Ejjeetto Press

Ejjeetto Press Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ejjeetto Press, Broadcasting & media production company, Hawassa.

30/08/2023

የጋቦን መሪ የነበሩት አሊ ቦንጎ ባሰራጩት አጭር ቪድዮ "ወዳጆቼ... ታስሬያለሁ፣ ድምፅ አሰሙልኝ (make some noise)" ብለዋል።

ዌል... ምናልባት የአባታቸውን የ41 አመት ስልጣን የወረሱት አሊ ቦንጎ በቁም እስር ላይ ስላሉ ያላወቁት ነገር ቢኖር በርካታ ጋቦናውያን ከስልጣን መነሳታቸውን ተከትሎ በጎዳናዎች ላይ ወጥተው "የደስታ ድምፅ እያሰሙ" መሆኑን ነው።

በነገራችን ላይ የዛሬ አምስት አመት ገደማ ጋቦንን የመጎብኘት እድል አግኝቼ ነበር።

ከነዳጅ ምርት በሚገኝ ገንዘብ በአለም እጅግ ሀብታም ከሚባሉት ሀገራት ውስጥ የምትመደበው ጋቦን ህዝቧ ግን በከፋ ድህነት ውስጥ ይገኛል። በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ምስል በወቅቱ ያነሳሁት የፕሬዝደንቱ ቅንጡ ፅ/ቤት ሲሆን የቦንጎ ቤተሰብ በፈረንሳይ የበርካታ ቪላዎች እና ውድ ተሽከርካሪዎች ባለቤት ነው።

30/08/2023

#ጃውሳ ከአፄ ሀይለስላሴ የሊግ ኦፍ ኔሽን ንግግር እስከ አብርሀም ሊንከን የጌትስበርግ እወጃ፣ ከማርቲን ሉተር ኪንግ "I have a dream" ንግግር እስከ ኔልሰን ማንዴላ "I'm prepared to die" አባባል ለዜጎቻቸው እንዲሁም ለመላው የሰው ልጅ መነቃቃት እና የወደፊት ህልም ማሳክያ ሆነው አገልግለዋል።

እኛ ሀገር ደግሞ በተለይ አሁን አሁን "አዋቂዎች" እና "ሹመኞች" ተብለው የተቀመጡ አንዳንዶች ህዝብ የሚፈራረጅበትን እና ጊዜ እየጠበቀ የሚሰዳደብበትን ቃላት መራጭ እና አስተዋዋቂ መሆናቸውን ቀጥለዋል።

#ጃውሳ #ጁንታ #የቀንጅብ #ህጋዊድሀ #መጤ

16/08/2023

one

• አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ?

• የሲዳማ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ቢሮ ?

(ይህ መረጃ ከፋና የምርመራ ዘገባ የተወሰደና አዘጋጁ መርማሪ ጋዜጠኛ ሞሊቶ ኤልያስ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአንባቢያን ያሳውቃል)

(ፅሁፍ ዝግጅት በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ)

ጉዳዩ እንዲህ ነው...

ታህሳስ 7 /2015 ዓ/ም በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኘው አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል በተጓደሉ የህክምና ባለሞያዎች ምትክ የሰው ኃይል ለማሟላት የቅጥር ማስታወቂያ ያወጣል።

በዚህም ማስታወቂያ መሰረት 286 ጠቅላላ ሃኪም፣ 67 የላብራቶሪ ባለሞያዎች፣ 117 የመድሃኒት ቤት ባለሞያዎች ፈተናውን ለመውሰድ ይመዘገባሉ።

ተወዳዳሪዎች በግልፅና በይፋ በወጣ የፅሁፍ ፈተና ማስታወቂያ ጥሪ መሰረት ጥር 3/2015 ዓ/ም ላይ ፈተና ወስደዋል። የፅሁፍ ፈተናውን በአብላጫ ውጤት ያለፉት ተወዳዳሪዎች ውጤቱን አይተው የቃል ፈተና ወስደዋል። ያሉ ተወዳዳሪዎችም በግልፅ ተለጠፈ።

ሆስፒታሉ ከተመዘገቡት ውስጥ ብቁ ናቸው ያላቸውን በአጠቃላይ 16 የጤና ባለሙያዎች፦
👉 8 ጠቅላላ ሀኪም
👉 5 ፋርማሲስት
👉 3 የላብራቶሪ ባለሞያዎች ይፋዊ ጥሪ አቅርቦ ቅጥር ፈፀመላቸው።

ከዚህ ለኃላ ባለሞያዎቹ የወር ደመወዝ ተከፏለቸው፣ እስከ መጋቢት 13 ጥዋት ድረስ በስራ ላይ ከቆዩ በኃላ ስብሰባ አዳራሽ ትፈላጋላችሁ ተብለው ይጠራሉ።

ባለሞያዎቹ ኑ ሲባሉ የመሰላቸው የ " እንኳን ደህና መጣችሁ " ስነስርዓት ነበር ነገር ግን ያልጠበቁት ዱብእዳ ተናገራቸው። ይህም የቅጥር ሂደቱ ላይ የህገወጥነት ጥርጣሬ ስላለ ምርመራ እስኪደረግ መታገዳቸው ተገለፀላቸው። እግዱን የሚመለከት ደብዳቤም ተሰጣቸው።

የእግድ ደብዳቤው መጋቢት 13 በሆስፒታሉ የበላይ ኃላፊ የተፃፈ ነው። ጥርጣሬ አለኝ ሂደቱ መረምራለሁ ያለው የሲደማ ፐብሊክ ሰትቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ነው።

ቢሮው ምንድነው የሚለው ?

- ከቅጥሩ ህጋዊነት ጋር በተያየዘ ጥቆማ ደረሰን እሱን አጣራን።
- የማጣራት ስራው የተሰራው በአጣሪ ቡድን ተቋዉሞ ነው። ቡድኑ ሁለት ሰዎች ነው ያሉት።
- የማጣራት ስራው የፈጀው ሁለት ቀን ነው።

ይኸው አጣሪ ቡድን ከሁለት ቀን የመረጃ ማሰባሰብ ስራ በኃላ የቅጥር ሂደቱ " ህገወጥ ነው " በሚል የህክምና ባለሞያዎቹ ቅጥር መሰረዝ አለበት የሚል ምክረ ሃሳብ ለቢሮው አቅርበዋል።

በዚህ ጥናት መነሻ ቢሮው " የተፈፀመው የስራ ቅጥር ተሰርዟል ፤ በምትካቸው አዲስ ማስታወቂያ ይውጣና የሰው ኃይል ይቀጠር " የሚል ውሳኔ አሳለፈ።

የቢሮው አጥኚ ቡድን ጥናት በተደረገበት ወቅት ሆስፒታሉ ምንም መረጃ ሳይደብቅ ሰጥቶታናል በሚል ምስጋና አቅርቧል። እውነት ሆስፒታሉ የደበቀው ነገር የለም ?

ጥናቱ ሲፈተሽ...

ለምን ቅጥሩ እንዲሰረዝ ተወሰነ ?

ይኸው 2 አባላት ያሉት አጥኚ ቡድን ወደ ሆስፒታሉ ሄጄ ከ " ሰው ሃብት አ/ደ/የሥ/ሂደት " አገኘሁ እና አሰባሰብኩ ባለው መረጃ መሰረት ለቅጥሩ መሰረዝ ምክንያቶች ናቸው ያላቸው፦

1. የአዳሬ ጠቅላላ ሆስፒታል የቅጥር ኮሚቴ ሕጉን ጠብቆ ቢቋቋምም የህክምና ባለሞያዎቹ ቅጥር ሲፈፀም ከኮሚቴው ሰብሰቢ አቶ በረከት አመሎ በስተቀር ሌሎች አባላት አልተሳተፉም የሚል ነው።

፦ ይህ የጥናቱ ውጤት የተሳሳተ ሲሆን ባለሞያዎቹ ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት የቅጥር ኮሚቴ አባላት ተሰብስበው በፈተናው አሰጣጥ ሂደት ላይ የተወያዩበትና የምልመላ መስፈርቶችን በተመለከተ ውሳኔ ያሳለፉበት ቃለ ጉባኤ ሰነድ ተገኝቷል። በዚህም የኮሚቴው ሰብሰቢ እና ፀሀፊ ጨምሮ 9 አባላት ውሳኔውን በፊርማቸው አፅድቀዋል።

  SFPየሲፌፓ ፖለቲካዊ ፕሮግራም ህገ ደንብን እና አደረጃጀትን በተመለከተ ከጊዚያዊ አስተባባሪ ኮሚተ የተሰጠ አጭር መግለጫ፦================================ከአንዳንድ እጩ...
13/07/2022

SFP

የሲፌፓ ፖለቲካዊ ፕሮግራም ህገ ደንብን እና አደረጃጀትን በተመለከተ ከጊዚያዊ አስተባባሪ ኮሚተ የተሰጠ አጭር መግለጫ፦
================================

ከአንዳንድ እጩ አባላት የሲፌፓ ፖለቲካዊ ፕሮግራምና ህገ ደንብ እንዱሁም አደረጃጀቱ ይፋ እንዲደረግ እየተጠየቀ መሆኑ ታውቋል። ለዚህም የሚከተለው ማብራሪያ ተሰቷል።

ሲፌፓ ያገኘው ፈቃድ ጊዜያዊ ፈቃድ ነው። በጊዜያዊ ፈቃድ መስራት የሚቻለው ፓርቲውን ለማቋቋም የሚያስፈልጉ ስራዎችን ብቻ ነው። ህገደንብና ፕሮግራም እንዲሁም አደረጃጀቱ ይፋ የሚሆነው ፓርቲው በጠቅላላ ጉባኤ ከአፀደቀ ብቻ ነው። አሁን ዋናው ነገር የፓርቲውን አስፈላጊነት ተረድቶ ለእጩ አባልነት መመዝገብ ነው።

ነገር ግን ጊዜያዊ ኮሚቴ አባላቱ የፓርቲውን አስፈላጊነት፣የፓርቲውን ፖሊቲካል አቅጣጫና ለፕሮግራሙም ሆነ ለአደረጃጀቱ ፍንጭ የሚሰጥ ጠቅለል ያለ ፅፍፍ በገፃችን ገልፀን ነበረ። ከዚያ ውጪ ህገ ደንብ፣ፖለቲካ ፕሮግራሙና አደረጃጀቱ ይፋ የሚሆነው በጠቅላላ ጉበኤ ስፀድቅና ፓርቲውም ከምርጫ ቦርድ ሙሉ ፈቃድ ሲያገኝ ብቻ መሆኑን እንገልፃለን።

ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ

ለአስፈላጊ መረጃዎች ጌጹን ተከታተሉ!

  መዝገባ ተጀምረዋል!ተመዝገቡ እንመዝገብ በድሞክራስያዊ መንገድ ተደራጅተን ለህዝባችን ጥቅም እንታገል!
12/07/2022

መዝገባ ተጀምረዋል!
ተመዝገቡ እንመዝገብ በድሞክራስያዊ መንገድ ተደራጅተን ለህዝባችን ጥቅም እንታገል!

 ...Tenne yannara,   gashshootu dagate looso loosa agurre tenne kalaqantanni noo uurrinsha hiitto assine hunno yitanno u...
11/07/2022

...

Tenne yannara, gashshootu dagate looso loosa agurre tenne kalaqantanni noo uurrinsha hiitto assine hunno yitanno umi aana calla woxeno, wolqano yannano hunate gambooshshe assinanni millinsanni hee'noonita mashalaqqe iillitanni noonke.

Xa tenne yannara sidaamaho jawu jawu baarigaari hettisantanno politiku uurrinsha lekka asidhannokki gede sakaalate looso loosanno wolqa ikkitinota baalunku afe sharrama hasiisanno.

Tini dagate baarigaarimmate birxeeti!

Hedote Badooshshi kaayyote ikkinina bao dikkino.

yannate qineesaano sayiisino sokkaati!

09/07/2022
አስደሳች ዜና==============የ2022 ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ አሸናፊ አቶ ለገሰ ቦታሳ ዲካሌ ከሲዳማ ክልል መሆኑ ታውቋል።አቶ ለገሰ ቦታሳ የ2022 የካፕ ኦፍ ኤክሰለንሰ የቡና ጥራት ውድ...
09/07/2022

አስደሳች ዜና
==============
የ2022 ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ አሸናፊ አቶ ለገሰ ቦታሳ ዲካሌ ከሲዳማ ክልል መሆኑ ታውቋል።

አቶ ለገሰ ቦታሳ የ2022 የካፕ ኦፍ ኤክሰለንሰ የቡና ጥራት ውድድር ውጤት 90.69 ነጥብ በማስመዝገብ ነው በአንደኝነት ያጠናቀቀው።

በውድድሩ 40 ምርጥ ቡና አምራቾች በሀገር ደረጃ ለመጨረሻ ዙር አጓግ በሆነ መንገድ ተፎካክረዋል።

በዚሁ መሠረት ከፍተኛ 5ቹ ወይም ከ90 ነጥብ በላይ ያስመዘገቡት

1ኛ ለገሰ ቦታሳ ከሲዳማ ክልል
2ኛ ከነአን አሰፋ ዱካሞ ከሲዳማ ክልል
3ኛ አባ ተማም አባ ኦሊ ከኦሮሚያ ክልል
4ኛ ሳሙኤል በላቸው ከሲዳማ ክልል
5ኛ ቡቃቶ ዱጌ ከሲዳማ ክልል መሆናቸው ታውቋል።

presss

 !የሲዳማ ፌደራሊስት ፖርቲ (ሲፌፖ) ጊዜያዊ ፌቃድ አገኘ***************************************ሲዳማ ህዝብ ራስን በራስ ለማስተዳደር፣ ባህሉንና ቋንቋውን ለማሳደግ ከ1...
08/07/2022

!

የሲዳማ ፌደራሊስት ፖርቲ (ሲፌፖ) ጊዜያዊ ፌቃድ አገኘ
***************************************
ሲዳማ ህዝብ ራስን በራስ ለማስተዳደር፣ ባህሉንና ቋንቋውን ለማሳደግ ከ135 አመታት በፊት ጀምሮ ብርቱ ትግል ሲያደርግ የቆየ ታጋይ ህዝብ ነው። ክልል የመሆን ጥያቄውን በህዝቡ መራራ ትግል እውን ያደረገ ቢሆንም ራስን በራስ የማስተዳደር ህገመንግስታዊ መብቱ ግን በተገቢው እንዳልተመለሰ ተገንዝቧል።

በተግባር ደረጃ፣ አሁን ባለው ሀገራዊ ስረዓት፣ ክልሎች የሚተዳደሩት ከማዕከላዊ መንግስት ይሁንታ በሚሾመው ሀይል ነው። ይህ የሆነው በህገመንግስቱ የተደነገጉ የክልሎች ስልጣን ባለቤትነት/ሉአላዊነት / ሀገሪቱን እያስተዳደረ ባለው ገዢ ፓርቲ ማዕከላዊነት ምክንያት እየተሸረሸረ በመሆኑ ምክንያት እንደሆነ ተመልክቷል።

በተጨማሪም በክልሉ በፖለቲካዊ፣በኢኮኖሚያዊ፣በማህበራዊ፣በባህላዊና በፍትህ ዘርፎች ትክክለኛ መስመር አለመያዙን ተገንዝቧል። በተለይ ክልሉ ምክንያታዊ ያልሆኑ የስራ አጥነት ቀውስ፣ፍትህ እጦት፣ ሙስና፣ ጎሰኝነት፣ አድሎአዊ አሰራር፣ ጥሎ የማለፍ ፖለቲካ ስርዓታዊ (systemic) እየሆነ መጥቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የሲዳማ ህዝብ መሠረታዊ የትግሉ አላማ እውን ለማድረግና ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮች ለመቅረፍ ወቅቱ በሚፈልገው ደረጃ ህዝቡን አደራጅቶ የሚታገል ጠንካራ ተፎካካሪ ፖርቲ እንደሌለ ተገንዝቧል።

ስለዚህ የህዝባችን መሠረታዊ ጥያቄዎች ለመመለስ ወቅቱ በሚፈልገው ደረጃ ሁሉን የህብረተሰብ ክፍል ባቀፈ መልኩ የተደራጀ፣ ሲዳማዊ እሴቶችን መርህ ያደረገ፣ በዴሞክራሲያዊና የህዝብ ስልጣን ባለቤትነትን ተግባራዊ እንዲሆን የሚታገል፣ በሀሳብ ብዙሃነትና በመነጋገር የሚያምን፣ እውነተኛ ህብረብሔራዊ ፌደራሊዝም የሚከተልና እውን ለማድረግ ተመሳሳይ ዓላማ ካላቸው ሀገራዊ ፖርቲዎች ጋር የሚሰራ አንድ ክልላዊ የፖለቲካ ፖርቲ ማቋቋም አስፈላጊ ሆኗል።

በዚህም መሠረት "የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ)" የሚል ክልላዊ ፓርቲ ለማቋቋም ጊዜያዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ ጊዜያዊ ፈቃድ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አግኝቶ የማቋቋሙ ስራ እየሰራ ይገኛል።

በአሁኑ ጊዜ ኮሚቴው ሙሉ ፈቃድ ለማግኘት የሚያስፈልጉ ስራዎች እያጠናቀቀ ይገኛል። ኮሚቴው ጊዜያዊ ቢሮ በሀዋሳ ከተማ መናኸሪያ ክፍለ ከተማ አቶቴ ሰፈር በሹ ህንጻ አንደኛ ፎቅ ጊዜያዊ ቢሮ ከፍቶ እንዲሁም በተለያዩ ወረዳዎች በአስተባባሪዎች አማካይነት አባላትን እየመዘገበ ስለሆነ መታወቂያ በመያዝ እንዲትመዘገቡ ጥሪያችን እናቀርባለን።

የተደራጀ ትግለ ለዘላቂ ለውጥ!

08/07/2022

Address

Hawassa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ejjeetto Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share