Horn Insight

Horn Insight Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Horn Insight, News & Media Website, Hawassa.
(3)

ወጣት ኢያሱ ክፍሌ በአጠቃላይ የ750 ካሬ ሜትር የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ተሸለመለሀገር ሰላምና ለጀግኖች አርበኞች መታሰቢያነት ትልቅ ዓላማ ሰንቆ ከጌዴኦ ዞን ቡሌ ከተማ እስከ አዲስ አበባ...
12/05/2026

ወጣት ኢያሱ ክፍሌ በአጠቃላይ የ750 ካሬ ሜትር የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ተሸለመ

ለሀገር ሰላምና ለጀግኖች አርበኞች መታሰቢያነት ትልቅ ዓላማ ሰንቆ ከጌዴኦ ዞን ቡሌ ከተማ እስከ አዲስ አበባ ድረስ ለ11 ቀናት 388 ኪሎ ሜትሮችን በእግሩ የተጓዘው ወጣት ኢያሱ ክፍሌ፣ ወደ ትውልድ ስፍራው ሲመለስ በደማቅ ሁኔታ ተቀብሎታል። ይህ ጉዞ ወጣቱ ለሀገሩ ያለውን ፍቅርና የሰላምን አስፈላጊነት ለመስበክ ያደረገው ጥረት ተደርጎ የተወሰደ ሲሆን፣ በከተማውና በዞኑ አስተዳደሮች ዘንድም ትልቅ ግምት ተሰጥቶታል።

የወጣቱን ቁርጠኝነትና በጎ ተነሳሽነት ለማበረታታትም ልዩ ልዩ ሽልማቶች ተበርክተውለታል። የጌዴኦ ዞን አስተዳደር በዲላ ከተማ በነበረው ቆይታ የ500 ካሬ ሜትር የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ የሰጠው ሲሆን፣ የቡሌ ከተማ አስተዳደር ደግሞ ተጨማሪ 250 ካሬ ሜትር መሬት በስጦታ አበርክቶለታል። ይህም ወጣቱ በአጠቃላይ የ750 ካሬ ሜትር መሬት ባለቤት እንዲሆን አስችሎታል።

ከመሬት ስጦታው በተጨማሪ፣ የቡሌ ወረዳ አስተዳደር ለወጣቱ ቀና አስተሳሰብ እውቅና በመስጠት የ50,000 (ሃምሳ ሺህ) ብር የገንዘብ ሽልማት ሰጥቶታል። የከተማው አስተዳደር በሰጠው መግለጫ፣ ኢያሱ ክፍሌ የጥንካሬና የሰላም አምባሳደር በመሆን የትውልድ አካባቢውን በበጎ ስም ማስጠራቱን ገልጿል።

ይህ ታሪካዊ አቀባበልና ሽልማት ሌሎች ወጣቶችም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገራቸው በጎ ተግባር እንዲሰለፉ የሚያበረታታ መሆኑ ተመላክቷል።

አንዳንድ የSBC አመራሮች የጎሰኝነት ቅለት ወደ ባለሙያዎች መስፋፋቱ ተገለጸበአለታ ጎሳ ስም የተደራጀው ይህ ቡድኑ ጎሳውን የማይወክልና ፖለቲከኞች የፖለቲካ አላማቸውን ለማሳካት ያቋቋሙት ነው...
12/05/2026

አንዳንድ የSBC አመራሮች የጎሰኝነት ቅለት ወደ ባለሙያዎች መስፋፋቱ ተገለጸ

በአለታ ጎሳ ስም የተደራጀው ይህ ቡድኑ ጎሳውን የማይወክልና ፖለቲከኞች የፖለቲካ አላማቸውን ለማሳካት ያቋቋሙት ነውም ተብሏል

በሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (SBC) ከፍተኛ አመራሮች ዘንድ በግልጽ ሲታይ የቆየው የጎሰኝነት እና የቡድንተኝነት አባዜ፣ አሁን ላይ ወደ ተቋሙ ጋዜጠኞችና ባለሙያዎች እየተጋባ መመጣቱ ተጋለጠ። ይህም ተቋሙ ከሕዝብ ሚዲያነት ወጥቶ የአንድ ወገን የጥላቻና የክፍፍል አጀንዳ ማስፈጸሚያ እየሆነ ነው የሚለውን ስጋት አጠናክሮታል።

ሰሞኑን የዚሁ ተቋም ጋዜጠኛ የሆነው አካሉ ጥላሁን፣ የአለታ ጎሳ እድር በሚል በተከፈተና ከአንድ ሺህ በላይ ሚስጥራዊ አባላት ባሉት የቴሌግራም ግሩፕ ውስጥ ያሰራጨው መልዕክት የዚሁ አደገኛ ዝንባሌ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል። ጋዜጠኛው በጽሁፉ የተወሰኑ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ጠባብ እና ትምክህተኛ በማለት የፈረጀ ሲሆን፣ ይህም በአንድ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ባለሙያ ሊነጸባረቅ የማይገባ፣ ሙያዊ ስነ-ምግባርን የጣሰ የጎሳ ፖለቲካ ወገንተኝነት መሆኑ ተመልክቷል።

ይህ የባለሙያዎች የሥነ-ምግባር ግድፈት በዘፈቀደ የመጣ ሳይሆን፣ በተቋሙ አመራሮች ሲተገበር የቆየው እኩይ አሠራር ውጤት መሆኑ ይነገራል። ከትላንት በስትያ ባወጣነው ዘገባ፣ የSBC የቴክኖሎጂ ዘርፍ ኃላፊና ምክትል የሥራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ዳምጠው ዳዊት፣ በተመሳሳይ መልኩ የጎሳ ሚዲያ ሰራዊት በማደራጀትና የተለየ ሐሳብ ያላቸውን ዜጎች በዲጂታል መንገድ እንዲጠቁ (Report እንዲደረጉ) መመሪያ ሲሰጡ መቆየታቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

አመራሩ የቴክኖሎጂና የስልጣን አቅሙን ተጠቅሞ በጎሰኝነት ተግባር ላይ መሰማራቱ፣ አሁን ላይ ጋዜጠኞችም በግልጽ ወገንተኝነታቸውን እንዲያሳዩና በሕዝቦች መካከል ክፍፍል የሚፈጥሩ መልዕክቶችን እንዲያሰራጩ መንገድ ከፍቶላቸዋል። ጋዜጠኞች የማህበረሰብን አንድነት የመገንባት ሙያዊ ኃላፊነት ቢኖርባቸውም፣ በSBC ውስጥ ግን የአመራሮቹን ፈለግ በመከተል ለቡድን አጀንዳ ቅድሚያ መስጠት የተለመደ አሠራር እየሆነ መጥቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ጋዜጠኛ አካሉ ጥላሁን ከድርጊቱ ከመጸጸት ይልቅ ትችት የሰነዘሩበትን አካላት መልሶ የሚያጠቃና ድርጊቱን የሚከላከል ጽሁፍ አውጥቷል። ጋዜጠኛው "ሲዳማን እኛ ካልመራን የሚል የጠባብነት አመለካከት" በሚል ርዕስ ባቀረበው ሐሳብ፣ እድርን የመሰሉ ማህበራዊ ስብስቦችን እንቅስቃሴ በጎሳ ፖለቲካ መነጽር ማየት የጥላቻ ፖለቲካን ያጠናክራል የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።

እሱ ቡድኑ ጤናማ የእድር ስብስብ ነው ብሎ ለማስተባበል ቢሞክርም፣ በቅርቡ በአለታ ጎሳ ስም የተደራጀው ቡድን በአላማው የተለየ መሆኑን የጎሳው አባል የሆኑ አስተያየት ሰጪዎች ገልጸዋል። ከሀያ ዓመት በላይ ያስቆጠረ ነባር የአለታ ጎሳ እድር እያለ ያንን ወደ ጎን በመተው፣ ይህ አዲስ ስብስብ ለፖለቲካ አላማ ተብሎ የተቋቋመ እንደሆነ ተናግረዋል። እንደ አስተያየት ሰጪዎቹ ገለጻ፣ ቡድኑ በውስን አካላት እንጂ አጠቃላይ ጎሳውን የማይወክልና ፖለቲከኞች የፖለቲካ አላማቸውን ለማሳካት ያቋቋሙት ነው።

ከዚህም ባለፈ፣ ቡድኑን የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እስከ ቢሯቸው ጠርተው ኦረንቴሽን በመስጠት ያደራጁት እንደሆነ አስተያየት ሰጪዎቹ ጠቁመዋል።

የአመራሮቹን ማንነትና ድርጊት ለሚዲያችን በአካል ቀርበው ለማጋለጥ ፍቃደኛ መሆናቸውን ነው የገለጹት።

በSBC ተቋም ውስጥ በአቶ ዳምጠው አደራጅነትና በአካሉ ጥላሁን ተባባሪነት፣ በተቋሙ ውስጥ የብሔር ተዋጽኦን የጠበቁ ጋዜጠኞች የሉም' በሚል ቅስቀሳ በማድረግ ተቋሙን እያወኩ መቆየታቸውን ከተቋሙ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በSBC ውስጥ የሚታየው ተከታታይ የሥነ-ምግባር ውድቀት ተቋሙ ለክልሉ ሕዝብ የሚሰጠውን አገልግሎት ጥያቄ ውስጥ የከተተ ከመሆኑም በላይ ለክልሉ ሰላምና አንድነት አደገኛ መሆኑ ተገክጿል ።

በመሆኑም የመንግስት መዋቅርንና የሚዲያ ተቋምን ሽፋን በማድረግ የጎሰኝነት ቅለትን ወደ ባለሙያዎች እያሰረጹ ባሉ አካላት ላይ የሚመለከተው አካል በአስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ ቀርቧል።

አርቲስት ናጩጫ(ሹሙሎ ሹንደ )በሲዳማ ቡና የክፍያ ችግር ዙሪያ አስተያየት ሰጡናጩጫ(ሹሙሎ ሹንደ) በማህበራዊ ሚዲያ ባጋሩት አስተያየት፣ ለአርሲ ነገሌ 50 ሚሊዮን ብር ቦነስ መሰጠቱ እየተነገ...
11/05/2026

አርቲስት ናጩጫ(ሹሙሎ ሹንደ )በሲዳማ ቡና የክፍያ ችግር ዙሪያ አስተያየት ሰጡ

ናጩጫ(ሹሙሎ ሹንደ) በማህበራዊ ሚዲያ ባጋሩት አስተያየት፣ ለአርሲ ነገሌ 50 ሚሊዮን ብር ቦነስ መሰጠቱ እየተነገረ ባለበት ሁኔታ፣ በሲዳማ ቡና ውስጥ የሚነሱ የደመወዝ ክፍያ ቅሬታዎች ትዝ እንዳሏቸው ገልጸዋል።

አርቲስቱ በአስተያየታቸው፣ አንዳንዴ ቁልቁል የመውረዳችን ችግር የክፍያ መዘግየት ይሆን ብዬም አስባለሁ ሲሉ የክለቡ ውጤት ከፋይናንስ ችግሮች ጋር ሊያያዝ እንደሚችል ጠቁመዋል።

በተጨማሪም፣ የሲዳማ ቡና ደጋፊዎችና ማህበረሰብ አባላት ከዚህ በፊት በክፍያ መዘግየትና በደመወዝ ጉዳዮች ዙሪያ ቅሬታ ሲያቀርቡ መቆየታቸው ይታወሳል።

ድምፃዊ ናጩጫ የአርቲስት ቴዲ አፍሮን የዘር ግንድ በሚመለከት ጥያቄ አዘል አስተያየት ሰነዘረየሲዳምኛ ቋንቋ ድምፃዊ ናጩጫ (ሹሙሎ ሹንደ) በታዋቂው ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አባ...
11/05/2026

ድምፃዊ ናጩጫ የአርቲስት ቴዲ አፍሮን የዘር ግንድ በሚመለከት ጥያቄ አዘል አስተያየት ሰነዘረ

የሲዳምኛ ቋንቋ ድምፃዊ ናጩጫ (ሹሙሎ ሹንደ) በታዋቂው ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አባታዊ የዘር ግንድ ዙሪያ በማህበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ ያሰፈረው መረጃ መነጋገሪያ ሆኗል። ድምፃዊው እንደገለጸው፣ የቴዲ አፍሮ አባት አቶ ካሳሁን ጋርማሞ የተወለዱት በሲዳማ ክልል በቀድሞው ዳራ ወረዳ በተፈሪ ኬላ ከተማ ነው። አርቲስቱ አያታቸው አቶ ጋርማሞ ባረፉ ጊዜም በተፈሪ ኬላ በአካል ተገኝቶ የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸውን ማስፈጸሙን ድምፃዊው እንደ ትልቅ ማሳያ ጠቅሷል።

ናጩጫ የአርቲስቱን የቅርብ ቤተሰቦች አሁን ያሉበትን ሁኔታ በዝርዝር በመጥቀስ ለሀሳቡ ተጨማሪ ማጠናከሪያዎችን አቅርቧል። የአቶ ካሳሁን ወንድም አቶ ኃይሉ ጋርማሞ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ በቴዲ አፍሮ የግል ድርጅቶች ውስጥ እየሰሩ እንደሚገኙ፣ ታሪኬ ጋርማሞ በተፈሪ ኬላ ጤና ጣቢያ ውስጥ በሙያዋ እያገለገለች እንደሆነ፣ እንዲሁም ስንታየሁ ጋርማሞ በተፈሪ ኬላ ከተማ በሌላ የሥራ ዘርፍ ተሰማርቶ እንደሚገኝ በዝርዝር አስፍሯል።

ድምፃዊው በመጨረሻም ቴዲ አፍሮ ኢትዮጵያዊ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በሲዳማ በኩል ያለውን የዘር ግንድ እና የቤተሰብ ትስስር በሚመለከት ያለው እውነታ በግልጽ ለምን እንደማይነገር ጥያቄ አቅርቧል። ሰፊው ሕዝብ እውነታውን ቢያውቅም፣ እውነቱን ለመናገር የተቸገሩት ለምንድነው? ችግሩስ ምንድነው? በማለት ጉዳዩ በግልጽ ሊወራ እንደሚገባ የራሱን ምልከታ አጋርቷል።

በመጨረሻም፣ እናንተ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ያላችሁ ሀሳብና አስተያየት ምንድነው? እውነታው ይፋ መደረጉስ ምን ፋይዳ ይኖረዋል? ያላችሁን አስተያየት ከታች ባለው የአስተያየት ሳጥን ውስጥ ግለጹልን።

የSBC አመራር የጎሰኝነት ቅለት ተጋለጠየሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ባዩ ቡንኩራ፣ የሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት (SBC) የቴክኖሎጂ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዳምጠው ዳዊት የተሰጣ...
09/05/2026

የSBC አመራር የጎሰኝነት ቅለት ተጋለጠ

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዶክተር ባዩ ቡንኩራ፣ የሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት (SBC) የቴክኖሎጂ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዳምጠው ዳዊት የተሰጣቸውን ተቋማዊ ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው በጎሳ ፖለቲካ ላይ ተሰማርተዋል ሲሉ በጽኑ ተችተዋል።

ኃላፊው የአላቲ ቤተሰብ አንድነት እድር በሚል ስም በተከፈተ የቴሌግራም ግሩፕ ውስጥ የጎሳ ሚዲያ ሰራዊት በማደራጀት፣ የኛ በሚሏቸው አካላት ላይ ትችት የሚሰነዝሩ ግለሰቦችንና ገጾችን እንዲከታተሉና ሪፖርት እንዲያደርጉ መመሪያ ሲሰጡ መቆየታቸውን ተመራማሪው በስክሪን ቅጅ አስደግፈው ገልጸዋል። ይህ ድርጊት በመንግስት መዋቅር ውስጥ ተሸሽገው የሚፈጸሙ በደሎችን የሚያሳይና በሲዳማ አንድነት ላይ ከፍተኛ መከፋፈል የሚፈጥር እኩይ ተግባር መሆኑ በትችቱ ተመላክቷል።

ተቋሙ (SBC) ሰሞኑን በተከታታይ በሚፈጽማቸው የሙያና የፕሮቶኮል ስህተቶች ሳቢያ ጠንካራ ትችት ሲሰነዘርበት መቆየቱ ይታወሳል። ለነዚህ ተደጋጋሚ ስህተቶችና ለተቋሙ ችግር እንደ አቶ ዳምጠው ያሉ የሥራ ኃላፊዎች ተቋማዊ አደራቸውን ለግልና ለቡድን የፖለቲካ ፍላጎት መጠቀሚያ ማድረጋቸው እንደ ዋነኛ ምክንያት ሊጠቀስ ይችላል። ኃላፊው ትኩረታቸውን የሕዝብ አገልግሎት በሚሰጠው ተቋም ላይ ከማድረግ ይልቅ በምስጢራዊ የዲጂታል ክትትልና በጎሳ ፖለቲካ ላይ ማሳለፋቸው፣ ለተቋሙ ሙያዊ ውድቀትና ለሚታዩት የአሠራር ግድፈቶች ቀጥተኛ ተጠያቂ ያደርጋቸዋል።

በምስጢራዊ የቴሌግራም ውይይቶች ላይ እንደታየው፣ አቶ ዳምጠው ሪፖርት (Report) በማድረግና ብሎክ (Block) በማስደረግ የተለየ ሃሳብ የሚያራምዱ ግለሰቦችን ዲጂታል የማጥቃት እርምጃ እንዲወሰድ መመሪያ ሲሰጡ ተስተውለዋል። ይህም የቴክኖሎጂ ዘርፍ ኃላፊነታቸውን የሐሳብ ነፃነትን ለመገደብና ለዲጂታል ሳንሱር እየተጠቀሙበት መሆኑን የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ በቡድኑ ውስጥ ቀደም ሲል በሙስና ተገምግመው የተባረሩ ግለሰቦች መሳተፋቸው ደግሞ የተቋሙን ገለልተኝነት ይበልጥ ጥያቄ ውስጥ ይጥላል።

ይህንን በጎሳ እድር ስም የተከፈተና የተለያዩ ይዘቶች ያላቸው መልዕክቶችን የሚያፈበረክ ቡድንን በተመለከተ ባደረግነው ማጣራት፣ ሁለት ስለ ቡድኑ አመሰራረት ቅርበት ያላቸው አካላት ቡድኑ የተቋቋመው በአንድ በክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣን ትዕዛዝ እንደሆነና ተልዕኮውም አደገኛ እንደሆነ አስረድተዋል። እንዲህ ያለ ልዩነትን የሚሰብክ ቡድን የተከበረውን የአለታ ጎሳ የማይወክልና እኩይ ተልዕኮ ባላቸው አካላት የተፈጠረ እንደሆነም ተናግረዋል።

በመሆኑም የተሰጣቸውን ኃላፊነት ሽፋን አድርገው እንዲህ ያለ ከፋፋይ አጀንዳን በሚያራምዱ አካላት ላይ መንግስት በአስቸኳይ እርምጃ ሊወስድ እንደሚገባ ዶክተር ባዩ እና አስተያየት ሰጭዎቹ አሳስበዋል።

ከጌዴኦ ዞን እስከ አዲስ አበባ በእግሩ የተጓዘው ወጣት ኢያሱ ክፍሌ ወደ ዞኑ ስመለስ  አቀባበል ተደረገለት‎‎ከጌዴኦ ዞን ከቡሌ እስከ አዲስ አበባ በእግሩ የተጓዘው ወጣት ኢያሱ ክፍሌ ወደ ጌ...
08/05/2026

ከጌዴኦ ዞን እስከ አዲስ አበባ በእግሩ የተጓዘው ወጣት ኢያሱ ክፍሌ ወደ ዞኑ ስመለስ አቀባበል ተደረገለት

‎ከጌዴኦ ዞን ከቡሌ እስከ አዲስ አበባ በእግሩ የተጓዘው ወጣት ኢያሱ ክፍሌ ወደ ጌዴኦ ዞን ስመለስ በዲላ ከተማ አቀባበል ተደርጎለታል።

‎ወጣት ኢያሱ ክፍሌ ዲላ ከተማ ሲደረሱ በጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር)፣ በዲላ ከተማ ከንቲባ መስፍን ደምሴ(ዶ/ር) ጨምሮ በሌሎች በዞንና በከተማ አስተዳደር ከፍተኛ በመንግስት ኃላፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል።

‎ወጣት ኢያሱ ይህንን አድካሚ ጉዞ ለማድረግ የወሰነው በኢትዮጵያውያን መካከል ያለውን ወንድማማችነት ጽናት እና ብሄራዊ አንድነትን ለማሳየት መሆኑ ተገልጿል።

‎@የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት!

06/05/2026

የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት 3D ዲዛይን

የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ዲዛይን የመጨረሻ ግምገማና  የገቢ ማሰባሰብያ ማስጀመሪያ መድረክ ተካሄደየሀዋሳ ከተማን የቱሪዝም መዳረሻነት ለማሳደግና ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ የታለመው የሐይቅ ዳርቻ ል...
06/05/2026

የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ዲዛይን የመጨረሻ ግምገማና የገቢ ማሰባሰብያ ማስጀመሪያ መድረክ ተካሄደ

የሀዋሳ ከተማን የቱሪዝም መዳረሻነት ለማሳደግና ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ የታለመው የሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የመጨረሻ ዲዛይን ግምገማ እና የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር በይፋ ተጀምሯል።

ይህ በሦስት ምዕራፎች ተከፍሎ የሚከናወነውና 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የልማት ፕሮጀክት፣ ሀዋሳን የኮንፍራንስ ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግና የከተማዋን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ያለመ ነው። የመጀመሪያው ምዕራፍ "የፍቅር ሐይቅ" ተብሎ የሚጠራውን አካባቢ በማልማት የሚጀምር ሲሆን፣ በቀጣይ ዙሮች የአሞራ ገደልና የጥቁር ውኃ አካባቢዎች እንደሚለሙ ታውቋል።

ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ 1.5 ቢሊዮን ብር ለማሰባሰብ የታቀደ ሲሆን፣ ወጪው ከመንግሥት በጀት በተጨማሪ ከንግዱ ማህበረሰብ፣ ከዲያስፖራውና ከነዋሪዎች በሚገኝ ተሳትፎ የሚሸፈን ይሆናል።

የዲዛይን ግምገማው መጠናቀቁን ተከትሎ ፕሮጀክቱ በይፋ ወደ ሥራ እንዲገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።

06/05/2026

የአንድ መምህር የዕውቀት ጉዞ፡ ከክፍል ውስጥ እስከ ዓለም አቀፍ መድረክ!

"ተማሪዎቼን 'ትልቅ አልሙ' እላቸዋለሁ፤ ዛሬ ግን የእኔን ህልም ዳር ለማድረስ የእናንተ እገዛ ያስፈልገኛል!"
ሰላም ጤና ይስጥልኝ፤ ስሜ የልጅ ማኛ (ፍላጎት አብርሃም) እባላለሁ።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፒ.ኤች.ዲ (PhD) ተማሪ እና በሙያዬ መምህር ነኝ። ዛሬ እዚህ የቆምኩት በታላቅ ትህትና እና በተስፋ ተሞልቼ ነው።

እንደ መምህርነቴ፣ በየቀኑ ተማሪዎቼን እውቀት ዓለምን እንደሚለውጥ አስተምራቸዋለሁ። እኔም ያንን እውነት በተግባር ለማሳየት ስደክም ቆይቼ፣ ጥናታዊ ጽሑፎቼ በሦስት ታላላቅ ዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ እንዲቀርቡ በክብር ተጋብዣለሁ።

ሆኖም ግን፣ የመምህርነት ገቢዬ እነዚህን እጅግ ውድ የሆኑ የጉዞ ወጪዎችን ለመሸፈን አቅም አልሆነኝም።

ጥናቴ የሚያተኩረው በ Servant Leadership (አገልጋይ መሪነት) እና Organizational Sustainability" (የተቋማት ዘላቂነት) ላይ ነው።

ጥያቄው፦እንደ እኛ ባሉ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት ውስጥ ያሉ ድርጅቶች፣ የሰራተኞቻቸውን ደህንነት ጠብቀው በውስጣዊ እና ውጫዊ ጫናዎች ሳይበገሩ እንዴት መቀጠል ይችላሉ? የሚለውን ሳይንሳዊ መፍትሔ የሚጠቁም ነው።

የጉዞ መርሃ ግብር እና የሚያስፈልጉ ወጪዎች

እነዚህን ሦስት ታሪካዊ እድሎች ለመጠቀም የገንዘብ እጥረት እንቅፋት ሆኖብኛል፦

1. ቱኒዚያ (AABD Conference):
* የቲኬት ወጪ $736 ዶላር + የሆቴል ወጪ (በቀን $100)

2. ስኮትላንድ (ICRBMF Conference - ኤድንበርግ):
* የምዝገባ ክፍያ ~$400 ዶላር + የቲኬት ወጪ $1,056 ዶላር

3.አሜሪካ (AOM Annual Meeting - ፊላዴልፊያ):
* የምዝገባ ክፍያ $275 ዶላር + የቲኬት ወጪ $978 ዶላር

ለምን የእናንተ ድጋፍ አስፈለገኝ?

"ይህ ጉዞ የኔ ብቻ አይደለም፤ የሀገሬ የኢትዮጵያ እና የእውቀት ፍለጋ ላይ ያሉ ሴቶች ሁሉ ድምፅ ነው!"
ይህ መምህር ያላትን እውቀት ለአለም እንድታካፍል እና የሀገሯን ስም እንድታስጠራ በምትችሉት ሁሉ እንድትረዱኝ እጠይቃለሁ።

የምታደርጉት እያንዳንዱ ሳንቲም ለኔ ትልቅ ትርጉም አለው። እውቀትን ስፖንሰር በማድረግ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ አብረን እንገንባ።

የጎ ፈንድ ሚ (GoFundMe) ሊንኩን መጀመሪያው ኮሜንት ላይ ያገኙታል።

ስለ ትብብራችሁ በቅድሚያ አመሰግናለሁ!

©️ልጅ ማኛ (ፍላጎት አብርሃም)

በሀዋሳ ከተማ በአንድ ባለሀብት ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ ተብሎ የተሰራጨ መረጃ የተሳሳተ መሆኑን የከተማው ፖሊስ መምሪያ ገለጸመምሪያው ሰው ወደ ውሻነት ተቀየረ የሚል መረጃም ፍጹም ከእውነት...
06/05/2026

በሀዋሳ ከተማ በአንድ ባለሀብት ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ ተብሎ የተሰራጨ መረጃ የተሳሳተ መሆኑን የከተማው ፖሊስ መምሪያ ገለጸ

መምሪያው ሰው ወደ ውሻነት ተቀየረ የሚል መረጃም ፍጹም ከእውነት የራቀና መሰረተ ቢስ ነው ብሏል ።

ሰሞኑን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አውታሮች በሀዋሳ ከተማ የሚገኙ አንድ ባለሀብት ላይ የግድያ ሙከራ እንደተደረገባቸው ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ ፍጹም ከእውነት የራቀ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገለጸ። መምሪያው እንዳስታወቀው፣ ይህ መረጃ የፖሊስ ተቋምን ስም ለማጥፋትና በከተማዋ ተቻችለው በሚኖሩ ብሔር ብሔረሰቦች መካከል ግጭት ለመቀስቀስ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ የሀሰት ወሬ ነው።

የመረጃው መነሻ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከታይም ካፌ ጀርባ ባለው መንገድ ላይ በባለሀብቱ ድርጅት ውስጥ የሚሰሩ ሁለት ሰራተኞች፣ ነዳጅን ከተሽከርካሪ ወደ ጀሪካን በመገልበጥ ላይ እያሉ በፖሊስ እጅ ከፍንጅ መያዛቸው እንደሆነ ተገልጿል። ፖሊስ ግለሰቦቹ ድርጊቱ ህገ-ወጥ መሆኑን አውቀው እንዲያስረዱ በጠየቃቸው ወቅት ለህግ ማስከበር ስራው ባለመተባበርና አላስፈላጊ ቃላትን በመጠቀም ጉዳዩን ወደ ሌላ መልክ ለመቀየር መሞከራቸውን መምሪያው አክሎ ገልጿል።

በወቅቱ በነበረው ሁኔታ ፖሊስ በሰከነ መልኩ የህግ ማስከበር ስራውን በማከናወን ድርጊቱን የፈጸሙትን ሰራተኞች ብቻ ለጥያቄ የያዘ ሲሆን፣ በባለሀብቱ ላይ የደረሰ ምንም አይነት ድብደባም ሆነ የአካል ጉዳት አለመኖሩ ተረጋግጧል። ይሁን እንጂ አንዳንድ አካላት ባለሀብቱ ተደበደቡ፣ በጥይት ተመቱ በማለት መረጃውን በማዛባት ለፖለቲካዊ አጀንዳ ፍጆታ ለማዋል መሞከራቸውን ፖሊስ ገልጾ፣ ህብረተሰቡ እንዲህ አይነት የተዛቡ ወሬዎችን ከመቀበል እንዲቆጠብ አሳስቧል።

በሌላ በኩል በታቦር ክፍለ ከተማ ሰው ወደ ውሻነት ተቀየረ በሚል የተናፈሰው ወሬ ከተፈጥሮ ህግ ጋር የሚጋጭና ምንም አይነት እውነትነት የሌለው መሆኑን ፖሊስ አረጋግጧል። እንዲህ አይነቱ የፈጠራ ወሬ ህብረተሰቡን ለማደናገርና የከተማዋን ሰላም ለማደፍረስ የሚንቀሳቀሱ ድብቅ አጀንዳ ያላቸው አካላት ተግባር በመሆኑ፣ ፖሊስ እነዚህን አካላት ከምንጫቸው ለማድረቅ ጥብቅ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።

በመጨረሻም ፖሊስ መምሪያው የከተማዋን ሰላምና የባለሀብቶችን ደህንነት የመጠበቅ ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። የሀሰት መረጃ በሚያሰራጩ አካላት ላይ ጥብቅ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድና ህብረተሰቡም በ7614 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ በመስጠት ከፖሊስ ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርቧል።

በትግራይ ክልል መፈንቅለ መንግስት የሚመስል የሥልጣን ሽግግር ተካሄደለሦስት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ስልጣን ወደ ጎን በመተው...
05/05/2026

በትግራይ ክልል መፈንቅለ መንግስት የሚመስል የሥልጣን ሽግግር ተካሄደ

ለሦስት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ስልጣን ወደ ጎን በመተው ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤልን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ ሰይሟል። በተጨማሪም ወ/ሮ ኪሮስ ሓጎስን በአፈ ጉባኤነት፣ ወ/ሮ ምህረት በርሄን ደግሞ በምክትል አፈ ጉባኤነት በመሾም አዲስ መዋቅር ዘርግቷል።

ይህ እርምጃ ጀነራል ታደሰ ወረደን ከስልጣን ያወረደና የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የሚጥስ ውስጣዊ መፈንቅለ መንግስት ተደርጎ የተወሰደ ሲሆን፣ ክልሉን ዳግም ወደ ጦርነት ሊመልስ እንደሚችል ስጋት ተፈጥሯል።

የፌዴራል መንግስቱም ሆነ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር በጉዳዩ ላይ እስካሁን የሰጡት ምላሽ የለም።

Address

Hawassa

Telephone

+251926498654

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Horn Insight posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Horn Insight:

Share