Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau

Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau, Hossana.
(3)

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እና የኢፌዴሪ የፌደሬሽን ምክር ቤት የስራ ኃላፊዎች  በሆሳዕና ከተማ በግንባታ ላይ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች ምልከታ እያደረጉ ነው (ሆሳዕና፣መስከረም 8/2018)...
18/09/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እና የኢፌዴሪ የፌደሬሽን ምክር ቤት የስራ ኃላፊዎች በሆሳዕና ከተማ በግንባታ ላይ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች ምልከታ እያደረጉ ነው

(ሆሳዕና፣መስከረም 8/2018)በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል በደመቀ ሁኔታ ለማክበር በክልሉ የቅድመ ዝግጅት ስራ እየተከናወነ ነው።

ይህን ተከትሎም የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በሆሳዕና ከተማ በግንባታ ላይ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ተመልክተዋል።

ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎቹ በግንባታ ላይ የሚገኙ የክልል ተቋማት ፣የአብዩ ኤርሳሞ ስታዲየም ግንባታ እና ሌሎች ለበአሉ አስፈላጊ የሆኑ የቅድመ የዝግጅት ስራዎችን አፈጻጸም ተመልክተዋል።

በልማት ስራ ምልከታው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣
የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል፣
በኢፌዴሪ የፌደሬሽን ምክር ቤት የመንግስታት ግንኙነት የዲሞክራሲ አንድነት የህገ መንግስት አስተምህሮ ቋሚ ኮሚቴ ፀሀፊ ወ/ሮ ባንቺ ይርጋ መለሰ እና ሌሎች የክልል እና የፌደራል የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በተስፋዬ መኮንን

ለተጨማሪ መረጃ ‼️

📌 በዌብሳይት https://www.cergcab.et/

📌በቴሌግራም https://t.me/CERGCAB

📌 በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100070605291100&mibextid=ZbWKwL

📌 በቲውተር https://twitter.com/CabCerg2678

📌 በቲክቶክ tiktok.com/

📌 በዩቲዩብ https://youtube.com/?si=Ipdg3R3A3hpPQEUV

📌 በኢንስታግራም https://www.instagram.com/cergcab/profilecard/?igsh=MWNseXBlaW05dnM3MA==

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

የህጻናትን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚፈጸሙ ተግባራት በጥናት መደገፍ እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ አስታወቀ።(ሆሳዕና፣ መስከረም 08/2018 ዓ/ም) ቢሮ...
18/09/2025

የህጻናትን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚፈጸሙ ተግባራት በጥናት መደገፍ እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕላንና ልማት ቢሮ አስታወቀ።

(ሆሳዕና፣ መስከረም 08/2018 ዓ/ም) ቢሮው በ2017 በጀት ዓመት በዩኒሴፍ በሚደረግ የበጀት ድጋፍ የህጻናትን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራትን ለመገምገምና የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች በተመለከተ ያዘጋጀው የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።

በምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት የቢሮው ኃላፊ ዶክተር ባዩሽ ተስፋዬ እንደተናገሩት የህጻናትን ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚፈጸሙ ተግባራት በጥናት መደገፍ ይገባል።

የጥናት ሥራዎቹም የህጻናትን ተጠቃሚነት መረጋገጥ እንዲሁም የተመዘገበ ውጤትና ለውጥ ላይ ማተኮር አለባቸው ብለዋል።

በማህበራዊ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት አደረጃጀትና አገልግሎት አሰጣጥ የሴቶችና ህጻናት ተጠቃሚነት ማካተቱን ቢሮው ድገፍና ክትትል ከማድረጉም በተጨማሪ ጉዳዩን በተመለከተ ጥናት እየሠራ መሆኑን ዶክተር ባዩሽ ጠቁመዋል።

በየደረጃው ያሉ ባለድርሻ አካላትም ለህጻናት የሚመደብ በጀት ተደራሽነትና ውጤታማነት በተመለከተ ችግር ፈች ጥናቶችን እንዲሰሩ ቢሮ ኃላፊዋ አሳስበዋል።

የቢሮው ምክትልና የልማት መረጃ አስተዳደር እና ስነ-ህዝብ ጉዳዮች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብርሃም አለሙ በበኩላቸው በ2017 በጀት ዓመት በዩኒሴፍ ድጋፍ ለህጻናት ጉዳይ በተያዘው በጀት የሚጠበቀው ውጤት እንዲመዘገብ በትኩረት ተሠርቷል።

ለህጻናት የሚመደብ በጀት በአግባቡ ሥራ ላይ እንዲውል መሥራት እንዲሁም ውጤቱንም በተከታታይ መገምገም ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።

ህጻናት በአካልና በአዕምሮ ጤነኛ ሆነው፣ መሠረታዊ መብቶቻቸው ተጠብቆ እንዲያድጉ የተቀመጡ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ ህጎችና ድንጋጌዎች እንዲከበሩ በትብብርና በቅንጅት መስራት ይገባል ያሉት አቶ አብርሃም ለዚህ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በርብርብ እንዲሠሩ ጠይቀዋል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ በዩኒሴፍ የበጀት ድጋፍ በ2017 በጀት ዓመት ለህጻናት ዘርፈ ብዙ ተጠቃሚነት የተፈጸሙ ዋና ዋና ተግባራት አፈጻጸም ሪፖርት እንዲሁም ውጤት ተኮር የመንግስት በጀት አስተዳደር በተመለከተ ሰነድና ገለጻ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በምክክር መድረኩ ከክልል፣ ከዞንና ልዩ ወረዳዎች የፕላንና ልማት እና ፋይናንስ ቢሮዎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

በአሳምነው ተከተል

ለተጨማሪ መረጃ ‼️

📌 በዌብሳይት https://www.cergcab.et/

📌በቴሌግራም https://t.me/CERGCAB

📌 በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100070605291100&mibextid=ZbWKwL

📌 በቲውተር https://twitter.com/CabCerg2678

📌 በቲክቶክ tiktok.com/

📌 በዩቲዩብ https://youtube.com/?si=Ipdg3R3A3hpPQEUV

📌 በኢንስታግራም https://www.instagram.com/cergcab/profilecard/?igsh=MWNseXBlaW05dnM3MA==

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር ) በሆሳዕና ከተማ እየተከናወኑ በሚገኙ የግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም  ምልከታ አደረጉ፣ሆሳዕና ፣ መስከረም 8፣ 2018 ፦ የማዕከላዊ  ኢትዮጵያ ክል...
18/09/2025

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር ) በሆሳዕና ከተማ እየተከናወኑ በሚገኙ የግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ምልከታ አደረጉ፣

ሆሳዕና ፣ መስከረም 8፣ 2018 ፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር ) በሆሳዕና ከተማ እየተከናወኑ በሚገኙ የግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ ምልከታ አድርገዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይም በግንባታ ላይ የሚገኘውን የርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤትና ተያያዥ ግንባታዎችን የአፈፃፀም ሂደት የሚገኝበትን ደረጃ ምልከታ አድርገዋል ሥራዉ እንዲፈጥንም ድጋፍና ክትትሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል ።

በተመሳሳይ ተጨማሪ ማሻሻያዎች ተደርገዉለት እየተገነባ የሚገኛዉ የአቢዩ ኤርሳሞ ስታዲየም ግንባታ ሂደት የሚገኝበትን ሁኔታ ተመልክተዋል።

በመስክ ምልከታዉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል እና ሌሎችም የክልል ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል ።

ለተጨማሪ መረጃ ‼️

📌 በዌብሳይት https://www.cergcab.et/

📌በቴሌግራም https://t.me/CERGCAB

📌 በፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100070605291100&mibextid=ZbWKwL

📌 በቲውተር https://twitter.com/CabCerg2678

📌 በቲክቶክ tiktok.com/

📌 በዩቲዩብ https://youtube.com/?si=Ipdg3R3A3hpPQEUV

📌 በኢንስታግራም https://www.instagram.com/cergcab/profilecard/?igsh=MWNseXBlaW05dnM3MA==

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

የሆቴል ኢንዱስትሪ ጥራት ያለውንና ፈጣን አገልግሎት እንዲሰጥ አገልግሎቱን ማዘመን ይገባል ተባለ( ሆሳዕና፦መስከረም 8/2018)   የፌዴራል ቱሪዝም ሚኒስቴር ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህል...
18/09/2025

የሆቴል ኢንዱስትሪ ጥራት ያለውንና ፈጣን አገልግሎት እንዲሰጥ አገልግሎቱን ማዘመን ይገባል ተባለ

( ሆሳዕና፦መስከረም 8/2018) የፌዴራል ቱሪዝም ሚኒስቴር ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመቀናጀት በሆሳዕና ከተማ ለሚገኙ የሆቴል ባለሙያዎች ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው ቅድመ የዓለም ቱሪዝም ቀን ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተጠናቀቀ።

በስልጠናው ማጠናቀቂያ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የኃላፊ አማካሪ አቶ አብድልበር ሻፊ እንደገለፁት ተጠቃሚ ህብረተሰብ ከአገልግሎት ሰጭ ተቋማት ትክክለኛውን አገልግሎት እንዲያገኙ በዘርፉ የሰለጠነ ባለሙያ ያስፈልጋል ብለዋል።

የሆቴል ኢንዱስትሪ እያደገ ሲሄድ ለበርካታ ስራ አጥ ዜጎች የስራ ዕድል ከማስገኘትም ባለፈ ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ ለከተማው ልማት የገቢ ምንጭ በመሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ መኖሩን ገልፀዋል።

የሆቴል ኢንዱስትሪ ጥራት ያለውንና ፈጣን አገልግሎት እንዲሰጡ አገልግሎቱን ለማዘመን ስልጠና መስጠቱ ተገቢ መሆኑን በመግለጽ የተገልጋዩ ፍላጎት መሰረት ያደረገ አግልግሎት መስጠት ከሁሉም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሚጠበቅ ተግባር እንደሆነም ጠቁመዋል ።

በክልሉ ለሚከበረው 20ኛው ብሔር ብሔረሰቦች ቀንን ብሎም የዓለም ቱሪዝም ቀን የሚከበር በመሆኑና በርካታ እንግዶች ወደ ክልሉ የሚመጡ በመሆኑ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አገልግሎት አስመጣቸውን ማዘመን እንደሚገባቸው ተናግረዋል።

ስልጠናውም ትኩረት ያደረጋቸው ጉዳዮች በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ፣ በምግብና መጠጥ አዘገጃጀት፣በመስተንግዶ፣በእንግዳ አቀባበል፣ አለባበስ ፣በደንበኛ አያይዝ፣ የግልና የተቋም ንፅህና መጠበቅ እና በሌሎች ተግባራት ዙሪያ መሰረት ያደረገ በመሆኑ ለቀጣይ ተግባር አጋዥ እንደሚሆን ተናግረዋል።

ሰልጣኞች እንደተናገሩት ለአንድ ሀገር ዕድገት የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ የተሰጠው ስልጠና በቀጣይ ለሚያከናውኗቸው ስራ ስልጠናው የተግባር ልምምድ የታከለበት በመሆኑ በቂ እውቀት እና ግንዛቤ ያገኙበት መሆኑን ተናግረዋል።

በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሚሰሩ ሰራተኞች ከእንግዶች እና ከተገልጋዩ ጋር በቅርበት የሚገናኙ በመሆኑ ተገልጋዮችን በመንከባከብ ብሎም ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት በአገልግሎታቸው የሚደሰቱ ደንበኞችን ለማብዛት እንደሚሰሩም ገልጸዋል ።

በአድነው አሰፋ

በሴቶች 5ሺህ ሜትር ማጣሪያ ሦስት ኢትዮጵያውያን ለፍጻሜ አለፉሆሳዕና፣ መስከረም 8፣ 2018  በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 5ሺህ ሜትር ማጣሪያ ሦስት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለፍጻሜ...
18/09/2025

በሴቶች 5ሺህ ሜትር ማጣሪያ ሦስት ኢትዮጵያውያን ለፍጻሜ አለፉ

ሆሳዕና፣ መስከረም 8፣ 2018 በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና 5ሺህ ሜትር ማጣሪያ ሦስት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለፍጻሜ አልፈዋል፡፡

በርቀቱ ኢትዮጵያን የወከሉት ጉዳፍ ጸጋይ፣ መዲና ኢሳ እና ፋንታዬ በላይነህ ፍጻሜውን የተቀላቀሉ ሲሆን፥ አትሌት ብርቄ ሀየሎም ወደ ፍጻሜ ማለፍ ሳትችል ቀርታለች፡፡(ኤፍ ኤም ሲ)

18/09/2025

አዲስ አበባ የአፍሪካውያን ተምሳሌት ትሆናለች-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

18/09/2025
 !በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሙዱላ  ከተማ  ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን በማስመልከት  ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል።(ሆሳዕና መስከረም 8/2018 "በኅብረት ችለናል" በሚል...
18/09/2025

!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሙዱላ ከተማ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን በማስመልከት ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል።

(ሆሳዕና መስከረም 8/2018

"በኅብረት ችለናል" በሚል መሪ ሀሳብ የሙዱላ ከተማ ነዋሪዎች ደስታቸውን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።

 !በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል  ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን በማስመልከት በቆሼ ከተማ ህዝባዊ የድጋፍ   ሰልፍ  እየተካሄደ ነውሆሳዕና፣መስከረም  8/2018"በህብረት_ችለናል "በሚ...
18/09/2025

!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን በማስመልከት በቆሼ ከተማ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው

ሆሳዕና፣መስከረም 8/2018

"በህብረት_ችለናል "በሚል መሪ ቃል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በማረቆ ልዩ ልዩ ወረዳ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን በማስመልከት ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው

 !ሆሳዕና መስከረም 8/2018በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሳጃ ከተማ  ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን በማስመልከት  ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል።
18/09/2025

!

ሆሳዕና መስከረም 8/2018

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሳጃ ከተማ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን በማስመልከት ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል።

የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ አስመልክቶ በወራቤ ከተማ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነውሆሳዕና፣ መስከረም 8/2018 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል "በህብረት ችለናል" በሚል መሪ ...
18/09/2025

የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ አስመልክቶ በወራቤ ከተማ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው

ሆሳዕና፣ መስከረም 8/2018 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል "በህብረት ችለናል" በሚል መሪ ቃል የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ምረቃ በማስመልከት በወራቤ ከተማ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል።

ታላቁ የህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን ምክንያት በማድረግ በህብረት ችለናል በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ላይ:- በህብረት ችለናል!
‎ የሕዳሴ ግድብ፣ የኢትዮጵያ ማንሰራራት ምልክት!ከጨለማ ወደ ብርሃን!፣ የሕዳሴ ግድብ የብልጽግናችን አሻራ! እና ሌሎችም መፈክሮች በድጋፍ ሰልፉ እየተስተጋቡ ነው።


በህዝባዊ ሰልፉ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማሕበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ እና የወራቤ ከተማ ህዝብ እየተሳተፈ ይገኛል።

 !ሆሳዕና መስከረም 8/2018ዓ.ም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀቤና ልዩ ወረዳ በወልቂጤ ከተማ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን በማስመልከት  ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ መሆኑን ከፓርቲ...
18/09/2025

!

ሆሳዕና መስከረም 8/2018ዓ.ም

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀቤና ልዩ ወረዳ በወልቂጤ ከተማ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን በማስመልከት ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ መሆኑን ከፓርቲ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ።

Address

Hossana
72

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau:

Share