Khalid Taha

Khalid Taha Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Khalid Taha, Digital creator, Amir Uga, Harar.

09/03/2026
02/03/2026
18/12/2025

⚡️ውድ የቅድመ ክፍያ ቆጣሪ ተጠቃሚ ደንበኞቻችን፤ ይህንን ያውቁ ኖሯል?⚡️

👉 ወደ ደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከላችን ወይም ካርድ መሙያ ጣቢያ ሄደው ወርሃዊ ኢነርጂ እንደገዙ /ካርድ አንዳስሞሉ/ ወዲያው ወይም በቀጣይ ባሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ውስጥ ካርዶዎን ከቆጣሪዎ ጋር ያስተዋውቁ ወይም ይገልብጡ፡፡

👉 ሆኖም ካርድ ከሞሉ በኋላ ባሉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ወደ ቆጣሪ ኢነርጂው ሳይገለብጡት ቢቀሩና በሌላ ቀን (ለምሳሌ በአራተኛው ቀን) ሊገለብጡ ቢሞክሩ፤ ቆጣሪው የገዙትን ኢነርጂ በመሰረዝ /Reject በማድረግ/ የኃይል አቅርቦቱን እንዲቋረጥ ያደርጋል፡፡

💡በመጀመሪያ 3 ቀናት ውስጥ ሲገለብጡ ቆጣሪው ያልተቀበሎዎት እና አገልግሎቱን ያቋረጠብዎት ከሆነ ወዲያውኑ በእለቱ ወደ ደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማእከልዎ በመሄድ ሪፖርት ያደርጉ፡፡

⚠️ ልብ ይበሉ፤ ኢነርጂ ሲገዙ በወር ውስጥ ሊያስጠቅምዎት የሚችለውን የኪሎ ዋት መጠን አስቀድመው ይወቁ

10/10/2025

ለጥገና ሥራ የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

ጥቅምት 01 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 8:00 ድረስ በሐረር ከተማ በ66 ኪ.ቮ. ከፍተኛ መስመር የቅድመ ጥገና ሥራ ስለሚከናወን በቀይ መስቀል ኮንዶሚኒየም፣ ቀበሌ 08፣ 09፣ 10፣ ጀጎል ሙሉ በሙሉ፣ ቀበሌ 13፣ 14፣ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ቀበሌ 15፣16፣17፣ ገብርዔል ቤ/ክ አከባቢ፣ ገለመሽራ ኮንዶሚኒዬም፣ ዶከርና አከባቢ፣ ሸኪብ ተ/ቤት እና አከባቢ፣ ድሬጥያራ ሙሉ በሙሉ፣ ቀላድ አምባ፣ ባቦሌ፣ ጉርሱም እና አከባቢው የሃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡

በተመሳሳይ ጥቅምት 02 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 አስከ ምሽቱ 12፡00 ሰዓት ድረስ በጋምቤላ ከተማ የጥገና ሥራ ለመስራት በጋምቤላ ከተማ ባሮ ማዶ፣ አበቦ እና አካባቢው ላይ የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡

በተጨማሪም ጥቅምት 02 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 እስከ ቀኑ 8:00 ድረስ በአዲስ አበባ በመካኒሳ የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ እና ከረጲስ-መካኒሳ፣ ከጎፋ መካኒሳ በተዘረገው መስመር ላይ የቅድመ ጥገና ሥራ ስለሚከናወን በቄራ፣ ጎፋ ኮንዶሚኒየም፣ ጀርመን አደባባይ፣ ጎፋ ካምፕ፣ ላፍቶ በታች፣ ላፍቶ ሚካኤል፣ ቦሌ ሚካኤል፣ አየር ጤና በከፊል፣ ጋርመንት፣ ሀና ማያም፣ ጀሞ፣ ሀጫሉ ጎዳና፣ ካፕታል ሴሚንቶ፣ ላፍቶ ኢንዱስትሪ፣ ለቡ እና አከባቢው የሃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡

የተቋማችንን ማህበራዊ የሚዲያ ገፆችን በመቀላቀል ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎችን ወዲያውኑ ያግኙ!!

[Facebook] http://www.facebook.com/EEUOfficial
[Telegram] https://t.me/eeuethiopia
[Website] http://www.eeu.gov.et
[YouTube] https://www.youtube.com/
[Tiwtter] https://x.com/EEUEthiopia
[TikTok] https://www.tiktok.com/.electri
[Whatsapp] https://www.whatsapp.com/channel/0029VbAAvBDE50UZXJlIl507

12/05/2025

ለመላዉ የክልላችን ነዋሪዎች እንኳን ደስ አለን!!

ሀረር ከተማ እግር ኳስ ክለብ ወደ ከፍተኛ ሊግ አደገ።

አዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ የማጠቃለያ ዉድድር ላይ ተሳታፊ የነበረዉ የከተማችን ብቸኛ ክለብ አስደናቂ ብቃት በማሳየት የምድቡ መሪ በመሆን ለጥሎ ማለፍ ዉድድር ማለፍ በማቻሉ ምክኒያት ወደ ከፍተኛ ሊግ ማለፉን አረጋግጧል።

ይህ አኩሪ ድል እንዲመዘገብ ላደረጋችሁ አመራሮች፣ አሰልጣኞች፣ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች በሐረሪ ክልል መንግስት ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ።

የሀረር የማንሰራራት ዘመን አሁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል !!

11/05/2025

Address

Amir Uga
Harar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Khalid Taha posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share