Green Light Media

Green Light Media Welcome to Green Light Media welcome to green Light Media

የለውጥና የብልጽግና መሃንዲስ፦ የክቡር ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ ስኬታማ የሥራ ጉዞ!የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከተመሠረተ ማግስት ጀምሮ ያጋጠሙትን ዘርፈ ብ...
27/04/2026

የለውጥና የብልጽግና መሃንዲስ፦ የክቡር ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ ስኬታማ የሥራ ጉዞ!

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከተመሠረተ ማግስት ጀምሮ ያጋጠሙትን ዘርፈ ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎች በብቃት በመወጣት፣ በአሁኑ ወቅት በአስተማማኝ የዕድገት ጎዳና ላይ ይገኛል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ የህዝብ የልማት አቅሞችን በማቀናጀት የተከተሉት ቁርጠኛ አመራር ለተመዘገቡት ድሎች ባለቤት ነው።

ክልሉ ገና ሲመሰረት የነበረበትን ከፍተኛ የዕዳ ጫና እና አሳሳቢ ሁኔታዎችን በመቀየር ረገድ ርዕሰ መስተዳድሩ የወሰዱት የፖሊሲ ውሳኔ (ወጪ ቅነሳ) ውጤት አምጥቷል።

በዚህም መሠረት የክልሉ ዕዳ ወደ ዜሮ እንዲወርድ የተደረገ ሲሆን፣ ቀደም ሲል ከነበረው 2 ቢሊዮን ብር የገቢ አሰባሰብ በአሁኑ ወቅት ወደ 18 ቢሊዮን ብር በላይ በማደግ በክልሉ ገቢ የመሰብሰብ አቅም በከፍተኛ ደረጃ አድጓል።

ሌላው በዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ አመራር የተመዘገበው ደማቅ ስኬት፣ ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተዘረጋው የክላስተር አደረጃጀት ነው።

ይህ አደረጃጀት ሕገ-መንግስታዊ መሠረት እንዲኖረው በማድረግ፣ በክልሉ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በጋራና በእኩልነት እንዲለሙ መንገድ የከፈተ ከመሆኑም በላይ ለደቡብና ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎችም እንደ ተሞክሮ የተወሰደ የላቀ አሠራር ሆኖ ተመዝግቧል።

በመሠረተ ልማት ዘርፍም ለበርካታ ዓመታት ተጀምረው ተጓትተው የነበሩ በርካታ ፕሮጀክቶች ፍጻሜ እንዲያገኙ ተደርጓል።

ርዕሰ መስተዳድሩና ካቢኔያቸው ከሥራ ማስኬጃ በጀት በመቀነስ ለካፒታል ፕሮጀክቶች ቅድሚያ በመስጠታቸው በስድስቱም ዞኖች የሚገኙ የውሃ፣ የመስኖ፣ የመንገድ፣ የጤና እና የትምህርት ተቋማት ተጠናቅቀው ለሕዝብ አገልግሎት በቅተዋል።

በክልሉ የተመዘገበው ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ መነቃቃትና ማህበራዊ ልማት በሕዝቡ ዘንድ ከፍተኛ አድናቆትና ተቀባይነትን አስገኝቷል።

ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ በሕዝቡ ዘንድ ያላቸው ከፍተኛ ተቀባይነት የመነጨው ከቃላት ይልቅ በተግባር ከሚያሳዩት ውጤት ነው። በክልሉ በተመዘገበው ሁለንተናዊ የልማት ድል የክልሉ ሕዝብ ደስተኛ መሆኑን በተለያዩ መድረኮች ሲገልጽ ቆይቷል።

በእሳቸው ብርቱ አመራር፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ዛሬ ላይ የሰላም፣ የልማትና የአንድነት ተምሳሌት ሆኗል።

በአሁኑ ወቅት ክልሉ እያስመዘገበ ያለውን ሁለንተናዊ ስኬትና የርዕሰ መስተዳድሩን ውጤታማ አመራር ለማጠልሸት በማህበራዊ ሚዲያ የሚነዙ አሉታዊ ትርክቶች ፍጹም ከእውነት የራቁ ናቸው።

20/04/2026

የነቀምቱ ነጻነት (አንዱአለም) የቤተሰብ ጨዋታ ለሙከራ አቅርቦ ተመልካች ጎረፈ 🔥

በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ለሙከራ የቤተሰብ ጨዋታ ሰርቷል፤ ከሰይፉ ጋርም እንግዳ ሆኖ የቀረበው አንዱዓለም እስቲመች የሙከራ ፕሮግራም በርካታ ተመልካች አግኝቷል።

18/04/2026
11/04/2026

✝️✝️✝️
ሀሹ ጋቲሲ!

02/04/2026

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የመጋቢት 24 የለውጥ ፍሬ ዉጤት መሆኑን ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ፣ የመጋቢት 24 የለውጥ ጉዞን ተከትሎ በክልሉ የታዩ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ልማት ውጤቶች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን አስታወቁ።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መግለጫ፣ የሕዝቦች የዘመናት የፍትሃዊነትና የራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎች በለውጡ መንግሥት ምላሽ ማግኘታቸው ለክልሉ መመሥረት መሠረት መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ርዕሰ መስተዳድሩ ገለጻ፣ ክልሉ ከተመሠረተበት ኅዳር 14 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በመደመር ዕሳቤ በርካታ የልማት ድሎች ተመዝግበዋል።

በፖለቲካና በመልካም አስተዳደር ረገድ የክልሉ መመሥረት ራሱ ትልቁ ስኬት መሆኑን የጠቀሱት ኢንጂነር ነጋሽ(ዶ/ር)፣ ሕዝቡ የራሱን ሕገ መንግሥት፣ ሰንደቅ ዓላማና አርማ በመቅረጽ እንዲሁም የክልልና የብሔረሰቦች ምክር ቤቶችን በማቋቋም ራሱን በራሱ እያስተዳደረ መሆኑን አብራርተዋል። ይህም ቀደም ሲል በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ይነሱ የነበሩ የመንግሥት ተደራሽነት ችግሮችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ማስቻሉን ጠቁመዋል።

በኢኮኖሚው ዘርፍ ክልሉ እያመዘገበ ያለውን ዕድገት በተመለከተ ርዕሰ መስተዳድሩ ሲያብራሩ፣ ክልሉ ከኦሮሚያ በመቀጠል በቡና ምርት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል። ከዚህም በተጨማሪ በኩታ ገጠም እርሻና በበጋ መስኖ ስንዴ ምርታማነት ማደጉን፣ የክልሉ ዓመታዊ የገቢ አቅምም ከነበረበት ሁለት ቢሊዮን ብር ወደ 18 ቢሊዮን ብር ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

በማዕድን ዘርፍም በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ የተገነባው የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ የሀገሪቱን 25 በመቶ ፍላጎት መሸፈን መጀመሩንና ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን በመግለጫቸው አመልክተዋል።

የመሠረተ ልማት ዝርጋታን በተመለከተ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን ከ32 በመቶ ወደ 43 በመቶ ማደጉንና የተለያዩ የአስፓልት መንገድ ፕሮጀክቶችም እየተሰሩ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ አስታውቀዋል።

በመጨረሻም፣ በ "ገበታ ለሀገርና ለትዉልድ" መርሃ ግብር የተገነቡት የሀላላ ኬላ፣ የጨበራ ዝሆን ዳና እና የደንቢ ኢኪ ሎጅ ፕሮጀክቶች ክልሉን ለቱሪዝም ዘርፍ ምቹ እያደረጉት መሆኑን የጠቀሱት ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ፣ የክልሉን ሰላምና ልማት ዘላቂ ለማድረግ ከፀጥታ መዋቅሩና ከሕዝቡ ጋር የተቀናጀ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አረጋግጠዋል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌በድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/
📌በዋትስአፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VbAiSCpGE56ue7VyJJ3x
📌በሊንክደን
https://www.linkedin.com/company/southwest-communications/
📌በትሬድስ
https://www.threads.com/
📌በብሉ ስካይ
https://bsky.app/profile/swc79.bsky.social
በደብልው ኤን ሶሻል
https://wnsocial.com/page/16775

"ሀሳቡን ወደን አመራሩን ጠላን"፦ የመነጠል ፖለቲካ ስልትብልጽግና ማለት ሀሳቡም፣ አመራሩም፣ መዋቅሩም አንድ ላይ ተሳስረው ለህዝብ የሚሰሩበት ፓርቲ ነዉ ነው።አሁኑ የምርጫ ዋዜማ አንዳንድ ተ...
30/03/2026

"ሀሳቡን ወደን አመራሩን ጠላን"፦ የመነጠል ፖለቲካ ስልት

ብልጽግና ማለት ሀሳቡም፣ አመራሩም፣ መዋቅሩም አንድ ላይ ተሳስረው ለህዝብ የሚሰሩበት ፓርቲ ነዉ ነው።

አሁኑ የምርጫ ዋዜማ አንዳንድ ተፎካካሪ ፓርቲዎች አዲስ ስልት ይዘው ብቅ ብለዋል። ይህም "ብልጽግናንና ሀሳቡን እንደግፋለን፣ አመራሩን ግን አንፈልግም" የሚል ነው። ይህ አካሄድ በላዩ ላይ ለስላሳ ቢመስልም፣ በውስጡ ግን በሴራ የታጨቀ የፖለቲካ ስልት ነዉ።

1. መሪ የሌለው ሀሳብ መሬት አይረግጥም!

ማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት የሚንቀሳቀሰው በሁለት ነገሮች ነው፦ በሀሳብ (Policy) እና በአስፈጻሚ (Leadership)።

ሀሳብ ብቻውን የትም አይደርስም። ዛሬ የምናያቸው የልማት ስራዎች፣ ሰላምና ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች የመጡት ሀሳቡን በተግባር የሚተረጉም አመራር ስላለ ነው።

አመራሩን መጥላት ማለት ሀሳቡ እንዳይፈጸም እጅና እግር ማሰር ማለት ነው። "አመራሩን እንጠላለን" ማለት "የተጀመሩ ስራዎች እንዲቆሙ እንፈልጋለን" ከማለት ተለይቶ አይታይም።

2. የመነጠል ፖለቲካ

ይህ ስልት ዓላማው በህዝብና በአመራሩ መካከል የጥርጣሬ ግንብ መገንባት ነው።
አመራሩን ለህዝብ የማይቆረቆር" አድርጎ በመሳል፣ ህዝቡ መሪውን እንዲጠራጠር ማድረግ ነው።

ተፎካካሪዎች ይህንን የሚያደርጉት ህዝቡን ለመጥቀም ሳይሆን፣ መሪውን አዳክመው ስልጣን ላይ ለመውጣት እንዲመቻቸው ነው።

3. የድል ባለቤትነትን የማሳጣት ስልት

ብልጽግና ፓርቲ ያስመዘገባቸው ድሎች በአመራሩ ቁርጠኝነትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የመጡ ናቸው።

ተፎካካሪዎች "አመራሩን እንጠላለን" ሲሉ፣ እነዚያን ታላላቅ ድሎች ያስመዘገቡ ሰዎችን ስብዕና በማጠልሸት፣ ድሉ የፓርቲው እንጂ የአመራሩ እንዳልሆነ ለማስመስል ይጥራሉ። ይህ ደግሞ ታሪክን የመካድ ያህል ከባድ ስህተት ነው።

4. የፓርቲን መዋቅር የማፈራረስ ግብ

አንድን ቤት ለማፍረስ የግድ ግድግዳውን መናድ አያስፈልግም፤ ዋና ማገሩን ማውጣት ይበቃል። አመራር ደግሞ የፓርቲ ማገር ነው።

አመራሩን ነጥሎ መምታት ማለት ፓርቲው በህዝብ ዘንድ ያለውን ቅቡልነት ማሳጣትና ድርጅታዊ አንድነቱን ማላላት ነው።

ብልጽግና ማለት ሀሳቡም፣ አመራሩም፣ መዋቅሩም አንድ ላይ ተሳስረው ለህዝብ የሚሰሩበት ድርጅት ነው።

አንዱን ነጥሎ ሌላውን እወዳለሁ ማለት፣ "መኪናውን እወዳለሁ ሞተሩን ግን እጠላለሁ" እንደማለት አይነት የሞኝ ዘፈን ነው።

አንዳንድ ተፎካካሪዎች አማራጭ ሀሳብ ሲያጡ ወደ ግለሰብ ስድብና ጥላቻ ይገባሉ። እውነተኛ ፖለቲከኛ የሚወዳደረው በሀሳብ እንጂ በአመራር ስብዕና ላይ ጥላቻ በመርጨት አይደለም።አባላችንና ህዝባችን ይህንን በጥንቃቄ ሊመለከተዉ ይገባል።

29/03/2026

የቀድሞ የክልሉ ከፍተኛ አመራር የነበሩት የአቶ ተዘራ ወልደማርያም 2ተኛ ሙት-ዓመት በሀይማኖታዊ ስነ-ስርዓት ይታሰባል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል እንደ ክልል እጅግ ተወዳጅ እና ጠንካራ አመራር አቶ ተዘራ ወልደማርያምን ያጣው ልክ የዛሬ 2 ዓመት ነበር። እኚህ የተወደዱ አመራር መጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም ነበር በሥራ ባሉበት በድንገት በገጠማቸው የጤና እክል በድንገት ነበረ ያረፉት።

በ1973 ዓ.ም በኤላ አውራጃ አመያ ከተማ ከሃምሳ አለቃ ወ/ማርያም ሱራ እና ከወ/ሮ በላይነሽ ጮቤ የተወለዱት አቶ ተዘራ፣ ከታችኛው የመምህርነት እርከን ተነስተው እስከ ከፍተኛ የክልል አመራርነት የደረሱበት የሕይወት ጉዟቸው ለብዙዎች ተምሳሌት የሚሆን የፅናት መንገድ ነበር።

ከአርባ ምንጭ መምህራን ኮሌጅ ተመርቀው በኦሽካ ዴንቻ፣ በኮንታ ኮይሻ፣ በጨበራ ሻሾ እና በሌሎችም ገጠራማ አካባቢዎች በመምህርነትና በርዕሰ መምህርነት ሲያገለግሉ የነበራቸው ቅንነትና ታማኝነት፣ በኋላ ላይ ተሸክመውት ለነበረው ትልቅ የፖለቲካ ኃላፊነት መሰረት የጣለ ነበር።

በትምህርት ላይ የነበራቸው ልዩ ፍላጎትም የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በዲላ ዩኒቨርሲቲ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በቢዝነስ አስተዳደር እንዲያገኙ አስችሏቸዋል።

አቶ ተዘራ የኮንታ ዞን (የቀድሞው ልዩ ወረዳ) ዋና አስተዳዳሪ እና የደቡብ ክልል የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ፣ በህዝቡ ዘንድ የነበራቸው ተቀባይነትና ተግባቢነታቸው ልዩ መለያቸው ነበር።

በተለይም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሲመሰረት የነበራቸው ሚናና በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው፣ ለክልሉ ሰላማዊ ምስረታና ዕድገት የከፈሉት መስዋዕትነት ሁሌም የሚታወስና በክልሉ ታሪክ በደማቅ የተጻፈ ሁልጊዜ የሚዘከር ታሪካቸው ነው።

በሥራ ገበታቸው ላይ እያሉ በገጠማቸው ድንገተኛ የጤና እክል ከሁለት ዓመት በፊት ቢያልፉም፣ እንደ መሪ ጠንካራ፣ እንደ ወንድም መካሪ፣ እንደ ጓደኛ ደግሞ ተጫዋችና ተግባቢ የነበሩት አቶ ተዘራ፣ በሦስት ልጆቻቸውና ባስቆጠሩት መልካም ስም ዛሬም በመካከላችን አሉ።

ለህዝብ ጥቅምና ክቡር የኖሩ፤ በፍቅር ከራስ ህዝብን እና የህዝብን ሥም ያከበሩ ሁሉ ለዘለአለሙ እየተዘከሩ ይኖራሉ። አቶ ተዘራም ሁሌም የሚዘከሩ የክልሉ ህዝቦች የሁል ጊዜ ጀግና ናቸው።

የአቶ ተዘራ ሁለተኛ የሙት ዓመት በነገው ዕለት በኮንታ ዞን ወዳጅ ዘመድ በተገኙበት በሀይማኖታዊ ስነ-ስርዓት ታስቦ ይውላል።
(ገብረማሪያም) ነፍስ ይማር🥺
via Doch HD

Address

Hirna
06

Telephone

0473450210

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Green Light Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Green Light Media:

Share