03/01/2026
ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ባለፉት 4 ዓመታት 🇪🇹
•ብስለት፤ ለክህደት የማይመች ውጤት!
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ህዳር 14 ቀን 2014 ዓ.ም ነበር በአሁኑ የሃላፊነት ሥፍራ ላይ ሃላፊነት የተሰጣቸው።
ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) በወቅቱ አንዳንድ የግል ማጣራቶችን ሳደርግ ጠንካራ የትምህርት እና የሃላፊነት ላይ ልምድ ያላቸው ግለሰብ መሆናቸውን መመልከት ችያለሁ።
ይህንን መመልከት ለሚሻ አሁንም ቢሆን ለማረጋገጥ እምብዛም የተሸሸገ የኋላ ታሪክ አይደለም ያላቸው። ማንም ሰው ቢሆን "ዶክተር ኢንጂነር" ተብለው ሲጠሩ የሠሯቸውን ምርምሮች መመልከት ባይችል እንኳን ያንን ለመሆን የሄዱባቸውን መንገዶች መመልከት ይችላል። የአረቄ ቤት የስድስተኛ ክፍል የማህበራዊ ሚዲያ ላይ ቅጥረኛ ካልሆነ ማለቴ ነው።
ከሠሞኑ እሳቸውን የተመለከቱ የተለመዱ የሀሰት መረጃዎችን ስመለከት መረጃው ፈገግ የሚያስብልና የተደራሲያኑ ክብር የነፈገም "እውር እና ማንበብ የማትችሉ ናችሁ" የሚልም ሆነ ተመለከትኩ።
ግለሰቦች በመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች ላይ በተለያዩ ምክኒያቶች ቂም ሊቋጦሩና ሊያኮርፉ ይችላሉ። ስለ ቀረባቸውም ጥቅም ሲሉ ሂሊናቸውን ክደው ሃሰት ማምረት ይጀምሩም ይሆናል። በግል ይህንን ማድረግ የሚያስችሉ አያሌ ምክኒያቶችን ብፈልግ አላጣም። ይህ ምክኒያት ግን በፍጹም ህሊናዬን ሊያሸጠኝ አይችልም።
ክልሉን ከቀድሞው የደቡብ ክልል አደረጃጀት ለተመለከተ ሰው ባዶ እንደነበር መመልከት እምብዛም ከባድ አይደለም። ባለፉት 4 ዓመታት እንደ ክልል የተመዘገቡ ውጤቶችን ለማሳነስ መሞከር ግን እልም ያለ ቅጥፈት ነውና ያንን ማድረግ ለትዝብት የሚዳርግ ይሆናል።
እድገቱ ፍፁምና እንከን አልባ ነው ባይባልም ያሉ ውስንነቶች በጊዜ ወደ ጊዜ እየታረሙ ልማቱ ፍትሃዊ እንዲሆን እየተደረገም ያለውን ጥረት ማድነቅ እጅጉን መሰልጠን ነውና ያንን በማድረጌ አላፍርበትም።
ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ እና መንግስታቸው ባለፉት 4 ዓመታት ያስመዘገባቸውን ውጤቶች አደንቃለሁ በተቻለኝም አቅም ለመደገፍ የቻልኩትን አድርጌያለሁ፤ አድርጋለሁም።
ያንን ለማድረግ ታዲያ እሳቸው የእኔ መንደር ሰው መሆን ያለባቸው አይመስለኝም። አጎናቸውም ነኝ ለማለት ጥቅም ሁሉ ወደ እኔ መጉረፍ አለበትም ብዬ አላምንም። ጥያቄው ህዝባዊ ላለመሆኑ ህዝባዊ እሴቶችን የካደ መሆኑ ማሳያ መሆን የሚችል ቢሆን የሰሞኑ አጀንዳ አሳፋሪና ተቀባይነት የሌለው መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
ዶች - (ዶ/ር)