Malela News

Malela News It is intended to enable people find current issues about Hossana town and Hadiya Zone

አርሰናል ለሚኬል አርቴታ አዲስ ኮንትራት ለመስጠት ንግግር ጀምሯል።አርቴታ በአርሰናል ከሁለት አመት በታች ኮንትራት ይቀረዋል ተብሏል።
14/11/2025

አርሰናል ለሚኬል አርቴታ አዲስ ኮንትራት ለመስጠት ንግግር ጀምሯል።አርቴታ በአርሰናል ከሁለት አመት በታች ኮንትራት ይቀረዋል ተብሏል።

በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ ነውሆሳዕና፡ ጥቅምት 25/2018 ዓ/ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ወደ ስራ ከገባ...
04/11/2025

በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ ነው

ሆሳዕና፡ ጥቅምት 25/2018 ዓ/ም

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ወደ ስራ ከገባ በኋላ ለተገልጋዮች ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

የማዕከሉ ስራ አስኪያጅ ከበደ ሻሜቦ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት፥ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ባለ ጉዳዮች ጊዜያቸውና ገንዘባቸው ሳይባክን ምቹ አገልግሎት እንዲያገኙ አስችሏል፡፡

ከዚህ ቀደም ህብረተሰቡ አገልግሎት ለማግኘት ወደተለያዩ ተቋማት ለአላስፈላጊ ወጪ ይዳረግ እንደነበር አስታውሰው፥ አሁን ላይ በአንድ ጣሪያ ስር የተቀናጀና ቀልጣፋ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል ነው ያሉት፡፡

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በክልሉ በሁሉም አገልግሎቶች ላይ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣና ችግር ፈቺ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ተገልጋዮች ክፍያ የሚፈፅሙበት በዲጂታል ሥርዓት መኖሩ ሙስናና ብልሹ አሰራርን የሚያስቀር መሆኑን ገልጸው፥ ህብሰረተሰቡ ወደ ማዕከሉ በመምጣት ያለ ተጨማሪ ወጪ እና እንግልት ፈጣን አገልግሎት በአንድ ቦታ ማግኘት ይችላል ብለዋል፡፡

ሰባት ተቋማት በማዕከሉ እንደሚገኙና 20 ያህል አገልግሎቶች ለማህበረሰቡ እየተሰጡ ሲሆን፥ በቀጣይ በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ወደ 60 ከፍ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በክልሉ በአምስት ከተሞች ለማስፋት እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

አዲሱ የመንግሥት ሰራተኞች የደመወዝ እርከን ይፋ ሆኗል።‎‎የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ይፋ ያደረገው አዲሱ የደመወዝ እርከን እንደሚከተለው ቀርቧል።‎‎
02/10/2025

አዲሱ የመንግሥት ሰራተኞች የደመወዝ እርከን ይፋ ሆኗል።

‎የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ይፋ ያደረገው አዲሱ የደመወዝ እርከን እንደሚከተለው ቀርቧል።

አርሰናል እውነትም ክለብ!!!
28/09/2025

አርሰናል እውነትም ክለብ!!!

09/09/2025
‎ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የለውጥ ሀሳቦችን ከማፍለቅ ባሻገር የቴክኖሎጂና ባህል እሴቶች መጎልበቻ ማዕከላት እንደመሆናቸው ለሀገር ግንባታ ጉልህ ሚና እየተወጡ መሆኑን የሀዲያ ዞን ዋና አስተ...
08/09/2025

‎ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የለውጥ ሀሳቦችን ከማፍለቅ ባሻገር የቴክኖሎጂና ባህል እሴቶች መጎልበቻ ማዕከላት እንደመሆናቸው ለሀገር ግንባታ ጉልህ ሚና እየተወጡ መሆኑን የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ገለፁ።

‎ዜድ ቫሊዩ ኮሌጅ ሆሳዕና ካምፓስ በዲፕሎማ ፣በመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ መርሃግብር ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቋል።

‎በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ እንደገለፁት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የለውጥ ሂደቶችን ከማፍለቅ በተጨማሪ የመልካም አስተዳደር ፣የቴክኖሎጂና ባህል እሴቶች መጎልበቻ ማዕከላት ናቸው።
‎መንግስት የትምህርቱን ዘርፍ በመደገፍ ጥራቱንና ተደራሽነቱን ለማስጠበቅ ስትራቴጂዎችን ቀርጾ በትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

‎ከዚህም ባሻገር ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተለየ ድጋፍ በማድረግ የተማረ እና የሰለጠነ ማህበረሰብ ከማፍራት አንፃር ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ አቶ ማቴዎስ ተናግረዋል።

‎ተመራቂ ተማሪዎችም በኮሌጁ ቆይታቸው ባገኙት ዕውቀት በማህበራዊ ህይወት ፣በአብሮነትና መቻቻል ባህል ሀገርንና ህዝብ በታማኝነትና በቁርጠኝነት እንዲያገለግሉም ዋና አስተዳዳሪው መልዕክት አስተላልፈዋል።

‎የዜድ ቫሊዩ ኮሌጅ ፕሬዝዳንት አቶ ዘውዴ ተሾመ ኮሌጁ ለስም ሳይሆን ለዕውቀት መስራት በሚል መርህ ላይ በመመስረት ብቁና በራሱ የሚተማመን ትውልድ ለመፍጠር በትጋት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

‎ኮሌጁ በብዙ ውጣውረድ ውስጥ ቢያልፍም የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ይበልጥ በመቋቋም ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎችን በመቅረፅ የሚጠበቅበትን ድርሻ በተገቢው ሁኔታ እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።

‎ኮሌጁም ለሀገር ወገን መከታ የሚሆንና የተማረ እንዲሁም በስነምግባር የታነፁ ዜጎችን የመፍጠር ሀላፊነት አንግቦ እየተገበረ እንደሚገኝም አቶ ዘውዴ አንስተዋል።

‎በዕለቱም በተለያዩ የትምህርት ደረጃዎች 831 ተማሪዎችን ማስመረቅ የቻለው ኮሌጁ ባለፉት አምስት ዓመታት ለአከባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ከፍተኛ ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ የገለፁት ደግሞ የኮሌጁ አካዳሚክ ዲን አቶ ምስጋና አዛዥ ናቸው።

‎ተመራቂ ተማሪዎች ወደማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ በሥራ ዓለም ጥራትን፣ትዕግስትንና ትጋት በመላበስ ማገልገል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

‎የዕለቱ ተመራቂ ተማሪዎች በሰጡት አስተያየት ከኮሌጁ ባገኙት ዕውቀትና ክህሎት ለማህበረሰቡ የተሟላና በዕውቀት የተደገፈ አገልግሎት ለማበርከት መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል።

የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ቀረበ።የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ቀርቧል፡፡የረቂቅ በጀቱን መግለጫ የገንዘብ...
10/06/2025

የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ቀረበ።

የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ቀርቧል፡፡

የረቂቅ በጀቱን መግለጫ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አቅርበው ውይይት እየተካሄደበት ነው።

ከ2018 ረቂቅ በጀት 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣ 415 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ፣ 315 ቢሊዮን ብር ለክልል መንግስታት ድጋፍ እንዲሁም 14 ቢሊዮን ብር ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ የሚውል ነው።

ከረቂቅ በጀቱ 1 ትሪሊዮን ብር ወይም 73 በመቶውን ከታክስ ገቢ 236 ቢሊዮን ብር ከልማት አጋሮች ቀሪውን ደግሞ ከፕሮጀክቶች ድጋፍ እና ልዩ ልዩ ገቢዎች ለማግኘት መታቀዱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሺዴ ገልፀዋል።

በረቂቅ በጀቱ ከጥቅል ሀገራዊ ምርት አንፃር ያልተጣራ የበጀት ጉድለት 2.2 በመቶ እንዲሁም የተጣራ የበጀት ጉድለት 1 በመቶ መሆኑንም የገንዘብ ሚኒስትሩ አንስተዋል።

መንግስት የበጀት ጉድለቱን በቀጥታ ከብሔራዊ ባንክ ብድር በመውሰድ ሳይሆን በግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭ እንደሚሸፍን ነው የገለፁት።

ጥብቅ የገንዘብ እና የበጀት ፖሊሲን በመከተል የመንግስት ወጪን በሀገራዊ ገቢ ለመሸፈን ትኩረት መሰጠቱንም ተናግረዋል።

ይህም የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት እና ውጤታማ የበጀት አጠቃቀምን ለመተግበር የሚያስችል መሆኑንም ነው ያስረዱት።

የ2018 ረቂቅ በጀት የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያን እና የ10 ዓመቱን መሪ የልማት እቅድ ታሳቢ ባደረገ መልኩ የተዘጋጀ መሆኑንም ሚኒስትሩ አስረድተዋል።

በ2018 በጀት ዓመት የ8.9 በመቶ የኢኮኖሚ እድገት እንደሚጠበቅም ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

Address

Gombora
Hossana

Telephone

+251982487589

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Malela News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share