Malela News

Malela News It is intended to enable people find current issues about Hossana town and Hadiya Zone

አርሰናል በዚህ የውድድር ዘመን 35 ጨዋታዎችን ማሸነፍ ችሏል። በአውሮፓ አምስቱ ትላልቅ ሊጎች ይህንን ያክል ጨዋታ ያሸነፈ ክለብ የለም።
09/03/2026

አርሰናል በዚህ የውድድር ዘመን 35 ጨዋታዎችን ማሸነፍ ችሏል። በአውሮፓ አምስቱ ትላልቅ ሊጎች ይህንን ያክል ጨዋታ ያሸነፈ ክለብ የለም።

6ኛው አገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ በሆሳዕና ከተማ ሊካሄድ ነውሆሳዕና፡ ጥር 29/2018 ዓ.ምበማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መዲና እና "የሰላም አምባሳደር" በሆነችው ሆሳዕና ከተማ፣ 6...
06/02/2026

6ኛው አገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ በሆሳዕና ከተማ ሊካሄድ ነው

ሆሳዕና፡ ጥር 29/2018 ዓ.ም
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መዲና እና "የሰላም አምባሳደር" በሆነችው ሆሳዕና ከተማ፣ 6ኛው አገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ እንደሚካሄድ ተገለጸ።

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ይህ ጉባኤ፤ የካቲት 4 እና 5 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸኃፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በሰጡት መግለጫ፤ የኮንፍረንሱ ዋነኛ ትኩረት በአገሪቱ እየታየ ያለውን አንፃራዊ ሰላም ይበልጥ ማጽናትና ማስፋት ላይ መሆኑን ገልጸዋል።

በመግለጫቸውም የሚከተሉትን ቁልፍ ነጥቦች አንስተዋል፡-
የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች የሰላም መልዕክተኛ በመሆን ከፈጣሪና ከአገር የተጣለባቸውን አደራ እንዲወጡ ማበረታታት።

ዜጎች ልዩነቶቻቸውን አክብረው በጋራ አገራዊ
የአገሪቱን ሁለገብ ዕድገትና ልማት ለማስቀጠል ሰላምን ማጽናት አማራጭ የሌለው ተግባር መሆኑን ማሳሰብ።
"ያለችን አንዲት የጋራ አገር ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለውን ሁለገብ ዕድገት ለማስቀጠል፣ ሰላምን በማጽናትና አብሮነትን በማጠናከር በጋራ ልንቆም ይገባል" — ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ

በመጨረሻም ኮንፍረንሱ በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ዜጋና የሚመለከታቸው አካላት የበኩላቸውን አወንታዊ ድርሻ እንዲወጡ ጥሪ ማቅረባቸውን ከጉባኤው የሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ አገልግሎት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

 #ሰሜን ኮርያ ክርስትናን አልይ አለች !መጽሐፍ ቅዱስ በመገኘቱ የሁለት ዓመት ህፃን በዕድሜ ልክ እስራት ተቀጣ !!በዓለማችን እጅግ ዝግ በሆነችው ሰሜን ኮሪያ ውስጥ በአንድ ቤተሰብ ቤት ውስ...
31/01/2026

#ሰሜን ኮርያ ክርስትናን አልይ አለች !

መጽሐፍ ቅዱስ በመገኘቱ የሁለት ዓመት ህፃን በዕድሜ ልክ እስራት ተቀጣ !!

በዓለማችን እጅግ ዝግ በሆነችው ሰሜን ኮሪያ ውስጥ በአንድ ቤተሰብ ቤት ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስ ተገኝቶ በመያዙ ምክንያት፣ ገና የሁለት ዓመት ዕድሜ ያለው ህፃን ከወላጆቹ ጋር የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበታል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው ዓመታዊ የሃይማኖት ነፃነት ሪፖርት ላይ እንደተመለከተው፣ ይህ አሰቃቂ ድርጊት የተፈጸመው እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2009 ቢሆንም በሀገሪቱ ያለውን የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማሳየት አሁን በሪፖርቱ ተካቷል።

ገና ቃላትን መጥራት ያልጀመረው ይህ ህፃንና ወላጆቹ ለቀሪው ሕይወታቸው ወደ አሰቃቂው የፖለቲካ እስር ቤት የተላኩት፣ የመንግስት የደህንነት ኃይሎች በቤታቸው ውስጥ መንፈሳዊ መጽሐፍ በማግኘታቸው ብቻ ነው።

በሰሜን ኮሪያ መጽሐፍ ቅዱስ መያዝ ወይም ክርስትናን መከተል እንደ ከባድ ወንጀል የሚቆጠር ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ50 ሺህ እስከ 70 ሺህ የሚደርሱ ክርስቲያኖች በእምነታቸው ምክንያት ብቻ በእስር ላይ እንደሚገኙ ይገመታል።

እነዚህ እስር ቤቶች ለሰው ልጅ የማይመጥኑና እጅግ አሰቃቂ የሚባሉ ናቸው። እስረኞች ምንም ዓይነት የሕግ ክርክርና የፍርድ ቤት ዋስትና ሳይኖራቸው ለከባድ የጉልበት ሥራ፣ ለረሃብና ለተለያዩ አካላዊ ስቃዮች ይዳረጋሉ ተብሏል።

የሰሜን ኮሪያ መንግስት ማናቸውንም መንፈሳዊ እምነቶች ለሥርዓቱ ታማኝነትን የሚያጎድሉ አደገኛ አስተሳሰቦች አድርጎ ስለሚመለከታቸው፣ ህፃናትን ሳይቀር ለእንዲህ ዓይነት የከፋ ስቃይ እየዳረገ ይገኛል ነው የተባለው።

ይህ ሁኔታ በሀገሪቱ ውስጥ የማመንና የማሰብ ነፃነት ምን ያህል በጭካኔ እንደሚታፈን ለዓለም ዳግም ያሳበቀ ክስተት ሆኗል።

Arsenal’s results this season:Man United 0-1 Arsenal ✅Arsenal 5-0 Leeds ✅Liverpool 1-0 Arsenal ❌Arsenal 3-0 Nottingham F...
26/01/2026

Arsenal’s results this season:

Man United 0-1 Arsenal ✅
Arsenal 5-0 Leeds ✅
Liverpool 1-0 Arsenal ❌

Arsenal 3-0 Nottingham Forest ✅
Athletic Club 0-2 Arsenal ✅
Arsenal 1-1 Man City 🤝
Port Vale 0-2 Arsenal ✅
Newcastle 1-2 Arsenal ✅
Arsenal 2-0 Olympiacos ✅
Arsenal 2-0 West Ham ✅

Fulham 0-1 Arsenal ✅
Arsenal 4-0 Atletico Madrid ✅
Arsenal 1-0 Crystal Palace ✅
Arsenal 2-0 Brighton ✅
Burnley 0-2 Arsenal ✅
Slavia Prague 0-3 Arsenal ✅
Sunderland 2-2 Arsenal 🤝

Arsenal 4-1 Tottenham ✅
Arsenal 3-1 Bayern Munich ✅
Chelsea 1-1 Arsenal 🤝
Arsenal 2-0 Brentford ✅
Aston Villa 2-1 Arsenal ❌
Club Brugge 0-3 Arsenal ✅
Arsenal 2-1 Wolves ✅
Everton 0-1 Arsenal ✅
Arsenal 1-1 Crystal Palace (8-7 on pens) ✅
Arsenal 2-1 Brighton ✅
Arsenal 4-1 Aston Villa ✅

Bournemouth 2-3 Arsenal ✅
Arsenal 0-0 Liverpool 🤝
Portsmouth 1-4 Arsenal ✅
Chelsea 2-3 Arsenal ✅
Nottingham Forest 0-0 Arsenal 🤝
Inter Milan 1-3 Arsenal ✅
Arsenal 2-3 Manchester United ❌

“ አርሰናል ሊጉን ወይም ሻምፒየንስ ሊጉን ያሸንፋል “ ሩኒ የቀድሞ እንግሊዛዊ ተጨዋች ዋይን ሩኒ ይህ አመት አርሰናል እድሉን የሚቀይርበት አመት ይሆናል በማለት ገልጿል። “ አርሰናል በፕሪሚ...
21/01/2026

“ አርሰናል ሊጉን ወይም ሻምፒየንስ ሊጉን ያሸንፋል “ ሩኒ

የቀድሞ እንግሊዛዊ ተጨዋች ዋይን ሩኒ ይህ አመት አርሰናል እድሉን የሚቀይርበት አመት ይሆናል በማለት ገልጿል።

“ አርሰናል በፕሪሚየር ሊጉ እና ሻምፒየንስ ሊጉ በምርጥ ደረጃ ላይ ይገኛል “ ሲል ዋይን ሩኒ ተናግሯል።

“ አርሰናል ከሁለት አንዱን ዋንጫ ያሸንፋል “ የሚለው ሩኒ ይህ አመት እጣ ፋንታቸውን የሚለውጡበት ይሆናል ብሏል።

Address

Gombora
Hossana

Telephone

+251982487589

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Malela News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share