Hola Media ሆላ ሚዲያ

Hola Media ሆላ ሚዲያ ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና! Hadiya Mass Media is the of voice of voiceless.

በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ መሸጋገሪያ እንጨት ተደርምሶ የበርካታ ሰዎች ህይወት አለፈ። ጃውሳ እሄንንም ፋኖ የወሰደ እርምጃ ነው ልለን ይችላል።በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ...
01/10/2025

በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ መሸጋገሪያ እንጨት ተደርምሶ የበርካታ ሰዎች ህይወት አለፈ። ጃውሳ እሄንንም ፋኖ የወሰደ እርምጃ ነው ልለን ይችላል።

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አረርቲ ማርያም ለግንባታ መሸጋገሪያ የተሰራ እንጨት ተደርምሶ የበርካታ ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡ የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አህመድ ገበየሁ እንደገለጹት፥ የመደርመስ አደጋው የደረሰው ምዕመናን በወረዳው እየተሰራ ያለውን ቤተክርስቲያን ግንባታ በመጎብኘት ላይ በነበሩበት ወቅት ነው፡፡

በአደጋው እስካሁን ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች ህይወት ማለፉንም ፖሊስ ከቦታው ገልጿል።

30/09/2025
ተፈርሟል!ኢትዮጵያ ከራሺያ ጋር የኒውክሌር ሃይል ጣቢያዎችን በማቋቋም፤ በወታደራዊ፤ በቴክኖሎጂ የመሳሰሉት ስራዎች ዙሪያ ወሳኝ ስምምነቶችን ተፈራርማለች። ከዚህ ቀደም በተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች...
26/09/2025

ተፈርሟል!
ኢትዮጵያ ከራሺያ ጋር የኒውክሌር ሃይል ጣቢያዎችን በማቋቋም፤ በወታደራዊ፤ በቴክኖሎጂ የመሳሰሉት ስራዎች ዙሪያ ወሳኝ ስምምነቶችን ተፈራርማለች። ከዚህ ቀደም በተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች ራሺያ በርካታ ኢትዮጵያዊ የኒውክሌር ሳይንስ ባለሞያዎችን አስተምራ አስመርቃለች።

"ምኞት ተግባራችን ሁሉ የተሻለች ኢትዮጵያን በኅብረት ገንብቶ ማቆየት ነው"       ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድይህ ትውልድ ጀምበር ወጥታ በገባች ቁጥር ለመጪው ትውልድ መስፈንጠሪያ የሚሆን ብሩህ እ...
25/09/2025

"ምኞት ተግባራችን ሁሉ የተሻለች ኢትዮጵያን በኅብረት ገንብቶ ማቆየት ነው"
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

ይህ ትውልድ ጀምበር ወጥታ በገባች ቁጥር ለመጪው ትውልድ መስፈንጠሪያ የሚሆን ብሩህ እና ፅኑ መሰረት ደልድሎ ያወርሳል። ምኞት ተግባራችን ሁሉ የተሻለች ኢትዮጵያን በኅብረት ገንብቶ ማቆየት ነው።

 🇪🇹ክብርት ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው 35 ትምህርት ቤቶችን የገነባች ታሪክ በወርቅ ብዕር የሚፅፈው ስራ የሰራች የዘመናችን ጀግኒት። ❤️❤️❤️HighLight
25/09/2025

🇪🇹
ክብርት ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው 35 ትምህርት ቤቶችን የገነባች ታሪክ በወርቅ ብዕር የሚፅፈው ስራ የሰራች የዘመናችን ጀግኒት። ❤️❤️❤️
HighLight

የበለፀገ አይምሮ የበለፀገውን አውቀት ያካፍላል። ዲያቢሎስን  ያንገበገበውና ያሳበደው፣ ፈረሶቹንም ያንጫጫቸው አውነቱ ብልፅግና የሚለው ስም ነው። ስሙ ከባድ ነው። ዲያቢሎስን አስነቅሎታል። የ...
25/09/2025

የበለፀገ አይምሮ የበለፀገውን አውቀት ያካፍላል። ዲያቢሎስን ያንገበገበውና ያሳበደው፣ ፈረሶቹንም ያንጫጫቸው አውነቱ ብልፅግና የሚለው ስም ነው። ስሙ ከባድ ነው። ዲያቢሎስን አስነቅሎታል። የዲያቢሎስ ጆሮዎች በየ ግዜው ይጭራሉ ይጭራሉ አይሳካላቸውም።

ከዶሮ ጋር ዶሮ አትሁኑ ከንስሩ መሪያችን ጋራ ንስር ሁኑ አሰብ በቅርቡ ገቢ ትሆናለች አትጠራጠሩ የኛ ነች የትላንት ስራዎቹ ለዛሬ ምስክር ናቸው።

ኢትዮጵያ አሰብን ያጣችበት መንገድ ጨዋታ የሚመስል ነው‼️በመጀመሪያ አሰብ አካባቢ ጣልያኖች የተቆጣጠሩትና የሰፈሩበት በቀላል መንገድ ነበር። እዚያ አካባቢ የሚኖሩ አንድ ሱልጣን ለአሳ አስጋሪ...
25/09/2025

ኢትዮጵያ አሰብን ያጣችበት መንገድ ጨዋታ የሚመስል ነው‼️

በመጀመሪያ አሰብ አካባቢ ጣልያኖች የተቆጣጠሩትና የሰፈሩበት በቀላል መንገድ ነበር። እዚያ አካባቢ የሚኖሩ አንድ ሱልጣን ለአሳ አስጋሪ ጣልያናዊ የተወሰነ አካባቢ የታጠረችን ቦታ ሸጡላቸው። ከዚያም በኋላ እንደፈልፍል እየፈለፈሉ ኤርትራ የምትባለውን አካባቢ ጣልያኖቹ በቁጥጥር ስር አደረጓት። አፄ ምኒልክ ከአድዋ ወደዚያ ማለፍ አቅም አልነበራቸውም። ምክንያቱም በኢትዮጵያ ታሪክ እጅግ አሰቃቂ የሚባሉ የክፉ ቀን ጊዜ ነበር። የኢትዮጵያ ከብቶች በበሽታ አልቀው እርሻ ቆሞ ገበሬውም ከባድ ረሀብ ላይ ነበር። ስንቅ አልነበረም ይህን እንደ አጋጣሚ ተጠቅመው ጣልያኖች ግዛታቸውን አስፋፉ። ባህሩን ተከትለው ወረሩትም።

በዚያ ስፍራም ከኤርትራዊ ሰሜናዊ ጫፍ እስከ ጅቡቲ መጨረሻ ድረስ ያለው ስፍራ ሲሆን ይህም ከ1000ኪ.ሜ በላይ የሚሆን የባህር በር ነው። 1000ኪ.ሜ በላይ የባህር በር የነበራት ሀገር እንዴት 10ኪ.ሜ ወይም 20ኪ.ሜ ባህር በር ትከለከላለች?!

ኢትዮጵያ ባህር በር የሌላት የአለም የመጨረሻ ትልቋ ሀገር ናት። ትልቅ ህዝብ ይዛ ባህር በር መውጫ የተነፈገች ሀገር መሆን ችላለች።

ሌላው ቀርቶ ከአፍሪካ በስተምዕራብ ያለው አትላንቲክ ውቅያኖስ ተራራ ራሱ የጥንታዊ ግሪካውያን አሳሾች ብለው ካርታ የሰሩለት መሆኑን ድርሳናት ያረጋግጣሉ። ኢትዮጵያ የባህር አይደለም የውቅያኖስ ባለቤት የነበረች ሀገር ናት። ኢትዮጵያ በአብረሀ ወአፅበሀ ዘመን ቀይ ባህርን ተሻግራ የዛሬ የመንና ኦማን መሰል ሀገሮችን ታስተዳድር ነበር። አንደ ውቅያኖስ ጭምር የራሷ እንደነበርም የትኛውም አካል ከታሪክ መረዳት ይችላል። አሁን ባህር በር ስጡኝ ስትል መንጫጫት የነበረውን ራስ ወዳድነታቸውን ካላሳየ በስተቀር ኢትዮጵያ ከያዘችው አቋም የሚያነቃንቃት አይደለም።

ለኢትዮጵያ ቅርብ የሆነው የቀይ ባህር ክፍል ቤይሉል ይባላል። ቤይሉል ከአሰብ ወደብ በሰሜን በኩል የሚገኝ የቀይ ባህር ዳርቻ ነው። በኢትዮጵያ በኩል ለቀይ ባህር ቅርብ የሆነ ቦታ በአፋር ክልል የቡሬ መንደር ነች። ይሄም ከመስቀል አደባባይ እስከ ቢሾፍቱ ካለው የሚርቅ አይደለም።

ሆኖም እንዴት በቅርብ ርቀት ካለው ባህር መውጫ እናጣለን? እንዴትስ ይሄን ተቀብለን እንኖራለን? በርግጥ መለስ ዜናዊና ስብሀት ነጋ ተቀብለውት አጀንዳውም እንዳይነሳ አርገውት ኖረዋል። ኢትዮጵያውያን ግን አልተቀበሉትም ነበር። ደግ ቀን መጥቶ ዛሬ ጥያቄው በመንግስት ደረጃ ተይዟል።.......

(Reposted)

የሻዕቢያ እና የህዉሃት ሴራ ከሽፏል ‼️******* የሻዕቢያ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ፀረ-ሰላም ሃይሎችን በማስተባበር  የጀመረዉ  የዉክልና  ዉጊያ ሳይሳካለት ከሽፏል፤ ህወሃ...
25/09/2025

የሻዕቢያ እና የህዉሃት ሴራ ከሽፏል ‼️
*******
የሻዕቢያ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሱ ፀረ-ሰላም ሃይሎችን በማስተባበር የጀመረዉ የዉክልና ዉጊያ ሳይሳካለት ከሽፏል፤ ህወሃትን ደግፉ ግጭት ለመቀስቀስ የሚያደርገው ጥረት ፍሬ አልባ ሆኗል።
አሁንም ሻዕቢያ እና ህዉሃት አይናቸዉ እያየ በመደመር ትዉልድ ቁርጠኝነት እና ትጋት በቀይ ባህር ላይ የነበረው የኢትዮጵያ ታላቅነት ዳግም ሊታይ ከጫፍ ደርሷል ።
በብልሃት እና በዲፕሎማሲ ቀይ ባህር ወደ እናት ሃገሩ ለማስመለስ ተቃርበናል፡፡

ገዱ አንዳርጋቸዉ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ወደ ትኬት ቆራጭነት አድጓል 😂😂******የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት  የአማራ ህዝብ እርስት ወልቃይትን በአደባባይ  ለህዉሃት ፈርመው...
25/09/2025

ገዱ አንዳርጋቸዉ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ወደ ትኬት ቆራጭነት አድጓል 😂😂
******
የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት የአማራ ህዝብ እርስት ወልቃይትን በአደባባይ ለህዉሃት ፈርመው በማስረከብ ታሪካቸው የሚታወቁት እና ወደ ፌደራል መንግስት ከመጡ በኋላ የሃገሪቱን ትልቁን ስልጣን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ጽንፈኛውን ጃዊሳ በመደገፍ ሃገር አፍራሽ ድርጊት ላይ ተዘፈቀዉ የቆዩት ገዱ አንዳርጋቸዉ ከስልጣናቸዉ ተሸቀንጥረዉ መጣላቸዉ የሚታወቅ ነዉ፡፡
ለጃዊሳዉ ቡድን ድጋፍ ለማድረግ ወደ ዉጭ የተሰደዱት አቅመ-ቢሱ ገዱ በውጭ ያሉት የጽንፈኛው ደጋፊዎች አምነው ስላልተቀበልዋቸው ባሰቡት ልክ በሙያቸው ስራ ስላላገኙት "የዕለት ከርሳቸዉ መሙያ የፓርኪንግ ስራ ገንዘብ መቀበል" እየሰሩ እንደሆነ ከታማኝ ምንጮች ሰምተናል፡፡
ገዱ አንዳርጋቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ወደ ትኬት ቆራጭ ወይም ገንዘብ ተቀባይ (parking attenedant) ሆነው መቀጠራቸው በስተርጅና ትልቅ የፖለቲካና የሞራል ሽንፈት ማሳያ ነዉ፡፡
የገዱ አይነት ውርደት ከዘራችሁ አይድረስ ጎበዝ 😂

ይህን ጀግና አለማድነቅ ምቀኝነት ነዉ አንድ ግዜ ጀግና በሉት።
14/09/2025

ይህን ጀግና አለማድነቅ ምቀኝነት ነዉ አንድ ግዜ ጀግና በሉት።

ከትዉልድን ትዉልድ የተሸጋገረዉን የዘመናት ቁጭትን ፀሎት  ተመልክቶ በሳቅና እልልታ የሞላዉ ፈጣሪ አምላክ ይመስገን !
12/09/2025

ከትዉልድን ትዉልድ የተሸጋገረዉን የዘመናት ቁጭትን ፀሎት ተመልክቶ በሳቅና እልልታ የሞላዉ ፈጣሪ አምላክ ይመስገን !

Address

Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hola Media ሆላ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hola Media ሆላ ሚዲያ:

Share