Jano-Media

Jano-Media ጠልተን የምንተወው ወይም ወደን የምንቀበለው እውነት የለም፤ እውነት የምርጫ ጉዳይ አይደለም

እውነት "ያው" እውነት ነው💚💛❤️

25/10/2025

በሠላም የዋለ ሰው
ብቻ
✍️ ተመስገን ይበል 🥰

21/10/2025

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ከዘንድሮ ዓመት ጀምሮ የክልሉ የትምህርት ቋንቋ አማርኛ እንዲሆን እና ሰባት የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች "እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት" እየተሰጡ እንዲቀጥሉ ወሰነ።
"ጊዜያዊ ነው" የተባለው ይህ አሠራር በዚህ ዓመት በቅድመ መደበኛ (ኬጂ) እና በአንደኛ ክፍል ተማሪዎች ላይ የሚተገበር ሲሆን በየዓመቱ ወደ ሌሎች የክፍል ደረጃዎች እያደገ እንደሚሄድ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።
https://www.facebook.com/100068240109154/posts/1116015184016475/?app=fbl

"ለመዝረፍ ነበር የመጣሁት" _ ጌታቸው ረዳ ጠ/ሚ አብይ አህመድን ፈገግ ያስባለው የአቶ ጌታቸው ረዳ ንግግር ........ባሌ የመጨረሻ የመጣሁት ከ 13 ዓመት በፊት ነበር ባሌ መልከዓምድር ...
21/10/2025

"ለመዝረፍ ነበር የመጣሁት" _ ጌታቸው ረዳ

ጠ/ሚ አብይ አህመድን ፈገግ ያስባለው የአቶ ጌታቸው ረዳ ንግግር ........

ባሌ የመጨረሻ የመጣሁት ከ 13 ዓመት በፊት ነበር ባሌ መልከዓምድር ነው ለእኛ እንጂ ሌላ ነገር የለውም ያኔ መንገድ ለመመረቅ ነበር የመጣሁት በስንት ዘመን የተሰራች ብቸኛ አንድ መንገድ ነበረች በሄሊኮፕተር ነበር የሄድኩት በጣም ሃብታም ምድር መሆኑ ምንም የሚያጠራጥር አልነበረውም ይሄንን ሃብት ለመጠቀም እንኳን መንገድ እንዴት ቀደም ብለው መስራት አልታየቸውም ነበር ብየ እጠይቅ ነበር ያኔ እንኳን ያልኩት ለመዝረፍ ነበር ።"ለመዝረፍ ነበር የመጣሁት" _ ጌታቸው ረዳ

ጠ/ሚ አብይ አህመድን ፈገግ ያስባለው የአቶ ጌታቸው ረዳ ንግግር ........

ባሌ የመጨረሻ የመጣሁት ከ 13 ዓመት በፊት ነበር ባሌ መልከዓምድር ነው ለእኛ እንጂ ሌላ ነገር የለውም ያኔ መንገድ ለመመረቅ ነበር የመጣሁት በስንት ዘመን የተሰራች ብቸኛ አንድ መንገድ ነበረች በሄሊኮፕተር ነበር የሄድኩት በጣም ሃብታም ምድር መሆኑ ምንም የሚያጠራጥር አልነበረውም ይሄንን ሃብት ለመጠቀም እንኳን መንገድ እንዴት ቀደም ብለው መስራት አልታየቸውም ነበር ብየ እጠይቅ ነበር ያኔ እንኳን ያልኩት ለመዝረፍ ነበር ።

20/10/2025

የመሬት መንቀጥቀጥ‼️
ዛሬ ጥቅምት 10/2018ዓ.ም ምሽት 1:27 ጀምሮ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። መቀሌ:አዲጉደም:ውቅሮ:አዲግራት፣ ሽሬ፣በአፋር አብአላ፣በራህሌ እና ሌሎች አካባቢዎች ከበድ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአዩዘሀበሻ ቤተሰቦች ጠቁመዋል። የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.3 ተለክቷል።
(አዩዘሀበሻ)
==========≠============
💎⬇️⬇️⬇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

🤔ገንደወይን ከተማ
20/10/2025

🤔ገንደወይን ከተማ

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች የዑለማእ ም/ቤት የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ!||✍ የሸሪዓን መሠረታዊ መርሆች መሰረት በማድረግና የኡማውን አንድነት የመጠበቅን የጋራ ጥቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት፣...
20/10/2025

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች የዑለማእ ም/ቤት የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ!
||
✍ የሸሪዓን መሠረታዊ መርሆች መሰረት በማድረግና የኡማውን አንድነት የመጠበቅን የጋራ ጥቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ የኢትዮጵያ ዑለማእ ምክር ቤት፤ የቀድሞው ሙፍቲ የክቡር ሐጂ ዑመር ኢድሪስ የቀብር ስነ-ስርዓት ላይ ለመሳተፍና በክቡር የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት፣ በምክትሎቻቸው፣ በበርካታ ዑለማዎችና መሻኢኾች እንዲሁም በሀገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ የእስልምና ልሂቃን ታጅቦ በአን-ኑር መስጂድ የተከናወነውን የጀናዛ ሰላት ለመስገድ ተገኝቷል።

በመቀጠልም፣ በኃላፊነት በተሰጣቸው አካላት በሚሊኒየም አዳራሽ በተዘጋጀው የሽኝት ሥነ-ሥርዓት ላይ በመገኘት ወደ መጨረሻ ማረፊያቸው ሸኝተናል።

በዚሁ አጋጣሚ ልናጤነው የሚገባው ነገር ቢኖር፣ በኑዛዜያቸው መሰረት ከሙስሊሞች መቃብር ውጪ በቤታቸው አጠገብ እንዲቀበሩ የተወሰነው ውሳኔ በሀገራችን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ክስተት መሆኑን ነው።
እኛም የተውሒድን ገጽታ ለመጠበቅ ስንል ይህንን ድርጊት አጥብቀን እንቃወማለን።

ድርጊቱ ለቀጣይ ትውልዶች ከጊዜ ሂደት በኋላ ወደ ሺርክና ወደ ቀብር አምልኮ የሚያመራ ሰበብ እና መንገድ እንዳይሆን እንሰጋለን። የዑለማእምክር ቤቱ ይህ ውሳኔ ሲወሰንና ተግባራዊ ሲደረግ ምንም አይነት ቅድመ-መረጃ እንዳልነበረው ሊታወቅ ይገባል።

በጉዳዩ ዙሪያ የጠቅላይ ምክር ቤቱን ክቡር ፕሬዝዳንት አነጋግረን የነበረ ሲሆን፣ ኑዛዜው እንዲሻርና ቀብሩ በሙስሊሞች መቃብር እንዲፈጸም ለማድረግ ከሸይኹ ቤተሰቦችና ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር ሙከራ እንዳደረጉ ነገር ግን እንዳልተሳካላቸው ገልጸውልናል።

በመሆኑም፣ ምክር ቤቱ ከሸሪዓህ መንፈስ ጋር የሚጋጩ እንዲህ አይነት ተግባራትን በብርቱ የሚቃወምና የሚያወግዝ መሆኑን ይገልጻል።

በተጨማሪም፣ ሁሉም ዑለማዎች የተውሒድን ክብር ለመጠበቅና ከሺርክ ለማስጠንቀቅ፣ በማህበረሰቡ ውስጥ መሰል ጉዳዮች ላይ ትክክለኛውን የሸሪዓህ ግንዛቤ እንዲያሰርጹና ግንዛቤ እንዲፈጥሩ አደራ ይላል።

ሸይኽ ዶ/ር ዐሊ ሙሐመድ
የኢትዮጵያ ዑለማእ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት

(ዘ-ሐበሻ ዜና ዳሰሳ) እ.ኤ.አ. በ1993 የተካሄደው የኤርትራ የነጻነት ሪፈረንደም፣ ህጋዊ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ሂደት ሳይሆን፣ ግብፅ ኢትዮጵያን ለማዳከም እና ወደብ አልባ ለማድረ...
15/10/2025

(ዘ-ሐበሻ ዜና ዳሰሳ) እ.ኤ.አ. በ1993 የተካሄደው የኤርትራ የነጻነት ሪፈረንደም፣ ህጋዊ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ሂደት ሳይሆን፣ ግብፅ ኢትዮጵያን ለማዳከም እና ወደብ አልባ ለማድረግ ለረጅም ጊዜ ስትከተለው የነበረው ስትራቴጂ ውጤት እንደነበር የሆርን ሪቪው ትንታኔ አመለከተ። ትንታኔው፣ በወቅቱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ የነበሩት ግብፃዊው ቡጥሮስ ቡጥሮስ ጋሊ፣ የሀገራቸውን ስትራቴጂካዊ ግብ ለማሳካት ሂደቱን በማመቻቸት ቁልፍ ሚና እንደተጫወቱ ይከራከራል።

ትንታኔው እንደሚለው፣ የቡጥሮስ ቡጥሮስ ጋሊ ሙሉ የዲፕሎማቲክ ህይወት ከግብፅ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ጋር የተቆራኘ ነበር። ዋና አላማቸውም የግብፅን የአባይ ወንዝ የበላይነት ማስጠበቅ፣ የቀይ ባህር ተጽዕኖን ማስፋት እና ኢትዮጵያን ማዳከም እንደነበር ይገልጻል። ጋሊ የተመድ ዋና ጸሐፊ ሆነው የተሾሙት፣ የግብፅ ተኪ ኃይሎች እንደሆኑ የተገለጹት ህወሓትና ሻዕቢያ አዲስ አበባ ላይ ስልጣን በያዙ በአመቱ መሆኑ፣ የካይሮን አጀንዳ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስፈጸም እንዳስቻላቸው ትንታኔው ያብራራል።

በተጨማሪም ትንታኔው ግብፅ ከ1950ዎቹ ጀምሮ የኤርትራን ተገንጣይ ቡድኖች (ጀብሃ እና ሻዕቢያ) በካይሮ ውስጥ በማደራጀት፣ የገንዘብ እና የሚዲያ ድጋፍ ስትሰጥ መቆየቷን ይጠቅሳል። ህወሓትም የተመሰረተው በግብፅ ድጋፍ እንደሆነ የሚከራከረው ጽሑፉ፣ የኤርትራን ነጻነት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ መቀበል ለህወሓት ምስረታ ከግብፅ የስለላ ተቋም የተቀመጠ ቅድመ ሁኔታ እንደነበር ይገልጻል።

በጥር 1993 ቡጥሮስ ጋሊ አዲስ አበባን በጎበኙበት ወቅት፣ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ሪፈረንደሙን በመቃወም ሰልፍ መውጣታቸውን ትንታኔው ያስታውሳል። ሰልፉ በኃይል የተበተነ ሲሆን፣ ጋሊ ለተፈጠረው ደም መፋሰስ ትኩረት ሳይሰጡ በማግስቱ ወደ አስመራ በማምራት ከሻዕቢያ ባለስልጣናት ጋር መገናኘታቸው፣ ለነጻነቱ ሂደት የነበራቸውን ድጋፍ ያሳየ ድርጊት ነበር ተብሏል።

ትንታኔው፣ በትጥቅ ትግል ስልጣን የያዘ የሽግግር መንግስት በዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ፊት ሪፈረንደም እንዲያካሂድ መፈቀዱ በተመድ ታሪክ ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ "ልዩ" ክስተት እንደነበር ይገልጻል። በወቅቱ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) ሊቀመንበርነት ከሰኔ 1993 ጀምሮ በግብፁ ፕሬዝዳንት ሆስኒ ሙባረክ እጅ መግባትም፣ ካይሮ በአፍሪካ ተቋማት ላይ የነበራትን ተጽዕኖ ያሳያል ሲል ይከራከራል።

የሆርን ሪቪው ትንታኔ በማጠቃለያው፣ የ1993ቱ የኤርትራ ሪፈረንደም የግብፅን ጥቅም ለማስጠበቅ እና ኢትዮጵያን ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ ለማዳከም የተቀነባበረ በመሆኑ፣ ሂደቱ ዓለም አቀፍ ህግጋትን የጣሰ ነበር ይላል። በቡጥሮስ ጋሊ የተመራው የተመድ ሚናም የሂደቱን ገለልተኝነት ጥያቄ ውስጥ እንደከተተው ይገልጻል።

በዚህም ምክንያት፣ ትንታኔው ኢትዮጵያ የሪፈረንደሙን ህጋዊነትና ውጤቱን ላለመቀበል "የሞራል፣ የታሪክ፣ የህግ እና የዲፕሎማሲያዊ መሰረት" እንዳላት በመግለጽ ይቋጫል።

አሳዛኝ ዜና በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን በጨፋ ሮቢት ከተማ ልዩ ስሙ ጃራ ድልድይ አከባቢ  ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኢት 73290 የሆነ ታታ ባስ እና ከደ...
12/10/2025

አሳዛኝ ዜና
በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን በጨፋ ሮቢት ከተማ ልዩ ስሙ ጃራ ድልድይ አከባቢ ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኢት 73290 የሆነ ታታ ባስ እና ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኢት 41157 ተሳቢ መኪና ተጋጭተው በደረሰ ዘግናኝ የትራፊክ አደጋ ለግዜው ቁጥሩ ያልታወቀ የበርካታ ሰዎች ህይዎት አልፏል በርካቶች የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በጨፋ ሮቢት ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል ።

እባካችሁ ሹፌሮች ህግና ደንብ አክብራችሁ በማሽከርከር የራሳችሁን እና የመንገደኞችን ህይዎት ጠብቁ ። 😭😭

©️Moha Wollo

ዘመን ተሻጋሪው

መንግስት በገለፀው መሰረት ከመስከረም ወር ጀምሮ አዲሱ የደሞዝ ጭማሪ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገለፀ+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++አዲስ አበባ መስከረም 2...
03/10/2025

መንግስት በገለፀው መሰረት ከመስከረም ወር ጀምሮ አዲሱ የደሞዝ ጭማሪ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገለፀ
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
አዲስ አበባ መስከረም 23 ቀን 2018 ዓ.ም የፊዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ለሁሉም ክልሎችና ለሁለቱ ከተማ መስተዳድሮች የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊዎች እና ለሚመለከታቸው አካላት በአዲሱ የመግስት ሰራተኞች በደሞዝ ጭማሪና በአበል ክፍያ ላይ መመሪያ አስተላልፈዋል።

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲ ትግበራ የሚያፋጥን የደሞዝና የአበል ማስተካከያ የተደረገው መንግስት የመክፈል አቅም ኖሮት ሳይሆን የመንግስት ሰራተኛውን የኑሮ ጫና ስለሚያውቅ ትልቅ ዋጋ ተከፍሎ ይህ ጭማሪ እንደተደረገ ኮሚሽኑ ተናግረዋል።

መንግስት ከሌለው ላይ የዚህን ያህል ደሞዝ የጨመረው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ገልፀዋል።

ሰራተኛው ይህን ተረድቶ ህዝቡን በቅንነት በታማኝነት ማገልገል አለበት ወደ ሥራ መግባት ይኖርበታል ሥራውን በአግባቡ ተገልጋዩን ሳያጉላላ ሥራውን መከወን አምራች ሀይል መሆን እንደሚገባው አሳስበዋል።

ደሞዙ ከመስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይከፈላል ክልሎች ምንአልባት አንዳንድ አካባቢዎች በዚህ ወር ካልደረሰ ያለውን ማንኛውንም ጫና ተቋቁማችሁ ለሰራተኛው ከዚህ ወር ጀምሮ አዲሱን የመግስት ሰራተኞች ደሞዝ መክፈል እንዳለባቸው ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰተዋል።

civil service commission

ልዩ ዜና ‼️ኢትዮጵያ ከኤርትራ የሃገርነት እዉቅና ልታነሳ ነዉ ‼️ *********************የአለማቀፍ ህጉ የሻዕቢያ መንግስት አሁን እያራመደ የሚገኘውን ከአለማቀፍ የሉዐላዊነት ፍላ...
02/10/2025

ልዩ ዜና ‼️
ኢትዮጵያ ከኤርትራ የሃገርነት እዉቅና ልታነሳ ነዉ ‼️
*********************
የአለማቀፍ ህጉ የሻዕቢያ መንግስት አሁን እያራመደ የሚገኘውን ከአለማቀፍ የሉዐላዊነት ፍላጎቶች ጋር የማይጣጣም አቋም እና ያለበት አጠቃላይ ግዛታዊ ውድቀትን ተከትሎ ኢትዮጵያ ‚ Mother State’s Permission ‛ በሚለው አለማቀፍ ህግ መሰረት በፈረንጆች በ 1993 ለኤርትራ መገንጠል የሰጠችውን እውቅና እንደገና እንድትመረምር የሚፈቅድ መሆኑና ህጉ ኢትዮጵያ ውሳኔዋን መሻር ከፈለገች እውቅናውን በዘላቂነት ማስቀጠል ይገባሻል በሚል ኢትዮጵያን የማያስገድድ ጭምርም እንደሆነ እየተነገረ ይገኛል ።
ኤርትራ አሰብን በሰላማዊ መንገድ የማትሰጥ ከሆነ የሃገርነት እዉቅና ተነጥቃ የኢትዮጵያ ግዛት መሆኗ የማይቀር ነዉ።

26/09/2025
ሰበር ዜና‼️"ለድርድር ዝግጁ ነኝ" ኤርትራ ➖➖➖➖➖ኤርትራ በቀይ ባህር ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ለመወያየት ዝግጁ መሆኑዋን ገለፀች ።የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዑስማን ሳሊህ ከፕሬዝዳንት...
26/09/2025

ሰበር ዜና‼️
"ለድርድር ዝግጁ ነኝ" ኤርትራ
➖➖➖➖➖

ኤርትራ በቀይ ባህር ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ለመወያየት ዝግጁ መሆኑዋን ገለፀች ።
የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዑስማን ሳሊህ ከፕሬዝዳንት ትራምፕ የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ጋር ባደረጉት ውይይት ኤርትራ በዓሰብ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ለመደራደር ዝግጁ መሆኗ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ "የመደመር መንግስት" በሚል የፃፉትን መፅሐፍ ባስመረቀበት መድረክ "ኢትዮጵያ ለዘላለም የጆኦግራፊ እስረኛ ሆና መቀጠል አትችል። ይሄ የማይቀር ጉዳይ መሆኑን ተገንዝበው ወንድ እና እህቶቻችን በአጠረ ጊዜ ለድርድር ዝግጁ መሆን አለባቸው" በማለት ጥሪ ማድረጋቸው ይታወሳል።

Address

Step
Injibara
ZION

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jano-Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Jano-Media:

Share