Malela News

Malela News It is intended to enable people find current issues about Hossana town and Hadiya Zone

የርገን ክሎፕ የጀርመን ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ በመሆን ለሚቀጥሉት 4 አመታት በይፋ ተሹመዋል።
24/07/2026

የርገን ክሎፕ የጀርመን ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ በመሆን ለሚቀጥሉት 4 አመታት በይፋ ተሹመዋል።

  የሃዲያ ሆሳዕና አሰልጣኝ ሆኗል። በሁለት ዓመት ውል የሃዲያ ሆሳዕና ዋና አሰልጣኝ በመሆን በዛሬው ዕለት ከስምምነት  ደርሷል።ከሰሞኑ ፋሲል ተካልኝን አሠልጣኝ አድርጎ ለመቅጠር ሙከራ አድር...
24/07/2026

የሃዲያ ሆሳዕና አሰልጣኝ ሆኗል። በሁለት ዓመት ውል የሃዲያ ሆሳዕና ዋና አሰልጣኝ በመሆን በዛሬው ዕለት ከስምምነት ደርሷል።

ከሰሞኑ ፋሲል ተካልኝን አሠልጣኝ አድርጎ ለመቅጠር ሙከራ አድርጎ የነበረው ሃዲያ ሆሳዕና የቀድሞ የሀረር ቢራ ፣ ስሁል ሸረ ፣ ድሬዳዋ ከተማ ፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ኢትዮጲያ ቡና ዋና አሰልጣኝ የነበረውን ሳምሶን አየለን ለመቅጠር ተስማምቷል።

አሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ከኢትዮጲያ ቡና ጋር የአንድ ዓመት ከስድስት ወር ቀሪ ኮንትራት እያለው መለያየታቸው የሚዘነጋ አይደለም።

13/07/2026

አፋልጉኝ

‎ተፈላጊ መሠረት አበራ ዕድሜው 20 ዓመት ከቤት ሲወጣ ግራጫ መልክ ያለው ኮት የለበሰ ሲሆን ነጭ ጫማ አድርጎል።
‎የተፈላጊ መሠረት አበራ መኖሪያ አድራሻ በሀዲያ ዞን 2ተኛ ጃጁራ ዊቅቄሳ ቀበሌ ሲሆን የኣዕምሮ ውስንነት ያለበት ሆኖ ብዙም መናገር አይችልም።

‎መሠረት አበራን ያየ ወይንም ያለበትን የሚያውቅ

‎በ0913109383/ በ0911640695 ወይም በ091025608 ደውሎ ቢያሳውቀን ወሮታ ከፋይ ነን ይላሉ ፤

‎ ፈላጊ ቤተሰቦቹ።

የሰው ልጅ ወሰን፦ ከ24 ሰዓት የነፍስ አድን ዘመቻ በኋላ የእግረኛ መንገድ ላይ የተኙት የእሳት አደጋና ነፍስ አድን ባለሙያዎች ሐምሌ 06 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በቻይና ጓንግዢ ግዛት...
13/07/2026

የሰው ልጅ ወሰን፦ ከ24 ሰዓት የነፍስ አድን ዘመቻ በኋላ የእግረኛ መንገድ ላይ የተኙት የእሳት አደጋና ነፍስ አድን ባለሙያዎች

ሐምሌ 06 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በቻይና ጓንግዢ ግዛት የጣለው ከባድ ዝናብ ያስከተለውን የጎርፍ አደጋ ለመቀልበስ የተሰማሩ ከ100 በላይ የእሳት አደጋና ነፍስ አድን ባለሙያዎች፣ ለአፍታም ሳያረፉ ለተከታታይ 24 ሰዓታት የሰዎችን ሕይወት ሲታደጉ ቆይተዋል። ይህን ሁሉ ሰዓት በጭቃና በውኃ ውስጥ ሲዋጉ የቆዩት እነዚህ ጀግኖች፣ በድንገት እንቅስቃሴያቸውን ለማቆም የተገደዱት አደጋው አብቅቶ ሳይሆን አካላቸው የመጨረሻው የድካም ደረጃ ላይ ደርሶ ከአቅማቸው በላይ ስለሆነባቸው ነበር ተብሏል።

የነፍስ አድን ባለሙያዎቹ የረጠቡና በጭቃ የተለወሱ የሥራ ልብሶቻቸውን እንደለበሱ፣ በተኙበት ቦታ ሁሉ የእንቅልፍ ማዕበል ወስዷቸዋል። አንዳንዶቹ የእግረኛ መንገዱን ኮንክሪት ጠርዝ እንደ ትራስ የተጠቀሙ ሲሆን፣ ሌሎቹ ደግሞ ከመንገዱ ዳር ባለው ሳር ላይ ተዘርግተው ተኝተዋል። ይሁን እንጂ ሌላ አዲስ የድረሱልኝ ጥሪ ከመጣ ፈጥኖ ለመድረስ እንዲያስችላቸው የደህንነት ኮፍያዎቻቸውና መሣሪያዎቻቸው እጃቸው በሚደርስበት አቅራቢያ ተቀምጠዋል።

ለእነሱ የተዘጋጀ ምቹ አልጋም ሆነ የሙቀት መቆጣጠሪያ ያለው ክፍል አልነበረም፤ ወደ ከባዱ ሥራቸው ከመመለሳቸው በፊት ጥቂት ውድ ደቂቃዎችን በዚያው በሜዳ ላይ ተኝቶ ማሳለፍ ብቻ ነበር የወቅቱ ምርጫቸው ተብሏል። ከእያንዳንዱ የነፍስ አድን ሥራ በስተጀርባ፣ አብዛኛው ሰው የማይመለከተው የረጅም ሰዓታት አድካሚ ጉልበት፣ የአካል ዝልፍልፍነትና ከቤተሰብ መለየት የመሳሰሉ ትልልቅ መሥዋዕትነቶች አሉት ነው የተባለው።

እነዚህ ነፍስ አድን ባለሙያዎችም ቢሆኑ የራሳቸው የሆነ የተፈጥሮ ወሰን ያላቸው የሰው ልጆች ናቸው። አካላቸው ሰው መሆናቸውን እስኪያስታውሳቸው ድረስ ግን የማያውቋቸውን ወገኖች ሕይወት ለመታደግ ሲሉ ብቻ መጓዛቸውን አያቆሙም ነው የተባለው። የሌሎችን ደህንነት ለመጠበቅ ሲሉ የራሳቸውን ሕይወት ለአደጋ ለሚያጋልጡ የእሳት አደጋና ነፍስ አድን ሠራተኞች በሙሉ ትልቅ ክብርና ምስጋና እንደሚገባቸው ተመላክቷል።

ማኑኤል ኑዌር ራሱን ከብሔራዊ ቡድን አገለለ *************የ40 ዓመቱ ግብ ጠባቂ ጀርመን በዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ በፓራጓይ ተሸንፋ ከተሰናበተች በኋላ ራሱን ማግለሉን አሳውቋል።የሙኒኩ...
30/06/2026

ማኑኤል ኑዌር ራሱን ከብሔራዊ ቡድን አገለለ

*************
የ40 ዓመቱ ግብ ጠባቂ ጀርመን በዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ በፓራጓይ ተሸንፋ ከተሰናበተች በኋላ ራሱን ማግለሉን አሳውቋል።

የሙኒኩ ግብ ጠባቂ ለሀገሩ በ128 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ መጫዎት የቻለ ሲሆን የምሽቱ የፓራጓይ ጨዋታ የመጨረሻው ሆኗል።

ኢትዮጵያን ጨምሮ በ'ኤል ኒኖ' ስጋት ውስጥ ያሉ 22 ሀገራትን ለመታደግ የ202 ሚሊዮን ዶላር አስቸኳይ ጥሪ ቀረበ።በኤል ኒኞ ሳቢያ ከፍተኛ የድርቅ ወይም የጎርፍ አደጋ ይደርስባቸዋል ተብለው...
30/06/2026

ኢትዮጵያን ጨምሮ በ'ኤል ኒኖ' ስጋት ውስጥ ያሉ 22 ሀገራትን ለመታደግ የ202 ሚሊዮን ዶላር አስቸኳይ ጥሪ ቀረበ።

በኤል ኒኞ ሳቢያ ከፍተኛ የድርቅ ወይም የጎርፍ አደጋ ይደርስባቸዋል ተብለው ከተለዩት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣ ኡጋንዳ፣ ካሜሩን፣ ማዳጋስካር፣ ማላዊ፣ ሞዛምቢክ፣ ናይጄሪያ እና ዚምባብዌ በቀዳሚነት ተጠቅሰዋል።

በሌሎች አህጉራት ደግሞ አፍጋኒስታን፣ ፓኪስታን፣ ፊሊፒንስ፣ ኮሎምቢያ፣ ኤል ሳልቫዶር፣ ጓቲማላ፣ ሄይቲ፣ ሆንዱራስ እና ቬንዙዌላ በስጋት መዝገቡ ውስጥ ይገኛሉ።

መረጃው ከFAO፣ WFP እና UN News የተጠናቀረ ነው።

‎የመንግሥት ኃላፊዎችን አምስት ዓመት የሚያስረው አዋጅ ፀደቀ።‎‎  | መረጃን የደበቀ ማንኛውም የመንግሥት ኃላፊ አምስት ዓመት የሚያሳስረው አዋጅ በምክር ቤቱ ጸድቋል።‎‎የሕዝብ ተወካዮች ም...
29/06/2026

‎የመንግሥት ኃላፊዎችን አምስት ዓመት የሚያስረው አዋጅ ፀደቀ።

‎ | መረጃን የደበቀ ማንኛውም የመንግሥት ኃላፊ አምስት ዓመት የሚያሳስረው አዋጅ በምክር ቤቱ ጸድቋል።

‎የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነጻ መረጃ ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል።

‎የዚህ አዋጅ አላማ ሙስናን፣ ሕገ-ወጥ አሠራርን ወይም የሥራ ብቃት ማነስን ለመሸሸግ ሲሉ መረጃና ሰነድ የሚደብቁ ወይም እንዲጠፉ የሚያደርጉ የመንግሥት ኃላፊዎችን ተጠያቂ ማድረግ ነው።

‎ጥፋቱ በፍርድ ቤት የተረጋገጠበት የማንኛውም የመንግሥት ወይም የግል ድርጅት የበላይ ኃላፊ፣ የመረጃ ኃላፊ ወይም ትዕዛዝ ሰጪ አካል እስከ 5 ዓመት በሚደርስ እስራት ይቀጣል ይላል።

‎ #የሕዝብተወካዮችምክርቤት
‎ #የነጻመረጃረቂቅአዋጅ

የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ በሕገ-ወጥ ስደተኞች ጉዳይ ከሰኔ 30 ቀን ጋር ተያይዞ የታቀደውን ተቃውሞ ተከትሎ አገሪቱን ለማወክ የሚሞክር ማንኛውም አካል የሕግ እርምጃ እንደሚገጥ...
26/06/2026

የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ በሕገ-ወጥ ስደተኞች ጉዳይ ከሰኔ 30 ቀን ጋር ተያይዞ የታቀደውን ተቃውሞ ተከትሎ አገሪቱን ለማወክ የሚሞክር ማንኛውም አካል የሕግ እርምጃ እንደሚገጥመው አስጠነቀቁ።

ፕሬዚዳንቱ መንግሥት መደበኛ የሕይወት እንቅስቃሴዎች እንዳይቋረጡ ዝግጁ መሆኑን ገልጸው፣ የጸጥታ ኃይሎችም ሕዝቡን ለመጠበቅና ሥርዓትን ለማስከበር በተጠንቀቅ ሁኔታ ላይ መሆናቸውን አሳውቀዋል።

ባለሥልጣናት በተጨማሪ ሕዝቡ የሕግ የበላይነትን እንዲያከብር እና የውጭ ዜጎችን የሚያነጣጥር ጥቃት (xenophobia) ሊያባብስ ከሚችል ማንኛውም ድርጊት እንዲቆጠብ ጥሪ አቅርበዋል።

Address

Gombora
Hossana

Telephone

+251982487589

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Malela News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share