Harari Mass Media Agency

Harari Mass Media Agency ሀረሪ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ
Harari Broadcasting Network (HBN) is a public media operating in Harar, Ethiopia.
ገፃችንን በመከተል ትኩስ ዜና እና መረጃዎችን ያገኛሉ።

በክልሉ በትምርት ዘርፍ የተመዘገበው ስኬት የጉዞው መጀመሪያ እንጂ መዳረሻ አይደለም፦ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ***በሐረሪ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን በዘርፉ ለተገኘው አመርቂ...
15/09/2026

በክልሉ በትምርት ዘርፍ የተመዘገበው ስኬት የጉዞው መጀመሪያ እንጂ መዳረሻ አይደለም፦ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ
***

በሐረሪ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን በዘርፉ ለተገኘው አመርቂ ውጤት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የእውቅናና የሽልማት መርሐ ግብር ተካሄዷል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በክልሉ በዘርፉ የተመዘገበው ስኬት የብዙ ዓመታት ጥረት ፍሬ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

የተመዘገበው የላቀ ውጤት የጉዞው መጀመሪያ እንጂ መዳረሻ አለመሆኑን የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ስኬቱን አስጠብቆ ለመቀጠል የበለጠ ትጋትና ጥረት እንደሚጠይቅ አሳስበዋል።

ተማሪዎች ያመጡት ውጤት የኃላፊነት ካባ እንጂ ማረፊያ አለመሆኑን በመገንዘብ፣ ለነገው ትልቅ ስኬት በትህትናና የመማር ፍላጎታቸውን ሳይቀንሱ አዲስ እውቀትን ለመገብየት ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

የተመዘገበው የላቀ ውጤት የአንድ ጊዜ አጋጣሚ ሳይሆን የትምህርት ቤቶች ቋሚ ባህልና መለያ ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል።

የተማሪዎች ስኬት ከጀርባው የቤተሰብ ያልተቋረጠ ድጋፍና መስዋዕትነት ያለበት በመሆኑ፣ ልጆቻቸው ወደ ላቀ ደረጃ በሚሸጋገሩበት ወቅት ድጋፋቸው ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም፣ ትምህርት ቤቶች የተሻለ የመማር-ማስተማር አካባቢ እንዲኖራቸው ለማድረግ፣ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን ለማጠናከርና ዝቅተኛ ውጤት ያመጡ ትምህርት ቤቶች ድክመታቸውን አርመው ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲመጡ ልዩ ክትትል እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።

በተጨማሪም በትምህርት ቤቶች መካከል ያለውን የውጤት ልዩነት ማጥበብ እንደሚገባ ጠቁመው፣ በቀጣይ የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተና የማለፍ ምጣኔን ወደ 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ለማድረስ ታቅዶ መሠራት እንዳለበት አሳስበዋል።

በክልሉ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሕፃናት በሙሉ ወደ ትምህርት ገበታ እንዲገቡ የተቀናጀ ንቅናቄ እንደሚያስፈልግም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ጥራት ያለው ትምህርት በውጤት ብቻ ሳይሆን በሥነ-ምግባር፣ በክህሎትና በእውቀት የሚለካ በመሆኑ ሙሉ አቅምን አውጥቶ መሥራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ነገዎ በበኩላቸው፤ በሐረሪ ክልል በትምህርት ጥራት፣ በሥርዓተ ትምህርት ሪፎርም እና በመሠረተ ልማት ላይ በተከናወኑ ሰፊ ሥራዎች በክልላዊና ሀገር አቀፍ ፈተናዎች አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በርካታ አዳዲስ ትምህርት ቤቶችና የመማሪያ ክፍሎች መገንባታቸውን፣ የመጽሐፍ ጥምርታ መሻሻሉን እና በ"ትምህርት ለትውልድ" ንቅናቄ 34 ሚሊዮን ብር ማሰባሰብ መቻሉንም አመልክተዋል።

በ2018 የትምህርት ዘመን 6ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱት ተማሪዎች መካከል 78.31 በመቶ የሚሆኑት 50 እና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸውን የገለጹት አቶ ጌቱ፣ በ8ኛ ክፍል ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥም 72.64 በመቶ የሚሆኑት ማለፍ መቻላቸውን ጠቁመዋል።

በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከተፈተኑት ተማሪዎች መካከል 22.76 በመቶ የሚሆኑት ከ300 በላይ ያመጡ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

በእውቅናና ሽልማት መርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም፣ የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ አፈ ጉባኤ አቶ ሙህየዲን አህመድ፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ኡመር፣ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ፣ መምህራን፣ ተማሪዎችና ወላጆች ተገኝተዋል።

በገዛኸኝ አራጌ
05/01/18

የብሪክስ (BRICS) አባል ሀገራት በወሳኝ ማዕድናትና በሰላማዊ የጠፈር ትብብር ላይ በጋራ ለመስራት ተስማሙ።****የBRICS አባል ሀገራት የወሳኝ ማዕድናት አቅርቦት ሰንሰለት ፍትሃዊ፣ ግል...
15/09/2026

የብሪክስ (BRICS) አባል ሀገራት በወሳኝ ማዕድናትና በሰላማዊ የጠፈር ትብብር ላይ በጋራ ለመስራት ተስማሙ።
****

የBRICS አባል ሀገራት የወሳኝ ማዕድናት አቅርቦት ሰንሰለት ፍትሃዊ፣ ግልፅ እና ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን እንዲሁም የጠፈር ቴክኖሎጂ ለሰላማዊ ዓላማ እንዲውል በትብብር ለመስራት የጋራ አቋም መያዛቸው አስታወቁ።

በውይይቱ ላይ የBRICS ሀገራት በዘመናዊ ኢንዱስትሪ፣ በታደሽ ኃይል፣ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ምርትና አስፈላጊ የሆኑ ወሳኝ ማዕድናት ላይ ጠንካራ ትብብር እንዲኖር አጽንኦት በመስጠት በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።

በተለይ የማዕድን ሀብት ያላቸው ሀገራት ጥሬ ሀብቶቻቸውን ብቻ ከመላክ ይልቅ በሀገራቸው ውስጥ ማቀነባበርና ተጨማሪ እሴት መፍጠር እንዲችሉ የትብብርና የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ማስፋፋት እንደሚገባ ተጠቁሟል።

በሌላ በኩል፣ የጠፈር ምርምርና ቴክኖሎጂ ለሰላማዊ ዓላማዎች መጠቀም እንዲቻል የጋራ ትብብርን ማጠናከር ላይም እንዲሁ።

በጠፈር ሳይንስ ትብብሩ የምድር ገፅታ ምልከታ፣ የአየር ንብረት ክትትል እና ሊከሰት ከሚችል የተፈጥሮ አደጋ የቅድመ ጥንቃቄ መረጃ ግብዕት ማጋራት በሻገር ቴክኖሎጂው ዘርፈ ብዙ የልማት እቅዶችን እንደሚያግዝ ተጠቅሷል።

በአጠቃላይ ውይይቱ የBRICS ትብብር ከኢኮኖሚና ንግድ ጉዳዮች ባሻገር ወደ በወሳኝ ማዕድናት ፣ በቴክኖሎጂ፣ በአረንጓዴ ኃይልና ወደ ጠፈር ምርምር እያደገ መምጣቱን ተመልክቷል፣ ዘገባው የአውትሉክ ኢንዲያ ድህረገፅ ነበር።

የአውትሉክ ኢንዲያ ዘገባ ነበር

በበሀር ጠንክር

05 01 2019

በሐረሪ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የትምህርት አካላት የማበረታቻ የሽልማትና እውቅና መርሐ ግብር እየተካሄደ ይገኛል።በሐረሪ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን ...
15/09/2026

በሐረሪ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የትምህርት አካላት የማበረታቻ የሽልማትና እውቅና መርሐ ግብር እየተካሄደ ይገኛል።

በሐረሪ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን በትምህርት የላቀ ውጤት እና አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም የትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች የማበረታቻ ሽልማትና የዕውቅና መስጠት ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው።

በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም፣ የሐረሪ ብሔራዊ ጉባኤ አፈ ጉባኤ አቶ ሙህየዲን አህመድ፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ኡመር፣ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ፣ መምህራን፣ ተማሪዎችና ወላጆች ተገኝተዋል።

በገዛኸኝ አራጌ
05/01/19

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ተደራሽ እና ቀልጣፋ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው ፦ አቶ ሙኸታር ሳሊህ******የሐረሪ መሶብ አንድ ማዕከል ቦርድ መደበኛ ስብሰባውን በ...
14/09/2026

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ተደራሽ እና ቀልጣፋ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው ፦ አቶ ሙኸታር ሳሊህ
******

የሐረሪ መሶብ አንድ ማዕከል ቦርድ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት አካሂዷል።

በስብሰባው የማዕከሉ አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ፣ በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችና ተቋሙን የማጠናከር ሥራዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በውይይቱ የሐረሪ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ተደራሽ እና ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችሉ ነጥቦች የተነሱ ሲሆን፣ የቦርዱ አባላት ለሥራው ውጤታማነት የድርሻቸውን እንዲወጡ የሐረሪ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ እና የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሙኽታር ሳሊህ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ማዕከሉ ለክልሉ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ያለው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ቦርዱ ክትትልና ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።

መደበኛ ስብሰባው በቀጣይ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን በመለየት የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።

04/01/19

14/09/2026

ሀረሪ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ ኸበር 4/1/19

በክልሉ የህዝቦችን አብሮነት በማሳደግ ሰላምን የማጽናት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - አቶ ቶፊቅ መሀመድ*********በሀረሪ ክልል የሕዝቦችን የአብሮነት እሴትን በማጎልበት ሰላምን የማጽናት ሥራ...
14/09/2026

በክልሉ የህዝቦችን አብሮነት በማሳደግ ሰላምን የማጽናት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - አቶ ቶፊቅ መሀመድ
*********

በሀረሪ ክልል የሕዝቦችን የአብሮነት እሴትን በማጎልበት ሰላምን የማጽናት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ቶፊቅ መሀመድ ገለጹ።

የቢሮ ኃላፊው በሰጡት መግለጫ እንዳሉት በክልሉ የህዝቦችን አብሮነት በማጠናከር የሰላም እሴት ግንባታን ለማጎልበት የተጀመረው ቅንጅታዊ ሥራ ይጠናከራል፡፡

የነዋሪዎችን የሰላም ባለቤትነትና የጸጥታ ኃይሎችን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስራን በማጠናከር የክልሉን ሰላምና ደኅንነት ይበልጥ ማጠናከር ተችሏል።

ሕዝቡን ያሳተፈ የጸጥታ ሥራ በማከናወን ክልሉ የሰላም ደሴት እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል።

በክልሉ ዘላቂና አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ለማስቻል የሰላም ሠራዊት አደረጃጀት ገንቢ ሚና እየተወጣ መሆኑንም አንስተዋል።

ሕዝቡን በንቃት በማሳተፍ ለእያንዳንዱ ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ ከጸጥታ ኃይሎች ጋር በቅንጅት የሚሰራበት አውድ ተፈጥሯል ነው ያሉት።

ወንጀል ፈጽመው ለማምለጥ የሚሞክሩ ኃይሎችን በቀላሉ በመቆጣጠር በቅንጅት በመሥራት ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል።

በቀጣይም የክልሉን የሰላም፣ የጸጥታና ደህንነት ሥራ በላቀ ደረጃ ለመፈጸም በቁርጠኝነት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም የወንጀል ምጣኔን መቀነስ፣ የዜጎችን የሰላም ባለቤትነት ሚና ማላቅ፣ ልዩነቶችን በንግግር የሚፈታ ማኅበረሰብ በመፍጠር በሰላም እሴት ግንባታ ላይ በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

ሕገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ፣ የመሬት ወረራና ሕገ ወጥ ግንባታ እንዲሁም ሌሎች ወንጀሎችን በመቆጣጠር የሕግ የበላይነት በዘላቂነት የሰፈነባት ክልል የማድረግ ራዕይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

4/1/2019

በሐረሪ ክልል የ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደት ነገ ይጀመራል።****በሐረሪ ክልል የሚገኙ ሁሉም የመንግሥትና የግል ትምህርት ቤቶች ነገ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም ተማሪ...
14/09/2026

በሐረሪ ክልል የ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደት ነገ ይጀመራል።
****

በሐረሪ ክልል የሚገኙ ሁሉም የመንግሥትና የግል ትምህርት ቤቶች ነገ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም ተማሪዎችን በመቀበል የመማር ማስተማር ሂደቱን በይፋ እንደሚጀምሩ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ጫላ ሙክታር እንደገለፁት በክልሉ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት ሥራ በማጠናቀቅ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የመማር ማስተማር ሂደቱ በተቀመጠው የትምህርት ካሌንደር መሠረት የሚከናወን መሆኑን ጠቅሰው፤ ወላጆችና አሳዳጊዎች ለትምህርት የደረሱ ልጆቻቸውን አስፈላጊውን የትምህርት ግብዓት በማሟላት ወደ ትምህርት ቤት እንዲልኩ ጥሪ አቅርበዋል።

አክለውም ለመማር ማስተማር ሂደቱ ስኬታማነት ተማሪዎች፣ መምህራን እና ወላጆች የበኩላቸውን ድርሻና ሀገራዊ ኃላፊነት እንዲወጡ ዳይሬክተሩ መልእክት አስተላልፈዋል።

4/1/2019

14/09/2026

ሀረሪ ክልል ከለውጡ ወዲህ

ማዕከሉ ለአርሶ አደሩ የገበያ ተጠቃሚነትና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው**** የክልሉ መንግሥት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የገነባው የሐረሪ ክልል አርሶ አደሮች የግብርና ...
14/09/2026

ማዕከሉ ለአርሶ አደሩ የገበያ ተጠቃሚነትና የኑሮ ውድነትን ለማቃለል ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው
****

የክልሉ መንግሥት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የገነባው የሐረሪ ክልል አርሶ አደሮች የግብርና ምርት መሸጫ ማዕከል፤ አርሶ አደሮችን በቀጥታ ከገበያ ጋር በማገናኘት፣ የንግድ ሰንሰለቱን በማሳጠር እና የገበያውን ሚዛን በመጠበቅ ረገድ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።

ማዕከሉ አርሶ አደሮች ያመረቱትን ምርት ፍትሃዊና አስተማማኝ ገበያ እንዲያገኙ በማድረግ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ እና ገቢያቸውንም ለማሳደግ አስችሏል።

በተጨማሪም ለህብረተሰቡ በቂ፣ ጥራቱን የጠበቀ እና ተመጣጣኝ ዋጋ ያለው የግብርና ምርት በቀላሉ እንዲደርስ በማድረግ ላይ ይገኛል።

በገበያ ላይ ሊከሰቱ የሚችሉ ያልተገቡ የዋጋ ንረቶችን በመቆጣጠር የተረጋጋና ጤናማ የገበያ ሥርዓት እንዲሰፍን ከማስቻሉም በላይ፣ በአምራቾችና በተጠቃሚዎች መካከል ያለውን ቀጥተኛ ትስስር በማጠናከር የደላሎችን ተፅዕኖ ቀንሷል።

ማዕከሉ የክልሉን አርሶ አደሮች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና በማረጋገጥ እና የኑሮ ውድነት ጫናን በማቃለል ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።

04/01/19

14/09/2026

Hararii Biroodkaastiing Neetwork Oduu Afaan Oromoo 4/1/19

Address

Red Cross Street
Harar
1331

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Harari Mass Media Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Harari Mass Media Agency:

Shortcuts

Share