Hola Media ሆላ ሚዲያ

Hola Media ሆላ ሚዲያ ትናንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና! Hadiya Mass Media is the of voice of voiceless.

ያለፉት ሁለት ዓመታት ጉዞ አድካሚ ቢሆንም በርካታ ያጋጠሙ ችግሮችን ማስተካከል በመቻሉ  ክልሉ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ መሆኑን ተገንዝበናል :- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) (ሆ...
05/12/2025

ያለፉት ሁለት ዓመታት ጉዞ አድካሚ ቢሆንም በርካታ ያጋጠሙ ችግሮችን ማስተካከል በመቻሉ ክልሉ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ መሆኑን ተገንዝበናል :- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

(ሆሳዕና፣ህዳር 26/2018)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)20ኛውን የኢትዮጵያ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በማስመልከት ከመገናኛ ብዙሀን ጋር ቆይታ አድርገዋል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )እንደገለጹት ከሌሎች የሀገሪቱ ህዝቦች ጋር ያለንን መስተጋብር ወደ ላቀ ደረጃ በማድረስ በወዳጅነት፣በወንድማማችነትና በእህታማማችነት ላይ የተመሰረተ ስራ ለመስራት ጽኑ ፍላጎት አለን ብለዋል።

በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች የሚከበሩ የመስቀል እና የዘመን መለወጫ በዓላት ብራንድ አድርጎ ማውጣት ይቻላል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል።

በክልሉ በኢንዱስትሪ፣በቱሪዝም እንዲሁም ለኤክስፖርት የሚሆኑ የእርሻ ምርቶችን በማስፋፋት ብራንድ ማድረግ የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት ተገቢ ስለመሆኑም አመላክተዋል።

በእነዚህ እና በመሳሰሉት ነጥቦች ላይ ጠንክረን በመስራት የክልሉ መገለጫ የሚሆኑ ጉዳዮች ላይ ብራንድ እንዲኖረን እንሰራለን ብለዋል።

ባለፉት ሁለት ዓመታት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በርካታ ናቸው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ መጀመሪያ ችግሮችን በደንብ መለየት እና መረዳት፣ለችግሮች መፍትሄ ለማበጀት ደረጃቸውን ጭምር መለየት ላይ ትኩረት አድርገናል ሲሉም ጠቁመዋል።

ካጋጠሙን ተግዳሮቶች ውስጥ የሰላም እጦት፣የደመወዝ ፣የማዳበሪያ፣ የጥሬ ገንዘብ እዳ እና ሌሎች በርካታ ችግሮችን መጥቀስ ይቻላል ብለዋል።

ሰራተኛው እና አመራሩ ለረጅም ጊዜ ስራ ላይ ባለመኖሩ በተቀዛቀዘ ስሜት ላይ ነበር ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በሌላ በኩል ከአፈር ማዳበሪያ ጋር የተያያዘ ስርዓት አልበኝነትም ተስተውሎ እንደነበር ጠቅሰዋል።

የእነዚህን ችግሮች ደረጃ በመለየት እንዴት እንፍታቸው፣መቼ እልባት እንስጣቸው በሚል እሳቤ አቅደን ወደ ተግባር ገብተናል በማለት አብራርተዋል።

አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ አንጻር አብዛኛዎቹን ችግሮች በጊዜ ሂደት መፍታት ተችሏል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ አልፎ አልፎ የሚመላለሱ ችግሮች ሊኖሩ ስለሚችሉ እያስተካከልን እንሄዳለን ብለዋል።

ባለፉት ሁለት ዓመታት ሁሉም አመራር ርብርብ ያደረገበት ስራ የሰላም ማስከበር ተጠቃሽ ስለመሆኑ የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ በተደጋጋሚ ስለ ዘላቂ ሰላም ስናነሳ ሰላም ወዳዱ ህብረተሰብ ከመንግስት ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

ነገር ግን በክልላችን በተለያየ ጊዜ ችግር ለመፍጠር የሚፈልጉ አካላት ይሄ ጉዳይ በጥብቅ ዲሲፕሊን እየተመራ መሆኑን ሲገነዘቡ ይከፋቸዋል ሲሉም ጠቁመዋል።

በዘርፉ የሚደረገውን ጥረት ለመቀልበስ በፕሮፓጋንዳ ስራ ላይ መጠመዳቸውንም ጠቅሰዋል።

በሰላም ጉዳይ ላፍታም ሳንዘናጋ ዛሬም፣ነገም ለሚቀጥሉት ቀናት ወራትና ዓመታት ስለ ሰላም እንሰራለን ብለዋል።

ሌላው ትኩረት አድርገን የሰራንበት ጉዳይ ግብርና ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ ቅድመ በልግና ጸደይን ጨምረን በቂ የምርት እድገት እንዲኖር በትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑም በአብነት ጠቅሰዋል።

ከዚህ ቀደም በክልሉ በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ገቢ ሲሰበሰብ እንደነበር ያስታወሱት ርዕሰ መስተዳድሩ አሁን ከዛሬ ሁለትና ሶስት ዓመታት ሲሰበሰብ ከነበረው ገቢ በእጥፍ አሳድገናል ብለዋል።

አንድ ከተማ አሊያም ክልል እራሱን ማሳደግ የሚፈልግ ከሆነ የገቢ እና የንግድ ስርዓቱን ፈትሾ ማስተካከል አለበት ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

በትምህርት፣በጤና በኢንቬስትመንት ፣በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም በመሰረተ ልማት ዘርፍ እንደ ውሃ፣መንገድ፣መብራት ቴሌኮም እና መሰል የልማት መስኮችን ማሟላት የክልሉ መንግስት የእለት ተዕለት ስራ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በክልሉ ህገወጥነትን መከላከል ሌላው አብይ የትኩረት መስክ መሆኑን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ ህገወጥነትን ስንከላከል ደግሞ የኑሮ ውድነትን መቀነስ ያስችላል ብለዋል።

የመጣንበት መንገድ አድካሚ ቢሆንም በርካታ ጉዳዮችን ለማሻሻል ሞክረናል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩእነዚህ በቂ ባለመሆናቸው ተጨማሪ ስራ መስራት ያስፈልጋል።

በክልሉ የቤተሰብ ብልጽግናን ለማሳካት በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ በግብርናው መስክ ጠንክሮ በመስራት ከእለት ፍጆታ ባለፈ ገበያውን ማረጋጋት የሚያስችል አቅም መፍጠር ያስፈልጋል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

የመደመር ፍልስፍና እና እሳቤ ከተለያዩ ችግሮች ወጥተን ወደ አንድ እንምጣ፣ወደ ኋላ ከሚጎትተን አጀንዳ በመውጣት በጋራ ጉዳዮቻችን ላይ በማተኮር መስራት ተገቢ ስለመሆኑም አመላክተዋል።

የጋራ አጀንዳችን ከሆኑ ጉዳዮች ውስጥ ልማት፣ዘላቂ
ሰላም እንዲሁም የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ስራዎች ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

የሁለት ዓመታት ጉዞችንን ስንፈትሽ ክልሉ በትክክለኛ አቅጣጫ ላይ መሆኑን ተገንዝበናል በማለት ነበር ርዕሰ መስተዳድሩ የገለጹት።

ለኢትዮጵያ ከፍታ ከግብርና መር ኢኮኖሚ በተጓዳኝ ማዕድን፣ቱሪዝምን፣ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ እንዲሁም በኢንዱስትሪ ዘርፉ ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባል ብለዋል።

የሰላም ሰገነቷ ሆሳዕና ሙሽሮችን እየጠበቀች ነው************ወትሮም የሰላም፣ የመቻቻል፣ የአንድነትና የፍቅር አምባ የሆነችው ሆሳዕና ከየአቅጣጫው የሚመጡ በርካታ እንግዶችን ሞቅ ባለ ፈ...
05/12/2025

የሰላም ሰገነቷ ሆሳዕና ሙሽሮችን እየጠበቀች ነው

************

ወትሮም የሰላም፣ የመቻቻል፣ የአንድነትና የፍቅር አምባ የሆነችው ሆሳዕና ከየአቅጣጫው የሚመጡ በርካታ እንግዶችን ሞቅ ባለ ፈገግታ ለመቀበል ተዘጋጅታለች።

በከተማዋ በሚገኙ ስማርት የመብራት ምሰሶዎች እና ከፊት ባሉ ቤቶች ደጅ ላይ የተሰቀሉ የኢትዮጵያ እና የፌዴሬሽኑ አባል ክልሎች ሰንደቅ ዓላማዎችን ንፋስ ሲያውለበልብ እንግዶች እንኳን ወደ ሆሳዕና በሰላም መጣችሁ የሚሉ ይመስላሉ።

ከሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተውጣጡ የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ልዑካን የሆሳዕናውን በረከት ለመቋደስ ወደዚህች የሰላም አምባ እየተመሙ ይገኛሉ፡፡

እንግዳ ወደዱ ህዝብ በዱባንቾ፣ በአምብቾ እና በሀይሴ በሮች ወደ ሆሳዕና ከተማ ሲገቡ አቀባበል ለማድረግ ዝግጅት አድርጓል።

እንግዶቿን ለመቀበል ወገቧን ታጥቃ ስትደግስና ሽርጉድ ስትል የሰነበተችው ሆሳዕና ከሰዓታት በኋላ ሙሽሮችን መቀበል ትጀምራለች።

በበዓሉ ዋዜማ ምሽት የሀድያ ዞን አስተዳደር በ'ሀዲይ ነፈራ' ከሁሉም አካባቢዎች የሚመጡ ከ3ሺህ በላይ እንግዶች የእራት ግብዣ ለማድረግ ተዘጋጅቷል። ይህም የሀድያ የእንግዳ አቀባበል ባህልና እሴት ለማስተዋወቅ ምቹ አጋጣሚ የሚፈጥር ነው።

በህዳር 29 በዓሉ በርካታ ዜጎች በታደሙበት በሆሳዕና ከተማ በአብዮ ኤርሳሞ መታሰቢያ ስታዲየም በደማቅ ሁኔታ ይከበራል ተብሎ ይጠበቃል።

30/11/2025

ሃያኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል...

መሪነት + እናትነት + ብቃት + ትጋት + ውጤት +..........
30/11/2025

መሪነት + እናትነት + ብቃት + ትጋት + ውጤት +..........

‘’ከነገ ሕልማችን ለመድረስ፣ ድልድዩን መዘርጋት ያስፈልጋል’’የመደመር መንግሥት ገጽ 344፣2018 ዓ.ምከትናንት በተሳበ፣ ዛሬ ላይ በተቃኘ እንጉርጉሮ ኃይላችን ዝሎ፣ ቅስማችን ተሰብሮ፣ እህ...
28/11/2025

‘’ከነገ ሕልማችን ለመድረስ፣ ድልድዩን መዘርጋት ያስፈልጋል’’
የመደመር መንግሥት ገጽ 344፣2018 ዓ.ም

ከትናንት በተሳበ፣ ዛሬ ላይ በተቃኘ እንጉርጉሮ ኃይላችን ዝሎ፣ ቅስማችን ተሰብሮ፣ እህህ በሚል ዜማ ነጋችንን ተሰርቀናል፡፡ ትናንትን ከዛሬ፤ ዛሬን ከትናንትና ከነገ ካላስተሣሠርን የጋራ ነገ የለንም፡፡ በተሰበረ ድልድይ፣ ባልጸና መሰላል መሻገር አይቻልም፡፡ ከፍታም አይገኝም፡፡ ከትናንት ጫፍ ተነሥተን በዛሬ ምንጣፍ ተጉዘን፣ ከነገ ሕልማችን ለመድረስ፣ ድልድዩን መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡

እንኳን አደረሰን 20 ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ህዳር 29/2018 ዓ.ም በሆሳዕና ከተማ በድምቀት ይከበራል።
28/11/2025

እንኳን አደረሰን 20 ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ህዳር 29/2018 ዓ.ም በሆሳዕና ከተማ በድምቀት ይከበራል።

28/11/2025

20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች በዓል በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ ቅድሚያ ዝግጅቱ ተጠናቋል።

መሪነት _በሀሳብም በተግባርም  ሞዴል መሆን ነዉ፣ልዩ ልዩ  አቅሞችን አስተባብሮ ለዉጤታማነት መሥራትና ለህብረተሰባዊ ተጠቃሚነት መትጋት ነዉ።ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ( ዶ/ር)
28/11/2025

መሪነት _በሀሳብም በተግባርም ሞዴል መሆን ነዉ፣ልዩ ልዩ አቅሞችን አስተባብሮ ለዉጤታማነት መሥራትና ለህብረተሰባዊ ተጠቃሚነት መትጋት ነዉ።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ( ዶ/ር)

ሰባት ዓመታት የለውጥ ጉዞ፡ ትውልድ ሲቆጭበት የኖረውን ታሪክ የለወጠ መንግስት!በጠ/ሚ/ዶ/ር/ዐቢይ አህመድ የሚመራው የለውጡ መንግስት ባለፉት ሰባት አመታት በሀገራችን በልዩነት የሚጠቀሱ ስኬ...
27/11/2025

ሰባት ዓመታት የለውጥ ጉዞ፡ ትውልድ ሲቆጭበት የኖረውን ታሪክ የለወጠ መንግስት!

በጠ/ሚ/ዶ/ር/ዐቢይ አህመድ የሚመራው የለውጡ መንግስት ባለፉት ሰባት አመታት በሀገራችን በልዩነት የሚጠቀሱ ስኬቶችን ማስመዝገቡ ብቻ ሳይሆን በጣም ባጠረ ጊዜ ውስጥ ትውልድ ሲቆጭባቸው የኖረን የተፈጥሮ ሀብታችንን ተጠቅመን ውጤት ያለማስመዝገብን ታሪክን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ መንግስት በመሆኑ ተፅዕኖ ፈጣሪነቱን ያጎላዋል። ብዙዎች በአሁኗ ኢትዮጵያ ውስጥ ሊከወን ቀርቶ በቅርብ ዘመን እንኳን ይታሰባሉ ብለው የማይገምቱትን ታላላቅ አጀንዳዎችን የተገበረ በድል ጎዳና እየተራመደ የሚገኝ አዋራን አራግፎ አሻራ ማኖርን ልምዱ ያደረገ የለውጥ መንግስት ነው። በጠቅላዩ የሚመራው የለውጡ መንግስት በኢትዮጵያ አዲስ የስራ ባህል ያስተዋወቀ ኢትዮጵያን ከውድቀት ታድጎ ወደ ቀደመ ሀያልነቷና ገናናነቷ የመለሰ ክስተት የሆነ መንግስት ነው።

የ20ኛው የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ለማክበር ከየክልሉ የሚመጡ የባህል አምባሳደር አቀባበል ዙሪያ የክልሉ ንዑስ ኮሚቴ ከሀድያ ዞን ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድር...
27/11/2025

የ20ኛው የኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል ለማክበር ከየክልሉ የሚመጡ የባህል አምባሳደር አቀባበል ዙሪያ የክልሉ ንዑስ ኮሚቴ ከሀድያ ዞን ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል ።

በአፋር የተከሰተው ቮልካኖ በህንድ የአየር በረራ ማስተጓጎሉ ተዘገበ********ያለፈው እሁድ በኢትዮጵያ አፋር ክልል የተፈጠረው የቮልካኖ ፍንዳታ በህንድ የአየር በረራዎች እንዲሰረዙ፣ እንዲዘ...
26/11/2025

በአፋር የተከሰተው ቮልካኖ በህንድ የአየር በረራ ማስተጓጎሉ ተዘገበ
********
ያለፈው እሁድ በኢትዮጵያ አፋር ክልል የተፈጠረው የቮልካኖ ፍንዳታ በህንድ የአየር በረራዎች እንዲሰረዙ፣ እንዲዘገዩ እና የበረራ አቅጣጫ እንዲቀይሩ ማስገደዱን የሀገሪቱ ሲቪል አቬሽን ባለስልጣን ባወጣው ማስጠንቀቂያ መልዕክቱ አስታውቋል።

በፍንዳታው የተፈጠረው ጭስ በሰዓት ከ100 እስከ 200 ኪ/ሜ ተጉዞ በሀገሪቱ ሰሜን ምዕራባዊ ሰማይ ላይ 10 ኪ/ሜትር ከፍታ ላይ እየተንሳፈፈ ይገኛል ሲል የህንድ ሜትሮዎሎጂ ኤጀንሲ ጨምሮ ገልጿል።

ኢንዲጎ፣ አካሳ ኤር እና የደች አየር መንገድ ኬኤልኤምን ጨምሮ ዋና ዋና አየር መንገዶች በአመድ ጭስ ምክንያት አንዳንድ በረራዎችን ለመሰረዝ ተገደዋል።

በዴሊህ አየር ማረፊያ እንደ ሆንግ ኮንግ፣ ዱባይ፣ ጄዳ፣ ሄልሲንኪ፣ ካቡል እና ፍራንክፈርት ወዳሉሉ መዳረሻዎች የሚደረጉ በርካታ ዓለም አቀፍ በረራዎችም ተሰርዘዋል።

ሌሎች በረራዎችም እንዲሁ አቅጣጫ ለመቀየር መገደዳቸውን ወይን የተሰኘው የሀገሪቱ ሚዲያ አስነብቧል።

Hola Media ሆላ ሚዲያ

በሐዋሳ ከተማ በማርበርግ ቫይረስ የተያዘ ሰው መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ******ግለሰቡ በጂንካ ከተገኘው የመጀመሪያው የማልበርግ ቫይረስ ተጠቂ ጋር ንክኪ የነበረው ወደ አካባቢው ተጉ...
26/11/2025

በሐዋሳ ከተማ በማርበርግ ቫይረስ የተያዘ ሰው መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ
******
ግለሰቡ በጂንካ ከተገኘው የመጀመሪያው የማልበርግ ቫይረስ ተጠቂ ጋር ንክኪ የነበረው ወደ አካባቢው ተጉዞ ወደ ሃዋሳ ተመላሽ የነበረ ነውም ተብሏል።

የጤና ሚኒስቴርና የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በማርበርግ ቫይረስ ዙሪያ እየሰሩት ያለውን ስራ በተመለከተ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ቫይረሱ ከተከሰተበት ከህዳር 5ቀን እስከ ህዳር 17ቀን 2017ዓ.ም ድረስ 73 የላብራቶሪ ምርመራዎች ተደርገዋል ያሉት ሚኒስትሯ በዚህም 11 ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተዋል፤ 6ቱ ህይወታቸው አልፏል፤ 5ቱ ደግሞ በህክምና ላይ ናቸው ማለቱን ሸገር ሬዲዮ ዘግቧል።
Hola Media ሆላ ሚዲያ

Address

Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hola Media ሆላ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hola Media ሆላ ሚዲያ:

Share