Halaale Media Network / ሀላሌ ሚዲያ ኔትወርክ

Halaale Media Network / ሀላሌ ሚዲያ ኔትወርክ የሚዲያ እና የፕሮዳክሽን ድርጅት።

‎የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቅሬታ ደብዳቤ አስገባ !!‎‎ሰኔ 1/2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ዋንጫ ክለባችን ሲዳማ ቡና ወላይታ ዲቻን 2-1 በማሸነፍ ያነሳዉ...
03/07/2025

‎የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቅሬታ ደብዳቤ አስገባ !!

‎ሰኔ 1/2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ዋንጫ ክለባችን ሲዳማ ቡና ወላይታ ዲቻን 2-1 በማሸነፍ ያነሳዉን ዋንጫ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት አላግባብ በሆነ መንገድ ከሲዳማ ቡና ተነጥቆ ለወላይታ ዲቻ ይሰጥ በማለት የወሰኑትን ዉሳኔ በመቃወም የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ በዛሬው እለት የቅሬታ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስገብቷል።

‎የቅሬታ ደብዳቤ ለማስገባት በተቀመጠዉ ቀነ ገደብ መሰረት ክለባችን በዛሬዉ እለት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አላግባብ ዋንጫው ከእኛ እንዲነጠቅ በማለት የወሰነዉን ዉሳኔ በድጋሚ እንዲያጤን እና እንዲያስተካክል በማለት የተለያዩ የFIFA እና የሀገራችን የእግር ኳስ መተዳደሪያ ደንቦችን በመጥቀስ በዉሳኔዉ ላይ ቅሬታዉን በመግለፅ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ በማለት ገልፆ ደብዳቤ አስገብቷል።

‎ክለባችን ሲዳማ ቡና የመጀመሪያ ምዕራፍ ህጋዊ ሂደቱን በተከተለ መልኩ ለፌዴሬሽኑ የቅሬታ ደብዳቤ ያስገባ ሲሆን በቀጣይም ፍትህ እስኪያገኝ ድረስ ህጋዊ ሂደቶችን እየተከተለ ወደተለያዩ ምዕራፎች የሚያመራ ይሆናል።

✍️ Biruk Hanchacha

ሲዳማ ሊግ በነገው እለት ፍፃሜዉን ያገኛል !!‎‎በሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ከየካቲት 22/2017 ዓ.ም ጀምሮ በ16 ክለቦች መሀከል ሲካሄድ የቆየዉ "ሲዳማ ሊግ" በነገዉ ...
28/06/2025

ሲዳማ ሊግ በነገው እለት ፍፃሜዉን ያገኛል !!

‎በሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ከየካቲት 22/2017 ዓ.ም ጀምሮ በ16 ክለቦች መሀከል ሲካሄድ የቆየዉ "ሲዳማ ሊግ" በነገዉ እለት ሰኔ 22/2017 ዓ.ም ፍፃሜውን ያገኛል።

‎ወደ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ለማለፍ ብርቱ ፉክክር እየተደረገበት የቆየዉ "ሲዳማ ሊግ" በነገዉ እለት ከፍተኛ የፌዴራል ፣ የሲዳማ ክልል ፣ የኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት የሚጠናቀቅ ሲሆን የሲዳማ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዚህ አጓጊ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ መላው የክልሉ ስፖርት አፍቃሪ ነዋሪ በሙሉ በመገኘት እንዲታደም ሲል ጥሪዉን ያቀርባል።

‎የማጠቃለያ ፕሮግራሙ በነገዉ እለት እሁድ ከቀኑ 8:00 ሰአት ጀምሮ በሀዋሳ አርተፊሻል ሜዳ ይካሄዳል።

‎አስደሳች ዜና ለመላው ለሲዳማ ቡና ደጋፊዎች በሙሉ !‎‎የሲዳማ ክልል የእግር ኳስ አባት የሆነው የክልላችን የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ አንበሴ አበበ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ...
25/06/2025

‎አስደሳች ዜና ለመላው ለሲዳማ ቡና ደጋፊዎች በሙሉ !

‎የሲዳማ ክልል የእግር ኳስ አባት የሆነው የክልላችን የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ አንበሴ አበበ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ የቦርድ አባል ተደርጓል።

‎የክለባችን የበላይ ጠባቂ የሆኑት የሲዳማ ክልል ፕሬዝዳንት የተከበሩ አቶ ደስታ ሌዳሞ ለሲዳማ ቡና እድገት እና ሁለንተናዊ ለዉጥ በሰጡት ትኩረት ክለቡ ተጠናክሮ መቀጠል ይችል ዘንድ መላው የክልሉ እና ከክልሉ ዉጪ የሚገኙ ስፖርት ወዳጆች በሙሉ የሚወዱትን እና የሚያደንቁትን አቶ አንበሴ አበበን ለክለባችን የቦርድ አባል አድርገው ስለመደቡልን ከልብ እናመሰግናለን።

‎እንደሚታወቀዉ አቶ አንበሴ አበበ ከዚህ በፊት የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ የደጋፊዎች ማህበር ም/ል ፕሬዝዳንት ሆኖ ባገለገለበት ወቅት ዘመን የማይሽረው ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ የሚታወቅ ነዉ።

‎ይህንን የእግር ኳስ አባት ለክለባችን እድገት ወደ ቦርድ አባልነት ላመጡልን ለክልላችን ፕሬዝዳንት ትልቅ አድናቆት እና ክብር አለኝ።

‎መጪዉ ዘመን ለሲዳማ ቡና ብሩህ ነዉ !!
‎እንኳን ደስስስስስስስስስስስስስስስ አለን !!

  !አርቲስት ዶ/ር አዱኛ ዱሞ እና አብርሃም ሻሻሞ ለሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ የሰሩትን አዲስ የሲዳምኛ ሙዚቃ በሲዳምኛ ሙዚቃዎች መገኛ Sidaama Music Tube የቴሌግራም ቻናላችን ...
25/06/2025

!

አርቲስት ዶ/ር አዱኛ ዱሞ እና አብርሃም ሻሻሞ ለሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ የሰሩትን አዲስ የሲዳምኛ ሙዚቃ በሲዳምኛ ሙዚቃዎች መገኛ Sidaama Music Tube የቴሌግራም ቻናላችን ላይ ስለለቀቅንላችሁ ከታች የሚገኘዉን የቴሌግራም ቻናላችንን ሊንክ በመንካት ገብተዉ ያግኙ።

👉 T.me/SidaamaMusic_Tube

Address

Hawassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Halaale Media Network / ሀላሌ ሚዲያ ኔትወርክ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share