Hola Media ሆላ ሚዲያ

Hola Media ሆላ ሚዲያ ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና! Hadiya Mass Media is the of voice of voiceless.

ምድር ነገ (ጁላይ 22) በፍጥነት በመሽከርከር በታሪክ አጭር ከሆኑ ቀናት አንዷን እንደምታስመዘግብ ተተነበየ  | የስነ ፈለክ ተመራማሪዎች ባወጡት አዲስ መረጃ መሰረት፣ ምድር ነገ ማክሰኞ ሐ...
21/07/2025

ምድር ነገ (ጁላይ 22) በፍጥነት በመሽከርከር በታሪክ አጭር ከሆኑ ቀናት አንዷን እንደምታስመዘግብ ተተነበየ

| የስነ ፈለክ ተመራማሪዎች ባወጡት አዲስ መረጃ መሰረት፣ ምድር ነገ ማክሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2017 በዘንግዋ ዙሪያ ያላትን የመሽከርከር ፍጥነት በመጨመር በታሪክ ውስጥ ከታዩት አጫጭር ቀናት መካከል ሁለተኛዋን እንደምታስመዘግብ ትንበያ ተሰጥቷል።

ይህ በቅርብ ዓመታት እየታየ ያለው የምድር የማሽከርከር ፍጥነት መጨመር የሳይንስ ማህበረሰቡን ትኩረት ስቧል።

እንደ space.com ባወጣው ዘገባ መሰረት፣ ነገ ምድር አንድ ሙሉ ዙር ለመጨረስ ከመደበኛው 24 ሰዓት ገደማ 1.34 ሚሊሰከንዶች ያነሰ ጊዜ ይወስድባታል ተብሏል።

ይህ በ2020 ከጀመረው የምድር የመሽከርከር ፍጥነት መፋጠን ጋር የተያያዘ ሲሆን፣ ቀደም ሲል የተመዘገቡ የፍጥነት ክብረ ወሰኖችን እየሰበረ ይገኛል ነው የተባለው።

ምድር ለረጅም ጊዜ በጨረቃ የስበት ኃይል ምክንያት እየቀዘቀዘች እና ቀናት እየረዘሙ ቢሆንም፣ ከ2020 ወዲህ እየታየ ያለው መፋጠን ግን ያልተጠበቀ ነው ተብሏል።

የሳይንስ ሊቃውንት ይህ ያልተለመደ የፍጥነት መጨመር መንስኤ ምናልባትም የምድር ፈሳሽ የውስጥ እምብርት (liquid core) ፍጥነት መቀነስ ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ።

የእምብርቱ ፍጥነት መቀነስ የማሽከርከር ኃይልን በማከፋፈል የውጪውን ንብርብሮች (ማንትል እና ቅርፊት) በፍጥነት እንዲሽከረከሩ ሊያደርግ ይችላል ነው የተባለው።

ይህ መፋጠን ከቀጠለ፣ እ.ኤ.አ. በ2029 አካባቢ "negative leap second" የሚባል፣ ከአቶሚክ ሰዓቶች ላይ አንድ ሰከንድ የመቀነስ ያልተለመደ እርምጃ እንዲወሰድ ሊያስገድድ ይችላል ተብሏል።

ምንም እንኳን ይህ በዕለት ተዕለት ህይወታችን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ባያሳድርም፣ እንደ ሳተላይቶች እና የጂፒኤስ (GPS) ሲስተሞች ያሉ ትክክለኛ ሰዓት ላይ የሚመሰረቱ ቴክኖሎጂዎች ላይ ተጽዕኖ ሊያሳድር ይችላል ነው የተባለው።

በዚህም የተነሳ፣ ዓለም አቀፍ የሰዓት ተቆጣጣሪዎች የሰዓት ትክክለኛነትን ለማስጠበቅ የሚደረጉ ማስተካከያዎች አስፈላጊ ይሆናሉ ነው የተባለው።

ዛሬ ላይ አቶ ደስታ ሌዳሞ በጎሳ እየከፋፈለ እንደልብ የሚጫወተው ክልል በሰው ደምና አጥንት የተመሰረተ ፣አፍላ በሆኑ ወጣቶችና ምሁራን እስራት ስደት የተመሰረተ ክልል ነው።    ✊Hola Me...
21/07/2025

ዛሬ ላይ አቶ ደስታ ሌዳሞ በጎሳ እየከፋፈለ እንደልብ የሚጫወተው ክልል በሰው ደምና አጥንት የተመሰረተ ፣አፍላ በሆኑ ወጣቶችና ምሁራን እስራት ስደት የተመሰረተ ክልል ነው።



Hola Media ሆላ ሚዲያ

አቶ አለማየሁ ጥሞትዎስ ብቻዉን ወንጀለኛ ልሆን አይችልም፣ አቶ ደስታ ለዳሞ እና አቶ አብርሃም ማርሻሎም ግንባር ቀደም ወንጀለኞች ናቸው‼️ ደስታ ሌዳሞ በሁለት ሳምንት ውስጥ ይነሳል፣ በዚያን...
21/07/2025

አቶ አለማየሁ ጥሞትዎስ ብቻዉን ወንጀለኛ ልሆን አይችልም፣ አቶ ደስታ ለዳሞ እና አቶ አብርሃም ማርሻሎም ግንባር ቀደም ወንጀለኞች ናቸው‼️

ደስታ ሌዳሞ በሁለት ሳምንት ውስጥ ይነሳል፣ በዚያን ጊዜ ነው የአለማየሁ ጢሞትዎስ ጉዳይም እልባት ማግኛት የምቻለው:: ሁሉም ወንጀሎች በአቶ አለማየሁ በኩል የተፈፀሙት አንዳንድ ጭፈራ ቤት ባልን አሳስሮ ሚስትን ይዞ ከመሄድ ውጭ የደስታ ሌዳሞ እጅ አለቤት ያለበት ነው።

ይህንን እዉነታ ሀዋሳ ኢንጆሪ ጭፈራ ቤት ህዱና ጠይቁ የሃዋሳ ዩኒቨሪስት ሌክችሬር የዶ/ር ሚስት የሆነችውን ቀድሞ የደቡብ ጋዜጠኛ ቀዳማዊትን ከጭፌራ ቤት ባሏን ፓቲሮል ጠርቶ አሳስሮ እሷን የዞ ሄዷል ከ2 ሳምንት በኃላ የልጅቷ ቤተሰብ በስንት መከራ ለምኖ አስፌትተቷል::

ሃዋሳ 05 ኦሲስ ሆቴል በአይኔ እያዬሁ 4 ፓቲሮል አስጠርቶ ከአዲስ አበባ ለመዝናናት የመጡ እንግዶችን እንደዝሁ በተመሳሳይ መልክ አሳስሮ ሚስቱን ቀምቶ አድሯል:: ይህ ለሃዋሳ ሕዝብ ግልጽ ነው፣ ጉዳዩን አቶ ደስታም ያውቃል:: የመሪኩር ጉዳይ ደግሞ በደቡብ አፍርካ ፒሪቶርያ ከተማ ወስዶ አሽጧል ለዚህም የደስታ ሌዳሞና አብርሃም ማርሻሎ የጥቅም ተጋር መሆናቸው ይታወቃል::

ሌላው ም/ቤት ያነሳ የወንጀል ሀሳቦች በሙሉ ተቀባይነት ያለው ሲሆን ለላው ደግሞ ደቡብ ዕዝ ቶጋ ያለው መከላከያ አንዳንድ አባላት ጋር በማበር በትግራይ ጦርነት ጊዜ በርካታ የትግራይ ተወላጆች ንብሬት ከመክና ጨምሮ v8 ሳይቀር ወደ ከንያ እድገቡና እስፔርፓርቲ ደግሞ ሃዋሳ መክኖቹ እየታረዱ እንድሸጡ አድርጓል:: ይህንን ጉዳይ አቶ ደስታና አንርሃም ያውቃሉ።

በየመ/ቤቱ ሙስና የበላ አመራር ለአለማየሁ፣ ለደስታና ለአብርሃም ድርሻ አላቸው፣ ለምሳሌ የሲዳማ ብ/ክ/መ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ባለሙያዎች ሲዳማ ክልል መስኖ ኤጀንስ በጨረታ ህደቱ ላይ ጥቆማ ደርሷቸው ገብቶ አስቸኳይ ለቃቹ ውጡ ብሎ ያስፈራራቸው ባለሙያዎች ምስክር ናቸው።

ለመሆኑ አለማየሁ ብቻውን የሰራው ወንጀል የቱ ነው? ከአቶ ደስታ ሌዳሞና ከአቶ አብርሃም ማርሻሎ ጋር አይደል የሰሩት??

ጊዜ ዳኛ ‼️‼️

የምርመራ  ዘገባ (ጥቆማ) በፕረዝደንቱ  ወንድም  እና ሌሎች ባለ ስልጣናት መሪነት የተነጠቀው የቀይ መስቀል ማህበር ቤትና ሰፊ መሬት ነገሩ እንዲህ ነው …አቶ ቸሩ  ሌዳሞ የተባሉ ግለሰብ (...
21/07/2025

የምርመራ ዘገባ (ጥቆማ)

በፕረዝደንቱ ወንድም እና ሌሎች ባለ ስልጣናት መሪነት የተነጠቀው የቀይ መስቀል ማህበር ቤትና ሰፊ መሬት

ነገሩ እንዲህ ነው …
አቶ ቸሩ ሌዳሞ የተባሉ ግለሰብ (የሲዳማ ክልል ፕረዝደንት አቶ ደስታ ሌዳሞ ወንድም) በሃዋሳ ከተማ በተለምዶ 05 ሰፈር 7 ላውንጅ ገባ ብሎ የሚገኝ አምስት ሺ ካሬ ሜትር መሬት ላይ የሚገኝ ቤት በተጭበረበረ መንገድ በመውሰድ ለአቶ ይድነቃቸው አስፋው ( የእንጆሪ ላውንጅ ባለቤት) ከሃያ ሶስት ሚልየን ብር በላይ በሆነ ገንዘን መሸጣቸውን መረጃ ይደርሳል።

መረጃው የደረሰው ሚዲያችንም ጉዳዩን ለማጣራት ባደረገው ሙከራ የጥቆማውን ትክክለኛነት የሚያመላክቱ የሰነድና የሰው ማስረጃ አግኝቷል።
*****
ከታች በታይፕራይተር ከተፃፈዉ ደብዳቤ መረዳት እንደሚቻለው ባለይዞታዋ ወይዘሮ ኒሻን ቤቱንና ግቢውን አስይዘው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተበደሩትን 27,314.32 ብር ዕዳ መመለስ ባለመቻላቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሐዋሳ ቅርንጫፍ ሀራጅ አውጥቶ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ሲዳማ ዞን ቅ/ጽ/ቤት 27,314.32 ብር በመክፈል ቤቱንና ቦታውን የግሉ አድርጓል።

ግዢዉን ተከትሎ ቀይ መስቀል ማህበር ቦታው ርክክብ እንዲደረግለት ለባንኩ እና ለሐዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ደብዳቤ ፅፎ ጠይቋል። [በታይፕራይተር የተፃፈ ደብዳቤ በመመልከት መረዳት ይቻላል]

ይሁን እንጂ ቅ/ጽ/ቤቱ የስም ዝውውርና ሳይት ፕላን እንዲሠራለት ተደጋጋሚ ጥያቄ ለሐዋሳ ከተማ ቢያቀርብም በየወቅቱ የቅ/ጽ/ቤቱ ሥራ አስኪያጆች እየተቀያየሩ እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሐዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ጉዳዩን እያጎተቱ ይዞታው ከወ/ሮ ኒሻን ወደ ሲዳማ ዞን ቀይ መስቀል ማህበር ስም ሳይዛወርና የሳይት ፕላንም ሳይሠራ ለዘመናት መቆየቱን ያገኘናቸው መረጃዎች ያሳያሉ።

በ2015 ዓ.ም የመሬት ምዝገባ በካደስትራል ሲጀመር ቦታው ምንም እንኳ ለረጅም ዓመታት በቀይ መስቀል ማህበር እጅ የቆየ ቢሆንም ( መጀመሪያ በክራይ መልክ ከዚያ በግዢ ) ሕጋዊ ፕላንና ሰነድ እንደሌለው በሐዋሳ ከተማ ሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ይደርስበታል።

ውስብስቡ የመሬት ንጥቂያ ሥራ እዚህ ጋ ይጀምራል።

የሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ከዋና ከተማ ማዘጋጀ ቤት ጋር በመተባበር የሲዳማ ቀይ መስቀል ማህበር ቅ/ጽ/ቤት ይዞታዬ ነው ሰለሚለው ቦታ ሕጋዊ ፕላን እንዲያቀርብ በደብዳቤ ይጠየቃል። የቀይ መስቀል ማህበር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤትም በእጁ ያሉትን መረጃዎችና ማስረጃዎች ይዞ ይቀርባል። ሆኖም በሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ይዞታው የቀይ መስቀል ማህበር ቅ/ጽ/ቤቱ አለመሆኑ ይነገረዋል። በዚህ ምክንያት ብዙ ጭቅጭቅ ተነስቶ በቀድሞ የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ረ/ፕ ፀጋዬ ቱኬ አማካኝነት ንብረቱ በቀይ መስቀል ማህብር እጅ እንዲቆይ ይደረጋል።

የአሁን የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ ወደ ኃላፊነት ከመጣ ቦኋላ ቦታው በወ/ሮ ፀዳል ውድነህ ስም የሳይት ፕላን ፎርጅድ ካርታም ተዘጋጅቶለት፣ የ15 ዓመት ውዝፍ ግብር በማትታወቅ ነገር ግን ሕጋዊ ውክልና ሰጥታለች በተባለችው በወ/ሮ ፀዳል ውድነህ ስም እንዲከፈል ይደረጋል።

በወቅቱ የሲዳማ ክልል ቀይ መስቀል ማህበር ቅርንጫፍ ጽ/ቤትና የቦርድ አባላት ፦

1. አቶ ተሰማ ዲማ (ሰብሳቢ)፣
2. ዶ.ር አራርሶ ገረመው (አቃቤ ንዋይ)፣
3. አቶ ዮሐንስ ላታሞ (ፀሐፊ)፣
4. አቶ አክሊሉ አዱላ (አባል)፣
5. ፓስተር ጌቱ አያለው (አባል) ጉዳዩን ከርዕሰ መስተዳደር ጽሕፈት ቤት ጀምሮ በተዋረድ ለሚለመለከተው አካል ሁሉ ቢያሳውቁም ሰሚ ሳያገኙ ቀሩ።

ከዚያ በኋላ የመሬት ንጥቂያ ሴራ ዋና አቀነባባሪ ናቸው የተባሉት አቶ ቸሩ ሌዳሞ (የአቶ ደስታ ሌዳሞ ወንድም) በወቅቱ በአቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ ተባባሪነት ልዩ ኃይል ይዘው ወደ ማህበሩ ፅህፈት ቤት በማምራት በግቢው የሚገኘውን የቡና ተክልና ሙዝ አውድመው፣ የቅ/ጽ/ቤቱ ሠራተኞች ላይ ዝተው፣ የቦርድ አባላቱን አስፈራርተው ግቢውን እንዲለቁ ካደረጉ በኋላ በወ/ሮ ፀዳለ ስም በተዘጋጀው ውክልና ስም ከ 23 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ገንዘብ ለአቶ ይድነቃቸው አስፋው (የእንጆሪ ላውንጅ) ባለቤት እንደተሸጠ በማለዳ ምርመራ ዘገባ ተረጋግጧል።

ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ቢወስደውም የፍትህ ሥርዓቱ በርዕሰ መስተዳድሩ ፍላጎት የተተበተበ በመሆኑ ከሲዳማ ክልል ፍትህ ፈፅሞ ልያገኝ ባለመቻሉ አቤቱታውን ወደ ቀይ መስቀል ማህበር የበላይ ጠባቂ አቅርቦ ምላሽ እየተጠባበቀ ይገኛል።

መንግሥት የህዝብ ተቋማት የበላይ ጠባቂ እንደ መሆኑ ለእነኚህ ተቋማት መወገን ሲገባው በግለሰቦች ስም የማጭበርበሪያ ሰነድ በማዘጋጀት የተቋም መሬት ነጥቆ እስከመሸጥ ድረስ የደረሰ መሆኑን ከታች የተያያዙ ማስረጃዎችን ብቻ በማየት መረዳት ይቻላል።

Hola Media ሆላ ሚዲያ

በክፍለ ዘመኑ አንዴ የሚከሰት ከልቡ ሰው የሆነ መሪ❤አረ አንተስ ትለያለህ🙏
14/07/2025

በክፍለ ዘመኑ አንዴ የሚከሰት ከልቡ ሰው የሆነ መሪ❤
አረ አንተስ ትለያለህ🙏

“አፍሪካን ከቀሪው ዓለም ማገናኘት — Connecting Africa to the World” የሚል መሪቃል በመያዝ እጅግ ውስብስብና ተለዋዋጭ በሆነው የአየር ትራንስፖርት በአፍሪካ ወደርየለሽ የሆ...
14/07/2025

“አፍሪካን ከቀሪው ዓለም ማገናኘት — Connecting Africa to the World” የሚል መሪቃል በመያዝ እጅግ ውስብስብና ተለዋዋጭ በሆነው የአየር ትራንስፖርት በአፍሪካ ወደርየለሽ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ $5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ በማድረግ ቢሾፍቱ ከተማ አቅራቢያ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ የታጠቀ በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነ ግዙፍ የአውሮፕላን ጣቢያ ግንባታ ህዳር ወር ያስጀምራል።

በመስከረም ወር የህዳሴ ግድብን እንደምናስመርቅና በታሪክ የመጀመሪያውን የጋዝ ምርት ለገበያ እንደምናቀርብ ሳይዘነጋ በያዝነው ሽያጭ 2018 ዓ.ም የበጀት ዘመን፦

➊ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ➔ $3 ቢሊዮን ዶላር፣
➋ የአውሮፕላን ጣቢያ (EAL) ➔ $5 ቢሊዮን ዶላር፣
➌ አራት የፍጥነት መንገዶች (ERA) ➔ $10 ቢሊዮን ዶላር፣
➍ የቴሌኮሙኒኬሽን ማስፋፊያ (ETC) ➔ $2ቢሊዮን ዶላር፣
➎ የኢትዮጵያ የኮሚዩኒኬሽን ሳተላይት ➔ $600ሚሊዮን ዶላር፣
➏ በዓባይ ወንዝ ላይ “ZZ” ግድብ ➔ $5.5ቢሊዮን ዶላር፣
➐ ከበርበራ ወደብ አዲስ አበባ የፍጥነት ባቡር ➔ $2 ቢሊዮን ዶላር፣
ጠቅላላ ድምር = $28.1 ቢሊዮን ዶላር

~
..ሌሎች ፕሮጀክቶችን እንመለስባቸዋለን!...

🇪🇹

ኢትዮጵያ ተስፋ አላት !!

«የኢትዮጵያ ዋና ነቀርሳና የጎጠኝነት መፈልፈያ ያረጀና ያፈጀው 'ፌክ' ኢትዮጵያዊነት ነው። 'ፌክ' ኢትዮጵያዊነትን ቀብረን፤ በብስባሹ ላይ ከዜሮ ጀምረን ሁሉንም ብሔር/ ብሔረሰብ የሚወክለውን...
14/07/2025

«የኢትዮጵያ ዋና ነቀርሳና የጎጠኝነት መፈልፈያ ያረጀና ያፈጀው 'ፌክ' ኢትዮጵያዊነት ነው። 'ፌክ' ኢትዮጵያዊነትን ቀብረን፤ በብስባሹ ላይ ከዜሮ ጀምረን ሁሉንም ብሔር/ ብሔረሰብ የሚወክለውን ኢትዮጵያዊነት እናደምቃለን!»

- መ/ር ታዬ ቦጋለ አረጋ

A colorful lake Hare Sheitan.It is close to Addis Ababa 🇪🇹. The beauty of the color is amazing. Water changes its color ...
14/07/2025

A colorful lake Hare Sheitan.It is close to Addis Ababa 🇪🇹. The beauty of the color is amazing. Water changes its color multiple times during the day.

The color changes not only with the season but also with the time difference.

The lake is nestled within sheer cliffs, with a diameter of about 880 meters and a depth of approximately 50 meters.
Significance:

The name "Hare Sheitan" translates to "Devil's Lake," possibly due to local legends or the lake's distinctive appearance. It is a popular tourist attraction, known for its tranquil atmosphere and natural beauty.

2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የትጋትና የስኬት ዓመት ነበር - አቶ አደም ፋራህዛሬ ሀምሌ 07/2017 ዓ.ም የብልፅግና ፓርቲ የ2017 በጀት ዓመት የፓርቲ ስራዎች ማጠቃለያ የግምገማ መድረክ በ...
14/07/2025

2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የትጋትና የስኬት ዓመት ነበር - አቶ አደም ፋራህ

ዛሬ ሀምሌ 07/2017 ዓ.ም የብልፅግና ፓርቲ የ2017 በጀት ዓመት የፓርቲ ስራዎች ማጠቃለያ የግምገማ መድረክ በድሬዳዋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚህ ወቅት የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንትና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ እንደገለፁት 2017 ዓ.ም በጀት ዓመት የትጋትና የስኬት አመት ነበር።

ፓርቲውን በሰብዓዊና በቁሳዊ ሀብት ማጠናከር፤ በዘመናዊ መረጃ ማደራጀት፤ ዲጂታል ብልፅግና እውን ከማድረግና ገዥ ትርክትና ቅቡልነት ከማረጋገጥ አኳያ በትጋት የተከናወኑ ስራዎች ስኬታማ ናቸው ብለዋል።

በአስተሳሰብ፤ በአደረጃጀትና በአሰራር የተዋሃደ ፓርቲ ለመፍጠር የተሰሩ ስራዎች ስኬታማ እንደነበሩ የተናገሩት አቶ አደም ፋራህ፥ በዚህም የፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ እና አምስተኛ ዓመት ምስረታ በዓል በተቀናጀና በተናበበ መንገድ መሳካት ችሏል ነው ያሉት።

የሀገራችንን የኢኮኖሚ ዕድገት ቀጣይነትና ዘላቂነት ያለው እንዲሆን በትኩረት ተሰርቷል በዚህም አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።

ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ህዝቡን በማሳተፍ በተቀናጀ መንገድ መስራት በመቻሉ በአገራችን አንፃራዊ ሰላም መስፈን እንደቻለ ተናግረዋል።

በንቅናቄ የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩ ያወሱት ም/ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ፥ ከተረጂነት ለመውጣት የተከናወኑ ስራዎች የሀገራችንን የተረጂነት ታሪክ ለመቀየር መሰረት የጣሉ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ምክትል ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው እንደጠቀሱት ህዝቡ አካታችች ሀገራዊ ምክክር ላይ እንዲሳተፍ መሰራቱን አመላክተዋል፤ በዚህም አካታች ሀገራዊ ምክክር ሂደት በተሳካ መንገድ እንዲቀጥል ተደርጓል ብለዋል።

ገዥ ትርክትና ቅቡልነት እንዲረጋገጥ በመሰራቱ ሀገራዊ አንድነትን የሚያጎለብቱ አዎንታዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል።

በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ድሎችን ማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በመቅረፍ ለሁለንተናዊ ብልፅግና መረጋገጥ ህዝብን በማሳተፍ መስራት ይገባል ብለዋል።

 !!👌🎯አቶ ጴጥሮስ ወ/ማሪያም የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ ሆነው ተሹመዋል።መልካም የሥራ እና የስኬት ጊዜ ይሁንልህ!👌🎯
14/07/2025

!!👌🎯
አቶ ጴጥሮስ ወ/ማሪያም የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ ሆነው ተሹመዋል።

መልካም የሥራ እና የስኬት ጊዜ ይሁንልህ!👌🎯

አንተ ትችላለህ‼️💪His Excellency Dr Abiy Ahmed Ali  Prime Minister of the Federal Democratic Republic of Ethiopia.Proud to cal...
14/07/2025

አንተ ትችላለህ‼️💪
His Excellency Dr Abiy Ahmed Ali Prime Minister of the Federal Democratic Republic of Ethiopia.
Proud to call you my prime minister.
ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ
fans

ኢትዮጵያ ለምትሻው የአፍሪካ የጋራ ዕድገት መንገድ ከፋች የሆነው ብሪክስ*********************************የትብብር መድረክ የሆነው ብሪክስ ኢትዮጵያ ለምትሻው የአፍሪካ የጋራ...
14/07/2025

ኢትዮጵያ ለምትሻው የአፍሪካ የጋራ ዕድገት መንገድ ከፋች የሆነው ብሪክስ
*********************************

የትብብር መድረክ የሆነው ብሪክስ ኢትዮጵያ ለምትሻው የአፍሪካ የጋራ ዕድገት መንገድ ከፋች መሆኑን ለኤፍ. ኤም አዲስ 97.1 "አዲስ መረጃ" ፕሮግራም አስተያየታቸውን የሰጡ የፖለቲካ ተንታኞች ገለጹ።

ብሪክስ የዓለማችንን 40 በመቶ ሕዝብ የያዘ እንደሆነ ያወሱት የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ጉዳዮች ተንታኙ አቶ ሚካኤል ማስሬ፣ ስብስቡ ከፀጥታ እስከ ሰው ሠራሽ አስተውሎት አጠቃቀም ተፅዕኖ ፈጣሪ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።

በቅርቡ በተካሄደው 17ኛው የብሪክስ ጉባኤ ወደ 40 ሀገራት መሳተፋቸውን አስታውሰው፣ ከአሥሩ አባላት መካከል የሆነችው ኢትዮጵያ የአፍሪካን ድምፅ ይዛ መሳተፏን እና ይህንንም በተግባር ማሳየቷን ተናግረዋል።

በምዕራባውያን የሚዘወረውን የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ አካሄድን ለመቀየር እየሠራ ያለው እና ባለአዳጊ ኢኮኖሚ ሀገራት የመሠረቱት ብሪክስ ሁሉን አቀፍ የዓለም ሥርዓትን ለመፍጠር እየሠራ እንደሆነም አቶ ሚካኤል ተናግረዋል።

ከብሪክስ ስብስብ ጋር የሚጣጣመውን የኢትዮጵያ ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ አካሄድ ኢንቨስትመንትን ከመሳብ አኳያም ለውጥ እያመጣላት እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ የምትከተለው ሰላማዊ የሆነው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲዋ በዕድገቷም ሆነ በፖለቲካ ለውጧ ተቀባይነቷ እየጨመረ እንዲሄድ አድርጓታል ነው ያሉት።

የፖለቲካ ሳይንስ መምህሩ አቶ አዋቂ በቀለ በበኩላቸው፣ ብሪክስ የደቡብ-ደቡብ ጥምረት መሆኑን አውስተው፣ ጥምረቱ የሚያካልለው የዓለም ከፍል በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ድምፅ እንዲኖረው እንደሚያደርገው ተናግረዋል።

ብሪክስ የትብብር መድረክ መሆኑን ጠቅሰው፣ እንደ ኢትዮጵያ እና ግብፅ ያሉ ሀገራት በአንድነት አባል መሆናቸው ጉዳዮቻቸውን ወደ ጠረጴዛ አምጥተው ወደ ጋራ ልማት አጀንዳ እንዲመጡ ያስችላቸዋል ብለዋል።

Address

Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hola Media ሆላ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hola Media ሆላ ሚዲያ:

Share