South Radio and Television Agency

South Radio and Television Agency This page is owned by South Radio and Television Agency, SNNPRS, Ethiopia.
(2)

In addition to this Meta Page, we have other social media accounts:

Website: https://srta.gov.et/

Telegram :
https://t.me/southRadioAndTelevisionAgency

Youtube:
https://www.youtube.com//featured

Twitter:
https://twitter.com/SouthRadioandTv
South Radio and Television Agency is a Government owned media that disseminates its news and programs worldwide via Television, Radio, and Website.

በሴቶች ላይ የሚከሰቱ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል ባለድርሻ አካላት በትኩረት መስራት እንደሚገባቸዉ ተገለፀ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት  ዳይሬክ...
07/11/2025

በሴቶች ላይ የሚከሰቱ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል ባለድርሻ አካላት በትኩረት መስራት እንደሚገባቸዉ ተገለፀ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ዳይሬክቶሬት የጡት እና የማህፀን ጫፍ ካንሰር የንቅናቄ መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር በጂንካ ከተማ አካሂዷል፡፡

የንቅናቄ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞችና የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ፤ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች በሴቶች ላይ ከፍተኛ ጫናና ሞት ከሚያስከትሉት መካከል የማህፀን ጫፍ ካንሰርና የጡት ካንሰር ዋነኞች ናቸዉ ብለዋል፡፡

የጡት ካንሰር ከመከሰት አንፃር በ1ኛ ደረጃ ሴቶችን የሚያጠቃ ሲሆን ከገዳይነት አንፃር የማህፀን ጫፍ ካንሰር 1ኛ ደረጃን የሚይዝ በሽታ መሆኑን የገለፁት ኃላፊዉ፤ ሴቶች ወደ ጤና ተቋማት በመሔድ ልየታ በማድረግና በሽታዉ ከተከሰተም ህክምና ማግኘት ከቻሉ በሽታዉን መታደግ እንደሚቻልና ይህ ሳይሆን ሲቀር ለሞት እንደሚዳርጉ ተናግረዋል፡፡

አክለዉም ሴቶችን ከጡት ካንሰርና ከማህፀን ጫፍ ካንሰር ለመታደግ በተሰሩ ስራዎች ጠንካራ አፈፃፀም ያላቸዉ መዋቅሮች እንዳሉ ሁሉ በአንፃሩ ዝቅተኛ አፈፃፀሞችም ስላሉ በየደረጃዉ ያሉ ባለድርሻ አካለት የህበረተሰቡ ግማሽ አካል የሆኑትን ሴቶች ከበሽታዉ ለመታደግ ትኩረት ሰጥተዉ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በሽታ መከላከል ዳይሬክቶሬት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ፕሮግራም አስተባባሪ ሲስተር ትዕግስት ተሰማ፤ በየዓመቱ ከሚታመሙት ወደ 17 ሺ የሚጠጉ ወደ 7 ሺ የሚሆኑት በየአመቱ እንደሚሞቱ እና በተመሳሳይ ከ6 ሺ በላይ የሚሆኑ ሴቶች በየዓመቱ የማህፀን ጫፍ ካንሰር እንደሚታመሙና ከእነዚህም ከ4 ሺ በላይ የሚሆኑት በበሽታዉ እንደሚሞቱ ተናግረዋል፡፡

በጤናዉ ዘርፍ የመድረኩ ተሳታፊ ከሆኑት መካከል የአሪ ዞን ጤና መመሪያ ኃላፊ አቶ በድሉ በጊማስ የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ኤካና የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይፉ አነቃና ሌሎችም በጋራ፤ የማህበረሰቡን ጤና መጠበቅ ዋና ኃላፊነታቸዉ በመሆኑ ከዚህ ቀደም ትኩረት ሳይሰጣቸዉ በበርካታ ሴቶች ላይ ጉዳት ሲያደርሱ የቆዩ አሁን ግን መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራባቸዉ ካሉ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች መካከል ከማህፀን ጫፍ ካንሰርና የጡት ካንሰር ሴቶችን ለመታደግ ከዚህ ቀደም ከነበረዉ አሰራር በተሻለ ሁኔታ በገጠር ያሉ ሴቶችን ተደራሽ በማድረግ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የማህበራዊ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ምህረት በላይ በበኩላቸዉ፤ ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመሆን በጡት ካንሰርና በማህፀን በር ካንሰር በርካታ ስራዎች ሲሰሩ ቢቆዩም የተመዘገቡ ዉጤቶች አሁንም ትኩረት የሚሹ በመሆናቸዉ ሴቶችን ከስቃይና ሞት ለመታደግ በቀጣይ የተሻለ ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

በመድረኩ የክልሉ ጤና ቢሮ የጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ቢሮ ኃላፊዎችና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የዞን ጤና መምሪያ ኃላፊዎች፣ የበሽታ መከላከል ዘርፍ ኃላፊዎችና ሌሎች ተገኝተዋል፡፡

ዘጋቢ፡ በናወርቅ መንግስቱ - ከጂንካ ጣቢያችን

በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-
ዩቲዩብ- https://www.youtube.com/southradioandtelevisionagency
ቴሌግራም -https://t.me/southRadioAndTelevisionAgency
ዌብ ሳይት - https://srta.gov.et/
ትዊተር - https://twitter.com/SouthRadioandTv

የሕብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን የገቢ ሥራዎች ዙሪያ በትኩረት እየተሠራበት እንደሚገኝ የራጴ ወረዳ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት አስታወቀ‎‎የራጴ...
07/11/2025

የሕብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን የገቢ ሥራዎች ዙሪያ በትኩረት እየተሠራበት እንደሚገኝ የራጴ ወረዳ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት አስታወቀ

‎የራጴ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዲስዓለም ጎበና በሰጡት ገለጻ የሕብረተሰቡን የመሠረተ ልማት ፍላጎት ለማሟላትና መንግሥታዊ ሥራዎችን ለማሳለጥ ገቢ ትልቁን ሚና እንደሚጫወት ጠቁመው÷ ከመደበኛው የገቢ አሰባሰብ ሥራ ጎንለጎን በማዐጤመ ሥራዎች ላይ በመረባረብ የሕብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የድርሻቸውን እየተወጡ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

‎ያለገቢ ማንኛውንም ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሥራዎችን መሥራት የማይቻል መሆኑን የገለጹት ኃላፊው÷ በወረዳው 2017 ዓ.ም በተሠሩ የማዐጤመ ሥራዎች 95 በመቶ አፈጻጸም መመዝገቡን ተናግረዋል፡፡

‎በ2018 በጀት ዓመት 70 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መታቀዱን የገለፁት ኃላፊው ይህንኑ ለማሳካት ቅዳሜን ተጨማሪ የመንግሥት የሥራ ዕለት አድርገው በመሥራት አስፈላጊውን ሁሉ እየተወጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

‎አቶ ሲሳይ ሳሙኤልና ተሰማ ሎሌ በወረዳው የራጴ ከለማና የላባጋሻ ቀበሌ ነዋሪዎች እንዲሁም የማዐጤመ ተጠቃሚዎች ናቸው። የማዐጤመ አገልግሎት የዜጎች የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ተገልጋዩ ሕብረተሰብ ክፍሎች ግዴታቸውን አውቀው የአገልግሎት ክፍያ በወቅቱ መክፈል ይኖርባቸዋል ነው ያሉት።

‎ከዚህ በፊት በሕብረተሰቡ ዘንድ በማዐጤመ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የግንዛቤ እጥረት በገቢው አሰባሰብ ላይ ክፍተቶች እንደነበሩ በመግለፅ በሚሰጣቸው ትምህርት በአሁኑ ሰዓት በባለቤትነት እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ የተናገሩት የገቢ አሰባሰብና ጥናት ባለሙያ አቶ ታምራት ፍስሐ ናቸው።

‎በዘንድሮው 2018 ዓ.ም በማህበረሰብ ዐቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ዘርፍ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ አቅደው ከባለድርሻው መሥሪያቤቶች ጋር በቅንጅት እየሠሩ መሆናቸውን የተናገሩት የራጴ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደጀኔ ሽብሩ ናቸው።

‎በበጀት ዓመቱ በወረዳው የጎላ የመድኃኒት እጥረት አለመኖሩን የገለፁት አቶ ደጀኔ፣ በ2017 ዓ.ም በዘርፉ የነበሩ ድክመቶችን በማረም በተያዘው በጀት ዓመት ላይ በተቀናጀ የሕብረተሰቡን የጤና ፍላጎት ለማሟላት በተግባር ወደሥራ መገባቱንም አስገንዝበዋል።

‎የራጴ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዮሐንስ ሂኔሲ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን በተለይም በዝቅተኛው የኑሮ ደረጃ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ለመርዳት ያለመ በመሆኑ ተገልጋዮች በተቀመጠላቸው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት የሚፈለግባቸውን ሁሉ እንዲወጡ አሳስበዋል።

‎አያይዘውም አገልግሎቱ በተሟላ ሁኔታ ለሕብረተሰቡ ተደራሽ እንዲሆን ዓመታዊ መዋጮውን በተገቢው መንገድ በመሰብሰብ ወደ ባንክ አካውንት ሲስተም ገብቶ ተግበራዊ የሚደረግበትን መንገድ ባለድርሻዎች ጋር ምቹ ሥነምህዳር ማመቻቸታቸውን አስታውቀዋል።

‎ዘጋቢ: እስራኤል ብርሃኑ - ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

ትውልዱን በጥሩ ስነ ምግባር ማነፅና ሀገር ወዳድ  ዜጋ እንዲሆኑ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ ተገለጸሀዋሳ፡ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ትውልዱን በጥሩ ስነ ምግባር ማነፅ...
07/11/2025

ትውልዱን በጥሩ ስነ ምግባር ማነፅና ሀገር ወዳድ ዜጋ እንዲሆኑ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ ተገለጸ

ሀዋሳ፡ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ትውልዱን በጥሩ ስነ ምግባር ማነፅና ሀገር ወዳድ ዜጋ እንዲሆኑ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ አስተያየታቸውን የሰጡ የዲላ ከተማና የጌዴኦ ዞን ነዋሪዎች ገለጹ፡፡

‎ቀደምት አባቶች ይዘውት የመጡትን የሰላም እሴት ከመገንባት ረገድ አሁን ካለው ብዙ እንደሚጠበቅ የወናጎ ወረዳ ነዋሪ ወ/ሮ ዕድገት ጴጥሮስ አስገንዝበዋል፡፡

‎ትውልዱ በጥሩ ስነ ምግባር በመታነፅ ሀገር ወዳድ ዜጋ እንዲሆን ወላጆች፣ የባህል አባቶች፣ የሀይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶችና ለሌሎች መዋቅሮች በትኩረት ሊሠሩ ይገባል ብለዋል የይርጋጨፌ ከተማ ነዋሪ አቶ ዋቅጅራ ዱካሌ፡፡

‎የዲላ ከተማ ነዋሪ አቶ ፍቃዱ ወሬራ እንደገለፁት በዓለም ትኩረት ከሚሹ ጉዳዮች ሰላም ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዝ ጠቁመው÷ ለመማር፣ ለንግድ ሥራ፣ ልጅ ወልዶ ለማሳደግ፣ ከቦታ ቦታ ለመዘዋወርና በየቀኑ የምናከናውነውን ተግባራት ለመፈፀም ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ነው የጌዴኦ ማህበረሰብ "ሰላምን እንሻማ" የሚለው፡፡

የሁሉም መሰረት የሆነውን ሰላም ለማስጠበቅ እያንዳንዱ የድርሻውን እንዲወጣ አቶ ፍቃዱ አሳስበዋል፡፡

ሁሉም ዜጋ አንዱን ከሌላው የሚከፋፈልና የጥላቻ ንግግሮችን በማህበራዊ ሚዲያ ከማንፀባራቅ በመቆጠብ ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት በተሰማራበት የሥራ መስክ መትጋት እንዳለበት አስተያየት ሰጪዎቹ አስገንዝበዋል፡፡

‎ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም - ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

የብልፅግና ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት(በምስል)
07/11/2025

የብልፅግና ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ያደረጉት የልማት ሥራዎች ጉብኝት(በምስል)

‎ሴቶች ጠንክረው ከሠሩና አስፈላጊው እገዛ ከተደረገላቸው ጥሩ ደረጃ ላይ መድረስ ይችላሉ - የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽህፈት ቤት ‎‎ሀዋሳ፡ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ)...
07/11/2025

‎ሴቶች ጠንክረው ከሠሩና አስፈላጊው እገዛ ከተደረገላቸው ጥሩ ደረጃ ላይ መድረስ ይችላሉ - የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽህፈት ቤት

‎ሀዋሳ፡ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ሴት ተማሪዎች ጠንክረው ከሠሩና አስፈላጊው እገዛ ከተደረገላቸው ውጤታማ በመሆን ጥሩ ደረጃ ላይ መድረስ እንደሚችሉ የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽህፈት ቤት ገልጿል።

‎ተማሪ ሀና አዱኛ እና ተማሪ አብሳላት አሰጋኸኝ እንደተናገሩት፤ ሴት ልጅ ከወንድ እኩል መማር፣ መሥራትና የፈለገችውን ነገር ማድረግ የምትችል ቢሆንም ከቤተሰብ፣ ከማህበረሰብና ከተቃራኒ ፆታ በሚፈጠርባት ተጽዕኖ ከትምህርቷ ወደ ኋላ ልትቀር ትችላለች።

‎ሴት ልጅ ዓላማዋ ላይ ካተኮረች፣ ጊዜዋን በሚገባ ከተጠቀመችና በራስ መተማመኗን ካዳበረች ውጤታማ መሆን እንደምትችል ያነሱት ተማሪዎቹ በዚህ ሁሉ ግን የቤተሰብ እገዛ ከፍተኛ መሆን እንዳለበት ነው የጠቆሙት።

‎መምህርት ዕጸገነት አየለ በበኩላቸው፤ በተለያዩ ዘርፎች የሴቶች ተሳትፎ አነስተኛ ቢሆንም በያሉበት የትምህርት ደረጃ ከፍተኛ ውጤት የሚያስመዘግቡ ሴት ተማሪዎች ቁጥር ቀላል የሚባል አይደለም ሲሉ ገልጸዋል።

‎የይርጋጨፌ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይ አቶ ደጀኔ ሙላቱ፤ ሴቶች ዕድል ከተሰጣቸውና አስፈላጊው ድጋፍ ከተደረገላቸው ውጤታማ መሆንና የተሻለ ደረጃ ላይ መድረስ እንደሚችሉ ነው የተናገሩት።

‎ሴቶችን ከማጠናከርና ከማብቃት አኳያ በትምህርት ቤቶች የንጽሕና መጠበቂያዎችን፣ የሴቶች መማክርት፣ የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲሁም ሌሎችም አስፈላጊ ነገሮችን ለማሟላት እየሠሩ እንደሚገኙና በየጊዜው ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉ አስረድተዋል።

‎ሴት ተማሪዎችን ከመደገፍ ባለፈ ወደ ኃላፊነት ደረጃ እንዲመጡ እናበረታታለን ያሉት አቶ ደጀኔ፤ በተለይ ወላጆች ሴት ልጆች በትምህርታቸው ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ የሥራ ጫና መቀነስና መከታተል አለባቸው ብለዋል።

ዘጋቢ፡ ለምለም ኦርሳ - ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-
ዩቲዩብ- https://www.youtube.com/southradioandtelevisionagency
ቴሌግራም -https://t.me/southRadioAndTelevisionAgency
ዌብ ሳይት - https://srta.gov.et/
ትዊተር - https://twitter.com/SouthRadioandTv

‎‎2 ሺህ 930 በላይ ቶን ቡና ለኢትዮጵያ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸሀዋሳ፡ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የታጠበና ያልታጠበ 2 ሺህ 930 በላይ ቶን ቡ...
07/11/2025

‎‎2 ሺህ 930 በላይ ቶን ቡና ለኢትዮጵያ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ

ሀዋሳ፡ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የታጠበና ያልታጠበ 2 ሺህ 930 በላይ ቶን ቡና ለኢትዮጵያ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን የኮሬ ዞን ቡናና ሻይ ቅመማቅመም ጽ/ቤት አስታወቀ።

‎በዞኑ ከ400 በላይ ስፔሻሊቲ/ልዩ ቅሽር ቡና በጥራት እየተዘጋጀ መሆኑም ተመላክቷል።

‎የኮሬ ዞን ቡናና ሻይ ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጃሌ እንደገለጹት በተከለሰው ዕቅድ የታጠበ 1 ሺህ 613፣ ቅሽር 924 ቶን እና ስፔሻሊቲ/ልዩ ቅሽር 405 ነጥብ 29 ቶን በድምሩ 2ሺህ 930 ነጥብ 59 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ በ6 ማዕከላት እየተዘጋጀ ይገኛል።

‎በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀ ስፔሻሊቲ ቅሽር ቡና በልዩ ዋጋ የሚሸጥ መሆኑን የተናገሩት አቶ አሸናፊ አርሶአደሮች ተደራጅተው በማዘጋጀት ኢኮኖሚያቸውን የሚያሳድጉበት ዕድል ተመቻችቷል ብለዋል።

‎በአማኑኤል ወልደሰንበት የእሸት ቡና ኢንዱስትሪ ሥራ አስኪያጅ አቶ ካህናት ዘለቀ በበኩላቸው ጥራቱ የተጠበቀ ስፔሻሊቲ ቅሽር ቡና ወዙን ጠብቆ እንዲደርቅ በተገደበ ሰዓት ለፀሐይ ክፍት በማድረግ በጥንቃቄ እያዘጋጁ እንደሆነ ነው የገለጹት።

‎ከኢንዱስትሪ ሠራተኞች መካከል ወይዘሪት ተዋበች ጌታሁንና ወጣት ናትናኤል ሀሰን በተሰጣቸው ግንዛቤ ከቅባትና ሽታ ካላቸው ባዕድ ነገሮች በተጠበቀ ሁኔታ ስፔሻሊቲ ቡናን በጥራት እንደሚያዘጋጁ ተናግረዋል።

‎ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ - ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የመረቁት የፋሲል ግቢ በምሥል፦
07/11/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የመረቁት የፋሲል ግቢ በምሥል፦

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የታደሰውን የፋሲል ጊቢ መርቀዋል የተከናወነው ሰፊ የእድሳት ሥራ ...
07/11/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የታደሰውን የፋሲል ጊቢ መርቀዋል

የተከናወነው ሰፊ የእድሳት ሥራ በቅርስ ስፍራው ነባሩን ታሪክ በመጠበቅ ውበቱን እና ተደራሽነቱን በማሻሻል አዲስ እስትንፋስ የሰጠ ሆኗል።

የእድሳት ሥራው የቤተመንግሥቱን የግንባታ መዋቅር መጠገን፣ የእግር መንገዶችን ማሻሻል፣ ቁልፍ የሆኑ ሕንፃዎችን ከዝግባ እና ዋንዛ በባሕላዊ ቁሳቁሶችን ተጠቅሞ በማደስ የስፍራውን ግለ ወጥ መልክ እና ባሕርይ ለመጠበቅ ተሰርቷል። ለጎብኝዎች ምቾት የተሰናዱ አገልግሎት መስጫዎችም ትርጉም ባለው ደረጃ ተሻሽለዋል። አዲስ የቱሪስት ማዕከልም ተከፍቷል። ዘመናዊ መጸዳጃ ቤቶች፣ የተሻሻሉ የመብራት እና የደኅንነት ሥርዓቶችም ተሰናድተዋል። እንደ አፄ ፋሲል፣ አፄ ቀዳማዊ ዮሃንስ እና አፄ ቀዳማዊ ኢያሱ አቢያተ መንግሥት ብሎም ድልድዮች፣ መታጠቢያ ሥፍራዎች፣ ታሪካዊ በሮች ወዘተ በጥንቃቄ ታድሰዋል።

በተጨማሪም ከ40,000 ስኴር ሜትር በላይ የአካባቢው ምድር የማስዋብ ሥራ ተሰርቷል። ይኸም ለጎብኝዎች ይበልጥ ሳቢ የሆነ ከባቢ ፈጥሯል። አጠቃላይ የእድሳት ሥራው ከአንድ አመት በታች የፈጀ ሲሆን የዚህን አስደናቂ የታሪክ እና የባሕል ሥፍራ ለረዥም ጊዜ ጠብቆ በሚያቆይ አኳኋን ተከናውኗል።

የብልፅግና ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ የብልፅግና ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የግብር...
07/11/2025

የብልፅግና ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ የብልፅግና ከፍተኛ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን እየተከናወኑ የሚገኙ የግብርና ክላስተሮችንና ሌሎች የልማት እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል፡፡

የብልፅግናም ክልሎች የተውጣጡ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች ባለፉት 10 ቀናት በአዳማ ከተማ ስልጠና ሲወስዱ ቆይተዋል።

ሰልጣኞቹ በዛሬው ዕለት በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ቦራ ወረዳ በክላስተር እየለማ ያለውን የፓፓ ማሳ ተመልክተዋል፡፡

በክላስተር እየለማ ያለው እና “red ready" የሚባለው የፓፓያ ዝርያ ከአንድ ዛፍ ላይ እስከ አንድ ኩንታል ምርት ሊያስገኝ እንሚችል በምሥራቅ ሸዋ ግብርና ቢሮ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

አመራሮቹ በዞኑ ሉሜ ወረዳ በክላስተር እየለማ ያለውን የዓሣ ምርትም የጎበኙ ሲሆን፣ በክላስተር እየለማ ያለው ዓሣ አመራረት ትምህርት የሚወሰድበት እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡

በሉሜ ወረዳ ቆቃ ባና ቀበሌ ለ80 ወጣቶች የሥራ ዕድል የፈጠረው የዓሣ ማርቢያ ፖንድም ሌሎች ክልሎች ጥሩ ተሞክሮ ያዩበት መሆኑ ተገልጿል።

በገጠር ትራንስፎርሜሽን ከማምረት ለውጪ ገበያ እስከማቅረብ የዘለቀ መሆኑንም ያስገነዘቡት ሚኒስትሯ፣ ገጠሩን ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ገጠሩን እና ከተማውን ለማስተሳሰር የተሄደበት ርቀት በጎ ጅምሮች መኖራቸውን ያመላከተ መሆኑን መግለጻቸውን ከብልጽግና ፓርቲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-
ዩቲዩብ- https://www.youtube.com/southradioandtelevisionagency
ቴሌግራም -https://t.me/southRadioAndTelevisionAgency
ዌብ ሳይት - https://srta.gov.et/
ትዊተር - https://twitter.com/SouthRadioandTv

07/11/2025

ጉልበት ይሸሻል፣ ጊዜ ይሸሻል፣ ስልጣን ይሸሻል፣ ሁሉ አላፊ ነው ፣ የማያልፈው እንደዚህ ያለው ታላቅ ስራ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ከሁሉም የኃይማኖት ተቋማት የተወጣጡ የኃይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች በከተማዉ ፀጥታ እንዲሁም በልማት ዙሪያ የጋራ ዉይይት አካሄዱበመድረኩም የሀገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት መሪዎች ልማ...
07/11/2025

ከሁሉም የኃይማኖት ተቋማት የተወጣጡ የኃይማኖት መሪዎችና የሀገር ሽማግሌዎች በከተማዉ ፀጥታ እንዲሁም በልማት ዙሪያ የጋራ ዉይይት አካሄዱ

በመድረኩም የሀገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት መሪዎች ልማትንና ሰላምን የሚያደናቅፉ አካላትን እንዲገስጹ ጥሪ ቀርቧል።

የዉይይት መድረኩን የመሩት የኬሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ዮሐንስ ኃይሉ፣ከልማት አኳያ ባለሃብቶች እንዲያለሙ ቦታ እያዘጋጁ መሆናቸዉን፣በማስፉፊያ አከባቢ ፕላን አዉርደዉ ድንጋይ መትከላቸዉን አብራርተዋል።

ኬሌ የኮሬ መገለጫ በመሆኑ ተባብረን ከሰራን በአጭር ጊዜ ዉስጥ ዉብና ጽዱ በማድረግ የኢንቨስትመንት ስበት ማዕከል ማድረግ እንደምቻል ተናግረዋል።

ከዉስጥ ፀጥታ አኳያ የተጀመረዉን ህግ የማስከበር ስራ አጠናክረዉ እንደሚቀጥሉ አንስተዉ፣ ህብረተሰቡ መረጃ በመስጠትና ማስረጃ በመሆን ከመንግስት ጎን በመቆም የበኩሉን መወጣት አለበት ሲሉ ገልፀዋል።

ከዉጭ ፀጥታ አኳያ አንፃራዊ ሠላም መምጣቱን ገልፀዉ፣ ዘላቂ ሰላም እንድመጣ ሁሉም የበኩሉን እንድወጣ አሳስበዋል።

የሀገር ሽማግሌዎችና የኃይማኖት መሪዎች ልማትንና ሰላምን የሚያደናቅፉ አካላትን እንድገስጹ ጥሪ አቅርበዋል።

የከተማዉ መንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት ክቡር አቶ ዮርዳኖስ ጭርዶ በበኩላቸዉ፣ አርሶ አደሩ ተጠቃሚ እንድሆን ፕላን ማዉረዳቸዉና ድንጋይ ማስተከላቸዉን ገልፀዋል።

ሆኖም የመሬት ደላላዉ ለባለይዞታዎች ካሣ እንደማይከፈል አድርጎ የዉሸት መረጃዎችን በህብረተሰብ ዉስጥ በማሰራጨት ልማቱን እያደናቀፈ መሆኑን ጠቅሰዉ፣ ህብረተሰቡ ከእነሱ ራሱን እንድጠብቅ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።

የኮሬን ባህል በማጠናከር ሰላምና ፀጥታ ማረጋገጥ እንደሚቻል አስረድተዋል።

በሌባ ላይ የተጀመረዉ ህግ የማስከበር ስራዉ ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ክቡር አቶ ዮርዳኖስ፣ ህብረተሰቡ ሮንድ በመጠበቅና ሌባን በማጋለጥ የድርሻዉን እንወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩም በዉስጥና በዉጭ ሰላምና ፀጥታን እና ልማት ላይ ተጋግዞ ለመስራት የጋራ መግባባት ተፈጥሮ መጠናቀቁን ከክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

በተጨማሪም የቪዲዮና ሌሎች መረጃዎቻችንን ለማግኘት የትክክለኛ አድራሻዎቻችን አባል በመሆን ይከታተሉ፡-
ዩቲዩብ- https://www.youtube.com/southradioandtelevisionagency
ቴሌግራም -https://t.me/southRadioAndTelevisionAgency
ዌብ ሳይት - https://srta.gov.et/
ትዊተር - https://twitter.com/SouthRadioandTv

የመገጭ የመስኖ ልማት ፕሮጀክት የሥራ ሁኔታ ግምገማ
07/11/2025

የመገጭ የመስኖ ልማት ፕሮጀክት የሥራ ሁኔታ ግምገማ

Address

Hawassa
Hawassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Radio and Television Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to South Radio and Television Agency:

Share