Harari Mass Media Agency

Harari Mass Media Agency Harari Mass Media Agency is a public media operating in Harar, Ethiopia.
ገፃችንን በመከተል ትኩስ ዜና እና መረጃዎችን ያገኛሉ።

በክልሉ የገቢ አሰባሰብ አቅምን በማሳደግ የታዩ ጉድለቶችን ለመሙላት በቅንጅት ይሰራል :- አቶ መሀመድ ያህያ*********በሀረሪ ክልል የገቢ አሰባሰብ አቅምን በማሳደግ የታዩ ጉድለቶችን ለመ...
02/01/2026

በክልሉ የገቢ አሰባሰብ አቅምን በማሳደግ የታዩ ጉድለቶችን ለመሙላት በቅንጅት ይሰራል :- አቶ መሀመድ ያህያ
*********

በሀረሪ ክልል የገቢ አሰባሰብ አቅምን በማሳደግ የታዩ ጉድለቶችን ለመሙላት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ሀላፊ አቶ መሀመድ ያህያ ገለፁ።

በሀረሪ ክልል የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱን ለመምራት የተቋቋመው ኮሚቴ በክልሉ በ5 ወር መሰብሰብ የነበረባቸውና ያልተሰበሰቡ ግብሮችን በአግባቡ መሰብሰብ በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል።

በዚህም የገቢ አፈጻጸምን በዝርዝር በማየትና በመገምገም ጉድለቶችን በመለየት በዕቅዱ መሰረት ያልተከናወነበት ችግሮች ላይ መግባባት ላይ ከተደረሰ በኃላ የማስተካከያ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል ።
የኮሚቴው ሰብሳቢ እና የሀረሪ ክልል የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ ያህያ እንደገለፁት ገቢን በመሰብሰብ ረገድ የባለድርሻ አካላት ድጋፍና ቅንጅት ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

በክልሉ የገቢ አሰባሰብ አቅምን በማሳደግ የታዩ ጉድለቶችን ለመሙላት በትኩረትና በቅንጅት እንደሚሰራ አስታውቀዋል።

24/ 04/18

''የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ ያምናል'' :- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)**** የመደመር መንግስት...
02/01/2026

''የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ ያምናል'' :- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
****

የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ እንደሚያምን እና ለተግባራዊነቱም እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ሀሳብ የለውጥ ኃይል ነው።ምሁራን ደግሞ የለውጥ ወኪሎች ናቸው ብለዋል።

ምሁራን በማኀበረሰብ ውስጥ የሚፈጥሩት ለውጥም ሀገርን ወደ ብልጽግና እንደሚወስድ ጠቅሰው፥ በዚህ ረገድም ምሁራን ሀሳብ አክባሪና አፍቃሪ፣ ጥልቅ አሰላሳይ፣ አንባቢ፣ ችግር ፈቺና መፍትሄ አሳሽ መሆን እንደሚጠበቅባቸው አመልክተዋል።

በዛሬው እለት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማስመልከት ዩኒቨርሲቲው ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጽሁፍ በማቅረብ መሳተፋቸውን ጠቁመዋል።

በመድረኩም የኢትዮጵያ ምሁራን በሁለንተናዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ሚና በሚመለከት ሰፊ ውይይት መደረጉን ተናግረዋል።

የመደመር መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ላይ አይተኬ ሚና እንዳላቸው በጽኑ ያምናል፣ ለተግባራዊነቱም እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት።

ተቋማቱም የመማር ማስተማር እንዲሁም የምርምር ስራዎችን ከቴክኖሎጂ ጋር በማናበብ ወደ ፈጠራና ተግባር መለወጥ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበው፥ ይህም የኢትዮጵያን ብልጽግና በተደመረ አቅም ለማፋጠን ሚናው ከፍተኛ ነው ብለዋል።

24/ 04/ 18

"ሀሳብ የለውጥ ኃይል ነው ምሁራን ደግሞ የለውጥ ወኪሎች ናቸው።"-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)*********የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምሁራን በማህበረሰብ...
02/01/2026

"ሀሳብ የለውጥ ኃይል ነው ምሁራን ደግሞ የለውጥ ወኪሎች ናቸው።"-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*********

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምሁራን በማህበረሰብ ውስጥ የሚፈጥሩት ለውጥ ሀገርን ወደ ብልጽግና እንደሚያሸጋግር በመጥቀስ ምሁራን የለውጥ ወኪልና የሀሳብ ኃይል መሆን እንደሚገባቸው አሳሰቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 75ኛ ዓመት በማስመልከት በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው። በመድረኩ ላይ የመወያያ ጽሁፍ ያቀረቡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ምሁራን በሁለንተናዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ሚና በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በመልዕክታቸው ምሁራን ሊላበሷቸው የሚገቡ እሴቶችን ሲገልፁ "ምሁራን የሀሳብ አፍቃሪ፣ ጥልቅ አሰላሳይ፣ አንባቢ፣ እንዲሁም ችግር ፈቺና መፍትሄ አሳሽ መሆን ይጠበቅባቸዋል" ብለዋል። በተጨማሪም "የመደመር" መንግስት ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ በመግለጽ፣ ተቋማቱ በሀገራዊ የብልጽግና ጉዞ ውስጥ ያላቸውን ድርሻ አይተኬ መሆኑን መንግስታቸው በጽኑ እንደሚያምንጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

በመጨረሻም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመማር ማስተማርና የምርምር ተግባራቸውን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በማናበብ ወደ ፈጠራና ተግባር መለወጥ እንዳለባቸውም አሳስበዋል። ይህም የኢትዮጵያን ብልጽግና በተደመረ አቅም ለማፋጠን የሚኖረው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአፅንኦት ተናግረዋል ፡፡

24/4/2018

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መንግስት ልማትን በዕውቀት ለመምራት ለጀመረው ስራ ተደማሪ ጉልበት ነው : -ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ****** አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መንግስት ልማ...
02/01/2026

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መንግስት ልማትን በዕውቀት ለመምራት ለጀመረው ስራ ተደማሪ ጉልበት ነው : -ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
******

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መንግስት ልማትን በዕውቀት ለመምራት ለጀመረው ስራ ተደማሪ ጉልበት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ75 ዓመታት ለኢትዮጵያ የእውቀት ብርሃን ያበራው የዕውቀት ቤት ነው ብለዋል።

በትጋት የሚመራ ምርምር፣ በሙግት የሚዳብር ሃልዮት፤ በአመክንዮ የሚበለጽግ ፍልስፍና የዩኒቨርሲቲው መለያ ቀለሞች መሆናቸውን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ የዕውቀት ብርሃን መፍለቂያ እና የለውጥ ጥሪ ማስተጋቢያ የሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ ዛሬም የጀመርነውን ልማት በዕውቀት ለመምራት ተደማሪ ጉልበት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው ከምሥረታው ጀምሮ የኢትዮጵያ የለውጥ እና የልማት ጥያቄዎች የፈለቁበት፤ የጊዜው ትንታግ ወጣቶች የለውጥ አብዮት የጎሰሙበት የታሪክም የዕውቀትም ቤት እንደሆነም ነው ያወሱት።

ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የተደረገው ምክክርም ትናንት እና ዛሬን እንዲሁም ዛሬን እና ነገን፤ ዘላቂ ብልጽግናን ከተሳካ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ጋር አሠናስሎ ለመምራት ጉልበት የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል።

በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ተምራችሁ፣ በዕውቀት ተኮትኩታችሁና ካባ ጭናችሁ ዛሬ በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ተቋማት ለምታገለግሉ ምሁራንና ባለሞያዎች እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ ብለዋል።

በተጨማሪም የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ ለመገንባት በርትታችሁ እየተማራችሁ ላላችሁ ጥበብ ፈላጊ ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት በዓል አደረሳችሁ ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

24/4/2018

የንባብ ባህልን ማጎልበት ትውልድን ለማነፅ የጎላ ሚና እንዳለው ተመላከተ።******************* በሀረሪ ክልል ባህል፣ ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ አዘጋጅነት በሙሜ ሰርጊሰ አንደኛና መካከለኛ...
02/01/2026

የንባብ ባህልን ማጎልበት ትውልድን ለማነፅ የጎላ ሚና እንዳለው ተመላከተ።
*******************

በሀረሪ ክልል ባህል፣ ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ አዘጋጅነት በሙሜ ሰርጊሰ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት የተማሪዎች የንባብ ውድድር ተካሂዷል ።

በመርሀግብሩ ላይ በሀረሪ ክልል ባህል፣ ቅርስ እና ቱሪዝም ቢሮ የሴቶች ህፃናት እና ወጣቶች ዳይሬክተር ወይዘሮ በድሪያ መሀመድ እንደገለፁት ተማሪዎች የንባብ ክህሎታቸዉን እንዲያዳብሩ ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ ነዉ ብለዋል።

ቢሮዉ ትዉልድን ከማነፅ አኳያ ለትምህርት ቤቶች የተለያዪ መፅሀፍቶችን እና ቁሳቁሶችን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

የሙሜ ሰርጊሰ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ርዕሰ መምህርት ነጃት ሲራጅ የተማሪዎችን የንባብ ባህልን ከማሳደግ አንፃር የዛሬው ቀን ትልቅ ፈይዳ እንዳለው ገልፀው የክልሉ ባህል፣ ቅርሰና ቱሪዝም ቢሮ ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በመድረኩ በት/ቤቱ ተማሪዎች መካከል የንባብ ውድድሮች የተካሄደ ሲሆን ከአንደኛ እሰከ 3ኛ ለወጡ ተማሪዎች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ።

በእለቱም የሐረሪ ክልል ባህል፣ ቅርስ እና ቱሪዝም ቢሮ ለሙሜ ሰርጊስ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 500 መፅሀፎችን አበርክቷል።

ዘጋቢ፦አያንቱ አህመድ
24/04/18

ተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

የጤና መድህን መዋጮ ጤናቸውን ከመጠበቅ ባሻገር የቁጠባ ባህላቸውን እያጠናከረ እንደሚገኝ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ገለፁ።******************የጤና መድህን ተጠቃሚ የሆኑት የሀረሪ ክልል...
02/01/2026

የጤና መድህን መዋጮ ጤናቸውን ከመጠበቅ ባሻገር የቁጠባ ባህላቸውን እያጠናከረ እንደሚገኝ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ገለፁ።
******************

የጤና መድህን ተጠቃሚ የሆኑት የሀረሪ ክልል ነዋሪዎች ከጤና መድህን አገልግሎት የተሻለ የጤና አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በየአመቱ የሚሰበሰበዉ የጤና መድህን መዋጮ ጤናችን ከመጠበቅ ባሻገር የቁጠባ ባህላችንን እያጠናከረ ይገኛል ብለዋል የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች።

የጤና መድህን አገልግሎት ከአቅም በላይ ከሆነ የህክምና ወጪ ያዳናቸዉ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ነዋሪዎቹ እንደገለፁት የኑሮአችን ዋስትና የሆነዉ ጤና መድህን በፈለግንበት ግዜ የጤና አገልግሎት የምናገኝበት ነዉ ሲሉም ገልፀዋል።

የጀጉላ ሆስፒታል የጤና ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ኤሪት ረመዳን እና እስማኢል አብዲ እንደገለፁት የጤና መድህን ተጠቃሚ የሆኑ ደንበኞች በእኩልነት እና ፍትሐዊ በሆነ መልኩ አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በሀረሪ ክልል ጤና ቢሮ የጤና መድህን ፕሮግራም አስተባባሪ ጀማል መሐመድ በሰጡት አስተያየት የህብረተሰቡን ኑሮ ለማገዝና ጤናቸውን ለማሻሻል የጤና መድህን አገልግሎት ከፍተኛ ሚና እንዳለዉ ተናግረዋል።

አስተባባሪዉ ጨምረው እንደተናገሩት በክልሉ 9 ወረዳዎች ጤና ጣቢያ እና 2 ሆስፒታል አገልግሎቱ እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዉ በ2017 ዓ.ም 33 ሺ 310 አባወራዎች አባላትን ማፍራት የተቻለ መሆኑን ገልጸው ከጥቂት ቀናት በኋላ በሚጀመረው የ2018 ዓ.ም የጤና መድህን ምዝገባ ደግሞ 46 ሺ 151 አባላትን ለማፍራት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

ዘጋቢ፦አደም ኢብራሂም
24/4/2018

ተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

በሀረሪ ክልል ሀገር በቀል እውቀቶችን በማጎልበት ሞያዊ በሆነ የምዘና ስርዓት ውስጥ እንዲያልፉ ቅድመ ዝግጅት ስራ ተጀመረ። *************************የክልሉ ምክር ቤት የማህበራ...
02/01/2026

በሀረሪ ክልል ሀገር በቀል እውቀቶችን በማጎልበት ሞያዊ በሆነ የምዘና ስርዓት ውስጥ እንዲያልፉ ቅድመ ዝግጅት ስራ ተጀመረ።
*************************

የክልሉ ምክር ቤት የማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ደሊላ ዩሱፍ ሀገር በቀል እውቀቶችን በማሳደግ በሀገር ብልፅግና ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ የማድረግ ስራዎች እየተሰሩ እየተሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ሀገር በቀል እውቀቶችን በማጎልበት ሞያዊ በሆነ ምዘና ስርዓት ውስጥ እንዲያልፉ ማድረግ በዘርፉ የተሰማሩ ሙያተኞች ተወዳዳሪና ብቁ እንዲሆኑ ያስችላል ብለዋል።

የሀረሪ ክልል ባህል ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ተወለዳ አብዶሽ በበኩላቸው ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት እየጠፋ የነበረው የእደ ጥበብ ሙያ ጠብቆና ለማቆየትና ለትውልድ ለማስተላለፍ ከማገዙም ባለፈ ስታንዳርድ ወጥቶለት በእውቀት እንዲመራ የሚያስችል ነው ሲሉ ተናግረዋል።

በክልሉም የኢናይ አቢዳ ማሰልጠኛ ከፌዴራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን የሞያዎቹ ምዘናና ደረጃ (level) የማውጣት ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ነው የገለፁት።

የሀረሪ ክልል የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ሃላፊ አቶ በዳሳ ገመዳ ሀገር በቀል የሙያ ደረጃዎችን በተከተለ እየተሰጡ የሚገኙ ስልጠናዎችን በማጠናከር ወደ ኢንዱስትሪው እንዲገቡ የማስቻል ስራዎች በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይም ስልጠና የጨረሱ ሰልጣኞች በምዘና እንዲያልፉ የማድረግ ስራ ለማከናወን በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

በመርሃግብሩ ላይም የሀረሪ ክልል ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ባለሞያዎችና ሰልጣኞች ተገኝተዋል።
24/4/18

ተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

የ75 ዓመት እድሜ ያላቸውን እናት በአሰቃቂ  ሁኔታ የገደለው ግለሰብ በእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተቀጣ።**************ተከሳሽ ሪያድ ዩሱፍ መሀመድ የተባለ ግለሰብ በሐረር ከተማ ሐኪም ወ...
02/01/2026

የ75 ዓመት እድሜ ያላቸውን እናት በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ግለሰብ በእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተቀጣ።
**************

ተከሳሽ ሪያድ ዩሱፍ መሀመድ የተባለ ግለሰብ በሐረር ከተማ ሐኪም ወረዳ ቀበሌ 17 ልዩ ስሙ ጁኔር ት/ቤት አጠገብ በሚገኘዉ መኖሪያ ቤት ጥቅምት 30 ቀን 2018 ከምሽቱ 3፡30 አካባቢ ሰውን ለመግደል አስቀድሞ በማሰብ አሳቻ ሰአት ጠብቆ የቅርብ ዘመዱና የ75 ዓመት ዕድሜ ያላቸውን እናት ሟች ኪሚያ ማዊ የተባሉትን ስለት ቢላዋ ይዞ ሟች የሚኖሩበት ሳሎን ቤት በመግባት በያዘዉ ቢላዋ ቀኝ አንገታቸው ላይ በመውጋት እንዲሁም በቦክስ ግራ አይናቸውን በመምታትና የተለያዩ አካላዊ ጉዳቶችን በማድረስ በ1996 የወጣውን የኢፌዲሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 539/1/ሀ በመተላለፍ ለፈጸመዉ ከባድ የሰው ግድያ ወንጀል ህግ ክስ አቅርቦበታል።

ተከሳሽ የወንጀል ድርጊቱን አልፈጸምኩም ጥፋተኛ አይደለሁም በማለት ክዶ ተከራክሯል።

ከሳሸሰ ዐቃቤ ህግ ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን መፈጸሙን ያስረዱልኛል ያላቸዉን ማስረጃዎች ያቀረበ ሲሆን፤ ተከሳሸ እንዲከላከል ፍርድ ቤቱ የሰጠዉን ብይን ተከትሎ ያለዉን የመከላከያ ማስረጃ እንዲያቀርብ በተደጋጋሚ እድል የተሰጠዉ ቢሆንም መከላከያ ማስረጃዉን ሳያቀርብ ቀርቷል።

ጉዳዩ ሲመለከት የቆየዉ የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ የወንጀል ችሎት ታህሳስ 24 ቀን 2018 በዋለው ችሎት ተከሳሽ ጥፋተኛ ነዉ ሲል ዉሳኔ ሰጥቷል።

የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በግራ ቀኙ ተከራካሪ ወገኖች የቀረበዉን የቅጣት አስተያየት ከመረመረ በኃላ ታህሳስ 24 ቀን 2018 በዋለዉ ችሎት ተከሳሽ በእድሜ ልክ ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ሲል የቅጣት ዉሳኔ ማስተላለፉን ከክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተገኘው መረጃ ያስረዳል።

24/04/18

ተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ :
https://www.youtube.com/

ቴሌግራም:
https://t.me/hararimassmediaagency

ሀረር ወርጊቢት 29ታኝ ዓመት ሒልቂ 17 ታሕሳስ 23/2018
01/01/2026

ሀረር ወርጊቢት 29ታኝ ዓመት ሒልቂ 17 ታሕሳስ 23/2018

Gaazeexaa Harar Waggaa 29ffaa lakko 17 Mudee 23/2018
01/01/2026

Gaazeexaa Harar Waggaa 29ffaa lakko 17 Mudee 23/2018

ሀረር ጋዜጣ 29ኛ ዓመት ቁጥር 17 ታሕሳስ 23/2018 ዓ.ም
01/01/2026

ሀረር ጋዜጣ 29ኛ ዓመት ቁጥር 17 ታሕሳስ 23/2018 ዓ.ም

01/01/2026

የኮሪደር ልማት ስራው ለረጅም ጊዜ የልማት ጥያቄአችንን በተጨባጭ ምላሽ የሰጠ በመሆኑ ተደስተናል፦ የጂንኤላ ወረዳ ነዋሪዎች

Address

Red Cross Street
Harar
1331

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Mass Media Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harari Mass Media Agency:

Share