Horn Insight

Horn Insight Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Horn Insight, News & Media Website, Hawassa.
(2)

ኢንስፔክተር ተስፋዬ ደምሴ (ዶ/ር) በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የመንገድና ትራፊክ ክትትል ዋና ክፍል ኃላፊ ሆነው ተሾሙበቅርቡ እየሱስ ይመጣል በማለት በአደባበይ ሲሰብኩ ታይተው ...
11/08/2026

ኢንስፔክተር ተስፋዬ ደምሴ (ዶ/ር) በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የመንገድና ትራፊክ ክትትል ዋና ክፍል ኃላፊ ሆነው ተሾሙ

በቅርቡ እየሱስ ይመጣል በማለት በአደባበይ ሲሰብኩ ታይተው በማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆነው የነበሩት ዋና ኢንስፔክተር ተስፋዬ ደምሴ (ዶ/ር) በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የመንገድና ትራፊክ ክትትል ዋና ክፍል ኃላፊ ሆነው ተሾሙ

ከወራት በፊት እየሱስ ይመጣል በሚል በአደባበይ ሲሰብኩ በሚያሳዩ ምስሎችና ተንቀሳቃሽ ምስሎች አማካኝነት በማህበራዊ ሚዲያ ሰፊ ትኩረትስበው የነበሩት ዋና ኢንስፔክተር ተስፋዬ ደምሴ (ዶ/ር) አዲስ የሥራ ሀላፊነት ተሰጣቸው።

በዚሁ መሠረት ዋና ኢንስፔክተር (ዶ/ር) ተስፋዬ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የመንገድና ትራፊክ ክትትል ዋና ክፍል ኃላፊ ሆነው የተሾሙ ሲሆን፣ የከተማዋን የመንገድ ላይ የትራፊክ እንቅስቃሴና ደህንነት በበላይነት እንደሚመሩ ታውቋል።

ኃላፊው በቀጣይ በከተማዋ የሚታዩ የትራፊክ መጭናነቅ እና አደጋዎችን ለመቀነስ፣ እንዲሁም የትራፊክ ህግ ማስከበር ሥራዎችን ለማጠናከር ከተለያዩ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሠሩ ከተሰጠው ኃላፊነት ጋር ተያይዞ ተገልጿል።

11/08/2026
መምህርና አክቲቪስት ሳሙኤል በላይነህ በሐዌላ ቱላ-ያዬ መንገድ ፕሮጀክት ላይ አዲስ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ጠራመምህርና አክቲቪስት ሳሙኤል በላይነህ በሐዌላ ቱላ-ዎታራራሳ-ያዬ-ዎራንቻ መንገድ...
10/08/2026

መምህርና አክቲቪስት ሳሙኤል በላይነህ በሐዌላ ቱላ-ያዬ መንገድ ፕሮጀክት ላይ አዲስ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ጠራ

መምህርና አክቲቪስት ሳሙኤል በላይነህ በሐዌላ ቱላ-ዎታራራሳ-ያዬ-ዎራንቻ መንገድ ፕሮጀክት ላይ የሚታዩ ችግሮች በዘላቂነት እስኪፈቱ ድረስ የህዝብ ድምፅ የሚሆን አዲስ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ መበየኑን ገለፀ። አክቲቪስቱ ይፋ ባደረገው የትግል ጥሪ መሠረት፣ ማክሰኞ ማታ ከምሽቱ 3:00 እስከ 5:00 በቲክቶክ (TikTok) በሚደረግ የቀጥታ ስርጭት ውይይት የወደፊት የትግል አቅጣጫዎች ይፋ ይደረጋሉ።

በዚህ የህዝብ ድምፅ ማስተጋቢያ ዘመቻ በዋናነት የክልሉ መንግሥት በአካባቢው ህዝብ ላይ ያሳየዋል የተባለውን ግዴለሽነትና አሉታዊ አቋም መንስኤ የሚጠየቅ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ላይም ጠንካራ የተጠያቂነት አሰራር እንዲሰፍን ግፊት ይደረጋል።

በተጨማሪም ዮቴክ የተባለው የኮንስትራክሽን ተቋራጭ ከገበያ እስኪወጣ ድረስ ህዝባዊ ግፊት እንደሚደረግና ከመንገድ ፕሮጀክቱ ጋር ተያይዞ የተፈጸሙ የሀገር ሀብት ምዝበራዎችንና የሙስና ወንጀሎችን የማጋለጥ ሥራ እንደሚሰራ ተገልጿል።

መምህርና አክቲቪስት ሳሙኤል በላይነህ ህዝባችን እፎይታ ሳያገኝ ለማንም እፎይታ አንሰጥም ሲል ለህዝቡ ጥሪውን አስተላልፏል።

ኢትዮጵያ በዓለም 5ኛ፣ በአፍሪካ 2ኛ ደረጃን ያዘች!አዲስ አበባ — በኦሪገን አሜሪካ የተካሄደው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና መጠናቀቁን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አ...
10/08/2026

ኢትዮጵያ በዓለም 5ኛ፣ በአፍሪካ 2ኛ ደረጃን ያዘች!

አዲስ አበባ — በኦሪገን አሜሪካ የተካሄደው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና መጠናቀቁን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አመርቂ ውጤት አስመዝግቦ ተመልሷል።

የነገዎቹ የአትሌቲክስ ኮከቦች በተሳተፉበት በዚህ ውድድር ኢትዮጵያ 2 የወርቅ፣ 3 የብር እና 1 የነሐስ ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ አጠቃላይ 6 ሜዳሊያዎችን በክብር ሰብስባለች።

ከ100 በላይ ሀገራት በተሳተፉበት በዚህ ሻምፒዮና የዓለም 5ኛ ደረጃን በመያዝ የጽናትና የብቃት አርአያነቷን አሳይታለች።

በአፍሪካ ደረጃ የረጅም ርቀት ተፎካካሪዋን ኬንያን በመከተል 2ኛ ደረጃን አጠናቃለች።

ውድድሩን በስተመጨረሻ በ10 የወርቅ ሜዳሊያዎች በሰንጠረዡ አናት ያስጨረሰችው አስተናጋጇ አሜሪካ ስትሆን፣ ኬንያ በ4 የወርቅ ሜዳሊያዎች 2ኛ ደረጃን ይዛለች።

ይህ ስኬት ሀገራችን በአትሌቲክስ ዘርፍ ያላት የተተኪ አትሌቶች መፍለቂያነት አሁንም በጠንካራ መሠረት ላይ እንደሚገኝ ማረጋገጫ ሆኗል።

ለወጣት አትሌቶቻችን እና ለሀገራችን ህዝብ እንኳን ደስ አለን!

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በሌላ አመራር ሊተኩ እንደሚችሉ ተገለጸየኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በሌላ አመራር ሊተኩ እንደሚችሉ የተለያዩ የዜና...
10/08/2026

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በሌላ አመራር ሊተኩ እንደሚችሉ ተገለጸ

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በሌላ አመራር ሊተኩ እንደሚችሉ የተለያዩ የዜና ምንጮችን ጠቅሰው በርካታ ሚዲያዎች ዘግቧል ። ይሁን እንጂ የአቶ ሽመልስ አብዲሳ ከኃላፊነት መነሳት ለተሻለ የሥራ ዕድገትና ድልድል ይሁን ወይም በጥፋተኝነት እንደሆነ እስካሁን በግልጽ የተገለጸ ነገር አለመኖሩ ተመልክቷል።

ከዚሁ የአመራር ሽግሽግ ጋር ተያይዞ እስከ ነሐሴ ወር አጋማሽ ድረስ ከአምስት በላይ የሚሆኑ ክልሎች አዲስ የክልል መንግሥታት ምስረታ እንደሚያከናውኑ ተገልጿል። ይህ ሂደትም በየክልሎቹ አዳዲስ አመራሮችን ወደ ኃላፊነት ለማምጣትና አወቃቀሮችን ለማስተካከል ያለመ እንደሆነ ምንጮቹ ያመላክታሉ።

በተጨማሪም በመስከረም ወር አጋማሽ ላይ በብልፅግና ፓርቲ መሪነት አዲሱ ሀገራዊ መንግሥት እንደሚመሠረት ታውቋል። ይህም አጠቃላይ ሂደት በፌደራል እና በክልል ደረጃ የሚከናወኑ የመንግሥት አደረጃጀትና የአመራር ድልድል አካል እንደሆነ ተዘግቧል።

ከዚሁ ከክልሎችና ከፌዴራል መንግሥት ምስረታዎች በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በሙስና እና በሌብነት ላይ ጠንከር ያለ እርምጃ እንደሚወስዱ መግለጻቸው የብዙዎችን ትኩረት የሳበና አቢይ የመነጋገሪያ ርዕስ የሆነ ጉዳይ ሆኗል።

ኢትዮጵያ በ20 ዓመት በታች ዓለም ሻምፒዮና የመጀመሪያ ወርቅ ሜዳሊያዋን አገኘችበአሜሪካ ኦሬጎን በተካሄደው የዓለም የ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች 3 ሺህ ሜትር ውድድር አትሌ...
08/08/2026

ኢትዮጵያ በ20 ዓመት በታች ዓለም ሻምፒዮና የመጀመሪያ ወርቅ ሜዳሊያዋን አገኘች

በአሜሪካ ኦሬጎን በተካሄደው የዓለም የ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች 3 ሺህ ሜትር ውድድር አትሌት አልማዝ ዮሐንስ በ9፡15.81 ሰዓት አንደኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አስግኝታለች። በዚህው ውድድር አትሌት ወሰኔ አሰፋ በ9፡30.50 ሁለተኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ አሸናፊ ሆናለች።

እንደ በላይነህ ዲንሳሞ፣ ቱርቦ ቱሞ እና ሳሙኤል ፍሬው ያሉ ታላላቅ አትሌቶች በተገኙበት የሲዳማ አርበጎና ምድር የበቀለችው አልማዝ ዮሐንስ፣ ድሉ ከተመዘገበ በኋላ በሰጠችው አስተያየት በስሜት ተውጣ «Maganu galatamo» (አምላክ ይመስገን) በማለት በአፍ መፍቻ ቋንቋዋ በሲዳሙ አፎ ደስታዋን ገልጻለች። አክላም «ለዛሬ አማርኛ ይቅርታ ያድርግልኝ» በማለት በልብ የሚነካ ስሜት አስተያየቷን አቅርባለች።

አልማዝ ገና በጠዋቱ አቅሟን ተመልካች ለዚህ ድል እንድትበቃ ላደረጋትና ከአርበጎና ምድር በርካታ አትሌቶችን ላፈራው ለአሰልጣኝ ሳሙኤል በቀለ እንዲሁም ለሁላ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ አዱላንና ለአሰልጣኝ አሰፋ ጋዲሳ የከበረ ምስጋናዋን አቅርባለች። ወደፊት በሚኖራት የስፖርት ዘመን የኦሎምፒክ ውድድርን ማሸነፍ ዋና ህልሟ እንደሆነም ተናግራለች።

ትላንትም ዛሬም በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሲዳማ ምሁራንና ባለሙያዎችን እያገለለ ያለው የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት እንደሆነ ተረጋገጠትላንት በአንዳንድ ሚዲያዎችና የማህበራዊ ገጾች በሀዋሳ ዩ...
08/08/2026

ትላንትም ዛሬም በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሲዳማ ምሁራንና ባለሙያዎችን እያገለለ ያለው የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት እንደሆነ ተረጋገጠ

ትላንት በአንዳንድ ሚዲያዎችና የማህበራዊ ገጾች በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሲዳማ ተወላጆችንና የአካባቢው ባለሙያዎችን ከስራና ከሃላፊነት ያፈናቀሉት የቀድሞው ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይረክተር አለሙ ጣሚሶ (ዶ/ር) ናቸው ተብሎ የተሰራጨው መረጃ በሰነድ የተደገፈ እውነት የሌለው መሆኑ ተረጋግጧል። ጉዳዩን በአለሙ ጣሚሶ (ዶ/ር) ላይ ለማሳበብ የተሞከረው ትርክታዊ ሽፋን መሬት ላይ ያለውን ተቋማዊ እውነታ የሚያስቀይስ መሆኑን ይፋ የሆኑት ሰነዶችና መረጃዎች ያመላክታሉ።

ይፋ የሆኑት የሰነድ ማስረጃዎችና መረጃዎች እንደሚያረጋግጡት፣ ትላንትም ሆነ ዛሬ የሲዳማ ምሁራንና ባለሙያዎችን ያለአግባብ ከስራ የማፈናቀል፣ የማገድ፣ ከደሞዝ የመከልከልና በተቋሙ ውስጥ የነበራቸውን ድርሻ በማዳከም በራሳቸው ሰዎች የመተካት እርምጃዎችን በቀጥታ እየመሩና እያስፈጸሙ ያሉት የዩኒቨርስቲው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዶክተር ችሮታው አየለ ናቸው። በዩኒቨርስቲው ደረጃ የተወሰዱት እግዶችና አስተዳደራዊ ውሳኔዎች በሙሉ በፕሬዚዳንቱ ቀጥተኛ መመሪያና ትዕዛዝ የተፈጸሙ መሆናቸው ተያይዘው በወጡት ይፋዊ ደብዳቤዎች ተረጋገጧል።

በመሆኑም የአካባቢውን ምሁራንና ባለሙያዎች ከስራ በማግለል በራሳቸው ሰዎች የመተካቱን ስራ በበላይነት እየሰሩ ያሉት እራሳቸው ተጠባባቂ ፕሬዚዳንቱ መሆናቸው የታወቀ ሲሆን፣ ድርጊቱን በሌሎች አመራሮች ላይ ለማሳበብና የብሔር ሽፋን ለመስጠት የተሄደበት መንገድ መሰረተ ቢስና በሰነድ ውድቅ የተደረገ ነው።

የጥርስ ሀኪም በዛበህ ብርሀኑ በማህበራዊ ሚዲያ በለጠፋቸው ጥላቻ አዘል ጽሁፎች ምክንያት የተቀሰቀሰው ቁጣ ተባብሶ ቀጥሏልየጥርስ ሀኪም እና በማህበራዊ ሚዲያ በንቁ ተሳትፎው የሚታወቀው ዶክተር...
07/08/2026

የጥርስ ሀኪም በዛበህ ብርሀኑ በማህበራዊ ሚዲያ በለጠፋቸው ጥላቻ አዘል ጽሁፎች ምክንያት የተቀሰቀሰው ቁጣ ተባብሶ ቀጥሏል

የጥርስ ሀኪም እና በማህበራዊ ሚዲያ በንቁ ተሳትፎው የሚታወቀው ዶክተር በዛበህ ብርሀኑ በፌስቡክ ገፁ ላይ የለጠፋቸው ተከታታይ ጽሁፎች በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ እና ህዝባዊ ቁጣ በማስከተል ላይ ይገኛሉ። ግለሰቡ በመጀመሪያ "ይሁዳ ሲዳማ ነው::" የሚል አጭር መልእክት ያሰፈረ ሲሆን፣ ይህ አባባሉ የመላውን የሲዳማ ህዝብ ክብር የሚያዋርድ እና የሚያንኳስስ ነው በማለት በርካታ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች፣ የህዝብ ተወካዮች እና የብሔሩ ተወላጆች ዘንድ ሰፊ ተቃውሞ ቀስቅሷል።

ከተሰጡት በርካታ ምላሾች መካከል ድርጊቱ እጅግ አሳዛኝ እና የሚያሳፍር መሆኑን በመግለጽ፣ ግለሰቡ ቀደም ሲልም ተመሳሳይ ድርጊቶችን ሲፈጽም እንደነበር በመጥቀስ በሰራው ህዝብን የሚያቋሽሽ ስራ በአስቸቋይ በህግ ሊጠየቅ እንደሚገባ ያሳሰቡ አሉ። በተመሳሳይ መልኩ ድርጊቱ ከፍተኛ ንቀት መሆኑን ገልጸው ቁጣቸውን ያስፈረሙ ሲሆን፣ ሌሎች በበኩላቸው የተማረ እና የሰለጠነ ሰው መላውን የሲዳማ ህዝብ ከአንድ አሳልፎ ከሰጠ አካል (ይሁዳ) ጋር አሳስቦ መናገሩ ተገቢ አለመሆኑን ገልጸው ጉዳዩ በጥብቅ ሊመረመር እንደሚገባ ጠቁመዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ጉዳዩን በአመዛዛኝ እይታ ለመመልከት የሞከሩ አስተያየት ሰጪዎች፣ የአንድን ግለሰብ ስህተት መነሻ በማድረግ መላውን ህዝብ በጥቂት ነገሮች መመደብ ስህተት መሆኑን በማስረገጥ ምላሽ ሰጥተዋል።

ነገሩ ሳይበርድ እና ህዝባዊ ቁጣው በረበበበት ሁኔታ፣ ዶክተር በዛበህ በጉዳዩ ዙሪያ "‘ይሁዳ ሲዳማ ነው’ ማለት ‘ሲዳማ ይሁዳ ነው’ ማለት አይደለም! እየለያችሁ ይሁዳዎች። ከኋላ መጥተው ለመውጋት ብቻ የተፈጠሩ ብዙ ይሁዳዎች አሉ፡፡ እንተዋወቃለን።" በማለት ተጨማሪ መልእክት ማጋራቱ ሁኔታውን ይበልጥ አባብሶት ቆይቷል።

በስተመጨረሻም ዶክተር በዛበህ ጉዳዩን ለማብራራት እና ይቅርታ ለመጠየቅ ባሰራጨው ጽሁፍ፣ አገላለጹ የአንዳንድ ግለሰቦችን ተግባር ለመግለጽ እንጂ ማንኛውንም ህዝብ ወይም ማህበረሰብ ለመወከል እንዳልነበረ ገልጾ፣ በመልእክቱ ምክንያት ላዘኑና ቅር ለተሰኙ ሁሉ ከልብ ይቅርታ ጠይቋል።
ሆኖም ይቅርታው የቀሰቀሰውን ቁጣ ሊያበርደው አልቻለም፤ ይልቁኑ ጉዳዩ ግለቱን ጨምሮ ግለሰቡ በህግ ቁጥጥር ስር ውሎ መጠየቅ አለበት የሚሉ ድምጾች ይበልጥ ተበራክተዋል።

ዶክተሩ ከወራት ወዲህ ጥላቻ አዘል ጽሁፎችን ማሰራጨት የጀመረው፣ የክልሉን ህዝብ ወክለው ከባህል ተወካዮች ጋር በጀርመን ፍራንክፉርት በሚከበረው የፍቼ ጫምባላላ በዓል ላይ ለመገኘት የተያዘውን ፕሮግራም በተመለከተ በተፈጠረ ክስተት እንደሆነ ሆርን ኢንሳይት ባደረገው ምርመራ ደርሶበታል። አንድ የህዝብ ባህልና መብት ተቆርቋሪ ቡድን "ግለሰቡና ቡድኑ የሲዳማን ህዝብ የሚወክሉ አይደሉም" በማለት በጀርመን ኤምባሲ ቅሬታ በማስገባቱ ጉዞው እንዲሰረዝ መደረጉን ተከትሎ ግለሰቡ ወደዚህ ድርጊት መግባቱን የምርመራ ዘገባው ያመላክታል።

ዶ/ር ደረጀ እንግዳ የጅማ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙትምህርት ሚኒስቴር አዲስ አመራር እንዲመደብላቸው ይፋ ካደረጋቸው 9 ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቀጥሎ ሁለተኛ...
07/08/2026

ዶ/ር ደረጀ እንግዳ የጅማ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ አመራር እንዲመደብላቸው ይፋ ካደረጋቸው 9 ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቀጥሎ ሁለተኛው የሆነው የጅማ ዩኒቨርሲቲ የአመራር ርክክብ ሥነ-ሥርዓት አካሄደ።

ላለፉት ሰባት ዓመታት ዩኒቨርሲቲውን በፕሬዝዳንትነት ሲመሩ የቆዩት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ፣ ኃላፊነታቸውን ቀደም ሲል የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ለነበሩት ለዶ/ር ደረጀ እንግዳ አስረክበዋል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ዶ/ር ጀማል ለተቋሙ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና የቀረበላቸው ሲሆን፣ አዲሱ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደረጀ እንግዳ ደግሞ ዩኒቨርሲቲው የጀመረውን የራስ-ገዝነት ሽግግር ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግሩታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል።

ሚኒስቴሩ በደብዳቤው ባሳወቀው መርሃ-ግብር መሰረት ከጎንደር እና ጅማ ዩኒቨርሲቲዎች በመቀጠል በበርካታ የአሰራርና የመልካም አስተዳደር ብልሽቶች ውስጥ ይገኛል የሚባለው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚከተል ይሆናል።

ሰበር ዜና!በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በዶ/ር ክብሩ ክፍሌ ላይ የሚደረገው መግፋት ወደ ማባረር እርምጃ እና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ማደጉ ተገለጸበሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የማ...
06/08/2026

ሰበር ዜና!

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በዶ/ር ክብሩ ክፍሌ ላይ የሚደረገው መግፋት ወደ ማባረር እርምጃ እና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ማደጉ ተገለጸ

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት በሆኑት ዶ/ር ክብሩ ክፍሌ ላይ የተወሰደው ከሥራና ከደመወዝ የመታገድ ውሳኔ፣ ሕግና ተቋማዊ አሰራርን የጣሰ መሆኑን የተለያዩ ምንጮችን ጠቅሰን ከዚህ ቀደም መዘገባችን ይታወሳል።

አሁን ደግሞ በጉዳዩ ላይ የማህበራዊ ሚዲያና የህዝብ ተቃውሞ በመበርታቱ፣ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ስልት ቀይሮ ዶክተሩን በይፋ ለማባረር በክልሉ ሚዲያ (SBC) በኩል የቅድመ ፕሮፓጋንዳ ዘመቻ መጀመሩን ለሚዲያችን የደረሰው ጥቆማ አመልክቷል።

ለእርምጃቸው ድጋፍ ለማሰባሰብ ያደረጉት ሙከራ የከሸፈባቸው የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ አሁን በSBC መግለጫ እንዲሰጡ የዩኒቨርሲቲውን ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ጅሎን መመደባቸው ታውቋል።

ዶ/ር ክብሩ በሆስፒታሉ ውስጥ በሙያቸው የተመሰከረላቸው ስፔሻሊስት ሲሆኑ፣ በ2016 ዓ.ም የተመሰረተባቸው የባንክ ሂሳብ ክስ በፍርድ ቤት በዋስትና የሚያስፈታ ሆኖ ሳለ፣ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ግን ከሕግ ውጭ ከስድስት ወራት በላይ ከሥራና ደመወዝ አግዷቸዋል።

ይህ እርምጃ የመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1064/2010ን የሚጥስ እና ከበስተጀርባው የዘመዳዊነትና የጥቅም ትስስር ሴራ ያለበት በመሆኑ፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጉዳዩን አጣርተው ሕጋዊ መፍትሔ እንዲሰጡ ጥሪ ቀርቧል።

በተጨማሪም የሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (SBC) ለአንድ ወገን የሀሰት ፕሮፓጋንዳ መጠቀሚያ ከመሆን እንዲቆጠብ ጥሪ ተላልፏል ።

Address

Hawassa

Telephone

+251926498654

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Horn Insight posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Horn Insight:

Shortcuts

Share