Horn Insight

Horn Insight Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Horn Insight, News & Media Website, Hawassa.
(3)

የጤና መኮንኑ ወጣት ምሳሌ ቡዙነህ ሕይወቱን በገዛ እጁ ማጥፋቱ ተሰማበሲዳማ ክልል በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን በሎካ አባያ ወረዳ እና በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት የነበረው ወ...
10/06/2026

የጤና መኮንኑ ወጣት ምሳሌ ቡዙነህ ሕይወቱን በገዛ እጁ ማጥፋቱ ተሰማ

በሲዳማ ክልል በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን በሎካ አባያ ወረዳ እና በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት የነበረው ወጣቱ የጤና ባለሙያ (HO) ምሳሌ ቡዙነህ፣ በትውልድ ቀዬው ሕይወቱ አልፎ መገኘቱ ተሰማ።

ከወረዳው ኩታዮ ቀበሌ ፈልቆ፣ በኦሳ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም በሀንጤጠ ከተማ በሚገኘው የሎካ አባያ መሰናዶ ትምህርት ቤት በነበረው የላቀ የትምህርት አፈጻጸምና ብሩህ አእምሮው የአካባቢው ኩራት መሆን የቻለው ይህ ወጣት፤ ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ በጤና መኮንንነት (Public Health Officer) በማዕረግ ከተመረቀ ሦስት ዓመታት የሆኑት ቢሆንም፣ ለሶስት አመታት የሥራ ዕድል ሳያገኝ ቆይቶ ነበር።

በቅርቡ በሞጆ ከተማ የመንግሥት ጤና ተቋም ውስጥ በውድድር ተቀጥሮ ሥራ የጀመረ ቢሆንም፣ የሥራ ዘመኑ ሁለት ወር ብቻ እንደሞላው ባልታወቀ ምክንያት ሥራውን አቁሞ ወደ ትውልድ ስፍራው ተመልሶ ነበር። ይሁን እንጂ በትናንትናው ዕለት አመሻሽ ላይ በራሱ ላይ በወሰደው አሳዛኝ እርምጃ ሕይወቱ አልፎ ተገኝቷል። ወጣቱን ባለሙያ ለዚህ ከባድ ውሳኔ ያነሳሳውና ለሞቱ መንስኤ የሆነው ምስጢር ምን እንደሆነ እስከ አሁን ድረስ የተጣራ ነገር የለም።

ለወላጆቹ ብቸኛ ወንድ ልጅ የሆነውና በቅንነቱ፣ በትሕትናውና በታታሪነቱ የሚታወቀው ወጣት ምሳሌ ቡዙነህ በዚህ መልኩ በድንገት መለየቱ መላውን የሎካ አባያ ወረዳ፣ የኦሳ እና የኩታዮ ማኅበረሰብ በከባድ ድንጋጤና ጥልቅ ሐዘን ውስጥ ጥሏል።

የወጣት ምሳሌ ቡዙነህ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በነገው ዕለት በተወለደበት በኩታዮ ቀበሌ ልዩ ስሙ ባዲቻ በሚባለው ቦታ ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ይፈጸማል።

ለተከበሩ ወላጆቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለጠቅላላው የሎካ አባያ ወረዳ፣ የኦሳ እና የኩታዮ ማኅበረሰብ ጥልቅ መጽናናትን እንመኛለን።

ነፍሱን በአጸደ ገነት ያኑራት! 🕯️

በሕገ-ወጥ መንገድ የፒ.ኤች.ዲ ትምህርታቸውን በሚከታተሉ አመራሮች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጥቆማ ቀረበበሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ያለምንም ይፋዊ ፈቃድና ከኃላፊነት ሳይነሱ በመደበኛ ፕሮ...
09/06/2026

በሕገ-ወጥ መንገድ የፒ.ኤች.ዲ ትምህርታቸውን በሚከታተሉ አመራሮች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጥቆማ ቀረበ

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ያለምንም ይፋዊ ፈቃድና ከኃላፊነት ሳይነሱ በመደበኛ ፕሮግራም የፒ.ኤች.ዲ (PhD) ትምህርታቸውን በሕገ-ወጥ መንገድ በሚከታተሉ የቢሮ ኃላፊዎችና አመራሮች ላይ አስቸኳይ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድ የሚጠይቅ ይፋዊ ጥቆማ ለአስተዳደር፣ ለፓርቲና ለቁጥጥር አካላት ቀረበ።

በቀረበው ጥቆማ መሠረት፤ ቀደም ሲል በነበሩበት የሥራ ኃላፊነት ላይ የነበሩት ዶክተር አክሊሉ ጡቄላ፣ እጩ ዶክተር ስኳሬ ሹዳ፣ እጩ ዶክተር ቃሬ ጫዊቻ፣ እጩ ዶክተር ፍቃዱ ጳውሎስ፣ እጩ ዶክተር አሸናፊ ደበበ፣ እጩ ዶክተር ማናሞ አናቶ፣ እጩ ዶክተር ዮካሞ ዮዬ እና እጩ ዶክተር ሊዲያ ታደሰ ሕጋዊውን መሥፈርት በመከተል ከኃላፊነታቸው በይፋ ተነስተው ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ። ይህ አሠራር የክልሉን ደንብ ቁጥር 3/2012 እና አዲስ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 45/2017 ዓ.ም የተከተለ ፍጹም ሕጋዊ መንገድ መሆኑ ተገልጿል።

ሆኖም ግን፣ በአሁኑ ወቅት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የተማሩ ወጣቶች የሥራ ዕድል አጥተው ቤት በተቀመጡበት አሳሳቢ ወቅት፣ የተወሰኑ የቢሮ ኃላፊዎችና አመራሮች የሕዝብን መደበኛ የሥራ ሰዓት ለግል ትምህርታቸው እያዋሉ የመንግሥትን ደሞዝና ጥቅማጥቅም ሙሉ በሙሉ መውሰዳቸው ከፍተኛ አድሎአዊነት ከመሆኑም በላይ በመንግሥትና በሕዝብ ሀብት ላይ የሚፈጸም ከባድ የብክነትና የሙስና ወንጀል ነው። ይህ ድርጊት ከኃላፊነት ሳይነሱና ሳይፈቀድላቸው በድብቅ የሚማሩ አካላትን ጥቅማጥቅም የማይፈቅደውን የሕግ መንፈስ በቀጥታ የሚጥስ የብልሹ አሠራር መሆኑ በጥቆማው ተመልክቷል።

በመሆኑም እነዚህ አካላት በአስቸኳይ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ፣ በሕገ-ወጥ የትምህርት ቆይታቸው የወሰዱት የመንግሥት ደሞዝና ጥቅማጥቅም ተሰልቶ ወደ መንግሥት ገቢ እንዲደረግ እና የቁጥጥር አካላት መደበኛ ፍተሻ እንዲያደርጉ ተጠይቋል። የሚመለከታቸው ተቋማት ማጣሪያ ማድረግ ከፈለጉ የእነዚህን አካላት ዝርዝር ማንነትና ሙሉ መረጃ በይፋ ለመስጠት ዝግጁነት መኖሩ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህንን የብልሹ አሠራር ጥቆማ ማቅረብ ተገቢውን የዜግነት ግዴታ መወጣት መሆኑም ተመልክቷል።

በትግራይ ክልል አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ፣ ምልመላን የሚቃወሙ ንግግሮችና መገናኛ ብዙኃን ላይ ቅጣቶችን የሚጥሉ ድንጋጌዎችን የያዘ ረቂቅ ሕግ ተዘጋጀ የክተት (ምልመላ) እና የጦርነት ጊዜ አ...
09/06/2026

በትግራይ ክልል አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ፣ ምልመላን የሚቃወሙ ንግግሮችና መገናኛ ብዙኃን ላይ ቅጣቶችን የሚጥሉ ድንጋጌዎችን የያዘ ረቂቅ ሕግ ተዘጋጀ

የክተት (ምልመላ) እና የጦርነት ጊዜ አስተዳደርን ሕጋዊ ማዕቀፍ ለማስያዝ የቀረበው ይህ ረቂቅ ሕግ፥ በምልመላ ወቅት በሲቪሉ፣ በነጻ ተቋማት እና በመገናኛ ብዙኃን እንቅስቃሴዎች ላይ ለባለሥልጣናት ሰፊ ሥልጣን የሚሰጡ ተከታታይ ድንጋጌዎችን አካቷል።

የረቂቁ ዋነኛ ማዕከል ለክተት የተጠሩ ዜጎች የምልመላ ትዕዛዞችን ማክበር እንዳለባቸው የሚደነግገው ግዴታ ነው። ረቂቅ ሕጉ ከወታደራዊ አገልግሎት የሚያመልጡ፣ ሲጠሩ ሪፖርት የማያደርጉ፣ ሌሎች ከምልመላ እንዲያመልጡ የሚረዱ ወይም በሌላ መልኩ የምልመላ ጥረቶችን የሚያስተጓጉሉ ግለሰቦች ላይ የሚጣሉ ቅጣቶችን ዘርዝሯል።

የ2019 ረቂቅ በጀት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ሆኖ ቀረበ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። ምክር ቤቱ...
09/06/2026

የ2019 ረቂቅ በጀት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ሆኖ ቀረበ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ምክር ቤቱ የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት የበጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቷል።

የ2019 የፌዴራል መንግሥት በጀት የዐሥር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነው የ2019-2021 የልማት እና ኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችን እና የመካከለኛ ዘመን (2019-2023) የማክሮ ኢኮኖሚ እና የፊሲካል ማዕቀፍን መሠረት በማድረግ፣ የ2018 በጀት ዓመት የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም መነሻ በማድረግ፣ በቀጣይ ሊኖር የሚችለውን የማኅበራዊ እና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን አቅጣጫዎች እና ዓላማዎች እንዲሁም በመንግሥት የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የመንግሥትን የፋይናንስ አቅም እና አስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች ከተሰጣቸው ተልዕኮ እና ኃላፊነት አንጻር የሚያስፈልገውን ወጪ በመገምገም ተዘጋጅቶ ቀርቧል።

በዚሁ መሠረትም ለመደበኛ ወጪዎች፣ ለካፒታል ወጪዎች፣ ለክልል መንግሥታት ድጋፍ፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ የሚውል 2 ትሪሊዮን 339 ቢሊዮን 268 ሚሊዮን 126 ሺህ 738 (ሁለት ትሪሊዮን፣ ሦስት መቶ ሠላሳ ዘጠኝ ቢሊዮን፣ ሁለት መቶ ስድሳ ስምንት ሚሊዮን፣ አንድ መቶ ሀያ ስድስት ሺህ፣ ሰባት መቶ ሰላሳ ስምንት) ብር በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቧል።

ምክር ቤቱም በቀረበው የፌዴራል መንግሥት የ2019 ረቂቅ በጀት አዋጅ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምፅ መወሰኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል።

በፊሊፒንስ በሬክተር ስኬል 7.8 በተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ቢያስን የ32 ሰዎች ህይወት አለፈ በፊሊፒንስ በደረሰ ሀይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ህንጻዎችን በማውደም እና በመላው እስያ የሱ...
08/06/2026

በፊሊፒንስ በሬክተር ስኬል 7.8 በተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ቢያስን የ32 ሰዎች ህይወት አለፈ

በፊሊፒንስ በደረሰ ሀይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ህንጻዎችን በማውደም እና በመላው እስያ የሱናሚ ማስጠንቀቂያ እንዲሰጥ አስገድዷል። የዩናይትድ ስቴትስ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ እንደገለጸው በሬክተር ስኬል 7.8 የተለካው የመሬት መንቀጥቀጡ በደቡባዊ ሚንዳናኦ ደሴት ላይ ሰኞ በሃገር ውስጥ ሰዓት አቆጣጠር 1፡40 ላይ ደርሷል ብሏል።

በመሬት መንቀጥቀጡ አደጋ ቢያንስ የ32 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ሌሎች ቢያንስ 129 ሰዎች መቁሰላቸውን ፖሊስ አረጋግጧል። የመሬት መንቀጥቀጡ በ37 ህንፃዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።የሱናሚ ማስጠንቀቂያ ከተሰጠባቸዉ ሀገራት መካከል ፊሊፒንስ፣ ኢንዶኔዥያ እና ጃፓን ተጠቃሽ ናቸዉ፡፡

የፊሊፒንስ የእሳተ ገሞራ እና የመሬት መንቀጥቀጥ ተቋም እንደገለጸው ከመጀመርያው የመሬት መንቀጥቀጥ ከአንድ ሰዓት በኃላ ከባዱ አደጋ ተመዝግቧል። በሳንቶስ ሲቲ ባለ ሶስት ፎቅ ህንጻ ወደ ፍርስራሽነት ተቀይሯል። ሌሎች ምስሎች የተሰባበሩ መስኮቶችን እና ጣሪያዎችን ጨምሮ በህንፃዎች ላይ ከፍተኛ ውድመት ያሳያሉ።

የፊሊፒንስ የመሬት መንቀጥቀጥ ባለስልጣን እንዳስታወቀው በደቡባዊው የሶክስክሳርገን ክልል ውስጥ የምትገኘው ከተማዋ "በጣም ጠንካራ" የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ አጋጥሟታል ብሏል። የመሬት መንቀጥቀጡ 10 ኪሎ ሜትር ጥልቀት እንደነበረው የፊሊፒንስ የእሳተ ገሞራ እና የመሬት መንቀጥቀጥ ተቋም ገልጿል።

ሰበር ዜና!በኢትዮጵያ የጫት ተጠቃሚነት መጨመር ለአእምሮ ጤና ከፍተኛ ስጋት መደቀኑ ተነገረ!በኢትዮጵያ በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ የመጣው የጫት ሱስ ስርጭት፣ በአገሪቱ የአእምሮ ጤና ላይ ከባ...
08/06/2026

ሰበር ዜና!

በኢትዮጵያ የጫት ተጠቃሚነት መጨመር ለአእምሮ ጤና ከፍተኛ ስጋት መደቀኑ ተነገረ!

በኢትዮጵያ በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ የመጣው የጫት ሱስ ስርጭት፣ በአገሪቱ የአእምሮ ጤና ላይ ከባድ አደጋ እየደቀነ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች አስጠነቀቁ።

የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የአእምሮ ህክምና ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር እስጢፋኖስ እንዳላማው እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት የጫት ተጠቃሚዎች ቁጥር በከፍተኛ መጠን ማደጉ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።

የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በቅርቡ ባወጣው መረጃ መሰረት፤ በሀገሪቱ የወጡ አዳዲስ የቁጥጥር ህጎችን ተከትሎ የአልኮል እና የሲጋራ ተጠቃሚነት መጠነኛ ቅናሽ አሳይቷል። ይሁን እንጂ ይህ የቁጥጥር ስራ በጫት ላይ ባለመዘርጋቱ የችግሩን ስፋት አባብሶታል።

ማንኛውም የሱስ ችግር በቀጥታ ከአንጎል ባዮሎጂካዊ አወቃቀር ጋር የተያያዘ በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ ባለሙያዎቹ ያሳስባሉ።

በተጨማሪም የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በጫት ቁጥጥር ላይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል።

የአእምሮ ህክምናን ከሌሎች የህክምና ዘርፎች ጋር አቀናጅቶ እየሰጠ የሚገኘው የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል፣ አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ 145 የመኝታ አልጋዎችን አዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል።

ዶ/ር እስጢፋኖስ እንደገለጹት፤ ሆስፒታሉ ከአማኑኤል ሆስፒታል ቀጥሎ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመኝታ አልጋ የያዘ ተቋም ነው።

በአሁኑ ወቅትም አገልግሎቱ ለህጻናት፣ ለአዋቂዎች፣ ለአረጋውያን እና በተለይም ከሱስ ጋር የተያያዙ ችግሮች ላለባቸው ዜጎች በተለያዩ ክፍሎች ተለይቶ በዘመናዊ መልኩ እየቀረበ ይገኛል።

ሪፖርተር፦ሊዲያ ደሳለኝ
ሰኔ 01 ቀን 2018 ዓ.ም
Via የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል

ምንጭ ጉርሻ Page

የአቶ ታሪኩ ለማ ነው ተብለው የተለቀቀው የድምፅ ቅጅ በማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆኖ ቀጥሏልየቀድሞ የኤጄቶ አባል፣ ያሁኑ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት አባል እና የሲዳማ ልማት ኮርፖሬሽን ዳይሬ...
07/06/2026

የአቶ ታሪኩ ለማ ነው ተብለው የተለቀቀው የድምፅ ቅጅ በማህበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆኖ ቀጥሏል

የቀድሞ የኤጄቶ አባል፣ ያሁኑ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት አባል እና የሲዳማ ልማት ኮርፖሬሽን ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለማ ተናገሩት የተባለ የድምፅ ቅጅ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት እየተሰራጨ መነጋገሪያነቱ ቀጥሏል።

ዛሬ የተለቀቀውና 48 ሰኮንዶች ርዝማኔ ያለው ይህ የድምፅ ቅጅ፣ አስነዋሪ ስድብና ዛቻ የተቀላቀለበት መሆኑ ተመልክቷል። ድምጹ የተሰነዘረው በማን ላይ እንደሆነ በግልጽ የተቀመጠ ነገር ባይኖርም፣ በማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ በስፋት እየተዘዋወረ ይገኛል። ይህንኑ የድምፅ ቅጅ አስመልክቶ ከተለያዩ ወገኖች የተለያየ አስተያየትና ሙግት እየቀረበ ነው። አንዳንዶች ጉዳዩን የሰው ሰራሽ አስተዋፅኦ (AI) ቅንብር ነው ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ ከስድስት ዓመታት በፊት የተቀረጸ የቆየ ድምፅ ነው በሚል ይከራከራሉ። በሌላ በኩል ደግሞ በንግግሩ ይዘት ላይ የተቃውሞና የትችት አስተያየታቸውን የሚሰነዝሩ አካላት አልጠፉም።

ጉዳዩን ካወገዙት መካከል የሲዳሙ አፎ አርቲስት ሹሙሎ ሹንደ /ናጩጫ አንዱ ሲሆን፣ በሰጠው አስተያየትም፦ በተራ ቃላት የተሞላውን አጸያፍ ስድብ እባካችሁን አትልቀቁብን በቃ። ከቤተሰብ፣ ከህጻናትና ከተከበሩ ሰዎች ጋር እያለን ድንገት ሶሻል ሚዲያ ስንከፍት እየተሸማቀቅን ነው ያለነው፤ አባካችሁን ቪዲዮውን ከፕሮፋይላችሁ ላይ አስወግዱት በማለት ጥሪ አቅርቧል።

አቶ ታሪኩ ለማ ከለውጥ ኃይሉ ኤጄቶ ወደ ክልል አመራርነት ከተቀላቀሉ ጥቂት ወጣቶች መካከል አንዱ ናቸው። ከእሳቸው ጋር ወደ ስልጣን የመጡ በርካታ የትግል አጋሮቻቸው በሴራ ፖለቲካ ከስልጣን ተጠራርገው ሲወጡ፣ በአመራርነት ጸንተው ከቀሩት አንድ ሁለት ወጣቶች መካከል እሳቸው ተጠቃሽ ናቸው። በተጨማሪም ሰሞኑን በማንና በምን ምክንያት እንደሆነ ባልታወቀ ሁኔታ በዚህ ወጣት አመራር ላይ መጠነ-ሰፊ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ተከፍቶባቸው ይገኛል።

የሲዳማ ፖሊስ መምሪያ አለአግባብ ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ነው ላላቸው አካላት ማስጠንቀቂያ ሰጠበመግለጫው ላይ የተቃውሞና የድጋፍ ምላሾች እየተሰጡ ነውየሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ እ...
07/06/2026

የሲዳማ ፖሊስ መምሪያ አለአግባብ ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ነው ላላቸው አካላት ማስጠንቀቂያ ሰጠ

በመግለጫው ላይ የተቃውሞና የድጋፍ ምላሾች እየተሰጡ ነው

የሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ እና የክልሉ የጸጥታ የጋራ ግብረ ኃይል ትላንት ማምሻው በጋራ ባወጡት መግለጫ፣ በማህበራዊ ሚዲያ የጥላቻ ንግግር፣ ግጭት ቀስቃሽ መልዕክቶችና ሐሰተኛ መረጃዎችን የሚያሰራጩ ግለሰቦችና ቡድኖች ላይ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል። መምሪያው በክልሉ ውስጥ ያለውን ሰላምና ደህንነት ለማወክ በማህበራዊ ሚዲያ አማካይነት ግጭት ቀስቃሽ ይዘቶች እንዲሁም ሐሰተኛ መረጃዎች እየተሰራጩ መሆናቸውን ገልጿል። በተለይም በመንግሥት ተቋማትና ኃላፊዎች ላይ ያተኮሩ መልዕክቶች በጽሑፍ፣ በምስል፣ በድምጽ እና በቪዲዮ መልክ ሲሰራጩ እንደሚስተዋሉ ጠቁሞ፤ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ድርጊት ተጠርጥረው ምክርና ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው የተለቀቁ አንዳንድ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዳልታረሙና በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች መኖራቸውን ገልጿል።

መግለጫው ማንኛውንም ግለሰብ በስም ባይጠቅስም፣ ድርጊቱ ከቀጠለ የክልሉ ፖሊስና የጸጥታ ግብረ ኃይል
እርምጃ እንደሚወስዱ አስጠንቅቋል።

ይህንን መግለጫ ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያና በተለያዩ የውይይት መድረኮች ላይ ጠንካራ ትችቶችና ተቃውሞዎች እየተሰነዘሩ ይገኛሉ። በርካታ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት፤ የክልሉ መንግስት የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃን ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ከአላማው ውጭ ዜጎችን ለማፈንና ለማሸማቀቅ እየተጠቀመበት ቆይቷል ። ይህ ዓይነቱ አቀራረብ በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ከማቆም ይልቅ፣ መንግስት እየወሰደ በቆየው ያልተገባ የእስር እርምጃ ምክንያት በእስር የጀገኑ በማህበራዊ ሚዲያ ጀግና ተብለው የሚታሰቡ አካላት እንደአሸን እንዲፈሉ ማድረጉን ይገልጻሉ። በዚህም የተነሳ በክልሉ ያለው የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ከሌሎች ክልሎች በተለየ መልኩ ከስርዓት ያፈነገጠ እንዲሆን መንግስት ራሱ በር ከፍቷል ሲሉ ይተቻሉ።

በተጨማሪም ከአፈናውና ከእስራቱ ለማምለጥ ሲሉ በርካታ ሰዎች በተለይ ወጣቶች ሀሳባቸውን ለመግለጽ ትክክለኛ ማህበራዊ ሚዲያ ስማቸውን ከመጠቀም እየተቆጠቡ መምጣቻው ተገልጿል። በዚህም ምክንያት ዜጎች በሀሰተኛ (Fake) አካውንት ስም ሀሳባቸውን ለመግለጽ እየተገደዱ በመሆኑ፣ ዛሬ በክልሉ የሀሰተኛ ፌስቡክ ስሞችና እንቅስቃሴዎች ከእውነተኛ ተጠቃሚዎች በላይ ቁጥራቸው እንዲበልጥና ድምጻቸው ከፍ ብሎ የመደመጥ እድል እንዳገኘ አስተያየት ሰጪዎቹ ያመለክታሉ።

ሌሎች የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በበኩላቸው፣ የህግ የበላይነት ሲባል ዜጎችን ዝም ማሰኘት ሳይሆን መብታቸው ተከብሮ፣ ግዴታቸው ተወጥቶ ሁሉም በህግ ፊት እኩል የሚዳኝበት ሥርዓት መሆኑን በማሳሰብ፤ መንግሥት የሚቀርብበትን ትችት በጸጥታ እርምጃዎች ለማፈን እየተንቀሳቀሰ ነው የሚል ስጋታቸውን አንስተዋል።

ከሚሰነዘሩት ጠንካራ ትችቶች በተቃራኒው፣ መንግስት ያወጣው መግለጫ ወቅቱን የጠበቀና አስፈላጊ ነው የሚሉ ወገኖችም በአመዛኙ ተስተውለዋል። እነዚህ ወገኖች የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት በክልሉ ሰላምና ደህንነት እንዲሁም በህዝቦች አብሮነት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ ስለሚችል፣ የህግ ማስከበር እርምጃዎች መወሰዳቸው ተገቢና ሊበረታታ የሚገባው ነው የሚል አቋም እያራመዱ ይገኛሉ።

በመጨረሻም የጋራ ግብረ ኃይሉ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ሐሳባቸውን ሲገልጹ ወይም መረጃ ሲለዋወጡ የህግን አግባብና የሌሎችን መብት እንዲያከብሩ በድጋሚ አሳስቧል።

እንደ ሆርን ኢንሳይት፤ መንግስት ማህበራዊ ሚዲያን ላላስፈላጊና ላልተገባ አላማ የሚጠቀሙ አካላትን ማስጠንቀቅና መምከር ተገቢና የተቋሙ መደበኛ ተልዕኮ እንደሆነ ያምናል። ሆኖም ግን በየጊዜው እየተባባሰ የመጣውንና ከስርዓት ያፈነገጠውን ድርጊት በዘላቂነት ለማቆም፤ ከጠንካራ የህግና የጸጥታ እርምጃዎች ባሻገር በህዝባዊ መድረኮች፣ በሰፊ ውይይቶች፣ በአሰራር ለውጦች፣ በመደበኛ ሚዲያ ሙግቶች፣ በትምህርቶች እንዲሁም በተከታታይ ስልጠናዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ በተደራጀ መልኩ ቢሰራ ይበልጥ ውጤታማ ይሆናል የሚል እምነት አለው ።

“ላለማነውም ሆነ ላጠፋነው ነገር ፊት ለፊት በመረጃና ማስረጃ ለመሞገት ዝግጁ ነኝ! “ አቶ ታሪኩ ለማበሲዳማ ክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ በቀድሞ የትግል አጋሮችና በንቅናቄው ውስጥ በነበሩ ታጋዮ...
05/06/2026

“ላለማነውም ሆነ ላጠፋነው ነገር ፊት ለፊት በመረጃና ማስረጃ ለመሞገት ዝግጁ ነኝ! “ አቶ ታሪኩ ለማ

በሲዳማ ክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ በቀድሞ የትግል አጋሮችና በንቅናቄው ውስጥ በነበሩ ታጋዮች መካከል በማህበራዊ ሚዲያ ሲሰነዘር የነበረው የእርስ በርስ ውንጀላ እና የድጋፍ ዘመቻ ወደ ፊት ለፊት የሕዝብ ሙግት ጥሪ ተሸጋግሯል። ይህ ውዝግብ ወደ አዲስ ምዕራፍ የተሸጋገረው በክልሉ የፊት አመራሮችና የሲዳማ ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለማ ላይ ያነጣጠረ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ እየተበራከተ በመምጣቱ ነው።

ለተነሳው ውዝግብ መነሻ የሆነው የቀድሞ የትግል አጋራቸው አቶ ሳሙኤል በላይነህ እና ጋዜጠኛ እዮብ ሽመልስ በአቶ ታሪኩ ላይ ያነጣጠረ የሰላ ወቀሳ በማህበራዊ ሚዲያ ማቅረባቸው ነው። ተቺዎቹ አቶ ታሪኩ በክልል ምስረታ ትግሉ (በኤጄቶ እንቅስቃሴ) የነበራቸውን ታሪክ ቢቀበሉም፣ ከክልል ምስረታ በኋላ ግን የስልጣን ኮታን በመጠቀም አመራሩንና ሕዝቡን መከፋፈል፣ የሲሚንቶና ነዳጅ ንግድን መቆጣጠር፣ የህዝብ ሀብት መዝረፍ፣ ተቋሙን ያለ አንዳች የሚታይ ስራ ለ6 ዓመታት መምራት፣ እንዲሁም ንጹሃንን በውሸት ክስ ማሳሰር የሚሉ ከባድ ወንጀሎችን ሰንዝረውባቸዋል።

በሌላ በኩል በአገር ውስጥና በውጭ አገር የሚገኙ በርካታ ደጋፊዎቻቸው "ትላንትን አንረሳም" በሚል መሪ ቃል ሰፊ የድጋፍ ዘመቻ ከፍተዋል። ደጋፊዎቹ አቶ ታሪኩ ለሲዳማ ነፃነትና ሕዝባዊ ትግል ያበረከቱት የወጣትነት ገድል ሊካድ የማይችል ሀቅ መሆኑን በመጥቀስ፣ በአሁኑ ወቅትም በኃላፊነት ቦታቸው ላይ ሆነው ሕዝባቸውን እያገለገሉ በመሆኑ ክብር እንጂ ስድብ አይገባቸውም ብለዋል። በእሳቸው ላይ የሚካሄደውን የተደራጀ የስም ማጥፋትና የጥላቻ ዘመቻም አጥብቀው እንደሚቃወሙ ገልጸዋል።

አቶ ታሪኩ ለማ ዛሬ ጠዋት በሰጡት ምላሽ፣ የሰላ ትችቶቹ የግልና የቤተሰብ ህይወታቸውን እስከማወክ የደረሰ የፕሮፓጋንዳ ጫና ቢያሳድሩባቸውም፣ አሁን ላይ የሚሰራጨው መረጃ አልባ ጥላቻ ንጹሃን ህጻናትንና ወጣቶችን እየበከለ በመሆኑ ዝምታቸውን ለመስበር መገደዳቸውን አብራርተዋል። በጥላቻና በሴራ ውስጥ ስላሉት አካላት ሲናገሩም "በምንና ለምን እንደተጣላን እርስ በእርስ በደንብ እንተዋወቃለን" በማለት በመካከላቸው ያለው የጥል ምስጢር ከሚወራው የተለየ መሆኑን ጠቁመዋል።

አቶ ታሪኩ አክለውም የቀረቡባቸው ክሶች በማስረጃ ፊት መቆም የማይችሉ ባዶ መሆናቸውን በምሳሌ አስረድተው፣ በትግሉ ወቅትም ሆነ ከክልል ምስረታ በኋላ ስላጠፉትና ስላለሙት ነገር ቀጣዩ ትውልድ እውነትን መዝኖ የጠራ መንገድ መምረጥ እንዲችል በሶሻል ሚዲያ ፊት ለፊት ለመሙገት የቲክቶክ አካውንታቸውን ጭምር ይፋ በማድረግ ዝግጁነታቸውን ገልጸዋል። ከጎናቸው ለቆሙት አካላት ምስጋና አቅርበው "ትናንት ለዛሬ ዋስትና አይሆንም" በማለት በትናንት ታሪክ ብቻ መኖር እንደማይቻልም አስገንዝበዋል።

ይህ በአመራሮችና ተችዎች መካከል የተፈጠረው የፊት ለፊት የሙግት ጥሪና ፍጥጫ በሲዳማ ፖለቲካ ልሂቃን መካከል ያለውን ጥልቅ የስልጣን፣ የሃሳብና የታሪክ ሽኩቻ ይበልጥ ወደ አደባባይ ያወጣው ክስተት ሆኗል።

ሆርን እንሳይት ጉዳዩን በገለልተኝነትና በሚዛናዊነት ለመዘገብ በትኩረት እየሰራ መሆኑን እየገለጽን ፣ የሁለቱንም ወገን ሀሳቦችና የፊት ለፊት ሙግቶች ለማስተናገድ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ መረጃቸውን የሚያቀርቡበት የጋራ መድረክ እንዲሆን ጥሪ እናቀርባለን ።

በሆለታ ፍርድ ቤት የደረሰ አሰቃቂ ግድያ ዛሬ ረፋድ ላይ በሆለታ ወልመራ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የተፈጠረው ክስተት መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ በከፍተኛ ድንጋጤና በቁጭት ውስጥ የከተ...
04/06/2026

በሆለታ ፍርድ ቤት የደረሰ አሰቃቂ ግድያ

ዛሬ ረፋድ ላይ በሆለታ ወልመራ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የተፈጠረው ክስተት መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ በከፍተኛ ድንጋጤና በቁጭት ውስጥ የከተተ አሰቃቂ ድርጊት ተፈጽሟል።

ፍትሕን ፍለጋ በተሰበሰቡበት የፍርድ ቤት አዳራሽ፣ በሰው ህይወት ላይ የተፈጸመው ግድያ የፍትሕ ሥርዓታችንን ደህንነት ጥያቄ ውስጥ የከተተ ሆኗል።

እንደደረሰን መረጃ፣ በዕለቱ የቤተሰብ ክርክርን ጉዳይ በመመልከት ላይ የነበረችው ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ፣ የፍርድ ውሳኔውን እያነበበች ባለችበት ወሳኝ ወቅት፣ ተከሳሹ በድንገት ባወጣው ሽጉጥ ዳኛዋን በጥይት በመምታት ህይወታቸውን ቀጥፏል። በዚሁ አጋጣሚ በችሎቱ ላይ በባለቤቷ ሲከራከሩ የነበሩት ባለቤታቸውም፣ በተከሳሹ በተተኮሰ ጥይት በተመሳሳይ ሁኔታ ህይወታቸው አልፏል።

ይህ አሳዛኝ ክስተት በዜጎች ዘንድ "የት ነው ደህንነት ያለው?" የሚል ጥያቄን አጭሯል። አንድ ግለሰብ ታጥቆ ወደ ፍርድ ቤት አዳራሽ መግባት መቻሉ፣ የፍርድ ቤቶቻችን የጸጥታና የፈተሻ አሰራር ምን ያህል ደካማ እንደሆነ በአሳዛኝ ሁኔታ አሳይቷል። "ሕግና ፍትሕ ይከበርባቸዋል" ተብለው በሚታመኑ የፍርድ ቤት አደባባዮች ላይ፣ የጦር መሣሪያ ይዞ መግባት መቻሉ የፍርድ ቤቶችን የውስጥ ጥበቃና የፍተሻ ስርዓት በዋናነት መፈተሽ እንደሚገባ ግልጽ መልእክት አስተላልፏል።

ዳኞችና የህግ ባለሙያዎች በስራ ገበታቸው ላይ ህይወታቸውን አሳልፈው መስጠት ካለባቸው፣ የፍትህ ተቋማቱ ለሰራተኞቻቸውና ለባለጉዳዮች ምን ያህል አስተማማኝ ጥበቃ እየሰጡ ነው? የሚለው ጥያቄ የዛሬው ቀን ትልቁ አሳሳቢ ጉዳይ ነው። ይህ ድርጊት የፍትሕ ሥርዓታችንን ታሪክ የዳሰሰ አሳዛኝ ክስተት ሆኖ የሚመዘገብ ነው።

ጉዳዩ በማህበራዊ ሚዲያና በህግ ባለሙያዎች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣንና ድንጋጤን ቀስቅሷል። በስራ ገበታዋ ፍትህን ለማስፈን ስትደክም የነበረችው ወጣት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ በግፍ መገደሏ፣ የመላው የህግ ማህበረሰብን ልብ ሰብሯል።

ለዳኛ ወርቄ ፈካንሳ ቤተሰቦችና ለሟች (ባለቤቱ) ወዳጅ ዘመዶች፣ እንዲሁም ለመላው የፍትህ አካላት መጽናናትን እንመኛለን።

Via A ዳኛው ከስፍራው

Address

Hawassa

Telephone

+251926498654

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Horn Insight posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Horn Insight:

Share