ፕሮጀክት ግብረሰናይ ድርጅት አማካኝነት እየተሰጠ ያለውን የአይን ሞራ ግርዶሽ ህክምናን ተመልክተዋል።

ለግብረ ሰናይ ድርጅቱ የአሜሪካ ኤንባሲ ድጋፍ የሚደረግለት መሆኑንና በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ህክምና አግኝተው አይታቸው መመለስ መቻሉ በመመልከታቸው አበረታች ተግባር መሆኑን አምባሳደሩ በጉብኝታቸው ወቅት ተጠቁሟል።

ኪዩር ብላይንድነስ ግብረሰናይ ድርጅት በጎርጎርያኑ የዘመን አቆጣጠር በ2012 የተመሰረተ ሲሆን በአብዛኛው የኢትዮጲያ አካባቢዎች ከ200ሺ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የአይን ሞራ ግረዶሽ ህክምና መስጠቱን የፕሮጀክቱ የክትትል ቁጥጥር እና የጥናትና ምርምር ማናጀር አቶ አገሩ ከበደ ገልጸዋል።

ባለፉት አመታት በምስራቅ ሃረርጌ ዞን ባቢሌ ወረዳ በሚገኘው ቢሲዲሞ ጠቅላላ ሆስፒታል ከምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢ ለመጡ 24ሺ በላይ ሰዎች የአይን ግርዶሽ ህክምና ማግኘታቸውን አቶ አገሩ ገልጸው በዚህ ዙርም እስከ አርብ በሚኖራቸው ቆይታ ከአንድ ሺ ሁለት መቶ በላይ ለሚሆኑ ታካሚዎች አገልግሎት ለመስጠት አቅደው እየሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል።

የህክምና አገልግሎቱን የሚሰጠው በጎ ፍቃደኛ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ሲፒሻሊስቶች መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም የተለያዩ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፎችንና የህክምና አገልግሎትን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አቶ አገሩ አስረድተዋል።

የቢሲዲሞ ጠቅላላ ሆስፒታል የአይን ህክምና ክፍል ሀላፊ እና የአይን ህክምና ባለሙያ የሆኑት አቶ ኢዘዲን ጀማል ፕሮጀክቱ ላለፉት አመታት ከምስራቁ የሀገሪቱ አካባቢዎች ለሚመጡ የአይን ሞራ ግርዶሽ ህክምናን በሆስፒታላቸው ሲሰጥ መቆየቱን ጠቁመዋል።
ማህበረሰቡ አገልግሎቱን እንዲያገኙ በተለያዩ አማራጮች መረጃን ተደራሽ በማድረግና የልየታ ስራን በመስራት ህክምና የሚያስፈልጋቸውን እንዲያገኙ የማድረግ ስራ ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅትም ከሰኞ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ከስምንት መቶ በላይ ታካሚዎች ህክምና ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

በእለቱ ህክምና የተደረገላቸው ታካሚዎችም ለረጅም ጊዜያት በእይታ ችግር ሲሰቃዩ እንደነበር ጠቁመው ያለምንም የገንዘብ ክፍያ የአይን ብርሀናቸው በመመለሱ መደሰታቸውንና ህክምናውን ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ቤተልሄም ደሴ
04.03.18

የዓለም ጤና ድርጅት (Who) ለኢትዮጵያ 300 ሺ የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ አደረገ።***የዓለም ጤና ድርጅት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለተከሰተው የቫይረስ በሽታ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት 300 ሺ ...
13/11/2025

የዓለም ጤና ድርጅት (Who) ለኢትዮጵያ 300 ሺ የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ አደረገ።
***
የዓለም ጤና ድርጅት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለተከሰተው የቫይረስ በሽታ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት 300 ሺ የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ ማደረጉን አሳውቋል።

የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንደገለጹት የተከሰተውን ቫይራል ሄሞራጂክ ፊቨር (Viral Hemorrhagic Fever) ህመም አፋጣኝ ድጋፍ ለመስጠት ከአለም ጤና ድርጅት የአደጋ ጊዜ ፈንድ 300 ሺ የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ ማደረጉን ገልጸዋል።

የዓለም ጤና ድርጅት አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ ድጋፍን ለማሳደግ ዝግጁ መሆኑንም ዳይሬክተሩ አክለው ገልጸዋል።

እንደ ዳይሬክተሩ መግለጫ ድንበር ዘለል የሆነ የበሽታ ስርጭትን ለመከላከል በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን የሚገኙ የዓለም ጤና ድርጅት ቢሮዎች በቅንጅት እየሰሩ መሆኑን ጠቁሟል።

ድርጅቱ በሽታው ወደ ተቀሰቀሰበት አካባቢ ባለሞያዎችን ጨምሮ የተለያዩ መድኃኒት እና ቁሳቁሶችን መላኩንም ዳይሬክተሩ አሳውቀዋል።

እስከ አሁን ድረስ 8 የሚሆኑ ዜጎች በቫይራል ሄሞራጂክ ፊቨር (Viral Hemorrhagic Fever) በሽታ ተጠርጥረው በማቆያ ውስጥ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ የጤና ሚንስቴር ና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት መረጃ ያሳያል።

ዘገባው የአለም ጤና ድርጅት (WHO) ነው
4/3/2018

Address

Red Cross Street
Harar
1331

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Mass Media Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harari Mass Media Agency:

Share