Hadiya.TV

Hadiya.TV Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hadiya.TV, Media, hossana, Hossana.

በየአካባቢው የሚገነቡ የልማት ፕሮጀክቶችን ህብረተሠቡ ጠብቆና አልምቶ የመጠቀም ኃላፊነት እንዳለበት ተገለጸ።ማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ውሃ መሥኖና ማዕድን ልማት ቢሮ  በሀዲያ ዞን ዱና ወረዳ...
08/07/2025

በየአካባቢው የሚገነቡ የልማት ፕሮጀክቶችን ህብረተሠቡ ጠብቆና አልምቶ የመጠቀም ኃላፊነት እንዳለበት ተገለጸ።

ማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል ውሃ መሥኖና ማዕድን ልማት ቢሮ በሀዲያ ዞን ዱና ወረዳ በ130 ሚሊዮን ብር የገነበው ቀንቅቾ ዋገበታ የዉሃ ፕሮጀክት ርክክብ ተደርጓል።

ሆሳዕና፦01/11/2017 (ሀድያ ቴሌቪዥን)

በርክክብ ፕሮግራሙ የተገኙት የአካባቢው ነዋሪዎች በሰጡት አሰተያየት የውሃ ፕሮጀክቱ ከዚህ በፊት በአካባቢው በዉሃ እጥረት ምክንያት ሲደርስ የነበረውን እንግልትና በንፁህ ውሃ እጦት የሚከሰተውን የጤና ችግር በመቅረፉ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ፕሮጀክቱ በነዳጅ የሚሰራ በመሆኑ የነዳጅ አቅርቦት እጥረት ሲገጥም የውሃ አቅርቦቱ እንዳይቋረጥ ስጋታቸውን በማስቀመጥ ለዘላቂ መፍትሄ የኤሌክትሪክ ኃይል መጠቀም እንዲቻል ትብብር እንዲደረግ ጠይቀው ፕሮጀክቱን ጠብቆ ለመጠቀም ቃል ገብተዋል።

የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የፐብሊክ ሰርቪስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ታምሬ ባደረጉት ንግግር የዉሃ ፕሮጀክቱ በማህበረሠቡ የረጅም ጊዜ የልማት ጥያቄ የመለሰ ትልቅ ፕሮጀክት እንደሆነ ጠቁመዋል።

የልማት ፕሮጀክቱን ህብረተሠቡ ከመንግስት ተረክቦ በመንከባከብና በመጠበቅ አቆይቶ የመጠቀም ኃላፊነት አለበት በማለት የወረዳው አስተዳዳርም የበኩሉን እንደሚወጣ ገልፀው በልማቱ የተሣተፉትን ሁሉ አመስግነዋል።

የሀድያ ዞን የዉሃ መስኖና ማዕድን ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ መለሰ ኃይሌ በበኩላቸው፤ የዉሃ ፕሮጀክቱ በክልል ደረጃ በከፍተኛ ትኩረት ሰፊ በጀት በመያዝ የተከናወነ መሆኑን አንስተው የልማት ተግባሩ 5 ቀበሌያት 40 ቦኖዎችን በመትከል 41ሺህ ህዝብ ንጹ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል።

ፕሮጀክቱ አልቆ አገልግሎት መጀመር ብቻውን በቂ ባለመሆኑ አገልግሎቱን ለማስቀጠል በሚያስፈልገው ሁሉ መሣተፍና በኃለፊነት ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል።

የማዕከላዊ ክልል ውሃ መስኖና ማዕድን ቢሮ ምክትል የመጠጥ ዉሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሙላቱ ጡሞሮ እንደገለፁት የውሃ ፕሮጀክቱ በክልሉ 130 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የተከናወነ ትልቅ ፕሮጀክት ነው ብለዋል።

የልማት ተግባሩ እስኪጠናቀቅና ከተመረቀም በኋላ በቂ ሙያዊ ክትትል እየተደረገ ቆይቶ ለርክብክብ ወቅት መድረሱን ተናግረዋል።

ፕሮጀክቱን የአካባቢው ህብረተሰብ የሚጠበቅበትን በማድረግ መጠቀም ያስፈልጋል በማለት ፕሮጀክቱን ከነዳጅ ወጪ ወደ ኤክትሪክ ለመቀየር በሚደረገው ጥረት ክልሉ የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያደርግም ጠቁመዋል።

የዉሃ ፕሮጀክቱ ሰኔ 2016 ዓ/ም የክልሉ ርዕሰ መሥተዳደር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።

አድማሱ ወልዴ

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመጀመሪያው ቀን   የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና በሰላም ተጠናቀቀሆሳዕና -01/11/2017(ሀድያ ቴሌቪዥን)በዛሬው ዕለት በወረቀት እና በበይነ-መረ...
08/07/2025

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመጀመሪያው ቀን የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና በሰላም ተጠናቀቀ

ሆሳዕና -01/11/2017
(ሀድያ ቴሌቪዥን)

በዛሬው ዕለት በወረቀት እና በበይነ-መረብ ሲሰጥ የነበረው የማህበራዊ ሳይንስ ስትሪም ተማሪዎች እንግሊዝኛ እና የህሳብ ትምህርት ፈተና በስኬት ተጠናቋል፡፡

ለፈተናው ስኬት ጉልህ ድርሻ ላበረከቱ አካላት የዩኒቨርሲቲው አካ/ምር/ቴክ/ሽግ/ማህ/አገ/ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳራ ሽኩር ምስጋናቸውን አቅርበዋል ሲል የህዝብ ግንኙነትና ዓለም ዓቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዘግቧል።

08/07/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ጉመር ወረዳ የ2017 የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ እና የገጠር ኮሪደር የማስጀመር መርሐ ግብር

ባለፉት ስድስት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ ፈርጀ  ብዙ ውጤት መመዝገቡን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሸው ጣሰው(ዶ/ር) ተናገሩ:: ሆሳዕና ሐምሌ 01/2017 (ሀድያ ቴሌቪ...
08/07/2025

ባለፉት ስድስት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ ፈርጀ ብዙ ውጤት መመዝገቡን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሸው ጣሰው(ዶ/ር) ተናገሩ::

ሆሳዕና ሐምሌ 01/2017 (ሀድያ ቴሌቪዥን)

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአረንጓዴ አሻራ እና ክልላዊ የገጠር ኮሪደር ማስጀመሪያ ፕሮግራም በጉራጌ ዞን ጉመር ወረዳ በይፋ ተጀመሯል::

በማብሰሪያው ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሸው ጣሰው(ዶ/ር) መንግስት በሁሉም መስክ ብልፅግና ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በተላይ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የአረንጓዴ አሻራ የምታይ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ተናግረዋል::

ባለፉት ስድስት ዓመታት በጠቅላይ ሚንስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ፈርጀ ብዙ ውጤት ማስመዝገቡን የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህም ተግባር የሕዝብ የላቀ ተሳትፎ ሚናው የጎላ እንደነበረ ተናግረዋል::

ባለፈው ወር በጠቅላይ ሚንስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ በክልሉ በአራት ዞኖች ስላስጀመሩት እና
ዛሬ በይፋ ስለተጀመረው ክልላዊ የገጠር ኮሪደር ፕሮጀክት ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ የገጠር ኮሪደር የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው በማለት ዛሬ የተጀመረው ክልላዊ የገጠር ኮሪደር ከነሐሴ አንድ ጀምሮ በክልሉ ባሉ 10 መዋቅሮች አንዳንድ ፕሮጀክት እንደሚሰራ ጠቁመዋል::

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በበኩላቸው በሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት አረንጓዴ አሻራ ትልቅ ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል በማለት አረንጓዴ አሻራ ለኢትዮጵያ ግብርና ኢትዮጵያዊ መፍትሄ ሆኗል በማለት ገልፀዋል::

ከሌማት ቱርፋት አንፃር በአረንጓዴ አሻራ እመርታዊ እድገት በክልሉ ተመዝግቧል ያሉት አቶ ኡሱማን ከ500 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በክልሉ በያዝነው ዓመት በአረንጓዴ አሻራ ለመትከል መታቀዱን ገልፀዋል::

በጠቅላይ ሚንስትሩ በቅርቡ የተጀመረው የገጠር ኮሪደር የአርሶ አደሩን ኑሮ ከማሻሻል አንፃር ከፍተኛ ሚና ይኖራዋል ያሉት አቶ ኡሱማን ግብርናን በማዘመን የበለፀጉ አርሶ አደሮችን እንደሚፈጥር እምነታቸውን ገልፀዋል::

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጉምራ በበኩላቸው በጉመር ወረዳ በአበኬ ቀበሌ የጉልቾ ጀፎረ መንደር ከትውልድ ትውልድ በሕዝብ የጋራ ጥረት የተገነባ ባህላዊ መንደር መሆኑን ጠቁመው መንግስት ለያዘው የገጠር ኮሪደር በአብነት ሊጠቀስ እንደሚችል ተናግረዋል::

በክልሉ በዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ 500 ሚሊዮን ችግኝ እንደሚተከል ሲገለፅ ከ310 ሚሊዮን በላይ የፍራፍሬ፣የቡና የእንስሳት መኖና፣ሌሎች ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንዲሁም ከ190 ሚሊዮን በላይ ዓላማ ተኮር የደን ልማትን ማዕከል ያደረጉ ችግኞች በ160 ሺ ሄክታር መሬት ላይ ይተከላሉ ተብሎ ታቅዷል።

በናሆም ዮሐንስ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ጉመር ወረዳ የ2017 የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ እና የገጠር ኮሪደር የማስጀመር መርሐ ግብር ተካሂዷል ።
08/07/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ጉመር ወረዳ የ2017 የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ እና የገጠር ኮሪደር የማስጀመር መርሐ ግብር ተካሂዷል ።

ግብር መክፈል ዕዳ ሳይሆን ግዴታ ስለሆነ ሁሉም የግብር ከፋዮች ጊዜ ጠብቀው መክፈል እንዳለባቸው ተገለጸ።በሀዲያ ዞን በጃጁራ ከተማ አስተዳደር  የ"ሐ" ደረጃ ግብር ከፋዮች ክፍያ መርሃ ግብር...
08/07/2025

ግብር መክፈል ዕዳ ሳይሆን ግዴታ ስለሆነ ሁሉም የግብር ከፋዮች ጊዜ ጠብቀው መክፈል እንዳለባቸው ተገለጸ።

በሀዲያ ዞን በጃጁራ ከተማ አስተዳደር የ"ሐ" ደረጃ ግብር ከፋዮች ክፍያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

ሆሳዕና -01/11/2017 ዓ.ም (ሀድያ ቴሌቪዥን)

"ተቋምን በልህቀት ገቢን በስኬት" በሚል መሪ ሀሳብ የ2018 ዓ.ም የግብር መክፈያ ወቅት ዛሬ ሐምሌ 01/2017 ዓ.ም በጃጁራ ከተማ አሰተዳደር በገቢዎች ጽ/ቤት ተጀምሯል።

የዕለቱ ክቡር እንግዳ የሀዲያ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪ እና በብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሳይ ተስፋዬ ግብር ራስን በራስ ለመምራት ካለው ጠቀሜታ አንፃር ድርሻው ከፍተኛ እንደመሆኑ የጃጁራ ከተማ ግብር ከፋዮች እንደተለመደው የዘንድሮውንም ግብር ከፍለው በማጠናቀቃቸው አመስግነዋል።

ራስን ከመንግሥት ትሬዣሪ በማላቀቅ መሰረታዊ የህዝብ ልማቶችን ለመጀመር እና ለማጠናቀቅ፤ የህዝብን ፍላጎት በራስ ለሟሟላት ግብር የውስጥ አቅምን ይጨምራል ያሉት አቶ መሳይ የጃጁራ ከተማ የገቢ አሰባሰብ እንቅስቃሴ ለሌሎችም ተምሳሌት እየሆነ እንዳለ ተናግረዋል።

"ግብር መክፈል እዳ ሳይሆን ግዴታም ጭምር እንደሆነ " በመገንዘብ የጃጁራ ከተማ አስተዳደር የ"ሐ" ደረጃ ግብር ከፋይ ማህበረሰብ ከራሳቸው የሚጠበቀውን ግዴታ ተወጥተዋል ያሉት የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ላይኩን ሱልዶዕሎ፥ይህም በጃጁራ ከተማ አስተዳደር የተጀመሩ በርካታ የልማት ስራዎችን በራስ ወጪ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል።

በተጨማሪም የደረጃ "ለ" እና "ሀ" ግብር ከፋዮች ከእነርሱ የሚጠበቅባቸውን የግብር ክፍያ ጊዜ ጠብቀው እንዲፈጽሙ ከንቲባው አሳስበዋል።

በጃጁራ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ወልዴ ቡቱሮ በበኩላቸው በዛሬው ዕለት የጃጁራ ከተማ አስተዳደር የ"ሐ" ደረጃ ግብር ከፋዮች በታቀደው ዕቅድ መሰረት የበጀት አመቱን ግብር ማልዶ በመነሳት በመክፈላቸው አመስግነዋል።

እንደ ጃጁራ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት የታቀደውን የግብር ክፍያ ሙሉ በሙሉ ለማሣካት ብርቱ የሆነ የአመራር ብቃት፣ የባለሙያዎች ትጋትና የከፋዮች ግንዛቤ ትልቅ ሚና እንደነበር አቶ ወልዴ አክለዋል።

ከ"ሐ" ደረጃ ግብር ከፋዮች መካከል ሀሳባቸውን የሰጡት አንዳንድ ግብር ከፋዮች ግብ ከጥንት ጊዜ ጀምሮ የነበረ እና ግዴታ ጭምር መሆኑን በመገንዘብ የሚጠበቅባቸውን ክፍያ በደስታ መፈጸማቸውን ተናግረዋል።

ማንደፍሮ ሎምብሶ

የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ እና አዳጊ የሆኑ ፍላጎቶችን ለማሟላት ግብርና ታክስ በአግባቡ መሰብሰብ ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመሆሳዕና ፦01/11/2017 (ሀድያ ቴሌቪዥን)በ2017 በጀ...
08/07/2025

የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ እና አዳጊ የሆኑ ፍላጎቶችን ለማሟላት ግብርና ታክስ በአግባቡ መሰብሰብ ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ

ሆሳዕና ፦01/11/2017 (ሀድያ ቴሌቪዥን)

በ2017 በጀት ዓመት በዛሬው ዕለት ከጧቱ 12 ሰዓት የጀመረውን የደረጃ"ሐ"ግብር ከፋዮች ቀን ምክንያት በማድረግ የክልል፣የዞን ፣የከተማ እና የቀበሌያት አመራሮች፣ የንግድና የገቢ ተቋማት ባለድርሻ አካለት በሆሳዕና ከተማ ባሉ በሁሉም ቀበሌያት በመዟዟር የሀምሌ ወር የግብር ከፋዮች ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሂዷል።

በ2017 በጀት ዓመት በሐምሌ ወር ከደረጃ "ሐ"ግብር ከፋዮች ብቻ ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በአጠቃላይ 146 ሚሊየን 135ሺ 194 ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አውላቸው ዮሐንስ ተናግረዋል።

በከተማ አስተዳዳሩ የሚገኙ ከ11 ሺህ 155 የሚሆኑ ግብር ከፋዮች ከሐምሌ 1/2017 ዓ/ም 15/11/2017 ድረስ የደረጃ "ሐ" በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ ግብራቸውን በመክፈል የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ለማሳለጥ የንግዱ ማህበረሰብ ግዴታውን መወጣት እንዳለበትም አሳስበዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ገቢዎች ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ደግፍ መለስ፣ የሀዲያ ዞን የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምራት ግዛው ፣የሆሣዕና ከተማ ከንቲባ አቶ ዳዊት ጡምዳዶ በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ በመገኘት ስለግብር አሰባሰብና በሚሰባሰበው ገቢ ከተማው ለነዋሪዎች ምቹ እንዲሆን ስላለው ፋይዳ ማብራርያ ሰጥተዋል።

ግብርን በወቅቱና በታማኝነት በመክፈል በከተማ አስተዳደሩ የተጀመሩ ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶችን ከዳር ለማድረስ የከተማው ግብር ከፋዮች የመደበኛና የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢን በአስራ አምስት ቀናት በመክፈል ግዴታቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል ።

በስፍራው አግኝተን ያነጋገርናቸው ግብር ከፋዮች በበኩላቸው፤ ግብርን መክፈል ከራስ ለራስ ነው በማለት ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ግብርን በመክፈል የተጀመሩ ልማቶች እንዲጠናቀቁ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

ቤተልሄም ደመቀ

"በተጠናቀቀው  በጀት ዓመት በሁሉም መስኮች በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው" - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሆሳዕና :-01/11/2017 (ሀድያ ቴሌቪዥን)ቢሮው  በ2...
08/07/2025

"በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም መስኮች በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው" - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ

ሆሳዕና :-01/11/2017 (ሀድያ ቴሌቪዥን)

ቢሮው በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም፣ በ2018 ዓመት የዕቅድ ዝግጅትና በ2017ዓ/ም የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማብሳሪያ ላይ የውይይት መድረክ በዱራሜ ከተማ እያከሄደ ይገኛል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሾ በዚህ ወቅት እንደገለፁት፤ የተጠናቀቀው
በጀት ዓመት በሁሉም መስኮች በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡበት ነው።

በክራምትና በጋ ወራት በ14 የትኩረት መስኮች የወጣቶችን አደረጃጀት በማጠናከር ከ4 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚዎች ማድረግ መቻሉን አቶ ጌታቸው አስረድተዋል።

ቢሮው በተለያዩ ዘርፎች ህብረተሰብን ተጠቃሚ ለማድረግ አቅዶ ወደ ተግባር በመግባት ዕቅዶችን በስኬት መፈጸሙን አብራርተዋል ሀላፊው።

የወጣቶችን የስብዕና ማዕከላትን በማጠናከር ወጣቶች በሰላም ግንባታ ከፍተኛ ሚና እንድወጡ መደረጉንም ተናግረዋል።

የህዝብ ለሕዝብ ትስስር ለማጠናከርም የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች ፣የተለያዩ ውድድሮች በተለያዩ አከባቢዎች መከሄዳቸውንም አስረድተዋል።

በዚሁ በተለያዩ ደረጃዎች በተደረጉ ስፓርታዊ ውድድሮች በርካታ ድሎች የተመዘገቡበትና ተተኪ ስፓርተኞችንም ማፍራት የተቻበት ዓመት ነው ብለዋል።

በዓመቱ በአንዳንድ ተግበራት የታዩትን ጉድለቶች በቀጣይ የዕቅዱ አካል በማድረግ ከ12 ቢሮዎች ጋር በቅንጅት ለመሥራት ዕቅድ መያዙን የጠቆሙት አቶ ጌታቸው በቀጣይ በ16 የበጎ ፈቃድ የትኩረት መስኮች ከ2 ሚሊዮን በላይ ወጣቶችን በማሳተፍ ከ5ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚዎች በማድረግ ከህዝብና ከመንግስት የሚወጠውን 2 ቢሊዮን ብር ለማዳን እንደሚሰራም አስረድተዋል።

በመድረኩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የማህበራዊ ክላስተር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ግዛቸው ዋሌራ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሾን ጨምሮ የክልል፣የዞኖች፣የልዩ ወረደዎች የዘርፉ ሀላፊዎች ፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻዎች ተሳትፈዋል።

በመድረኩም የቢሮው የ2017 ዓ/ም አፈጻጸም ሪፓርት፣ የቀጣይ ዓመት ዕቅድና የክራምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዕቅድ ቀርቦ ወይይት እየተደረገ ነው።

ደለለኝ ጋሻሁን (ከዱራሜ)

‎የጌዴኦ ቴሌቪዥን የስራ ሃላፊዎች በሚዲያ አሰራር፣ አመራር እና አደረጃጀት ዙሪያ  ከሀድያ ቴለቪዥን ስራ ኃላፊዎች ጋር የልምድ ልውውጥ አድርገዋል ‎‎ሆሳዕና- 01/11/2017 (ሀዲያ ቴሌቪ...
08/07/2025

‎የጌዴኦ ቴሌቪዥን የስራ ሃላፊዎች በሚዲያ አሰራር፣ አመራር እና አደረጃጀት ዙሪያ ከሀድያ ቴለቪዥን ስራ ኃላፊዎች ጋር የልምድ ልውውጥ አድርገዋል

‎ሆሳዕና- 01/11/2017 (ሀዲያ ቴሌቪዥን)

‎የሀድያ ቴሌቪዥን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወንድሙ አቡሌ በተገኙበት፣የጊዲኦ ቴሌቪዥን የስራ ኃላፊዎች ከሀድያ ቴሌቪዥን ማኔጅመንት አባላት ጋር በሚዲያ ይዘትና አመራር ስርዓት፣ በቴክኖሎጂ ዘርፍ እና አጠቃላይ በስራ እንቅስቃሴ ላይ የልምድ ልውውጥ አድርገዋል።

‎የጌዲኦ ቴሌቪዢን ዋና ስራአስኪያጅ አቶ ደሳለኝ በቀለ ጌዴኦ ቴሌቪዢን ክልላዊና አካባቢያዊ መረጃዎችን በጥራት ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ ቅደመ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ተናግሯል።

‎ሀዲያ ቴሌቪዥን ካለው ጠንካራ አቅም እንፃር ለልምድ ልውውጥ መመረጡን አንስተው፣ ለተደረገልን አቀባበልና ላጋሩን ልምድ እናመሰግናለን ብለዋል።

‎ቴሌቪዢኑ ለሚያደርገው ለሙሉ ጊዜ ስርጭት ሽግግር እጅግ ጠቃሚ እና አጋዥ ግብዓት ማግኘት መቻሉን ገልጿል ።
‎ጌዴኦና ሀዲያ ወንድማማች ህዝብ ነው ያሉት ስራ አስኪያጁ፣ ይህ የልምድ ልውውጥ ለህዝብ ለህዝብ ትስስርና ወንድማማችነት ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰው፣እንደ ሀገርም የጋራ ትርክት ለመፍጠር የሚደረገውን እንቅስቃሴ የሚደግፍ መሆኑን አብራርቷል።

‎የሁለቱ ተቋማት ግኑኝነት በልምድ ልውውጡ ብቻ ተገድቦ የሚቀር ሳይሆን፣ ጠቃሚ የሆኑ እሴቶችን የምንለዋወጥበት ኦና ፣ህዝቡ በጋራ እንዲሰራ እንዲለማ ብሎም ተጠቃሚ እንዲሆን በጋራ እንደሚሰራም ተናግሯል ።

‎የጌዲኦ ቴሌቪዢን ም/ክ ስራአስኪያጅ አቶ እምነት ሺፈራው በበኩላቸው ጌዴኦ ቴሌቪዢን ባለፉት 4 ወራት በሙከራ ስርጭቱ ወቅታዊ ዜናዎችንና ፕሮግራሞችን ወደ ህዝቡ ተደራሽ እያደረገ መቆየቱን አስታውሰው፣ ቴሌቪዥኑ ወደ ሙሉ ስርጭቱ ሲገባ ለሚያከናውኗቸው ተግባራት ገንቢ ግብዓት የተወሰደበት ነው ብለዋል።

‎ሀዲያ ቴሌቪዥን ባለው ውስን የሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ ጥራቱን የጠበቀ ወቅታዊ መረጃዎችን ለህዝቡ ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ ሀዲያ ቴሌቪዥን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወንድሙ አቡሌ ገልፀዋል።

‎በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደረጃ በሙሉ ስርጭት የተለያዩ ይዘት ያላቸውን ዜናዎችና ፕሮግራሞችን ወደ ህብረተሰቡ ተደራሽ እያደረገ ያለው ብቸኛ ተቋም ነው ያሉት ዋና ስራአስፈፃሚው፣ በክልሉ ሁሉም ቦታ በመገኘት ሽፋን እየሰጠ ይገኛል ብለዋል።

‎ሚዲያውን ተገቢ ያልሆነ ገጽታ ለማላበስ የሚሞክሩ አንዳንድ አካላት ተግባራቸው ተገቢነት የሌለው መሆኑን ጠቅሰው፣ ክፍተት ካለ ገንቢና ተገቢ የሆነ አስተያየት በመስጠት ሚዲያውን መደገፍና ማብቃት እንደሚገባም ነው ያብራሩት።

‎የዞኑ አስተዳደር ለቴሌቪዥኑ እያደረገ ላለው ድጋፍ አመስግነው ህብረተሰቡም ሚዲያውን በባለቤትነት ስሜት መደገፍ እንዳለበትም አሳስበዋል።

‎የሀድያ ቴሌቪዥን በማህበረሰብ ቴሌቪዥን ደረጃ ካሉ ሚዲያዎች ግንባር ቀደም ተቋም መሆኑን አንስተው፣ የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት የልምድ በተለያዩ ወቅቶች ልምድ ልውውጥ ተመራጭ ማድረጋቸው አብራርተዋል።

‎ጌዴኦ ቴሌቪዥን ያደረገው የልምድ ልውውጥ በጋራ ተደጋግፎ ለመስራትና ትስስርን ለማጠናከር አቅም የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመው፣ለልምድ ልውውጡ መመረጥ በራሱ ለተሻለ ስራ የሚያነሳሳ ነው ብለዋል።

‎ምንትዋብ ኢያሱ

በ2018 በጀት ዓመት  ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን  በሀዲያ ዞን የሌሞ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት አስታወቀ።በወረዳው የሚገኙ  1ሺህ 55 የደረጃ"ሐ" ግብር ከፋዮች  ግብራ...
08/07/2025

በ2018 በጀት ዓመት ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን በሀዲያ ዞን የሌሞ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት አስታወቀ።

በወረዳው የሚገኙ 1ሺህ 55 የደረጃ"ሐ" ግብር ከፋዮች ግብራቸውን ከፍለዉ እንዲያጠናቅቁ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል ።

ሆሳዕና፦ 01/11/2017 (ሀድያ ቴሌቪዥን)

የሌሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ደምሴ በወረዳው በተለያዩ የግብር መክፈያ ማዕከላት የግብር ማስከፈል ስነ-ስርአት በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት፤ ግብር ለሀገር ክብር የሚከፈል የዜግነት ግዴታ በመሆኑ ሁሉም ግብር ከፋይ የሚጠበቅበትን አመታዊ ግብርን በወቅቱና በታማኝነት መክፈል አለበት።

በወረዳው አዳዲስ የገቢ አመራጮችን በመፍጠር ከባለፈው ዓመት ከፍ ያለ ገቢ ለመሰብሰብ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው የግብር ከፋዩን ማህበረሰብ የልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የሌሞ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሽፈራው አለቃ በበኩላቸው በወረዳው 1ሺህ 88 ግብር ከፋዮች መኖራቸውን ገልጸው፤ ከእነዚህም ውስጥ 1ሺህ 55 የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች መሆናቸውንና እነዚህም በጥቂት ቀናት ውስጥ ግብራቸውን አጠናቀው እንዲከፍሉ ለማድረግ መታቀዱንም ተናግረዋል::

በ2017 በጀት ዓመት 237 ሚሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 239 ሚሊየን ብር መሰብሰብ መቻሉን የጠቀሱት ኃላፊው በ2018 በጀት ዓመት እንደ ወረዳ 250 ሚሊየን ብር ገቢ ከመደበኛና ከማዘጋጃ ቤታዊ የገቢ ምንጮች ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱንም አስታውቀዋል።

ሐምሌ 1/2017 ዓ.ም በወረዳው በ10 ማዕካላት የ "ሐ" ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብር የመሰብሰብ ሥራ ተጀምሮ መጠናቀቁን የተናገሩት አቶ ሽፈራው ሁሉም ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ዓመታዊ ግብር በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ በመክፈል ሀገራዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ሲሉም አሳስበዋል ።

በበሌሳና በሹርሞ ግብራቸውን ሲከፍሉ አግኝተን ያነጋገርናቸው አንዳንድ ግብር ከፋዮች በሰጡት አስተያየት በግብር የሚሰበሰበውን ገንዘብ መንግስት ለዜጎች ልማት የሚያውል መሆኑን በመረዳት ግብርን በወቅቱና በታማኝነት እየከፈሉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ዋበላ ወርቁ

‎"በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል  በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው 7ኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሲጀመር የክልሉ ርዕስ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው...
08/07/2025

‎"በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው 7ኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሲጀመር የክልሉ ርዕስ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) መርሃ ግብሩን በፎቶ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አረንጓዴ አሻራ እና ክልላዊ የገጠር ኮሪደር ማስጀመሪያ ፕሮግራም በጉራጌ ዞን ጉመር ወረዳ ተጀመረ:: ‎‎ሆሳዕና ሐምሌ 01/2017 (ሀድያ ቴሌቪዥን) ‎‎"በመትከል...
08/07/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አረንጓዴ አሻራ እና ክልላዊ የገጠር ኮሪደር ማስጀመሪያ ፕሮግራም በጉራጌ ዞን ጉመር ወረዳ ተጀመረ::

‎ሆሳዕና ሐምሌ 01/2017 (ሀድያ ቴሌቪዥን)

‎"በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው 7ኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሲጀመር የክልሉ ርዕስ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) መርሃ ግብሩን በይፋ አስጀምረዋል::

ናሆም ዩሐንስ

Address

Hossana
Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hadiya.TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Hadiya.TV:

Share

Category