South Radio and Television Agency

  • Home
  • South Radio and Television Agency

South Radio and Television Agency This page is owned by South Radio and Television Agency, SNNPRS, Ethiopia.
(2)

In addition to this Meta Page, we have other social media accounts:

Website: https://srta.gov.et/

Telegram :
https://t.me/southRadioAndTelevisionAgency

Youtube:
https://www.youtube.com//featured

Twitter:
https://twitter.com/SouthRadioandTv
South Radio and Television Agency is a Government owned media that disseminates its news and programs worldwide via Television, Radio, and Website.

ማህበሩ የተቋቋመበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ተጨማሪ አባላትንና በጎ ፈቃደኞችን በማፍራትና ሁለንተናዊ ድጋፍ በማድረግ በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በኢትዮጵያ ቀይ ...
23/07/2025

ማህበሩ የተቋቋመበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ተጨማሪ አባላትንና በጎ ፈቃደኞችን በማፍራትና ሁለንተናዊ ድጋፍ በማድረግ በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጠየቀ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በማህበሩ መርሆዎች እና ዓላማ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የምክክር መድረክ አካሂዷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶር ዳንኤል አንጭሶ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በዘር፣ በቀለም፣ በፆታ፣ በዜግነት፣ በሃይማኖት እና በፖለቲካ አመለካከት ሳይለይ በተፈጥሮ እና በሰው ሰራሽ አደጋዎች ለተጎዱ ዜጎች አፋጣኝ እርዳታ የሚያቀርብ ሰብአዊ ተቋም ነው።

የድርቅና የረሃብ አደጋዎችን ቀድሞ በመዘጋጀት እና በመከላከል ረገድም በየደረጃው ካሉ አጋር አካላት ጋር በትብብር የተጣለበትን ሰብዓዊ ኃላፊነት እየተወጣ እንደሚገኝም አብራርተዋል።

የአምቡላንስ አገልግሎት፣ የመድኃኒት አቅርቦት፣ የተፈጥሮ ሀብቶችን የመንከባከብ ደም የማሰባሰብ መሰል ተግባራት ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር የድርሻውን ኃላፊነት እየተወጣ ያለ ማህበር ስለመሆኑ አስረድተዋል።

በክልሉ በ2017 በጀት ዓመት ብሔራዊ ማህበሩንና የተለያዩ አካላትን በማስተባበር 1 መቶ 6 ሚሊዮን 7 መቶ 63 ሺህ 9 መቶ 15 ብር የሚገመት የተለያዩ እርዳታዎችን በማድረግ ማህበሩ ለወገን ደራሽ መሆኑን በተግባር አረጋግጧል ብለዋል።

ማህበሩ የተቋቋመበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ሁለንተናዊ ድጋፍ ማድረግ የሁሉም ኃላፊነት እንደሆነም አሳስበዋል።

ማህበሩ ለተጎጂዎች አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት የተረጋጋ ማህበረሰብ መገንባት እንዲችል የባለድርሻ አካላት ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችንም በዝርዝር አቅርበዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ ዶክተር መለሰ ዘውገ በበኩላቸው፤ ክልሉ ያለውን ፀጋዎች በመጠቀም በቁጭት ከተሰራ በዘርፉ ለውጥ ማምጣት ይቻላል ብለዋል።

በአስተሳሰብ ላይ ከተሰራ ተግባር ቀላል ነው ያሉት ዕጩ ዶክተር መለሰ፤ ለዚህም በጥንካሬም ሆነ በጉድለት የታዩ ተግባራትን ለባለድርሻ አካላት ግልፅ ማድረግ ለውጤታማነቱ አጋዥ እንደሆነም አስገንዝበዋል

ማህበሩ ለህዝብ ተጠቃሚነት የሚሠራ በመሆኑ በቅንነት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመድረኩ የተገኙት የሀዲያ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዶክተር በፈቃዱ ገብረ ሃና፤ የዞን ሴክተሮች የአባልነት ገቢ በተመለከተ የፋይናንስ አሰራር ስርዓትን በተከተለ መልኩ የሚጠበቀውን ለማድረግ ይሰራል ብለዋል።

ሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትንና የንግዱን ማህበረሰብ በማስተባበር ማህበሩን ለመደገፍ እንደሚሰራም ተናግረዋል።

በመድረኩ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በባለድርሻ አካላት በኩል ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።

ዘጋቢ፡ ኤርጡሜ ዳንኤል - ከሆሳዕና ጣቢያችን

በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-
ዩቲዩብ- https://www.youtube.com/southradioandtelevisionagency
ቴሌግራም -https://t.me/southRadioAndTelevisionAgency
ዌብ ሳይት - https://srta.gov.et/
ትዊተር - https://twitter.com/SouthRadioandTv

የደሬቴድ ዲጂታል ሚዲያ የሐምሌ 16/2017 ዓ.ም የዕለቱ ዋና ዋና ዜናዎች፡- 👉ለኢትዮጵያውያን ባህልና ዕሴት የሚስማማ ዴሞክራሲን በጋራ ለመቀመር የፓርቲዎች ፉክክር ብቻ ሳይሆን ትብብርም እ...
23/07/2025

የደሬቴድ ዲጂታል ሚዲያ የሐምሌ 16/2017 ዓ.ም የዕለቱ ዋና ዋና ዜናዎች፡-

👉ለኢትዮጵያውያን ባህልና ዕሴት የሚስማማ ዴሞክራሲን በጋራ ለመቀመር የፓርቲዎች ፉክክር ብቻ ሳይሆን ትብብርም እንደሚያስፈልግ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

👉በሁሉም ዘርፍ የተጀመረው የማንሰራራት ጉዞ እውን እንዲሆን በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ ገለጹ፡፡

👉በተጠናቀቀው በጀት አመት የተጣሉ ግቦችን ለማሳካት የሚያስችሉ በርካታ ስኬታማ ተግባራት መከናወናቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) አስታወቁ።

👉በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) የተመራ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ቡድን በዳውሮ ዞን ሎማ ቦሳ ወረዳ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭ፣ የገጠር ኮሪደር ልማት እና ሌሎች የልማት ስራዎችን ተዟዙረው ጉብኝት አደረጉ።

👉በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ልማት ሥራዎች በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን እንቅስቃሴ እንደሚያፋጥኑ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ገለጹ።

👉የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለዘላቂ ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጂጌ (ዶ/ር) ገለጹ።

👉በኢትዮጵያ ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመትከልና ሰላምን ለማፅናት በሚደረገው ጥረት ሚናቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ ገለጹ።

👉የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የወጣቶችን የቴክኖሎጂ እውቀት በማሳደግ የስራ እድል እየፈጠረ መሆኑን የወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ዲን አቶ ኸይሩ አህመዲን ገለፁ፡፡

በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-
ዩቲዩብ- https://www.youtube.com/southradioandtelevisionagency
ቴሌግራም -https://t.me/southRadioAndTelevisionAgency
ዌብ ሳይት - https://srta.gov.et/
ትዊተር - https://twitter.com/SouthRadioandTv

በበጀት አመቱ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር እንዳሻው ጣሰው አስታወቁ፡፡ ‎‎ዘጋቢ፡ አብደላ በድሩ #ደሬቴድ
23/07/2025

በበጀት አመቱ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር እንዳሻው ጣሰው አስታወቁ፡፡

‎ዘጋቢ፡ አብደላ በድሩ

#ደሬቴድ

‎በበጀት አመቱ የተከናወኑ ተግባራት ስኬታማ መሆናቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር እንዳሻው ጣሰው አስታወቁ፡፡ ‎‎ዘጋቢ፡ አብደላ በድሩ #ደሬቴድ ...

‎በኢትዮጵያ የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ ከተስፋ ወደ ሚጨበጥ ውጤት እየተሸጋገረ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ ገለጹ፡፡ ‎ ‎ዘጋቢ...
23/07/2025

‎በኢትዮጵያ የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ ከተስፋ ወደ ሚጨበጥ ውጤት እየተሸጋገረ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ ገለጹ፡፡

‎ዘጋቢ ፡ አብደላ በድሩ

#ደሬቴድ

‎በኢትዮጵያ የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ ከተስፋ ወደ ሚጨበጥ ውጤት እየተሸጋገረ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ ገለጹ፡፡ ‎ ...

የክልሉን ህዝብ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየዘርፉ በተሰሩ ስራዎች አበራታች ውጤት መገኘቱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር  ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ ዘጋቢ ፡ቴዎድሮስ ወ...
23/07/2025

የክልሉን ህዝብ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየዘርፉ በተሰሩ ስራዎች አበራታች ውጤት መገኘቱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ

ዘጋቢ ፡ቴዎድሮስ ወርቅነህ

#ደሬቴድ

የክልሉን ህዝብ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየዘርፉ በተሰሩ ስራዎች አበራታች ውጤት መገኘቱን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ ዘጋቢ ፡ቴዎ.....

የማታ 1፡00 ዜና 24፤ ሀዋሳ፡ ሐምሌ 16/2017 ዓ.ም #ደሬቴድ ፡   ቀጥታ ስርጭት
23/07/2025

የማታ 1፡00 ዜና 24፤ ሀዋሳ፡ ሐምሌ 16/2017 ዓ.ም

#ደሬቴድ ፡ ቀጥታ ስርጭት

#ደሬቴድ ፡ ቀጥታ ስርጭት የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛዎቹ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-ዩቲዩብ- http...

23/07/2025

የማታ 1፡00 ዜና 24፤ ሀዋሳ፡ ሐምሌ 16/2017 ዓ.ም

#ደሬቴድ - ቀጥታ ስርጭት

በጤናው ዘርፍ ከዚህ ቀደም በመደበኛ መርሃ ግብር ብቻ ሲሰሩ የነበሩ ተግባራት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመታገዙ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ እንደሚገኝ ተገለፀ‎የማዕከላዊ ኢ...
23/07/2025

በጤናው ዘርፍ ከዚህ ቀደም በመደበኛ መርሃ ግብር ብቻ ሲሰሩ የነበሩ ተግባራት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመታገዙ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ እንደሚገኝ ተገለፀ

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የክረምት የጤና በጎ ፈቃድ አገልግሎት የእውቅና አሰጣጥ እና የ2018 በጀት ዓመት ይፋዊ የስራ ማስጀመሪያ ፕሮግራም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።

በፌደራል ጤና ሚኒስቴር የሜዲካል አገልግሎት ስራ አስፈፃሚ ተወካይና የጤና በጎ ፈቃድ አገልግሎት አስተባባሪ ዶ/ር ሀብታሙ መንጌ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት የጤና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጤና ሚኒስቴር ባለፉት ሰባት ዓመታት ሲሰራ መቆየቱን አውስተው በዚህም በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

‎በተለይ በዚህ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በጤናው ዘርፍ 197 ሚሊዮን የሚገመት ብር እንደ ሀገር ማዳን መቻሉን የተናገሩት ዶ/ር ሀብታሙ፤ ለዚህም ውጤታማነት በቅንነትና በቁርጠኝነት የሰሩ ባለሙያዎች እውቅና ይገባቸዋል ነው ያሉት።

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትልና የህክምና አገልግሎቶች ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሀብቴ ገ/ሚካኤል የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለረጅም ጊዜ ሲሰራ የቆየ ቢሆንም በዕቅድና በተደራጀ መልኩ መሰራት ከተጀመረ ወዲህ የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል።

‎በዚህ አገልግሎት የበርካታ አቅመ ደካማ ሰዎችን ቤት ግንባታና እድሳት እንዲሁም ሌሎች የኢኮኖሚ አቅም የሌላቸው ዜጎችን በመደገፍ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት አቶ ሀብቴ።

በጤናው ዘርፍ ከዚህ ቀደም በመደበኛ ስራ ብቻ ሲሰሩ የነበሩ ተግባራት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ጭምር በመሰራቱ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ እንደሚገኝም ምክትል ሃላፊው ገልፀዋል። ከእነዚህ ተግባራት መካከልም የበርካታ ህፃናትና እናቶችን ህይወት እየታደገ ያለው የደም ልገሳ ስራ፤ ነፃ የጤና ምርመራና ህክምና አገልግሎት እየተሰሩባቸው የሚገኙ ተግባራት በዋናነት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ፍቅረፅዮን ደገሙ በበኩላቸው፤ ሆስፒታሉ በዙሪያው ለሚገኙ ከ4 ሚሊየን በላይ ታካሚዎች የሪፈራል አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም በውስጥ ደዌ፣ በማህፀንና ፅንስ ህክምና፣ በህፃናት ህክምናና በስፔሻሊቲ የተሻለ አገልግሎት በመስጠቱ ለሽልማት መብቃቱን ገልፀዋል።

‎በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የሀዲያ፣ የስልጤና የጉራጌ ዞኖች ጤና መምሪያ ሀላፊዎች በሰጡት አስተያየት ባለፈው የ2017 በጀት ዓመት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ህብረተሰቡ ተግባሩን ባህል አድርጎ እንዲያስቀጥል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዉ በጤና አገልግሎት ዘርፍ በተለይም የደም ልገሳ፣ ነፃ ምርመራና የህክምና አገልግሎቶች እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ዘርፎች ላይ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል።

‎በዚህ ክረምት ወቅትም ተግባሩን በየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እንደሚሰራም አክለዋል።

በዕለቱ ከበጎ አግልግሎት መርሃ ግብር ጎን ለጎንም በሆስፒታሉ በአዲስ መልክ የተጀመረው የካንሰር ህክምና ክፍልን ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎት እየሰጡ ያሉ ክፍሎች ጉብኝት የተደረገ ሲሆን በመጨረሻም በተሳታፊዎች የደም ልገሳና የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተከናውኗል።

ዘጋቢ፡ ተዘራ በቀለ - ከወልቂጤ ጣቢያችን

በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-
ዩቲዩብ- https://www.youtube.com/southradioandtelevisionagency
ቴሌግራም -https://t.me/southRadioAndTelevisionAgency
ዌብ ሳይት - https://srta.gov.et/
ትዊተር - https://twitter.com/SouthRadioandTv

"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፈታ" በሚል መሪ ቃል የክረምት ወራት  የወጣቶች  በጎ  ፈቃድ  አገልግሎት የንቅናቄ መድረክ በሳውላ ከተማ ተካሄደበጎፋ ዞን በሳውላ ከተማ በዘንድሮው የክረም...
23/07/2025

"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፈታ" በሚል መሪ ቃል የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የንቅናቄ መድረክ በሳውላ ከተማ ተካሄደ

በጎፋ ዞን በሳውላ ከተማ በዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ 16 ሺህ ወጣት አባላት በ15 አይነት የሰራ መሰኮች እንደሚሳተፉ ተገልጿል፡፡

የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ የሣውላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶ/ር ንጉሴ መኮንን፤ በበጋ ወራት በርካታ በጎ ተግባራት መሰራታቸውን አንስተው፤ በክረምት ወቅት የተጀመረውን የአረንጎዴ አሻራ የአቅመ ደካሞች ቤት መገንባትና የጤና ዘርፎችን ጨምሮ በ15 የሥራ መስኮችን ለማሳካት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የሳውላ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አንተነህ በለጠ፤ በአካባቢው የሚታዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመቅረፍ በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ወጣቱ ውድ የሆነውን እውቀቱንና ጉልበቱን የሚለግስበት ነው ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች የተጀመሩ የመሠረተ ልማት ሰራዎችን የመጨረስና ለወጣቶች የሥራ ባህሎችን በማሻሻል ዙሪያ ግንዛቤ ማሰጨበጫ ትምህርት መስጠት እንዳለበት አንሰተዋል፡፡

የሳውላ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊና የወጣት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ምንያህል ባቤና፤ በዘንድሮ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ከ16 ሺህ በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ 15 የሥራ መስኮች 45 ሺህ የህብረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ በማድረግ ከ21 ሚሊየን ብር በላይ ከወጭ ለማዳን የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የጎፋ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ምክትል ኃላፊና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላም እንግዳ፤ በበጋው ወራት ለተሰሩ ጠንካራ ተግባራት አመስግነው የክረምቱ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራም የተሳካ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት ሊሠሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ዘጋቢ፡ ስንታየሁ ሙላቱ - ከሳውላ ጣቢያችን

በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-
ዩቲዩብ- https://www.youtube.com/southradioandtelevisionagency
ቴሌግራም -https://t.me/southRadioAndTelevisionAgency
ዌብ ሳይት - https://srta.gov.et/
ትዊተር - https://twitter.com/SouthRadioandTv

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ #ደሬቴድ ፡  ሐምሌ 16/2017  - ቀጥታ ስርጭት
23/07/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ

#ደሬቴድ ፡ ሐምሌ 16/2017 - ቀጥታ ስርጭት

#ደሬቴድ ፡ ሐምሌ 16/2017 - ቀጥታ ስርጭት የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛዎቹ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታ...

በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚያስችሉ የሪፎርም ተግባራት  መከናወኑ ተገለፀሀዋሳ: ሐምሌ 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል  የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የ...
23/07/2025

በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚያስችሉ የሪፎርም ተግባራት መከናወኑ ተገለፀ

ሀዋሳ: ሐምሌ 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚያስችሉ የሪፎርም ተግባራት መከናወኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባዔውን እየተካሔደ ነው።

የትምህርት ጥራትና የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የሚያስችል የትምህርት ቤት አመራሮች ሪፎርም መካሄዱን የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ ለ3 ሺህ 720 የትምህርት ቤት አመራሮች የመማር ማስተማር መሪነት ሚና፣ የፈተና አዘገጃጀት ቢጋር እና ተከታታይ የሙያ ማሻሻያ ርዕሶች ላይ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው የዘርፉ ምሁራን ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉን አስረድተዋል፡፡

በሪፎርሙ ትክክለኛ ሰው በትክክለኛ ቦታ ተመድቧል ያሉት ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው፥ የተጠያቂነት ስርዓት በመዘርጋት የትምህርት ቤት አመራሮች የስራ ተነሳሽነታቸው ተሻሽሏል ነው ያሉት፡፡

በተጨማሪም በትምህርት ቤት አመራር ሪፎርም በርካታ ብልሹ አሰራሮች የታረሙ ሲሆን ያለአግባብ ለደመወዝ ሲከፈል የነበረ ከ59 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን መቻሉንም አስረድተዋል፡፡

በክልል እና አገር አቀፍ ፈተናዎች የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ከዋቸሞ፣ ወልቂጤ እና ወራቤ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር ለ29,418 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት ለአገር-አቀፍ ፈተና እንዲዘጋጁ የተደረገ ሲሆን የሆሳዕና ትምህርት ኮሌጅም ለ2ሺ 928 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት ለክልል-አቀፍ ፈተና እንዲዘጋጁ ተደርጓል ብለዋል፡፡

ጥቅል የትምህርት ተሳትፎ በቅድመ አንደኛ በ2016 ትምህርት ዘመን ከነበረበት 80 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 86 ነጥብ 1 በመቶ ማድረስ መቻሉን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ ንጥር ተሳትፎ 79 በመቶ ከነበረበት 79.45% ለማድረስ ታቅዶ 78.4% ማድረስ መቻሉ ተመላክቷል፡፡

ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

በይርጋጨፌ ከተማ በኢንተርፕራይዝ የተደራጁ ማህበራት ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናገሩዘጋቢ፡ ወርቃገኘው ወልደየስ ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
23/07/2025

በይርጋጨፌ ከተማ በኢንተርፕራይዝ የተደራጁ ማህበራት ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናገሩ

ዘጋቢ፡ ወርቃገኘው ወልደየስ ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

ዘጋቢ፡ ወርቃገኘው ወልደየስ ከይርጋጨፌ ጣቢያችን #ደሬቴድ የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛዎቹ አድራሻዎቻችን አባል ...

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Radio and Television Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to South Radio and Television Agency:

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share