HOSSANA AT A GLANCE

HOSSANA AT A GLANCE መዝናኛ ስፖርት ጤና ታሪክ ጠቅላላ እውቀት ማስታወቂያና ሁለገብ መረጃዎች ይቀርባሉ።

06/09/2026

ጤና ለጤና ...!! መልካም አዲስ ዓመት
💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧

የ250 ሺህ ብር ሽልማት - ከሊች ጎጎ አዳሪ ት/ቤት 590.08 ነጥብ ከ600 ያስመዘገበውና በሀገሪቱ 2ኛውን ደረጃ ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ ሮቤል ጌታቸው ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ ...
04/09/2026

የ250 ሺህ ብር ሽልማት - ከሊች ጎጎ አዳሪ ት/ቤት 590.08 ነጥብ ከ600 ያስመዘገበውና በሀገሪቱ 2ኛውን ደረጃ ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ ሮቤል ጌታቸው ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ሽልማትና የዕውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶለታል።

ተማሪ ሮቤል ጌታቸው በ2018 ዓ.ም በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ ከሚገኘው ሊች ጎጎ አዳሪ የልህቀት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት ቤቱን፣ የዞኑን የክልሉን 1ኛ የሆነ ውጤት እንዲሁም የሀገሪቱን 2ኛ የሆነ ውጤት ማለትም 590.08 ነጥብ ከ600 ማስመዝገቡ የሚታወስ ሲሆን፤

በዛሬው ዕለት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ባዘጋጀው ፕሮግራም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እጅ የ250 ሺህ ብር እና ዘመናዊ የታብሌት ሽልማት እንዲሁም የዕውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶለታል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አካላት እውቅና ተሰጠ፤ በክልሉ 1ኛ እና በሀገሪቱ 2ኛ ለወጣው ለተማሪ ሮቤል ጌታቸው በልዩነት የ250 ሺህ ብር ...
04/09/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ2018 የትምህርት ዘመን የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አካላት እውቅና ተሰጠ፤ በክልሉ 1ኛ እና በሀገሪቱ 2ኛ ለወጣው ለተማሪ ሮቤል ጌታቸው በልዩነት የ250 ሺህ ብር ሽልማት ተበርክቷል።

በክልሉ በሀገራዊና ክልላዊ ፈተናዎች ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ፣ በ2018 በጀት ዓመት በአጠቃላይ የትምህርት ስራ ዎች የላቀ ውጤት ላመጡ ለዞኖች እና ለልዩ ወረዳዎች፣ ለአዳሪ ትሞህርት ቤቶች፣ ለ2ኛ ደረጃ ፣ለአንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በመድረኩም ተማሪ ሮቤል ጌታቸው በ2018 ዓ.ም በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ ከሚገኘው ሊች ጎጎ አዳሪ የልህቀት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት ቤቱን፣ የዞኑን እና የክልሉን 1ኛ የሆነ ውጤት እንዲሁም የሀገሪቱን 2ኛ የሆነ ውጤት ማለትም 590.08 ነጥብ ከ600 በማስመዝገቡ በክልሉ ብቸኛው የ 250 ሺህ ብር ተሻላሚ ሊሆን ችሏል።

ከዋቸሞ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 539.92 ነጥብ ከ600 ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ ቶማስ ወንድሙ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ሽልማትና የዕውቅና ሰር...
04/09/2026

ከዋቸሞ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 539.92 ነጥብ ከ600 ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ ቶማስ ወንድሙ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ሽልማትና የዕውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶለታል።

ተማሪ ቶማስ ወንድሙ ኃይለማሪያም በ2018 ዓ.ም በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ ከሚገኘው ከአንጋፋው ዋቸሞ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት ቤቱን 1ኛ የሆነ ውጤት ማለትም 539.92 ነጥብ ከ600 ማስመዝገቡ የሚታወስ ሲሆን፤

በዛሬው ዕለት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ባዘጋጀው ፕሮግራም ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እጅ ዘመናዊ የታብሌት ሽልማትና የዕውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶለታል።

በሆሳዕና ከተማ ሊች ጎጎ አዳሪ የልህቀት ት/ቤት በ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ 2ኛውን ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበው ተማሪ ሮቤል ጌታቸው የ2 መቶ ሺህ ብር ሽልማትና ዕውቅ...
30/08/2026

በሆሳዕና ከተማ ሊች ጎጎ አዳሪ የልህቀት ት/ቤት በ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ 2ኛውን ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበው ተማሪ ሮቤል ጌታቸው የ2 መቶ ሺህ ብር ሽልማትና ዕውቅና ከሀዲያ ዞን አስተዳደርና ትምህርት መምሪያ ተበረከተ!!

ከወርልድ ብራይት ኮሌጅና አካዳሚ ቦርድ ጽ/ቤት የተላለፈ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት!!በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ መልቀቂያ ፈተና የወሰዳችሁ የወርልድ ብራይት አካዳሚ አጠቃላይ ...
29/08/2026

ከወርልድ ብራይት ኮሌጅና አካዳሚ ቦርድ ጽ/ቤት የተላለፈ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት!!

በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ መልቀቂያ ፈተና የወሰዳችሁ የወርልድ ብራይት አካዳሚ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ!

የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ መልቀቂያ ፈተና መንግሥት በሀገር ደረጃ ባስተዋወቀው ዘመናዊና ዲጂታል የትምህርት፣ የፈተናና የምዘና ሥርዓት መሠረት መሰጠቱ ይታወቃል። በዚህ ስርዓት ሀገራዊ ፈተና ከወሰዱት የአካዳሚያችን ተማሪዎች መካከል 85% በመቶዎቹ በቀጥታ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችል ውጤት ማስመዝገባቸውን በታላቅ ደስታና ኩራት እንገልጻለን። ቀሪዎቹ 15% በመቶ ደግሞ በአቅም ማሻሻያ መርሃ ግብር ወይም ወደ ኮሌጅ ለመግባት የሚያስችል ውጤት በማስመዝገባቸው ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶናል።

በተለይም ከ300 በላይ እስከ 533.25 ድረስ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ለሀገራችን፣ ለክልላችን፣ ለዞናችን እንዲሁም ለአካዳሚያችን ኩራት የሆናችሁ ተማሪዎቻችንን ከልብ እናመሰግናለን፤ እንኳንም ደስ አላችሁ!

በተጨማሪም ለዚህ ውጤት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላደረጋችሁ የተማሪዎች ወላጆች፣ ለወርልድ ብራይት ኮሌጅና አካዳሚ ማኅበረሰብ፣ መምህራን፣ አመራሮች፣ ሠራተኞች እና አጋር ድርጅቶች ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳንም ደስ አለን!
ከ450 በላይ እስከ 533.25 ድረስ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ስማቸው ከዚህ በታች በተከታታይ ይገለጻል።

ውድ ተማሪዎቻችን፣ ወደ ዩኒቨርሲቲ በምታደርጉት ቀጣይ የትምህርት ጉዞ የላቀ ስኬት እንመኝላችኋለን። መጪው የትምህርት ዘመን በዕውቀት፣ በስኬትና በብሩህ ተስፋ የተሞላ እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን።
እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳንም ደስ አለን!

ከወርልድ ብራይት ኮሌጅና አካዳሚ ቦርድ ጽሕፈት ቤት

የመንግስት ት/ቤቶች የተሻለ ትኩረት ከተሰጣቸው ከአዳሪ ት/ቤቶች ውጤት እኩል እንደሚሆኑ በሆሳዕና ከተማ የዋቸሞ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ "ተማሪ ቶማስ ወንድሙ ሐይለማሪያም" ውጤት አንዱ ማሳያ ...
29/08/2026

የመንግስት ት/ቤቶች የተሻለ ትኩረት ከተሰጣቸው ከአዳሪ ት/ቤቶች ውጤት እኩል እንደሚሆኑ በሆሳዕና ከተማ የዋቸሞ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ "ተማሪ ቶማስ ወንድሙ ሐይለማሪያም" ውጤት አንዱ ማሳያ ነው።

የተማሪ ቶማስ ወንድሙ እናት ሒሩት በየነ ከዛሬ 28 ዓመት በፊት የማትሪክ ፈተና ውጤት ለማለፍ ጠባበብ በነበረበት ዘመን በ1990 ዓ.ም በዋቸሞ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 3.8 ውጤት በማስመዝገብ በወቅቱ ከተመዘገቡ ከከፍተኞቹ ውጤት ተርታ ነበረች እናቱ ሒሩት በየነ በተመሳሳይ አባቱ አቶ ወንድሙ ሐይለማሪያም በሌላኛው 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በወቅቱ ከፍተኛ ውጤት ከነበራቸው ተማሪዎች አንዱ ነበር።

ዛሬም ቶማስ ወንድሙ ሐይለማሪያም የአባቱን ፈለግ በመከተልና እናቱ ታሪክ በሰራችበት ት/ቤት ዳግም የእናቱን ታሪክ በመስራት የዋቸሞ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ወደ ቀድሞው ገናና ስምና ዝና እንዲመለስ በር ከፋች የሆነ 539.92 ነጥብ ከ600 ውጤት ከማስመዝገቡም ባሻገር የመንግስት ትምህርት ቤቶች በተሻለ ትኩረት ከተሰራባቸው ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት እንደሚያስመዘግቡ ተጨባጭ ማሳያ ነው።

በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 590.08 ውጤት ያስመዘገበው ሌላኛው የኢትዮጵያ ተስፋ - ተማሪ ሮቤል ጌታቸው ********************* በአንድ ሀገር የዕድገት ጉዞ ውስጥ ትልቁ ካ...
28/08/2026

በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 590.08 ውጤት ያስመዘገበው ሌላኛው የኢትዮጵያ ተስፋ - ተማሪ ሮቤል ጌታቸው
*********************

በአንድ ሀገር የዕድገት ጉዞ ውስጥ ትልቁ ካፒታል የነገን ራዕይ ሰንቀው የሚነሡ ምጡቅ አዕምሮ ያላቸው ወጣቶች ናቸው።

የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ሲገለጽም፣ ኢትዮጵያ መፃኢ ጊዜዋን በልበ ሙሉነት ልታስረክባቸው የምትችላቸውን ብሩህ ተስፋዎች ተመልክታለች።

ከእነዚህ ሀገር አኩሪ ኮከቦች መካከል ደግሞ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ሀድያ ዞን፣ ሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የሊች ጎጎ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው ሮቤል ጌታቸው አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል።

በሀገር አቀፍ ፈተናው ከፍተኛው ውጤት 591.6 ሆኖ በተመዘገበበት በዚህ ዓመት፣ ተማሪ ሮቤል ከ600 ውስጥ 590.08 ውጤት በማስመዝገብ በሀገር ደረጃ ሁለተኛውን ከፍተኛ ደረጃ ተቆናጥጧል።

ይህ አኩሪ ስኬት በአጋጣሚ የተገኘ ሳይሆን በዓላማ፣ በጠንካራ የጥናት ስልት እና በማያወላውል ትኩረት የተገነባ፣ የለፋበትን እና የደከመበትን እልህ አስጨራሽ ጉዞ የሚያሳይ የድካም ፍሬ ነው።

የሮቤል ስኬት ከኋላው ብዙ የሚነገሩ ትምህርት ሰጪ ታሪኮች አሉት። ይህም የንባብ ጊዜውን በከፍተኛ ትኩረት ማሳለፍ፣ ማስታወሻ የመያዝ እና በርካታ ጥያቄዎችን የመሥራት የዳበረ ልምድ ያለው መሆኑ ነው።

ሮቤል ለ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና የተዘጋጀበት መንገድ ውጤታማ እንዳደረገው ይናገራል። ከምንም በላይ ደግሞ ለደረሰበት ከፍታ የወላጆቹ ዐሻራ ጎልቶ ይታያል። እናት እና አባቱ መምህራን መሆናቸውን እና እነሱ በትምህርት ዘርፍ ውስጥ መሆናቸው እርሱም ሙሉ ትኩረቱን ትምህርቱ ላይ እንዲያደርግ አስችሎታል።

የምናልመው ነገር ትልቅ ከሆነ የሚመጣው ውጤትም በተመሳሳይ ከፍተኛ እንደሚሆን ጽኑ እምነት አለው፤ ይህንንም በተግባር አሳይቷል።

በዚህ አስደናቂ ውጤቱ ምክንያት የክልሉ መንግሥት እና የትምህርት ቢሮ ከፍተኛ ኩራት እንደተሰማቸው በመግለጽ፣ ልዩ የማበረታቻ ሽልማት አበርክተውለታል።

ሮቤል ጌታቸው፣ ቀጣይ ጉዞው ሰማየ ሰማያትን ሰንጥቆ መብረር ነው። ከልጅነቱ ጀምሮ በልቡ ያሳደገውን የአውሮፕላን አብራሪነት (ፓይለት) ሕልሙን እውን በማድረግ፣ በአቪዬሽኑ ዘርፍ ጥሩ ቦታ የመድረስ ጽኑ ራዕይ እንዳለው አጽንኦት ሰጥቶ ይናገራል።

በእርግጥም የሮቤል ታሪክ የውጤት ብቻ ሳይሆን፣ የትልቅ ሕልም፣ የዓላማ ጽናት፣ እና የትኩረት ማሳያ ነው። እሱ ለትውልዱ አብነት፣ ለሀገሩም ሌላኛው ብሩህ ተስፋ ነው!

539.92 ነጥብ ከ 600 - በዋቸሞ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ከፍተኛው (1ኛ) ውጤት በተማሪ ቶማስ ወንድሙ ሐይለማሪያም (ባቢ) ተመዝግቧል!!"CONGRATULATIONS !!539.92 ነጥብ ከ 60...
27/08/2026

539.92 ነጥብ ከ 600 - በዋቸሞ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ከፍተኛው (1ኛ) ውጤት በተማሪ ቶማስ ወንድሙ ሐይለማሪያም (ባቢ) ተመዝግቧል!!

"CONGRATULATIONS !!

539.92 ነጥብ ከ 600

በተማሪ ቶማስ ወንድሙ

በአንጋፋው ዋቸሞ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት

የተመዘገበ ከፍተኛው (1ኛ) ውጤት

539.92 ነጥብ ከ 600 - ከዋቸሞ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እጅግ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡት ተማሪዎች መካከል ቶማስ ወንድሙ ሐይለማሪያም (ባቢ) አንዱ ሲሆን ይህም ውጤት በትምህርት ቤ...
27/08/2026

539.92 ነጥብ ከ 600 - ከዋቸሞ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እጅግ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡት ተማሪዎች መካከል ቶማስ ወንድሙ ሐይለማሪያም (ባቢ) አንዱ ሲሆን ይህም ውጤት በትምህርት ቤቱ 1ኛ ሆኖ ተመዝግቧል።

Address

Hossana

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when HOSSANA AT A GLANCE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share