HOSSANA AT A GLANCE

HOSSANA AT A GLANCE መዝናኛ ስፖርት ጤና ታሪክ ጠቅላላ እውቀት ማስታወቂያና ሁለገብ መረጃዎች ይቀርባሉ።

"የበሌሳ ሆስፒታል በሀድያ ምድር ከተመሰረቱ ቀደምት የጤና ተቋማት መካከል አንዱ ሲሆን፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገር ተቋም ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል ይደረጋል" - ዶ/ር...
04/06/2026

"የበሌሳ ሆስፒታል በሀድያ ምድር ከተመሰረቱ ቀደምት የጤና ተቋማት መካከል አንዱ ሲሆን፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገር ተቋም ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል ይደረጋል" - ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የበሌሳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግንባታ ተረከበ

ሆሳዕና 27/09/2018 ዓ.ምበሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ሌሳ ቀበሌ በሕዝብ ተሳትፎ ግንባታው ተጀምሮ ለረጅም ጊዜ ሳይጠናቀቅ የቆየውን የበሌሳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግንባታ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በይፋ ተረክቦ እስከ ፍጻሜው ድረስ የማስገንባት ኃላፊነት መውሰዱን አስታውቋል።

በግንባታው ርክክብ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዋና የመንግሥት ተጠሪ ድላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር) የበሌሳ ሆስፒታል በአካባቢው ለዘመናት ጤና አገልግሎት ሲሰጥ የነበረ ታሪካዊ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ ተቋሙ የትውልድ ቅርስ በመሆኑ ግንባታው መጠናቀቅ አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል።

ዶ/ር ድላሞ አክለውም ተቋሙ በሀድያ ምድር ከተመሰረቱ ቀደምት የጤና ተቋማት መካከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገር ተቋም ሆኖ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ ገልጸዋል።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዳዊት ሀዬሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው የዩኒቨርሲቲው አመራር ከዚህ ቀደም ፕሮጀክቱን በመጎብኘት ሁኔታውን መገምገሙን ጠቅሰው፣ ግንባታውን በመረከብ ለማጠናቀቅ የነበረውን እቅድ አስታውሰዋል።

ፕሬዚዳንቱ እንዳሉት፣ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ በጀትና ጊዜ የሚጠይቅ ቢሆንም፣ በመንግሥት፣ በሕዝብና በተቋማት ትብብር በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ እምነታቸውን ገልጸዋል።

በመጨረሻም ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ግንባታውን እስከ መጨረሻው በኃላፊነት በመምራት ለማጠናቀቅ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በበኩላቸው፣ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ግንባታውን ቢመራም የክልሉ ጤና ቢሮ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

አክለውም የጤና ሚኒስቴር የተጀመሩ የጤና ተቋማትን ግንባታ ወደ ፍጻሜ ለማድረስ እቅድ መያዙን ጠቅሰው፣ ሆስፒታሉ ሲጠናቀቅ የመድኃኒትና የቁሳቁስ ድጋፍ እንደሚደረግ ተናግረዋል።

የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ በበኩላቸው ለፕሮጀክቱ መጀመርና መቀጠል አስተዋፅኦ ያደረጉ ሁሉንም አካላት አመስግነው፣ ሆስፒታሉ ለሰፊው ማኅበረሰብ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት እንደሚሰጥ ተናግረዋል።

ዞኑም ለግንባታው ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

የሌሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ደምሴ በበኩላቸው፣ የ7ኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ በሰላም በተጠናቀቀበት ማግስት መርሐ ግብሩ መካሄዱ ለአካባቢው ልዩ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል።

የአካባቢው ነዋሪዎችም ሆስፒታሉ ታሪካዊ ተቋም መሆኑን ጠቅሰው፣ በሕዝብ አቅም ተጀምሮ ለረጅም ጊዜ ሳይጠናቀቅ መቆየቱን ገልጸዋል።

ይሁን እንጂ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ግንባታውን በመረከብ ሥራውን በይፋ ማስጀመሩ ተስፋ እንደሰጣቸው እና ደስታ እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።

ሀድያ ቴሌቪዥን በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የዘገባ ስራ ላይ ለተሳተፉ ባለሙያዎች ምስጋና አቀረበግንቦት 26/2018 ዓ.ም (ሆሳዕና) ሀድያ ቴሌቪዥን በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ወቅት ዘገባዎችን...
03/06/2026

ሀድያ ቴሌቪዥን በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የዘገባ ስራ ላይ ለተሳተፉ ባለሙያዎች ምስጋና አቀረበ

ግንቦት 26/2018 ዓ.ም (ሆሳዕና) ሀድያ ቴሌቪዥን በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ወቅት ዘገባዎችን በብቃት ላከናወኑና ስኬታማ ለነበሩ የተቋሙ ባለሙያዎች እውቅናና ምስጋና አበረከተ።

ተቋሙ ምስጋናውን ያቀረበው የምርጫ ዘገባ ስራ አፈጻጸሙን ከተቋሙ ባለሙያዎች ጋር በጋራ በገመገመበት መድረክ ላይ ነው።

በግምገማው ወቅት እንደተገለጸው፤ ጣቢያው ከቅድመ-ምርጫ እስከ ድህረ-ምርጫ ባሉት ሂደቶች መረጃዎችን በቴሌቪዥንና በማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ለህብረተሰቡ በስፋት ተደራሽ አድርጓል።

የተሰሩ ዘገባዎች ለሌሎች መገናኛ ብዙሃንም ጭምር የመረጃ ግብዓት መሆን የቻሉ ሲሆን፣ ለዚህ ስኬትም የባለሙያዎችና የአመራሩ ቅንጅት እንዲሁም የህብረተሰቡ ተሳትፎ ትልቅ ሚና ተጫውቷል።

የሀድያ ቴሌቪዥን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ወንድሙ አቡሌ በበኩላቸው፤ ተቋሙ ቀደም ሲል በብሄር ብሄረሰቦች እና በያሆዴ በዓላት ላይ የነበረውን ጠንካራ የዘገባ ልምድ በመጠቀም በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይም ውጤታማ ስራ ማከናወኑን ገልጸዋል።

ተቋሙ ያስቀመጠውን ግብ ማሳካቱን የጠቀሱት ዋና ስራ አስኪያጁ፣ ለስራው መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት ሰራተኞችና አብረዋቸው ለሰሩ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

02/06/2026

ከምርጫው ጋር በተያያዘ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምርጫው በሠላማዊ ሁኔታ ስለመጠናቀቁ ለሀዲያ ቴሌቪዥን ከተናገሩት

02/06/2026

በምርጫው ዙሪያ ለሀዲያ ቴሌቪዥን ከተናገሩት

CLASSIC Café & Restaurant Located @ Hossana City around Mesalemiya beside Mega book store.🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆
30/05/2026

CLASSIC Café & Restaurant Located @ Hossana City around Mesalemiya beside Mega book store.
🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆🏆

በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሀዲያ ዞን በሚገኙ ዘጠኝ የምርጫ ክልሎች የብልጽግና ፓርቲን ወክለው ለኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች እና ለክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚወዳደሩ ዕጩዎች እኝ...
25/05/2026

በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሀዲያ ዞን በሚገኙ ዘጠኝ የምርጫ ክልሎች የብልጽግና ፓርቲን ወክለው ለኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች እና ለክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚወዳደሩ ዕጩዎች እኝህ በቀጣይ ምስሎች የሚታዩ ናቸው።

17/05/2026

የብልጽግና ፓርቲ 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊና ክልላዊ የምረጡን ቅስቀሳ በሙሉ ሀዲይሳ መዝሙር...

Address

Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when HOSSANA AT A GLANCE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share