ስንክሳር

ስንክሳር Ethiopian Synaxarium

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"

"የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል"
(አባ ጊዮርጊስ) ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንድት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን።

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።ሐምሌ 14 ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ➛ ዳግመኛም በዚሀች ዕለት የታላቁ አባ መቃርስና የሰማዕቱ የአሞን...
21/07/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።

ሐምሌ 14 ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡
➛ ዳግመኛም በዚሀች ዕለት የታላቁ አባ መቃርስና የሰማዕቱ የአሞንዮስ መታሰቢያቸው ሆነ፡፡

🔥 ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ

ትውልዱ ከኢየሩሳሌም ነው፡፡ የአባቱ ስም ክርስቶፎሮስ ነው ትርጓሜውም ‹‹ክርስቶስን የለበሰ›› ማለት ነው፡፡ አባቱም አማኝ ክርስቲያን ነበር፣ እናቱ ቴዎዶስያ ግን አስቀድማ ጣዖታትን ታመልክ ነበር፡፡ አባቱ በሞት ሲለየው እናቱ ከብዙ ገንዘብ ጋር ወደ አንጾኪያ ወሰደችው፡፡ በዚያም በእስክንድርያ ገዥ አድርጎ ይሾመው ዘንድ ልጇን ለከሃዲው ንጉሥ ለዲዮቅልጥያኖስ ከብዙ እጅ መንሻ ጋር ሰጠችው፡፡ ይኸውም አብሮኮሮንዮስ ከዲዮቅልጥያኖስ ጋር አብሮ አደግ ስለነበር አሁን በመስፍንነት ሾመው፡፡ ዲዮቅልጥያኖስም አብሮኮሮንዮስን ከሾመው በኋላ ‹‹ክርስቲያኖችን ሰብስበህ ግደል›› ብሎ አዘዘው፡፡
አብሮኮሮንዮስም በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ከተሾመ በኋላ ክርስቲያኖችን ሰብስቦ ለመግደል ከአንጾኪያ ከተማ እንደወጣ የሚያስፈራ ቃል ወደ እርሱ መጣና በስሙ ጠርቶት ‹‹ከሃዲው ዲዮቅልጥያኖስ እንዳዘዘህ ብታደርግ አንተ በክፉ አሟሟት ትሞታለህ›› አለው፡፡ አብሮኮሮንዮስም እጅግ ደንግጦ ‹‹ራስህን ትገልጥልኝ ዘንድ ጌታዬ ሆይ እለምንሃለሁ›› አለው፡፡ ወዲያውም የብርሃን መስቀል ታየው፡፡ ዳግመኛም ‹‹እኔ በኢየሩሳሌም የተሰቀልኩ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ እኔ ነኝ›› የሚል ቃል ሰማ፡፡ ይህንንም ከሰማ በኋላ ወደ አንጥረኛ ዘንድ ሄዶ በተመለከተው የብርሃን መስቀል ቅርጽ አድርጎ የወርቅ መስቀል አሠራ፡፡ ወደ እስክንድርያም ሲጓዝ በመንገድ ላይ ዐመፀኞች አረማውያን ሊገድሉት ሲሉ አሠርቶ በያዘው መስቀል ድል አደረጋቸው፡፡
እስክንድርያም ከደረሰ በኋላ እናቱ ‹‹በጦርነት ለረዱህና ላዳኑህ አማልክት መሥዋዕትን ሠዋ›› አለችው፡፡ ልጇ አብሮኮሮንዮስም ‹‹እኔስ አዳኝ በሆነ በመስቀሉ ኃይል ላዳነኝ ለእግዚአብሔር እሠዋለሁ›› አላት፡፡ እርሷም ወደ ዲዮቅልጥያኖስ መልእክት በመላክ ልጇ ክርስቲያን መሆኑን ነገረችው፡፡ ከሃዲውም ንጉሥ ጭፍሮቹን ልኮ ወደ ቂሣርያ ከተማ አስወሰደውና የቂሣርያውን ገዥ ስለ እርሱ እንዲመረምርና እንዲያሠቃየው አዘዘው፡፡
መኮንኑም ወደ እርሱ አቅርቦ በመረመረው ጊዜ አብሮኮሮንዮስ በጌታቸን ታመነ፡፡ መኮንኑም ለመሞት የሚያደርስ ብዙ ጽኑ ግርፋቶችን ከገረፈው በኋላ እሥር ቤት ውስጥ ጣለው፡፡ በዚያች ሌሊት ክብር ይግባውና ጌታችን በታላቅ ብርሃን ውስጥ ሆኖ ታየውና በቃሉ አጽናንቶት ሰማዕትነቱን በድል እንዲፈጽም ነገረው፡፡ ብርሃናዊ በሆኑ መለኮታዊ እጆቹም ዳስሶ ቁስሎቹን ሁሉ ፈወሰለት፡፡ ማሠሪያውንም ፈታለት፡፡ በማግሥቱም መኮንኑ አብሮኮሮንዮስ ሞቶ እንደሆነ እንዲያረጋግጡ ጭፍሮቹን ወደ እሥር ቤቱ ላካቸው፡፡ ከጽኑ ግርፋቱ የተነሣ አስቀድሞ የሞተ መስሎት ነበር፡፡ ጭፍሮቹም አብሮኮሮንዮስን ፍጹም ደህና ሆኖ ቢያገኙት እጅግ ተደንቀው ከእሥር ቤቱ በማውጣት በመኮንኑ ፊት አቆሙት፡፡ ንጉሡም ተደነቀ፡፡ በዚያ ያሉ ሁሉ ‹‹እኛ ሁላችን በአብሮኮሮንዮስ አምላክ አምነናል…›› እያሉ ጮሁ፡፡ ከእርሱም ጋር ሁለት የንጉሡ መኳንንትና ብዙ ሴቶች ነበሩ፡፡ ከሰማዕታቱም ውስጥ እናቱ ቅድስት ቴዎዶስያም ሌሎች ሴቶችና ወንዶች ሰማዕታትን አስከትላ ሰማዕትነቷን ፈጸመች፡፡ መኮንኑም የሁሉንም ራስ ራሶቻቸውን በሰይፍ አስቆረጣቸውና ሐምሌ 6 ቀን የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ፡፡
ቅዱስ አብሮኮሮንዮስን ግን ሦስት ቀን በእሥር አቆዩት፡፡ መኮንኑም ከዚያ አውጥቶ ለአጣዖታቱ እንዲሠዋ በድጋሚ አዘዘው፡፡ ቅዱሱም ‹‹ከጌታዬ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ አውቄያለሁ፣ ያንተ ጣዖታት ግን ከድንጋይና እንጨት በሰው እጅ የተሠሩ የማይጎዱ የማይጠቅሙ ራሳቸውንም ማዳን የማይችሉ ናቸው›› አለው፡፡ መኮንኑም እጅግ ተቆጥቶ ጎኖቹን በሰይፍ እንዲሰነጣጥቁት አዘዘ፡፡ አንዱም ጭፍራ እንደታዘዘው ጎኖቹን በሰይፍ ሊሰነጥቅ እጁን ሲዘረጋ ያንጊዜ እጁ ደረቀች፣ ወድቆም ሞተ፡፡ በዚህም ድጋሚ ተናደው በመሬት ላይ ጥለው በጽኑ ግርፋቶች ካሠቃዩት በኋላ ጎኖቹን በሰይፍ ሰንጥቀው በቁስሉ ውስጥ መጻጻ ጨመሩበትና እሥር ቤት ውስጥ ወረወሩት፡፡ በዚያም ሲሠቃይ ከቆየ ከሁለት ቀን በኋላ በጉድጓድ ውስጥ እሳት አንድደው በእሳቱ ውስጥ ወረወሩት፡፡ ጌታችንም አዳነውና ምንም እንዳልነካው ሆነ፡፡ ከዚህም በኋላ መኮንኑ ማሠቃየቱ በሰለቸው ጊዜ በመጨረሻ ራሱን በሰይፍ አስቆረጠውና የቅዱስ አብሮኮሮንዮስ የሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ 5 አክሊላትም ወርደውለታል፡፡ ጌታችንም ተገልጦለት ታላቅ ቃልኪዳን ከገባለት በኋላ ነፍሱን በክብር ተቀበላት፡፡ የቅዱስ አብሮኮሮንዮስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን።

🔥 ሰማዕቱ አባ አሞንዮስ

ጨካኙ አርያኖስ የክርስቲያን ደም እንደውኃ እያፈሰሰ ወደ እስና አገር በደረሰ ጊዜ ብዙ ሰዎች ተሰብስበው በአባ አሞንዮስ ሥር ተቀምጠው ሃይማኖትን ሲማሩ አገኛቸውና ሁሉንም ይዞ ገደላቸው፡፡ አባ አሞንዮስን ግን አሥሮ ወስዶ ለጣዖታቱ እንዲሰግዱና እንዲሠው አዘዛቸው፡፡ አባ አሞንዮስ ግን ‹‹ከንቱ የሆነ የእንቆቅልሽ ጨዋታህን ብላሽ የሆነ ነገርህንም መስማት አልወድም፣ የረከሱ ጣዖቶችህንም ማየት አልፈልግም›› ብለው ለመኮንኑ ለአርያኖስ መለሱለት፡፡ አርያኖስም በዚህ ጊዜ እጅግ በቁጣ ተመልቶ አባታችንን በሕይወት ሳሉ እሳት ውስጥ እንዲጣሉ አዘዘ፡፡ አባታችንም ወደ እሳቱ ውስጥ ከመጣላቸው በፊት እጅና እግራቸውን እንደታሰሩ ስለ አርያኖስ ጸለዩለት፡፡ ጸሎታቸውንም ከፈጸሙ በኋላ አርያኖስም ተመልሶ እርሱም ራሱ ሰማዕት እንደሚሆን በእርሱ ላይ ትንቢት ተናገሩ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ አሞንዮስ ወደ እሳቱ ተወርውረው ያማረ ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጸሙ፡፡ የድል አክሊልንም ተቀዳጁ፡፡ ሥጋቸውንም እሳቱ ከነደደበት ቦታ ባወጡ ጊዜ የእሳቱ ነበልባል ምንም አልነካቸውም ነበር፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡
በአባ አሞንዮስም ትንቢት መሠረት ጨካኙ መኮንን አርያኖስም በመጨረሻ ዘመኑ በጌታችን አምኖ ሰማዕት ሆኖ በክብር አርፎ የሰማዕትነት አክሊልን ተቀብሏል፡፡ የአባ አሞንዮስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን።

🔥 ታላቁ መቃርስ

መቃርስ (መቃርዮስ) ማለት ‹‹ቅዱሱ ለእግዚአብሔር›› ማለት ነው፡፡ ከደቡባዊ ግብፅ ከተወደዱ ደጋግ ክርስቲኖች የተገኘ ታላቅ አባት ነው፡፡ አባታቸው አብርሃም እናታቸው ሣራ ይባላሉ፡፡ እነርሱም መጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዳሉት እንደ አብርሃምና ሣራ እጅግ ደጎች ነበሩ፡፡ ልጅ ግን አልነበራቸውምና በስለት መቃርስን ወለዱ፡፡ ሲያድጉም በግድ ያለፈቃዳቸው ሚስት አጋቧቸው፡፡ አባ መቃርስ ግን ወደ ሙሽራይቱ በገቡ ጊዜ ዐውቀው እንደታመሙ ሆነው ተኙ፡፡ ‹‹ከበሽታዬ ለጥቂት ጊዜ ጤና ባገኝ ወደ ገዳም ልሂድ›› ብለው ወደ አስቄጥስ በረሃ ሄዱ፡፡ መልአክም ተገልጦ ‹‹ይህች አስቄጥስ የአንተና የልጆችህ ርስት ናት›› አላቸው፡፡ ወደ ቤተሰባቸውም በተመለሱ ጊዜ ሙሽራ እጮኛቸው በድንግልና እንዳለች ሞታ ደረሱ፡፡ ከጥቂት ቀንም በኋላ እናትና አባታቸውም ዐረፉ፡፡ እርሳቸውም ንብረታቸውን ሁሉ ለድሆች መጽውተው ገዳም ገቡ፡፡ ሕዝቡም ደግነታቸውንና እውነተኛነታቸውን አይተው ትንሽ ማረፊያ ሠርተው ሌሎች እንዲያገለግሏቸው አደረጉ፡፡
ከዕለታትም በአንድ ቀን አንዲት ሴት ልጅ ከጎረምሳ አርግዛ ሳለ ጎረምሳው ‹‹አባትሽ ሲጠይቅሽ ከአባ መቃርስ አረገዝኩ በይ›› ብሎ መከራትና ለአባቷ እንደተባለችው ተናገረች፡፡ ‹‹አባ መቃርስ በግድ ደፍረውኝ አረገዝኩ›› አለች፡፡ የከተማው ሰውም አባ መቃርስን ከበዓታቸው አውጥተው ለሞት እስኪደርሱ ድረስ ደበደቧቸው፡፡ መላእክትም በሰው አምሳል ተገልጠው ዋስ ሆነው ለልጅቷም ምግቧን ሊሰጡ ተስማምተው ወደ በዓታቸው መለሷቸው፡፡ አባ መቃርስም ለራሳቸው ‹‹መቃርስ ሆይ እንግዲህ ባለ ሚስትና ባለ ልጅ ሆነሃልና ሌሊትና ቀን መሥራት ይገባሃል›› እያሉ ቅርጫቶችን እየሠፉ ለሚያገለግላቸው ልጅ እየሰጡት እርሱ ሸጦ እያመጣ ብዙውን ለዚያች በዝሙት ጸንሳ በሳቸው ላሳበበች ሴት ይሰጡ ጀመር፡፡ መውለጃዋም በደረሰ ጊዜ እስከ 4 ቀን ድረስ በጽኑ ሥቃይ ቆየች፡፡ እውነቱንም ተናግራ ንስሓ በገባች ጊዜ ወደ አባ መቃርስ ዘንድ አደረሷት፡፡ ሕዝቡም ሁሉ ‹‹አባታችን ይቅር በሉን›› ብለው ከእግራቸው ላይ ሲወድቁ ይቅር ብለዋቸው ቀድሰው አቆረቧቸው፡፡
ከዚህ በኋላ መልአኩ ወስዶ አስቄጥስ ገዳም አደረሳቸው፡፡ የቅዱሳኑ የመክሲሞስና የዱማቴዎስ በዓት ወደ ሆነች ቦታም አስገብቶ በዚያ በልጆቻቸው ቦታ ላይ በዓታቸውን እንዲያጸኑ ነገራቸው፡፡ አባ መቃርስ ወደ አባ እንጦንስ ዘንድም በመሄድ በረከታቸውንና ምክራቸውን ይቀበሉ ነበር፡፡ ሰይጣናትም በእርሳቸው ላይ የሚያደርሱትን ክፉ ነገር ሲመካከሩ ይሰሟቸው ነበር፡፡ በእሳት እያቃጠሉ ፈተኗቸው፣ የዝሙት መንፈስ እያመጡም ፈተኗቸው፣ በዚህም ትዕግስትን ቢያደርጉ በሌላም ዓለማዊ ክብርን መውደድን፣ ትዕቢትን፣ መመካትን፣ ታካችነትን፣ ስድብን፣ ሃይማኖት ማጣትን፣ ተስፋ መቁረጥን በልባቸው አሳደሩባቸው፡፡ በአጋንንት ምክንያት ይህም እንደሚመጣባቸው አባ እንጦንስ አስቀድመው ነግረዋቸው ነበር፡፡ ወደ አባ እንጦንስም በመሄድ በአጋንንቱ የደረሰባቸውን ፈተናና ጾር ነገሯቸው፡፡ አባ እንጦንስም አመንኩሰው እንዲጸኑ በመምከር ወደ በዓታቸው ሸኟቸው፡፡ አንድ እርኩስ መንፈስ ያደረበት ባሕታዊ አግኝቶ ትንሣኤ ሙታንን አላምንም ቢላቸው ሙት አስነሥትው አሳይተው አሳምነውታል፡፡ ሙቱንም አጥምቀው አመንኩሰውት 7 ዓመት በተጋድሎ ኖሮ በሰላም ዐረፈ፡፡
አባ መቃርስ በበረሃ ውስጥ ራቁታቸውን ጌታችን ከብርዱም ሆነ ከሙቀቱ እየጠበቃቸው 40 ዘመን የኖሩ ጻድቃንን አገኟቸውና ‹‹እንደ እናንተ እንድሆን ምን ላድርግ?›› ቢሏቸው ‹‹ወደ በዓትህ ተመልሰህ ስለ ኃጢአትህ አልቅስ አንተም እንደ እኛ ትሆናልህ›› አሏቸው፡፡ አባ መቃርስም የጻድቃኑን በረከታቸውን ተቀብለው ወደ በዓታቸው ተመልሰው ማልቀስ ጀመሩ፡፡ ጻዲቁ በመጨረሻ ነፍሳቸውን መላእክት ሲያሳርጓት ይፈትኗቸው የነበሩ አጋንንት ‹‹መቃርስ ሆይ አመለጥከን አሸነፍከን…›› እያሉ ሲጮኹ አባ መቃርስም ‹‹እስከ ዛሬ ገና ነኝ፣ በጌታዬ በቀኙ ልቁም በግራው አላወኩምና›› ብለው በትሕትና መለሱላቸው፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን።

ምንጭ፦ የሐምሌ 1️⃣4️⃣ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 🍃🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔸https://m.facebook.com/MeseleNigatuDek0

ሐምሌ 1️⃣3️⃣ ቀን 2011 ዓ.ም

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።ሐምሌ 13 ነቢያት እየተገለጡለት ትንቢታቸውን የተረጎሙለትና የእጆቹም ጣቶች እንደፋና የሚያበሩለት የከበረ አባ ብስንድዮስ ዕረፍ...
19/07/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።

ሐምሌ 13 ነቢያት እየተገለጡለት ትንቢታቸውን የተረጎሙለትና የእጆቹም ጣቶች እንደፋና የሚያበሩለት የከበረ አባ ብስንድዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡
➛ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ሰማዕቱ ቅዱስ አሞን ምስክር ሆኖ ዐረፈ፡፡

🔥 አባ ብስንድዮስ

ቅዱሳት መጻሕፍትን በሙሉ ጠንቅቆ ያጠና በተጋድሎውም እጅግ የታወቀ መነኩሴ ነው፡፡ የነቢያትን መጻሕፍት ለጸሎት አንብቦ እስኪጨርስ ድረስ ትንቢቱን የሚያነብለት ነቢይ ይገለጥለትና የተሰወረውን ምሥጢር ይገልጥለት ነበር፡፡ የአባ ብስንድዮስ የእጆቹም ጣቶች እንደፋና ያበሩ ነበር፡፡ እግዚአብሔር በአባ ብስንድዮስ እጆች ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን አደረገ፡፡
አባ ብስንድዮስ በዕድሜው ዘመን ሁሉ የሴት ፊት አላየም፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን በሆዷ ውስጥ ታላቅ ደዌ የነበረባት አንዲት ሴት ነበረች፡፡ እርሷም ከአባ ብስንድዮስ በዓት በር ላይ ጠብቃ በድንገት አገኘችው፡፡ አባ ብስንድዮስም ባያት ጊዜ ትቷት ሮጠ፡፡ ሴቲቱ ብትከተለውም እንዳልደረሰችበት ባየች ጊዜ እግሩ የረገጣትን አንዲት አፍኝ አፈር ዘግና በእምነት ብትበላ ከደዌዋ ፈጥና ዳነች፡፡
በአንዲት ዕለትም ለአባ ብስንድዮስ ሦስት ሰዎች ተገለጡለትና ‹‹የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትመግባት አለህ›› ብለው መክፈቻ ቁልፍን ሰጡት፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ብስንድዮስ ቅፍጥ በሚባል አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ተሾመ፡፡ የቁርባን ቅዳሴ በሚቀድስ ጊዜ ጌታችንን እጆቹ በመሠዊያው ላይ ሆነው ይመለከተው ነበር፡፡ መላእክቶቹም በዙሪያው ቆመው ያያቸው ነበር፡፡ በሌላ ጊዜም አንድ ላይ ቄስ እየቀደሰ ሳለ በመሠዊያው ፊት ምራቁን ተፋ፡፡ ቅዳሴውም በተፈጸመ ጊዜ አባ ብስንድዮስ ያንን ቄስ ‹‹…የተፋኸው ምራቅ በመሠዊያው ዙሪያ በቆሙ በኪሩቤል ክንፎች ላይ እንደወደቀ አታውቅምን›› ብሎ ገሠጸው፡፡ ያን ጊዜም ያንን ቄስ መንቀጥቀጥ ያዘው ተሸክመውም ወ ቤቱ ወሰዱትና ታሞ ሞተ።
ቅዱስ አባ ብስንድዮስ አንደበቱ ጣዕም ያለው ነበር በሚያነብ፣ በሚያስተምርምና በሚመክርም ጊዜ አይጠገብም ነበር። ከዚህም በኋላ አባ ብስንድዮስ የዕረፍቱን ጊዜ ዐውቆ ሕዝቡን ጠርቶ በቀናች ሃይማኖት እስከመጨረሻ እንዲጸኑ ከመከራቸው በኋላ ነፍሱን ለእግዚአብሔር ሰጠ፡፡ የአባ ብስንድዮስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

አርኬ

ሰላም ለብስንድዮስ ዘይኔጽር ነቢያተ
እስከ ይፈጽም አንብቦ እንተ ጸሐፉ ትንቢተ
ወሰሚዓ ካዕበ ዘገብረ ትእምርተ
ብእሲት ጥዕየት እምደዌሃ ወሐይወት ሕይወተ
እምአሠረ እግሩ ቅድስት በሊዓ መሬተ።

🔥 ሰማዕቱ ቅዱስ አሞን

ይኸውም ቅዱስ ከደቡባዊ ግብጽ ከቡና አውራጃ የተገኘ ሰማዕት ነው፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገለጠለትና በጌታችን ስም ሰማዕት ይሆን ዘንድ እንዳለው አስረዳው፡፡ ቅዱስ አሞንም ወደ እንዴናው ገዥ በመሄድ በከሃዲው መኮንን በአውግስጦስ ፊት ቀርቦ በጌታችን ታመነ፡፡ መኮንኑም በመንኮራኩር ውስጥ ከቶ አሠቃየው፡፡ በእሳት ላይ በመጣል በእሳት በጋለ ብረት አስደበደበው፡፡ በውሽባ ቤት እሳት ማንደጃ ውስጥ በመክተት በእሳት አቃጠሉት፡፡ የእራሱንም ቆዳ ገፈው በራሱ ላይ የእሳት ፍሕም በማኖር በእጅጉ አሠቃዩት፡፡ እግዚአብሔርም ከመከራው ሁሉ አስታግሶት ያለ ምንም ጉዳት ጤነኛ አድርጎ አስነሣው፡፡ ጌታችንም በጎልማሳ አምሳል በብርሃን ሠረገላ ሆኖ ተገለጠለትና ‹‹ወዳጄ አሞን ሆይ እኔ ሁልጊዜ ከአንተ ጋር እኖራለሁ፣ ስምህን የሚጠራውን መታሰቢያህን የሚያደርገውን ገድልህን የሚጽፈውን ሁሉ እኔ በመንግሥቴ ውስጥ አስበዋለሁ›› ብሎ ሰላምታ ሰጥቶት በክብር ዐረገ፡፡
ቅዱስ አሞንም በሥጋው ሳለ ብዙ ታላላቅ ተአምራትን አደረገ፡፡ ብዙዎችንም ጌታችንን ወደማመን መለሳቸው፡፡ መኮንኑንም እርሱን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ የቅዱስ አሞንን ራስ በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ አዘዘ፡፡ ቅዱሱም ሰማዕትነቱን በድል ፈጽሞ የክብርን አክሊል ተቀዳጀ፡፡ ቅዱስ ዮልዮስም በዚያ ነበረና የቅዱስ አሞንን ሥጋ ወስዶ በመልካም ልብስ ገንዞ ከሁለት አገልጋዮቹ ጋር ወደ አገሩ ላከው፡፡ የቅዱሱም ሥጋ በላይኛው ግብጽ አሁንም ድረስ ብዙ አስደናቂ ተአምራትን እየሠራ አለ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ሰማዕት ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

አርኬ

ሰላም ለአሞን ለእግዚአብሔር ሐራሁ
እንተ ተካየዶ ኪዳነ በዘኢይሔሱ ቃለ አፉሁ
እለ ይነጽሩ ትዕግሥቶ ሶበ ኢደንገፁ ወኢፈርሁ
አነዳ ርእሱ በመጥባሕተ ጠብሑ
ወአፍሐሙ እሳት ዲቤሁ ወጥሁ።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ምንጭ፦ የሐምሌ 1️⃣3️⃣ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 🍃🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።

ወርኀዊ በዓላት

፩. እግዚአብሔር አብ
፪. ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት
፫. ዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት
፬. ቅዱስ አስከናፍር
፭. አሥራ ሦስቱ ግኁሳን አባቶች
፮. ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ ገዳማዊ
፯. አቡነ ዘርዐ ቡሩክ


ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ምንጭ፦ የሐምሌ 1️⃣3️⃣ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 🍃🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔸https://m.facebook.com/MeseleNigatuDek0

ሐምሌ 1️⃣2️⃣ ቀን 2011 ዓ.ም

.           ✝️  አልዕሉ አልባቢክሙ   ✝️በቅዳሴ ጸሎት ጊዜ ከሚታወጅ እና ከሚሰጡ መመሪያዎች አንዱ፤ ልቦናችንን ከፍ ከፍ እንድናደርግ ነው። ይኸው የልባችንን ናፍቆት፥ ሰማያዊውን የ...
19/07/2025

. ✝️ አልዕሉ አልባቢክሙ ✝️
በቅዳሴ ጸሎት ጊዜ ከሚታወጅ እና ከሚሰጡ መመሪያዎች አንዱ፤ ልቦናችንን ከፍ ከፍ እንድናደርግ ነው። ይኸው የልባችንን ናፍቆት፥ ሰማያዊውን የማያልቀውን ምስጋና እንድናስብ እና የዘለዓለምን ሕይወት ነሥተን ወደ ርስታችን እንድንገባ ነው።

👉 ዘለዓለማዊ ሕይወት እንዴት ይገኛል?

ለክርስቶስ አካል በሆነችው በቤተክርስቲያን በኩል። ይኸውም አማናዊውን የክርስቶስ ሥጋና ደም በመቀበል ነው።

“አልዕሉ አልባቢክሙ፤ በጥበበ እግዚአብሔር ንንሣእ ዘተውኅበ ለነ በጸጋ”

ልቦናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ፤ ወደ ሕይወት መድኃኒት እንቅረብ፤ ጸጋ ሆኖ የተሰጠንንም ሥጋውና ደሙን በእግዚአብሔር ጥበብ እንቀበል። (ቅዳሴ እግዚእ)

በማለት ሕይወት እንደሚገኝበት ይነግረናል። በዚህ የእግዚአብሔር ረቂቅነት ስለሚገለጥ ማለትም በሚታይ መቀበል የማይታይ ጸጋ ሕይወት ስለሚፈጸም፤ ምሥጢር ተብሎ ይጠራል። ለዚህም ነው በዚህ ምስጢር ያገኘነው ጸጋ እና ሕይወት ልዩ እንደሆነ ሲያመላክት በቅዳሴ መጨረሻው ላይ “ጸጋ ነሣእነ ወሕይወተ ረከብነ” ጸጋን ተቀበልን ሕይወትንም አገኘን! የምንለው። ይህን ስንፈጽም ዲያቆኑ “እትው በሰላም” በሰላም ግቡ ብሎ ወደ ናፈቅናት መንግሥት በልባችን እንድንገባ ያሰናብታል። (ከላይ ላለው ማብራሪያ “ዮሐንስ ፮፥፶፫-፶፰”)

👉 በብዎች ዘንድ ያለ አንድ አመለካከት አለ! ይኸውም አንድ ሰው ቅዱስ ቊርባን ከተቀበለ የሚያበቃለትና ታስሮ የሚኖር አድርገው ያስባሉ። ይህ ፍጹም ስህተት ነው የምንቀበለው ነጻ ለመውጣት እንጂ ለመታሰር አይደለም። በበደል ወድቀን እንዳንጠፋ እራሳችንን የምናድስበት ነው። ገላችን ሲቆሽሽ በውሃ እንደምናነጻው ሁሉ በንስሃ ታጥበን የምንለብሰው ሕይወት ነው።

👉 ቅዱስ ቊርባን የዕድሜ ገደብ እንዳለው የሚያስቡ ብዙዎች አሉ! ጥያቄ ምግብ ለመመገብ የእድሜ ገደብ አለው? የለውም መሠርታዊና ለመኖር አስፈላጊ ስለሆነ ሁሉም ይመገባል። ቅዱስ ቊርባንም በጣም አስፈላጊ ነው ሕይወትን ለማግኘት ሁሉም መቀበል አለበት። የዕድሜ ገደብ የለውም ለሁሉም የተሰጠ ጸጋ ነው። በተለይ በወጣትነት ላለ ሁሉ እርጋታን የሚሰጥ፣ ጥበብን የሚገልጥ፣ ማስተዋልን የሚጨምር እና በመልካም ጎዳና የሚመራ ነው። እንግዲህ ኑ ልባችንን ከፍ ከፍ እናድርግ።

“ብነ ኅበ እግዚአብሔር አምላክነ”
በአምላካችን በእግዚአብሔር ዘንድ አለን።

ቴሌግራም 👉 https://t.me/Synaxarium
ስንክሳር

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።ሐምሌ 12 ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ንጉሥ ሕዝቅያስን ረድቶ በትዕቢት እግዚአብሔርን የሰደበውን ንጉሥ ሰናክሬምንና 185,00...
19/07/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።
ሐምሌ 12 ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ንጉሥ ሕዝቅያስን ረድቶ በትዕቢት እግዚአብሔርን የሰደበውን ንጉሥ ሰናክሬምንና 185,000 ሠራዊቱን በአንዲት ሌሊት ጨርሶ በመግደል ታላቅ ተአምር ያደረገበት ዕለት ነው፡፡
➛ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት አባ ሖር ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡

🔥 አማላጅነቱ ለሁላችን ለጥምቀት ልጆች ይደረግልንና ሊቀ መልአክት ቅዱስ ሚካኤል ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡-

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን በዚህች ዕለት የመላእክት ሁሉ አለቃቸው የቅዱሳንም ረዳታቸው የሆነው ደጉ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ንጉሡን ሕዝቅያስን ግሩም በሆነ ተአምር ረድቶታል፡፡

ከጌታችን ልደት 700 ዓመታት በፊት ሕዝቅያስ የሚባል ንጉሥ በይሁዳ ላይ ነግሦ ነበር፡፡ ደጋጓቹ ነገሥታት ዳዊትና ሰሎሞን ካረፉ በኋላ የሕዝቅያስን ያህል ቅንና የእግዚአብሔር ሰው በእሥራኤል ላይ አልነገሠም፡፡ ንጉሡ ጣዖት አምልኮን ነቃቅሎ አጥፍቶ ሕዝቡ እግዚአብሔርን ብቻ እንዲያመልክ አድርጓል፡፡

ነገር ግን ቅዱስ ሕዝቅያስ በነገሠ በ14ኛው ዓመት የአሕዛብ (የአሦር) ንጉሥ ሰናክሬም በጠላትነት ተነሳበት፡፡ ወደ አካባቢውም መጥቶ ከቦ አስጨነቀው፡፡ ሰናክሬም በጦር እጅግ ኃይለኛ ነበር፡፡ የሠራዊቱም ብዛት ከ185,000 በላይ ነውና ንጉሥ ሕዝቅያስ እንደማይችለው ዐውቆ መልእክተኛ ላከበት፡፡ ‹‹ግብር እገብርልሃለሁ፣ የፈለግከውንም እሰጥሃለሁ፣ ነገር ግን ሀገሬን አታጥፋ፣ ኢየሩሳሌምን አታቃጥል፣ ሕዝቤንም አትግደል›› ብሎ ለመነው፡፡ እጅ መንሻ ግብሩንም ከከተማዋ የተገኘውን ወርቅና ብር ሁሉ ጭኖ ላከለት፡፡
ሰናክሬም ግን ሰይጣን ያደረበት ነውና የሕዝቅያስን ልመና በመናቅ አምላኩን እግዚአብሔርንም ተሳደበ፡፡ ‹‹ከእኔ እጅ የሚያድንህ ማነው? ሕዝቡንም እግዚአብሔር ያድናል ብለህ አታታልላቸው›› ሲል ላከበት፡፡ ሕዝቅያስም በዚህ ጊዜ የፈጣሪው ስም ሲሰደብ ሰምቷልና ፈጽሞ አዘነ፡፡

መልእክተኞችን ወደ ነቢዩ ቅዱስ ኢሳይያስ ልኮ እርሱ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ልብሱን ቀድዶ ማቅ ለበሰ፡፡ ስለ ኢየሩሳሌምና ሕዝቡም ፈጽሞ አለቀሰ፡፡ በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር የሰናክሬምን መገዳደርና የሕዝቅያስን ልመና ሰምቷልና ‹‹ስለ ባሪያዬ ስለ ዳዊት ከተማዋን አድናታለሁ›› ብሎ ለነቢዩ ኢሳይያስ ነገረው፡፡ ኢሳይያስም የእግዚአብሔርን መልእክት ለንጉሥ ሕዝቅያስ ነገረው፡፡

በዚያችም ሌሊት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከሰማያት በግርማ ወርዶ የሰናክሬምን 185 ሺውንም የጦር ሠራዊት በአንዲት ሌሊት በእሳት ሰይፉ ፈጅቷቸው አደረ፡፡ በለኪሶ የነበረው ሰናክሬምም በጧት ቢነሳ ሠራዊቱን ሁሉ የአስከሬን ክምር ሆኖ አገኘው፡፡ በታላቅ ድንጋጤ ሆኖ ወደ ነነዌ በመሄድ ወደ ጣዖት ቤቱ ሲገባ የራሱ ልጆች በሰይፍ ገደሉት፡፡ ትዕቢተኛው ሰናክሬምም ለአሕዛብ ሁሉ መዘባበቻ ሆነ፡፡

ቅዱስ ሕዝቅያስ ግን በፈጣሪው ታምኗልና ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ሞገስና ረዳት ሆኖታልና የዓለም ነገሥታት ሁሉ ፈሩት፣ እጅግ አከበሩትም፡፡ 2ኛ ነገ 18፡13፣ 19፡1፡፡

"በዚያችም ሌሊት የእግዚአብሔር መልአክ ወጣ፥ ከአሦራውያንም ሰፈር መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ገደለ፤ ማለዳም በተነሡ ጊዜ፥ እነሆ፥ ሁሉ በድኖች ነበሩ።"
(መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 19:35)

የሊቀ መልአክት ቅዱስ ሚካኤል አማላጅነቱ ለሁላችን ለጥምቀት ልጆች ይደረግልን።

🔥 ሰማዕቱ አባ ሖር

አባቱ ስርያቆስ በምትባል አገር ይኖር የነበረ አንጥረኛ ነው፡፡ ልጁን ሖርንም እግዚአብሔርን በመፍራት በሃይማኖት በምግባር አሳደገው፡፡ ጎልማሳ በሆነም ጊዜ ዘመነ ሰማዕታት ስለመጣ አባ ሖር በጌታችን ስም ሰማዕት ይሆን ዘንድ ፈርማ ወደምትባል አገር ሄደ፡፡ በዚያም በከሃዲው መኮንን ፊት ቀርቦ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡ መኮንኑም ይዞ በጽኑ አሠቃየው፡፡ ጌታችንም ከሥቃዩ ፈውሶት ተነሣ፡፡

ከሃዲ የነበረው መኮንንም ጌታችን ለአባ ሖር ያደረገለትን ታላቅ ተአምር አይቶ ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር በጌታችን አመነ፡፡ እርሱም በማመኑ በሌላ መኮንን ዘንድ በተራው ብዙ ተሠቃይቶ ከነቤተሰቡ በሰማዕትነት ዐረፈና በመንግሥተ ሰማያት የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ ይኽም ሌላኛው መኮንን አባ ሖርን ወደ እንዴና ላከው፡፡ በዚያም ከሃዲዎች በእጅጉ አሠቃዩት፡፡ በመንኮራኩር አበራዩት፣ ዘቅዝቀው ሰቅለው በእሳት በጋለ ብረት ደበደቡት፡፡ መኮንኑም አባ ሖርን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ የከበረች ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ ቅዱስ አባ ሖር አንገቱን ተሰይፎ የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጀ፡፡ የእርሱም ማኅበርተኞቹ የሆኑ 127 ወንዶችና 20 ሴቶች አብረውት ተሰይፈው የድል አክሊልን ተቀዳጅተዋል፡፡

የአባ ሖር ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ምንጭ፦ የሐምሌ 1️⃣2️⃣ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 🍃🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔸https://m.facebook.com/MeseleNigatuDek0

ሐምሌ 1️⃣1️⃣ ቀን 2011 ዓ.ም

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።ሐምሌ 11 ተአምረኛው ቅዱስ ዮሐንስና ደቀ መዝሙሩ የሆነ የወንድሙ ልጅ ቅዱስ ስምዖን በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡➛ ዳግመኛም በዚህች ...
18/07/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።
ሐምሌ 11 ተአምረኛው ቅዱስ ዮሐንስና ደቀ መዝሙሩ የሆነ የወንድሙ ልጅ ቅዱስ ስምዖን በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
➛ ዳግመኛም በዚህች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ ስምንተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ገብርኤል አረፈ።
➛ ዳግመኛም በዚህች ቀን በአስቄጥስ ገዳም የነበረ ቅዱስ አባት ኢሳይያስ መታስቢያው መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሰዋል።

🔥 ተአምረኛው ቅዱስ ዮሐንስ

እናቱ መካን ስለነበረች ቤተክርስቲያን ሄዳ ከተሳለች በኋላ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ በራእይ ተገልጦላት ልጅ እንደምትወልድ ነገራት፡፡ የሚያምር ወንድ ልጅ ስትወልድም ስሙን ዮሐንስ አለችው፡፡ ዮሐንስም አድጎ 11 ዓመት በሆነው ጊዜ የአባቱ በጎች እረኛ ሆነ፡፡ ምሳውንም ለድኆች እየሰጠ እስከማታ ድረስ ይጾም ነበር፡፡ አባቱ ይህን ሰምቶ አንድ ቀን ምሳውን ለድኆች እንደሰጠ ካረጋገጠ በኋላ ወደ ልጁ ሄዶ ‹‹ዛሬ ምሳህን አሳየኝ›› አለው፡፡ ዮሐንስም ፈርቶ ወደ መጠለያው ይዞት ገባና አገልገሉን ቢከፍተው በተአምራት በትኩስ እንጀራ ተመልቶ አገኘው፡፡ አባቱም ይህን ካየ በኋላ ጸጋ እግዚአብሔር እንዳደረበት ዐውቆ ‹‹ከእንግዲህ ወዲህስ በግ ጠባቂ አይደለህም›› በማለት ወስዶ ለቤተ ክርስቲያን ሰጠው፡፡
ዮሐንስም መጻሕፍትን ሁሉ ተምሮ ቅስና ሲሾም የወንድሙ ልጅ የሆነ ስምዖን በጎቹን ትቶ ደቀ መዝመሩ ሆነ፡፡ ዮሐንስም እጅግ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን ያደርግ ጀመር፡፡ ዜናውም በንጉሥ ማርያኖስ ዘንድ ተሰማ፡፡ ብቸኛ የሆነች አንዲት ሴት ልጁ በጽኑ ታማ ተኝታ ነበርና ገንዘቡን ሁሉ ለባለ መድኃኒት ሰጥቶ ነበር ግን አልዳነችለትም፡፡ ከንጉሡም ወታደሮቹ አንዱ ዮሐንስ የሚባል ጻድቅ የአንዱን ወታደር ዕውር ዐይኑን እንዳበራለት ነገረው፡፡ ንጉሡም ወደ ዮሐንስ ጭፍራውን ልኮ ወደ እርሱ እንዲመጣና ልጁን እንዲፈውስለት መልእክት ላከበት፡፡ ዮሐንስም ይህንን አስቀድሞ በመንፈስ ዐውቆ በደመና ተጭኖ አንጾኪያ ደረሰና ንጉሡ መኝታ ቤት ተገኘ፡፡ ንጉሡም መናፍስት መስሎት እጅግ ሲደነግጥ ‹‹መልእክተኛህን ልከህ ልታስመጣኝ የተመኘኸው ሰው ዮሐንስ ነኝ›› ብሎ አረጋጋውና በልጁ ላይ አድሮ የነበረውን ከይሲ አውጥቶ ፈወሳት፡፡ የቤተ መንግሥቱም ሰዎች ከእርሱ ተባረኩ፡፡
ከዚህም በኋላ ንጉሡ ብዙ ገንዘብና ንብረት ሲሰጠው ቅዱስ ዮሐንስ ግን ምንም ነገር አልተቀበለውም፡፡ ተመልሶ ሊሄድም ሲል ንጉሡ የልብሱን ጫፍ ይዞ እንዳይሄድ ለመነው፡፡ ያመጣችው ደመናም ነጥቃ ስትወስደው የልብሱ ቁራጭ በንጉሡ እጅ ላይ ቀረችለት፡፡ ንጉሡም ቤተ ክርስቲያን ሠርቶ የልብሱን ቁራጭ ወስዶ በውስጧ አኖራት፡፡ በእርሷም ብዙ ድንቅ ተአምራት ተደረጉ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በቍርባን ጊዜ ያልተገባቸውን ሰዎች ለይቶ ያውቃቸውና በቅድሚያ ንስሓ ይሰጣቸው ነበር፡፡ ዮሐንስም የነበረበት ዘመን ከሃዲውና አረመኔው ዲዮቅልጥያኖስ በነበረበት ዘመን ነበርና መኰንኑን ልኮ ቅዱስ ዮሐንስንና የአባቱ ወንድም ልጅ የሆነውን ረድኡን ስምዖንን አሳሰራቸው፡፡ እጅግ ጽኑ ሥቃይንም አሠቃያቸው፡፡ በመጨረሻም ሐምሌ 11 ቀን አንገታቸውን በሰይፍ ቆረጠውና የሰማዕትነት ፍጻሜያቸው ሆነ፡፡
የሰማዕታቱ የቅዱስ ዮሐንስና የቅዱስ ስምዖን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።

አርኬ
ሰላም ለዮሐንስ ንጹሕ እምአበሳ። ምስለ ሰምዖን በስምዕ ለመንግሥተ ሰማይ ዘኃሠሣ። ደመና ተጽዒኖ አምሳለ እንስሳ። አውጽአ ከይሴ ለወለተ ንጉሥ እምከርሣ። ወለዐይነ ገብር ዕውርት በእዴሁ ፈውሳ።


🔥 ዳግመኛም በዚች ቀን በአስቄጥስ ገዳም የነበረ ቅዱስ አባት ኢሳይያስ መታሰቢያው ነው በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።


አርኬ
ሰላም ለከ ኢሳይያስ ቀሲስ። ወግኁሥ ባሕታዊ ዘደብረ መቃርስ። ከመ አአምኅከ ዘልፈ በመሥዋዕተ ስብሐት ሐዲስ። አጒይይ እከይየ በመንፈስ ቅዱስ። እስመ ለኃጥእ ተብህለ መሥዋዕቱ ርኲስ።


🔥 ዳግመኛም በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ ስምንተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ገብርኤል አረፈ።

የዚህ ቅዱስ ወላጆች በእግዚአብሔር ሕግ የጸኑ ደጋጎች ፈቃዱንና ትእዛዙንም የሚፈጽሙ ነበሩ።

ይህንንም ቅዱስ በወለዱት ጊዜ በፈሪሀ እግዚአብሔር አሳደጉት። በአንዲት ዕለትም ቅዱሳን መነኰሳት ወደርሱ መጡ ከውስጣቸውም መልካም ገድል ያለው አንድ አረጋዊ ነበረ። እርሱም ብዙዎች ኤጲስቆጶሳት ሕፃኑን ከበው እጃቸውን እንደሚጭኑበት እንደሚባርኩትና ይሁን ይሁን ይገባዋል እንደሚሉ ራእይን አየ።

ሽማግሌውም ይህን ራእይ በአየ ጊዜ ሕፃኑ ታላቅ እንደሚሆን አሰበ ለአባቱም ይህን ሕፃን አስተምረው ለብዙዎች ሕዝቦች አለቃ ይሆን ዘንድ አለውና አለው። አባቱም ሰምቶ እግዚአብሔርን አመሰገነው ከዚህ ሕፃን ምን ይደረግ ይሆን አለ።

ሕፃኑ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን ፈቃድ አባቱ አረፈ ብህና በሚባል አገርም ገድሉ የተደነቀ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትን ብሉያትንና ሐዲሳትንም የሚያውቅ የእናቱ ወንድም ስሙ ጴጥሮስ የሚባል ኤጲስቆጶስ ነበረ ሕፃኑንም ወስዶ አስተማረው ከተሰጠውም ጸጋና ከዕውቀቱ የተነሣ ያዩት ሁሉ ያደንቁ ነበር ዲቁናም ተሾመ።

ዐሥራ ሁለት ዓመትም በሆነው ጊዜ የምንኵስናን ልብስ ሊለብስ ወደደ ይህንም ኃላፊውን ዓለም ናቀ ኤጲስቆጶሱ አባ ጴጥሮስም በገድል ተጸምዶ ለሚኖር ለቀሲስ አባ ጴጥሮስ ሰጠው እርሱም በጥቂት ቀኖች የምንኵስናን ገድል አስተማረው ከእርሱም ብዙ ትሩፋቶች ታዩ።

ከዚህም በኋላ መምህሩ ቀሲስ አባ ጴጥሮስ በአረፈ ጊዜ ከዚያ ተነሥቶ ወደ አባ እንጦንስ ገዳም ሔደ በዚያም በጾምና በጸሎት በስግደት በመትጋት እየተጋደለ ያለ ማቋረጥ ብዙ ዘመናት ኖረ።

ከዚህም በኋላ ወደ አስቄጥስ ገዳም ወደ አባ መቃርስ ደብር ሔደ። በደብረ ማርስ ባለች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን አበምኔት አደረጉት ሕንፃዋንም አደሰ።

ከዚህም በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ሒዶ ከቅዱሳት መካናት ተባረከ በዚያም በቅድስት ትንሣኤ በተሰየመች ቤተ ክርስቲያን በጳጳሱ በአባ ሚካኤል እጅ ቅስና ተሾመ። ከዚያም ወደ ምስር አገር ተመልሶ በማዕልቃ ባለች በእመቤታችን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍትን እየጻፈ ተቀመጠ።

በዚያም ወራት ሉቀ ጳጳሳቱ አባ ቄርሎስ አረፈ። የወንጌላዊው የማርቆስ መንበርም ያለሊቀ ጳጳሳት ነበር። ስለዚህም ኤጲስቆጶሳት፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ሕዝቡ ሁሉ ተሰብስበው ይሾሙት ዘንድ በአንድ ምክር ተስማሙ ሰይጣን ግን ክፉዎች ሰዎችን አነሣሥቶ ተቃወሙት። ሹመቱንም አልፈቀዱም። ነገር ግን መንፈሳዊ አባት የነበረውን የከሊል ልጅ አባ አትናቴዎስን ሾሙት። እርሱም መንጋውን በበጎ አጠባበቅ ጠበቀ።

እርሱም በአረፈ ጊዜ ኤጲስቆሳትና የሕዝብ አለቆች ዳግመኛ ተሰበሰቡና በእጃቸው ጽፈው አባ ገብርኤል እንዲሾም ፈቀዱ ሁለተኛም በሕዝቡ መካከል ሁከት ተነሣ ከሌሎችም ጋራ ዕጣ ያጣጥሉት ዘንድ ተስማሙ ስሞቻቸውንም ጽፈው በመንበሩ ላይ አኖሩ በላዩም እየጸለዩና እየቀደሱ ሦስት ቀኖች ሰነበቱ። ከዚህም በኋላ ታናሽ ብላቴና አምጥተው በውስጡ የአባ ዮሐንስ ስም ያለበትን ክርታስ አወጣላቸው። ያም አባ ዮሐንስ ተሾመ። ይህን አባ ገብረኤልን ግን ለማዕልቃ ቤተ ክርስቲያን ተከራካሪ አድርገው ሾሙት።

በዚያ ወራትም በግብጽ ቤተ ክርስቲያን ላይ ችግር ሁኖ ነበር። ይህ አባ ገብርኤልም ወደ አባ እንጦንስ ገዳም ሒዶ በጾምና በጸሎት በስግደትም በቀንና በሌሊት ሲጋደል ኖረ። ከቅዱሳን መነኰሳትም ብዙዎች መልካም ራእይን አዩለት ከእርሳቸው በእስክንድርያ ከተማ የሊቀ ጳጳሳት ልብስን እንደሚአለብሱት ብዙዎች ከአሕዛብ የተመለሱ ክርስቲያኖችም እንደሚያጅቡት ያየ አለ። ደግሞም ይሾምባት ዘንድ ወደ አስቄጥስ ወደ አባ መቃርስ ገዳም ሲሔድ ያየለት አለ። ቁጥር የሌላቸውንም መክፈቻዎችን ሲቀበል ያዩ አሉ።

ከገዳሙም ሊወርድ ብዙ ጊዜ ይሻ ነበር ነገር ግን አልተቻለውም። ከዚህ በኋላ አባ እንጦንስ በራእይ ተገልጦ እንዲህ አለው ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ ከዚህ ገዳም ትወርድ ዘንድ እኔ አልፈቅድም ጊዜው ሳይደርስ አትውረድ አለው።

ከሦስት ዓመት በኋላም አንዱ አረጋዊ የከበረ መልአክ እንግዲህስ አባ ገብርኤልን ወስደው በእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ጵጵስና ይሾሙታል እያለ እንደሚያነጋግረው ራእይ አየ። በዚያችም ቀን የሀገረ እንጣፊ መኰንን መጣ ከእርሱም ጋር ብዙዎች መሳፍንቶች ነበሩ። አባ ገብርኤልን አምጥተው በእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ የሚያዝዝ የንጉሥ ደብዳቤም ከእርሱ ጋር ነበረ።

ከዚህም በኋላ ያለ ፈቃዱ ወስደው በወንጌላዊው በማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስናን ሾሙት። በዚያችም ቀን እርሱ ለኢየሩሳሌም አንድ ጳጳስና ሌሎችንም ኤጲስቆጶሳት ቀሳውስትንና ዲያቆናትንም ሾመ። ከዚህም በኋላ ሦስት ጊዜ ሜሮን አከበረ ባረከ እንደዚህም አድርጎ አንድ ዓመት ከአንድ ወር ኖረ።

በዚያን ጊዜም አባ እንጦንስ ተገልጦ እንዲህ አለው እነሆ ዕረፍትህ ቀርቦአል ከዐሥራ ስምንት ወሮች በኋላ ወደ እግዚአብሔር ትሔዳለህ የዘላለም ሕይወትንም ትወርሳለህ።

ከዚህም በኋላ በክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራ ሆነ። ይህም አባት ወገኖቹን ያድን ዘንድ ወደ ጌታችን ለመነ ክብር ይግባውና ጌታችንም ልመናውን ተቀብሎ ሕዝቡን ይቅር አለ።

ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱ ከመንበረ ሢመቱ ወጥቶ በምስር አገር ዓመት ሙሉ ተሠወረ። ከአንድ ምእመን በቀር ማንም አላወቀበትም በቀንና በሌሊት በገድል ከመቀጥቀጡ የተነሣም መልኩ ተለወጠ ሥጋውም ደረቀ።

ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር እርሱን ለሚፈራው ለአንድ ምእመን ሥራውን ገለጠ። እርሱም ከዚያ ቦታ አውጥቶ በሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን አስቀመጠው በጸሎትና በቅዳሴ እያገለገለ ኖረ። ድኆችንም ይጐበኛቸው ነበር። የሚሹትንም ይሰጣቸው ነበር። ወደ ርሱ የሚመጡትንም ሕዝቦች ያስተምራቸውና ያጽናናቸው ነበር።

በአንዲት ዕለትም ሊቀ ጳጳሳት አባ አትናቴዎስ በግልጽ ታየው እንዲህም አለው ስለዚህ ፈጽሞ አትዘን ከዚህ ብዙ ድካምና መከራ እግዚአብሔር ያሳርፍሃልና አነሆ ምድራዊ ኑሮህን የሚፈጽም ደዌ በአንተ ላይ ይመጣል ነገር ግን ደስ ይበልህ ታላቅ የሆነ የእግዚአብሔርን ጸጋ ተቀብለሃልና። የዘላለም ሕይወትንና የማያልቅ ተድላ ደስታንም ትወርሳለህና አለው።

በዚያን ጊዜም በሚያስጨንቅ ደዌ ታሞ እየተጨነቀ ኖረ። ስለ ነፍሱም መውጣትና በእግዚአብሔር ፊት ስለ መቆሙ ይፈራና ይደነግጥ ነበር የእመቤታችን ማርያም ሥዕልም በዚያ ነበረ። ወደርሷም አዘውትሮ ይማልድ ነበረ በዚያን ጊዜም ክብር ይግባውና ራሱ እግዚአብሔር በብሩህ ገጽ ተገለጠለት መንግሥተ ሰማያትን አግኝተሃልና ደስ ይበልህ እንጂ አትፍራ እስከ ሦስት ቀንም ከዚህ ከኃላፊው ዓለም ትወጣለህ በማለት አረጋጋው። ይህንንም ብሎ ከእርሱ ተሠወረ በሦስተኛውም ቀን በሰላም አረፈ። በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያንም በታላቅ ክብር ተቀበረ።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን አኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።


አርኬ
ሰላም ለከ ብእሲ መስተጋድል። ሊቀ ጳጳሳት ገብርኤል። አመ አደንገዐከ ሞት በሰዓተ ሰይል። ሰማዕከ ቃሎ እምሥዕላ ለወልደ ማርያም ድንግል። መንግሥተ ሰማያት ነሣእከ ኢትፍራህ ዘይብል።

" ሒዳችሁም መንግሥተ ሰማያት ቀርባለች ብላችሁ ስበኩ። ድውዮችን ፈውሱ: ሙታንን አንሱ፣ ለምጻሞችን አንጹ፣ አጋንንትን አውጡ። በከንቱ ተቀብላችሁ በከንቱ ስጡ። ወርቅ፣ ወይም ብር፣ ወይም ናስ በመቀነታችሁ ወይም ለመንገድ ከረጢት ወይም ሁለት እጀ ጠባብ ወይም ጫማ ወይም በትር አታግኙ። ለሠራተኛ ምግቡ ይገባዋልና። (ማቴ. 10 ፥ 7)

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ምንጭ፦ የሐምሌ 1️⃣1️⃣ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 🍃🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔸https://m.facebook.com/MeseleNigatuDek0
https://www.facebook.com/meselenigatudeko

ᴍᴇsᴇʟᴇ ɴɪɢᴀᴛᴜ ᴅᴇᴋᴏ
ሐምሌ 1️⃣0️⃣ ቀን 2011 ዓ.ም

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።ሐምሌ 10 ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል (ስምዖን ቀለዮጳ) ዕረፍቱ ነው፡፡➛ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ልደታቸው ነው፡፡➛ በውኃ ...
17/07/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።

ሐምሌ 10 ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል (ስምዖን ቀለዮጳ) ዕረፍቱ ነው፡፡
➛ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ልደታቸው ነው፡፡
➛ በውኃ ጉድጓድ ውስጥ ቆሞ ሲጋደል የኖረውና መላእክትም ይጎበኙትና ዘጠኝ ክንድ ያህል በሠረገላ ከፍ ከፍ ያደርጉት እንደነበር ስንክክሳሩ በስም የጠቀሰው አባ ብስንዳ ዕረፍቱ ነው፡፡

➛ቅድስት ቴዎና በሰማዕትነት ዐረፈች፡፡
ይኽችውም ቅድስት ከሐዋርያው ስምዖን ቀለዮጳ ጋር በሰማዕትነት ያረፈች ናት፡፡

🔥 ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ

ሐዋርያው ናትናኤል በሌላኛው ስሙ ስምዖን እየተባለም ይጠራል፡፡ ናትናኤል ብሎ የሰየመው ጌታችን ነው፡፡ የተወለደው በናዝሬት ቃና ዘገሊላ ሲሆን ከነገደ ብንያም ነው፡፡ የትውልድ ዘመኑ ጌታችን በተወለደበት ዘመን አካባቢ ነው፡፡ ምክንያቱም ሄሮድስ ዕድሜአቸው ከሁለት ዓመት በታች የሆኑ የቤተልሔም እልፍ ሕፃናትን በሚያስፈጅበት ጊዜ የናትናኤል እናቱ ከበለስ ሥር ደብቃ አትርፋዋለች፡፡ ሐዋርያው ፊሊጶስ ናትናኤልን ጠርቶት ወደ ጌታችን ካመጣው በኋላ ናትናኤል ጌታችንን ‹‹ወዴት ታውቀኛለህ?›› ሲለው ጌታችንም ‹‹ፊሊጶስ ሳይጠራህ ከበለስ ሥር ሳለህ ዐውቅሃለሁ›› በማለት ከሕፃንነቱ ጀምሮ የጠበቀው አምላኩ እርሱ መሆኑን ነግሮታል፡፡ ቅዱስ አውግስጢኖስ ናትናኤል ምሁረ ኦሪት እንደነበር ጠቅሷል፡፡ ምክንያቱም ፊሊጶስ ሲጠራው ‹‹ከናዝሬት መልካም ነገር አይወጣም›› በማለት የነቢያትን ቃል የጠቀሰው የመጻሕፍትን ቃል በማወቁ ነው፡፡ ዮሐ 11፡44-52፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል በባቦሎን፣ በሶርያ፣ በግብፅና በኑቢያ እየተዘዋወረ ወንጌልን ሰብኳል፡፡ ብዙውን የአገልግሎት ጊዜውን ያሳለፈው በሰሜን አፍሪካ ነው፡፡ በግብፅ ሲያስተምር አማኞች በመብዛታቸው አረማውያን ቀኑበትና በሐሰት ‹‹ሕዝቡ የማይፈልገውን ሃይማኖት ያስተምራል›› ብለው በከንቱ ከሰሱትና ከንጉሡ ፊት ለፍርድ አቅርበው በሐሰተኞች አስመስክረው ሐምሌ 10 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆርጠውት ሰማዕትነቱን በክብር ፈጽሞ የድል አክሊልን ተቀዳጅቷል፡፡ የሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን።

🔥 ጻዲቁ አቡነ ሳሙኤል

እንድርያስና አርሶንያ ከሚባሉ የበቁ ደጋግ አባትና እናታቸው የተወለዱት በሸዋ ሀገረ ስብከት በቀድሞ ጽላልሽ ዛሬ ቡልጋ በሚባለው አውራጃ ነው፡፡ የወላጆቻቸው በጎ ምግባርና ሃይማኖት ቅዱስ ተክለሃይማኖትን ከደብረ ሊባኖስ አነሣስቶ በቤታቸው ሄደው እንዲስተናገዱ አድርጓል፡፡ ልጅ ስላልነበራቸው ያዝኑ ነበርና አቡነ ተክለሃይማኖትም በጸጋ እግዚአብሔር ተገልጾላቸው ‹‹እግዚአብሔር ጣዖታትን የሚሰብር፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኃጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ›› ብለው ትንቢት ነግረዋቸዋል፡፡ በትንቢቱም መሠረት አቡነ ሳሙኤል ሐምሌ 10 ቀን 1248 ዓ.ም ሲወለዱ መልካቸው በአራት ልዩ ልዩ ሕብረ መልክ እየተለዋወጠ አንድ ጊዜ እንደ በረዶ፣ አንድ ጊዜ እንደ እሳት፣ አንድ ጊዜ እንደ ልምላሜና ቢጫ ሆነው ታይተዋል፡፡ አቡነ ተክለሃይማኖትም በአባቱ እንድሪያስ በኩል የሥጋ ዘመዱ ሲሆኑ የመንፈስ ቅዱስም አባት ሆኑትና በ40 ቀን ክርስትና አንስተው ስመ ክርስትናቸውን ‹‹ሳሙኤል›› አሉት፡፡ ትርጓሜውም ‹‹እግዚአብሔር ጸለቴን ሰማኝ›› ማለት ነው፡፡ ዳግመኛም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከሕፃንነት ጀምረው በምግባር በሃይማኖት ኮትኩተው አሳድገው ለዲቁና አብቅተው በኋላም አመንኩሰውታል፡፡ የአባታችን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን።ይክፈለን።ረድኤት በረከቱ ይደርብንና በዚኽች ዕለት ሐምሌ 10 ቀን በዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ ታስቦ የሚውለው ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡- የከበሩ ሐዋርያት ዓለምን በዕጣ ከተከፋፈሉ በኋላ ቅዱስ ናትናኤል ወደ ሰማርያ ሔደ፡፡ በዚያም የከበረች ወንጌልን በማስተማር ብዙዎችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት እንዲያምኑ አደረጋቸው፡፡ ይኽንንም ያዩ ክፉዎች በክፋት ተነሱበትና በጽኑ ድብደባ ካሰቃዩት በኋላ ከከተማው ውጭ ጎተቱት፡፡ ነገር ግን ሐዋርያው ዳግመኛ ወደ እነርሱ ተመልሶ በመካከላቸው ቆመ፡፡ በዚያም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እያስተማረ ለሦስት ቀን ቆየ፡፡
ከዚኽም በኋላ በሦስተኛው ቀን መጨረሻ አንድ ጎልማሳ ታመመና ሞተ፡፡ አባቱም ባለጸጋ ነበርና ስለ ልጁ ሞት እጅግ አዘነ፡፡ ከአገልጋዮቹም ውስጥ አንዱ ወደ አባቱ ሄዶ ‹‹የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያው እነሆ ከዚህ አለ፣ እርሱን ጥራውና በጸሎቱ የሞተውን ልጅህን ያስነሣልሃል‹‹ አለው፡፡ ባለጸጋውም ቅዱስ ናትናኤልን አስጠራውና በሞተ ልጁ ላይ እንዲጸልይለት ለመነው፡፡ ቅዱስ ናትናኤልም ከሞተው ጎልማሳ አጠገብ ቆሞ አባቱን ‹‹አይሁድ በሰቀሉት በእግዚአብሔር ልጅ ካመንክ የእግዚአብሔርን ተአምር ታያለህ›› አለው፡፡ ባለጸጋውም ‹‹የሞተው ልጄ ሕያው ሆኖ ከተነሣ ድኖም ካየሁት የተሰቀለው እርሱ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ አምናለሁ›› አለው፡፡ ሐዋርያውም በዚህ ጊዜ ‹‹በጴንጤናዊው በጲላጦስ ፊት የተሰቀልክ በተቀደሰው ስምህ እንዳስተምር ለዚህ ተግባር የመረጥከኝ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ!....›› እያለ ፊቱን መልሶ ረጅም ጸሎት ጸለየ፡፡ በጸሎቱም መጨረሻ ‹‹… ዛሬም በፈቃድህ ወደሞተው ወደዚህ ጎልማሳ ተመልከት፤ ይነሣና ስምህን ያመሰግን ዘንድ እዘዝ፣ በዚኽች አገር ያሉ ሕዝቦች ሁሉ በስምህ ያምኑ ዘንድ›› አለ፡፡ ቅዱስ ናትናኤል ይህንን በተናገረ ጊዜም ጎልማሳው ወዳለበት ቦታ ፊቱን መለሰ፡፡ ‹‹በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተነሥና ቁም ከዚህ የተሰበሰቡት ሁሉ ምስጋና ይግባውና በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ያምኑ ዘንድ›› አለ፡፡ ወዲያውም የሞተው ጎልማሳ ዐይኖች ተከፈቱ፡፡ ተነሥቶም ቆመ፡፡ የሚበላውንና የሚጠጣውንም ያመጡለት ዘንድ ሐዋርያው አዘዘ፡፡
የተሰበሰቡትም ሰዎች ሁሉ ይኽንን ድንቅ ተአምር ባዩ ጊዜ ወደምድር ዝቅ ብለው ለቅዱስ ናትናኤል ሰገዱለት፡፡ ሁሉም በቅዱስ ናትናኤል አምላክ በክብር ባለቤት በጌታችን አመኑ፡፡ የጎልማሳውም አባት ቀድሞ አመነ፡፡ ሕዝቡም ሁሉ ‹‹የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ሆይ! የምንድንበትን ነገር ንገረን›› ባሉት ጊዜ የሃይማኖትን ነገር ቅዱሳት መጻሕፍትንም አስተማራቸው፡፡ ሐዋርያው አስተምሮ ካሳመናቸውም በኋላ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃቸው፡፡ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙንም አቀበላቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያንም እንዲሠሩ አዘዛቸው፡፡ ቆርኔሌዎስ የሚባለውንም ሰው ኤጲስቆጶስ አድርጎ እንዲሁም ሌሎች ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ሾመላቸው፡፡ ቅዱስ ወንጌልንም ሰጣቸው፡፡ ከእርሱም ጋር ለ30 ቀናት አብሮ ከቆየና በሃይማኖት ካጸናቸው በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ፡፡
የሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ረድኤት በረከት ይደርብን።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ምንጭ፦ የሐምሌ 1️⃣0️⃣ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 🍃🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔸https://m.facebook.com/MeseleNigatuDek0

ሐምሌ 9️⃣ ቀን 2011 ዓ.ም

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።ሐምሌ 9 አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ እራሳቸው ተዘቅዝቀው ባሕር ውስጥ መቆም የጀመሩበት እና ከዘጠኝ ዓመት በኃላ ጌታችን ተገልጦ...
16/07/2025

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን።

ሐምሌ 9 አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ እራሳቸው ተዘቅዝቀው ባሕር ውስጥ መቆም የጀመሩበት እና ከዘጠኝ ዓመት በኃላ ጌታችን ተገልጦላቸው "ኢትዮጵያን ምሬልሃለሁና ና ከባሕሩ ውስጥ ውጣ" በማለት ከባሕር ካወጣቸው በኃላ ለአባታችን ቃልኪዳኑን ያጸናበት ዕለት ነው፡፡
➛ የአምስቱ አሕጉር ኤጲስቆጶስ ቅዱስ ቴዎድሮስ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
➛ የቆጵሮሱ ቅዱስ ታኦድሮስ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ ከታኦድሮስም ጋራ ሦስት ሴቶችና እርሱን ያሠቃዩት የነበሩት ሁለቱ መኳንንት ሉክያኖስና ድግናንዮስ በጌታችን አምነው መስክር ሆነው ዐረፉ፡፡
➛ መሥተጋድል አባ ኅልያን ዕረፍቱ ነው፡፡
➛ የግብፃዊው የቅዱስ ሰርጊስ ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ዕለት ነው፡፡
➛ ከአባ ኤሲ ጋራ በሰማዕትነት ያረፉ 5504 ሰማዕታት መታሲቢያቸው መሆኑን ስንክሳሩ ይጠቅሳል፡፡

🔥 ቅዱስ ቴዎድሮስ ሰማዕት

ዲዮቅልጥያኖስ በካደና ጣዖታትን ባመለከ ጊዜ ምእመናንን ያስሩና ይገድሉ ዘንድ መኳንንቱን ሁሉ ወደ አገሮች ሁሉ ላከ፡፡ ስሙ ፍላጦስ የሚባል መኮንንም ወደ አፍራቅያ አገር ላከው፡፡ በዚያም ለክርስቲያኖስ ወገን መምህር የሆነውን ቅዱስ ቴዎድሮስን ወደ እርሱ አስጠርቶ ለጣዖታት እንዲሠዋ አዘዘው፡፡ ቅዱሱም ‹‹ሰማይንና ምድርን ለፈጠረ ለእውነተኛው አምላክ ለኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው የምሠዋው እንጂ በሰው እጅ ለተሠሩና ለረከሱ ጣዖታት አልገዛም›› አለው፡፡ መኮንኑም ይህንን ኃይለ ቃል ከቅዱስ ቴዎድሮስ አንደበት በሰማ ጊዜ በታላቅ ቁጣ ሆኖ ለ40 ቀን በፍርፋትና በስቅላት፣ በእሥራትና በመንኮራኩር እንዲያሠቃዩት አዘዘ፡፡ እንዳዘዘውም ለ40 ቀን በእጅጉ ካሠቃዩት በኋላ በመጨረሻ አንገቱን በሰይፍ ቆረጡትና ሰማዕትነቱን በድል ፈጽሞ የክብርን አክሊል ተቀዳጀ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን።

🔥 ሰማዕቱ ቅዱስ ታኦድሮስ

ይኽንንም ቅዱስ ክርስቲያን በመሆኑ ይልቁንም የቆጵሮስ ኤጲስቆጶስ በመሆኑ ብቻ በመኳንንቶቹ በሉክያኖስና በድግናንዮስ ዘንድ ከሰሱት፡፡ መኳንንቱም ወደ እነርሱ አስቀርበው በመረመሩት ጊዜ ቅዱስ ታኦድሮስም በጌታችን ታመነ፡፡ እነርሱም እየደበደቡት ለጣዖት እንዲሠዋ ባስገደዱት ጊዜ ቅዱሱ ከወደቀበት እየተዳኸ ሄዶ ጣዖቱን ረገጠውና ከመንበሩ ላይ ገልብጦ ጣለው፡፡ መኳንንቶቹም የሚያመልኩትን ስላቃለለባቸው በዚህ ተቆጥተው ቅዱስ ታኦድሮስን በእጅጉ አሠቃዩት፡፡ ሥጋውንም በማቅ ጨርቅ፣ ጨውና ኮምጣጤ ነክረው ፋቁት፡፡ እርሱም ጣዖታቱን ይረግም ነበር፡፡ የሚናገርበትንም ምላሱን ቆረጡት፡፡ አንዲትም ሴት የተቆረጠች ምላሱን አንሥታ ሆዱ ላይ ቢያደርጋት በተአምራት ተዘርግታ አፉ ውስጥ ገባችና እንደቀድሞው ሆነች፡፡ አንዲት ነጭ ርግብ መጥታ በቅዱሱ ላይ ስትዞር ሌላም ሶሪት ወፍ መጥታ በላዩ ተቀመጠች፡፡ በዚህም ጊዜ መኮንኑ ሉክያኖስ በጌታችን አመነ፡፡
ድግናንዮስ ግን ተቆጥቶ ቅዱስ ታኦድሮስን ይከተሉት የነበሩትን ሦስት ሴቶች በሰማዕትነት ገደላቸው፡፡ ቅዱስ ታኦድሮስም ነፍሱን አሳልፎ በሰጠ ጊዜ ርግቧና ሶሪት ወፏ በርረው ሄዱ፡፡ ሉክዮስም ድግናንዮስን የክርስቲያኖች ሃይማኖት የቀናችና እውነትም እንደሆነች መከረው፡፡ እርሱም የተመለከታቸውን ተአምራት አስተውሎና የጓደኛውን ምክር ሰምቶ በጌታችን አመነ፡፡
ከዚህም በኋላ ሉክያኖስና ድግናንዮስ ከቆሮንቶስ አገር ወደ ቆጵሮስ በመርከብ ሄዱ፡፡ በዚያም ሌላኛው መኮንን ክርስቲያኖችን ሲያሠቃይ ሉክያኖስ ከጓደኛው ተሠውሮ በመሄድ በመኮንኑ ፊት የጌታችንን ክብር በመመስከር የጣዖታቱን መንበር ገለበጠው፡፡ መኮንኑም ራሱን በሰይፍ አስቆረጠውና የሰማዕነት አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ ድግናንዮስም ሥጋውን ወስዶ ገንዞ ቀበረውና እርሱም በተራው በመኮንኑ ፊት ቀርቦ ጣዖታቱን በመርገም የጌታችንን አምላክነት መሰከረ፡፡ አሁንም ከሃዲው መኮንን የድግናንዮስን ራስ በሰይፍ አስቆረጠው፡፡ የክብር አክሊልንም ተቀበለ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን።

🔥 መሥተጋድል አባ ኅልያን

የዚህም ቅዱስ አገሩ ዐይነ ፀሐይ ይባላል፡፡ አባቱ ዲስጣ እናቱ ካልሞና ይባላሉ፡፡ ኅልያንም በወጣትነት የተመሰገነ የወርቅና የብር አንጥረኛ ነበር፡፡ በአንዲት ዕለት ከዐረብ አገልጋዮች የሆነች ሴት መጥታ የጆሮ ጉትቻ ከሠራላት በኋላ ዋጋውን ቢጠይቃት ‹‹ወንዶች ከሴቶች የሚሹትን ብትሻ እነሆኝ አለሁ ሌላ ገንዘብ ግን የለኝም›› አለችው፡፡ እርሱም ይህንን በሰማ ጊዜ ‹‹አንቺ የጨለማው አበጋዝ ልጅ ከእኔ ራቂ›› ብሎ ገሠጻት፡፡ ከዚህም በኋላ የነፍሱን ድኅነት አስቦ ገንዘቡን ለእናቱ ሰጥቶ ራቅ ወዳለ ገዳም ይሄድ ዘንድ ተነሣ፡፡ እግዚአብሔርም መንገዱን አቅንቶለት ረጅሙን መንገድ አቅርቦለት ወደ ኤርትራ ባሕር ዳርቻ በአንዲት ቀን ደረሰ፡፡
በዚያም ቆሞ ሳለ ነጭ ልብስ የለበሱና እንደፀሐይ የሚያበራ መስቀልን የተመረኮዙ ሦስት ሰዎች ተገለጡለትና ከእነርሱ ጋራ ወሰዱት፡፡ ወደ አትክልት ቦታም በደረሱ ጊዜ በትርና የዕንቁ መስቀል ሰጡት፡፡ በዚያም በአንድነት ጸለዩና ሰገዱ፡፡ ቅዱስ ኅልያንም ሰግዶ ቀና ሲል እነርሱን አጣቸው፡፡ በመለየቱም አዝኖ አለቀሰ፡፡ በዚያም በአትክልቱ ቦታ ቅጠል እየተገመበ ልብሱም ቅጠል ሆኖ ኑሮውን በብሕትውና አደረገ፡፡ ወደ ዋሻዎችም ለመሄድ ባሰበ ጊዜ የሰጡት በትረ መስቀሉ ታበራለት ነበር፡፡
ሰይጣንም መልካም ተጋድሎውን ስላየ ቀናበትና በፈተና ሊጥለው በማሰብ በሰው ተመስሎ ወደ ክፉዎች ሰዎች ዘንድ ሄዶ ‹‹እዚህ ቦታ የተሠወረ ገንዘብ አለ፣ ጠባቂውም አባ ኅልያን ነው፣ እርሱን ከያዛችሁት ያለበትን ያሳያችኋል›› አላቸው፡፡ ሰዎቹንም እየመራ አመጣቸውና ከወንዝ ማዶ በደረሱ ጊዜ መሻገሪያ አጡ፡፡ ውኃም እጅግ ተጠምተው ነበርና ሰይጣንም ወደ አባ ኅልያን በመሄድ ‹‹ውኃ ተጠምተውና መሻገሪያ አጥተው ተቸግረው ሳለ ውኃ የማታጠጣቸው ለምንድነው? አለው፡፡ እርሱም ሲሄድ ሰዎቹ የሚይዙት መስሎት ነበር፡፡ አባ ኅልያን ሄዶ ውኃ ቀድቶ አጠጣቸው፡፡ እነርሱም ባዩት ጊዜ ምንም የሌለው ድኃ መሆኑን ዐውቀው ተውት፡፡ ሰይጣንም ተንኮሉ ስለከሸፈበትና ስላፈረ ዳግመኛ በደጋግ በሆኑ መነኮሴዎች ተመስሎ አባ ኅልያንን ሊያስተው ወደ በዓቱ ሄደ፡፡ ቅዱሱም በብርሃን መስቀሉ ባማተበ ጊዜ እንደትቢያ በነው ጠፉ፡፡
የአባ ኅልያንም የዕረፍቱ ሰዓት በቀረበ ጊዜ እነዚያ መጀመሪያ የተገለጡለት ሦስት ሰዎች ዳግመኛ ተገለጡለትና ገድሉን ጻፉለት፡፡ ቅዱሱ ባረፈም ጊዜ በክብር ቀበሩት፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን።

🔥 አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ

አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ አባታቸው መልአከ ምክሩ እናቱ ወለተ ማርያም ይባላሉ፡፡ የተወለዱበት ልዩ ቦታው ወሎ ክፍለ ሀገር ዳውንት ነው፡፡ በተወለዱ ዕለት ተነሥተው በእግራቸው ቆመው ሦስት ጊዜ ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ብለው ፈጣሪያቸውን አመስግነዋል፡፡ የስማቸው ትርጓሜ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ አንድም የክርስቶስ እስትንፋስ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል እየጠበቃቸውና በመንገዳቸው ሁሉ እየመራቸው ነው ያደጉት፡፡ መንፈስ ቅዱስ ልቡናቸውን ብሩህ አድርጎላቸው በ5 ዓመታቸው የቅዱሳት መጻሕፍት ቃላትን፣ ብሉያትንና ሐዲሳትን፣ ድርሳናትንም ጠንቅቀው ዐውቀዋል፡፡
በተወለዱ በ14 ዓመታቸው ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ደብረ ሐይቅ ገዳም ሄደው ከባሕር ዳር ቆመው የሙሴን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር በጸለዩ ጊዜ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ባሕሩን አሻግሯቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብተዋል፡፡ ለ3 ዓመታት ያህል በኃይቅ ገዳም ለመነኮሳት እንጨት በመልቀምና ውሃን በመቅዳት ለአባቶች መነኮሳት ምግብ የሚሆናቸው ዓሣ ከባህር ውስጥ በማውጣት አገልግለዋል፡፡ አባታችን እስትንፋሰ ክርስቶስ 40 መዓልትና 40 ሌሊት ከጾሙ በኋላ ምንም እህል ሳይቀምሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስቀድሞ ለሙሴ በደብረ ሲና እንደሰጠው ለአባታችንም ወደ እርሳቸው መጥቶ ዓሥሩን ቃላተ ኦሪትና ስድስቱን ቃላተ ወንጌል በውስጣቸው የተጻፈባቸው ሁለት ጽላቶችን ሰጥቷቸዋል፡፡ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ከሠሩ በኋላ ዕለቱን ስንዴ ዘርተው፣ ወይን ተክለው፣ ጽድን ወይራንና ግራርን ተክለው በአንዲት ቀን ለቤተክርስቲያን አገልግሎት ዕለቱን አድርሰዋል፡፡ ስንዴውን ለመሥዋዕት ወይኑን ለቍርባን በተአምራት አድርሰዋል፡፡
አባታችን በጸሎት ላይ እንዳሉ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተልኮ መጥቶ አባታችንን በደመና ጭኖ ወስዶ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፊት አቆማቸው፡፡ ጌታንም በቅዱሳኑ ሁሉ እንዲባረኩ ካደረጋቸው በኋላ መልአኩን ‹‹ወደ ተወለድኩባትና ወደ ኖርኩባት ቦታ ወደ ኢየሩሳሌም አድርሰው›› ብሎት ኢየሩሳሌምን አሳልሞ ሀገራችን መልሶ አምጥቷቸዋል፡፡ አባታችን ሁሉንም የኢትዮጵያን ቅዱሳት ገዳማትን ተዘዋውረው ሲጎበኙ በሕይወተ ሥጋ የሌሉት የየገዳማቱ ቅዱሳን ሁሉ በአካል ይገለጡላቸው ነበር፡፡ ጎጃም ውስጥ እያስተማሩ፣ እያጠመቁ፣ የታመሙትን እየፈወሱ፣ የዕውራንን ዐይን እያበሩና ሙታንን እያሥነሱ ብዙ ካገለገሉ በኋላ ለዘጠኝ ዓመታት በባሕር ውስጥ ገብተው ቁልቁል ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ጸልየው የምሕረት ቃልኪዳን ተቀብለዋል፡፡ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ጌታችን መጥቶ ‹‹ከመነኮሳት ሁሉ ብልጫ ያለህ ወዳጄ ሆይ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ምሬልሃለሁ ከዚህች ባሕር ውጣ›› በማለት በሞት የሚያርፉበትን ቦታ ነግሯቸዋል፡፡
ጻድቁ ወደ ደብረ አሰጋጅ በሚሄዱበት ጊዜ ጸሐይ ልትገባ ስትል ‹‹በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አውግዤሻለሁ ለመስፍን ኢያሱ በገባኦን እንደቆምሽ አሁንም ቀጥ ብለሽ ቁሚ›› ብለው ገዝተው ፀሐይን አቁመዋል፡፡ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስም ደብረ አሰጋጅ ሲደርሱ ፀሐይ አፍ አውጥታ ‹‹አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ሆይ እገባ ዘንድ ፍታኝ›› ስትላቸው ‹‹እግዚአብሔር ይፍታሽ›› ባሏት ጊዜ ጠልቃለች፡፡ ጻድቁ ሌላው በእጅጉ የሚታወቁበት አንድ ትልቅ ቃል ኪዳን አላቸው፡፡ በአምላክ ልቡና የሚገኝ፣ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ልቡና የሚገኝ፣ በቅዱስ ሚካኤልና በቅዱስ ገብርኤል ልቡና የሚገኝ እንደ መልክአ መድኃኔዓለም ያለች እጅግ አስገራሚ ጸሎት አለቻቸው፤ እርሷን ጸሎት በጸለዩ ጊዜ እልፍ ነፍሳትን ከሲኦል ያወጣሉ፡፡ ጸሎቷም የመድኃኔዓለምን የሰውነት ክፍሎች በሙሉ እየጠቀሰች እያንዳንዱ የሰውነት ክፍሎቹ የተቀበሉትን ጸዋትዎ መከራዎች ሁሉ ታዘክራለች፡፡ በእያንዳንዱ ክፍልም የጸሎት ማሳረጊያ አቡነ ዘበሰማያት ይደግማሉ፡፡ ንስሓ የገባ ኃጢአተኛ ሰው እንኳን ቢሆን ይህችን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስን ጸሎት በጸለየ ጊዜ ሺህ ነፍሳትን ከሲኦል እንደሚያወጣ ጌታችን በማይታበል ቃሉ ለአባታችን ነግሯቸዋል፡፡ እያንዳንዱን የመድኃኔዓለምን የሰውነት ክፍሎች በሙሉ እየጠቀሰች መከራዎቹን የምታዘክረውን ይህቺን በአምላክ ልቡና ያለች ግሩም የሆነች ጸሎት ነፍሳትን ከሲኦል አታወጣም ብሎ የሚጠራጠር ቢኖር መንግስተ ሰማያትን አያያትም፡፡ ይህንን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስን ጸሎት የምናገኘው ከገድላቸው ላይ ነው፡፡ ጻድቁ ታኅሣሥ 8 ቀን ተወልው ሚያዝያ 9 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡
የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡

ምንጭ፦ የሐምሌ 9️⃣ ስንክሳር

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 🍃🍃🍃🍃

ዘአቅረብኩ ማኅሌተ አዘኪርየ አእላፈ
እምእለ ተጸምዱከ ዘልፈ
ለለአነብብ ተወከፍ ዘንዴትየ መጽሐፈ
እንተ ረሰይከ እግዚኦ ጸሪቀ መበለት ውኩፈ
እም እለ አብዑ ብዑላን ዘተርፈ።

ነቢያት ቅዱሳን ወሐዋርያት ሰባኪያን
ሰማዕታት ወጻድቃን ወመላእክት ትጉሃን
ደናግል ዓዲ ወመነኮሳት ኄራን
ባርኩ ባርኮ ጉባኤ ዛቲ መካን
እስከ አረጋዊ ልሒቅ እምንዑስ ሕፃን።

ለዘጸሐፎ በክርታስ
ወለዘአጽሐፎ እንዘ ይደርስ
ለዘአንበቦ ወለዘተርጐሞ በልሳን ሐዲስ
ወለዘሰምዐ ቃሎ በእዝነ መንፈስ
በጸሎተ እሙ ማርያም ዐራቂተ ኲሉ እምባእስ
ኅቡረ ይምሐረነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ወይፈኑ ለነ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ
እምይዜ ወእስከ ለዓለም አሜን።

ጌታ ሆይ ከብልጽግናቸው ብዛት የተነሳ ብዙ መባ ካገቡት ይልቅ የደሀይቱን አነስተኛ መባ እንደተቀበልህ ለሁል ጊዜ የሚያገለግሉህ አእላፍ መላእክትን እያሳሰብሁ በችግሬ ጊዜ የማቀርብልህን ምስጋና ተቀበል።

እናንተም ቅዱሳን ነቢያት የወንጌል ሰባኪያን ሐዋርያት ሰማዕታትና ጻድቃን ትጉሃን መላእክት ፍጹማን ደናግል እንዲሁም ደጋጎች መነኰሳት ሆይ ልጅ አዋቂ ሳይለይ የምንሰበሰብበትን የጉባኤ ቦታ ባርኩ።

ይህን መጽሐፍ ወረቀት አዘጋጅቶ ብራና ደምጦ የጻፈውንና ያጻፈውንም የተረጐመውን ቃለ ንባቡን በእርጋታ መንፈስ እና በተመስጦ ሕሊና ያዳመጠ በደለኛን ሁሉ የምታስምር የጌታ እናቱ በማርያም ጸሎት ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድነት ይማረን። አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼⁼
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ - https://t.me/Synaxarium

Fᴀᴄᴇʙᴏᴏᴋ
🔸https://m.facebook.com/MeseleNigatuDek0

ሐምሌ 8️⃣ ቀን 2011 ዓ.ም

Address

Hawassa

Telephone

+251926265782

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ስንክሳር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ስንክሳር:

Share

Category