Jano-Media

Jano-Media ጠልተን የምንተወው ወይም ወደን የምንቀበለው እውነት የለም፤ እውነት የምርጫ ጉዳይ አይደለም

እውነት "ያው" እውነት ነው💚💛❤️

የወለደችውን የሶስት ቀን ህጻን  አባቱን ባለማወቋ  ከነህይወቱ የአፈር ማዳበሪያ ኮምፖስት ውስጥ ከታ የገደለችው እናት በእስራት ተቀጣች በምዕራብ ወለጋ ዞን አንድ አነስተኛ ቀበሌ ውስጥ  ያደ...
01/09/2025

የወለደችውን የሶስት ቀን ህጻን አባቱን ባለማወቋ ከነህይወቱ የአፈር ማዳበሪያ ኮምፖስት ውስጥ ከታ የገደለችው እናት በእስራት ተቀጣች

በምዕራብ ወለጋ ዞን አንድ አነስተኛ ቀበሌ ውስጥ ያደገችው ጠጂቱ ካሳ ወደ ጊቢ ከተማ በመምጣት በሰራተኝነት ተቀጥራ የተለያዩ ግለሰቦች ቤት ሰርታለች።በዚህም የብዙ ሰዎችን አመልና ጓዳ በደንብ ማወቅ ችላለች።
ግለሰቧ በመጨረሻ በመስተግዶ ስራ የተቀጠረችው ጊንቢ ከተማ ታዋቂ ሆቴል ሲሆን ከወጣቶች ጋር የመተዋወቅ እድል አግኝታለች።ከተዋወቀቻቸው ወጣቶች መካከል ከአንድ ሁለቱ ጋር የፍቅር ግኑኝነት መስርታለች። በዚህም ሂደት ላይ እያለች ለእርግዝና መጋለጧ የምዕራብ ወለጋ ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የኮሙኒኬሽን ክፍል ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ቹቹ ኢቱ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

እርግዝናው በፈጠረባት ተጽእኖ ስራ ለማቆም የተገደደች ሲሆን የተጸነሰው ልጅ አባት አለማወቋ ደግሞ የስሜት ውዝግብ ውስጥ ከቷታል።ይህ በእንዲ እንዳለ አብራቸው ከቆየቻቸው ወንዶች መካከል የእርግዝናዋን ሁኔታ ስትነግራቸው አንዱም የእርጎዝናውን ውጤት ተቀብሎ አባት ነኝ የሚል ያጣች በመሆኑ ጓደኞቿ ጋር ተጠግታ ወንድ ልጅ ትገላገላለች።

ከሶስት ቀን ቧኋላ ከአራስ ቤት ተነስታ ሀምሌ 22ቀን 2017 ዓ.ም ሰባት ሰዓት ላይ ለአፈር ማዳበርያ የተዘጋጀ ኮምፖስት ውስት አባቱን ያላወቀችውን ጨቅላ ልጅ ከነህይወቱ ከታው መመለሷ ተገልጿል ።ከአራት ቀን በኋላ ደግሞ የምትቀብርበትን ቦታ አዘጋጅታ ከማዳበሪያው ኮምፖስት ውስጥ ስታወጣ የተመለከቱ ነዎሪዎች ወዲያውኑ ለፖሊስ ሪፖርት ያደርጉና በቁጥጥር ስር ያውሏታል።

ፖሊስም ወዲያው ምርመራውን በበቂ ማስረጃና የአስክሬን ምርመራ አጠናክሮ ለአቃቢ ህግ የላከ ሲሆን አቃቢ ህግም ከፖሊስ የቀረበውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በወንጀል ሕግ ቁጥር 544 ህፃንን መግደል ወንጀል ክስ ይመሰርታል።በዓቃቢ ህግ የተመሰረተውን ክስ የተከታተለው የምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጠጂቱ ካሳ ጥፋተኛ መሆኗ በአቃቢ ህግ ማስረጃ በመረጋገጡ በአስራ ሶስት ዓመት እስራት እንድትቀጣ የወሠነባት መሆኑን የምዕራብ ወለጋ ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የኮሙኒኬሽን ክፍል ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ቹቹ ኢቱ ለብስራት ሬዲዮ ገልጸዋል ።

31/08/2025

የኢትዮጵያ ስም ሊቀየር ነው እና ማን ተብላ ትጠራ 🤔

በኢትዮጵያ ጦርነት እንዲቆምና የሽግግር ጊዜ እንዲመቻች የቀረበ ጥሪበኢትዮጵያ በዘር ላይ የተመሰረተ ያለው ፖለቲካና የሚካሄደው ጦርነት በአስቸኳይ እንዲቆም፣በአሜሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ትብብ...
28/08/2025

በኢትዮጵያ ጦርነት እንዲቆምና የሽግግር ጊዜ እንዲመቻች የቀረበ ጥሪ
በኢትዮጵያ በዘር ላይ የተመሰረተ ያለው ፖለቲካና የሚካሄደው ጦርነት በአስቸኳይ እንዲቆም፣በአሜሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ትብብር ንቅናቄ ጥሪ አቀረበ። የንቅናቅው ሊቀመንበር ዶክተር ባደገ ቢሻው ለዶቼ ቬለ እንዳሉት፣በሀገሪቱ ሁኔታዎች እየተረጋጉ ሲሄዱም ፍትህና ዲሞክራሲ የሚሰፍንበት የሽግግር ሂደት መፈጠር አለበት።

በኢትዮጵያ በዘር ላይ የተመሰረተ ያለው ፖለቲካና የሚካሄደው ጦርነት በአስቸኳይ እንዲቆም፣በአሜሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ትብብር ንቅናቄ ጥሪ አቀረበ። የንቅናቅው ሊቀመንበር ዶክተር...

25/08/2025

“የደመወዝ ማሻሻያ ይደረጋል” መባሉና የፈጠረው የዋጋ ጭማሪ
ዓለምነው መኮንን
አዲስ የመንግሥት ሠራተኛ የደመውዝ ጭማሪ ይደረጋል በሚል የአንዳንድ ሸቀጦች ዋጋ መጨመሩን የአማራ ክልል ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በበኩሉ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ አካላት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ አመልክቷል፡፡ የደመውዝ ጭማሪ ሊደረግ ነው” በሚል አንዳንድ ነጋዴዎች የዋጋ ጭማሪ እያደረጉ ነዉም ተብሏል።

የአፍሪካ ሀገራት የመንግስት ተቀጣሪዎች አማካይ ደመውዝ ንጽጽር።**********************************Countries    Salary (USD)   Salary(ETB)1 South...
25/08/2025

የአፍሪካ ሀገራት የመንግስት ተቀጣሪዎች አማካይ ደመውዝ ንጽጽር።
**********************************
Countries Salary (USD) Salary(ETB)

1 South Africa 3,400$ 421,600 birr

2 Moroco 3,300$ 409,200 birr

3 Botswana 3,000$ 372,000 birr

4 Kenya 3,000$ 372,000 birr

5 Namibia 2,700 334,800 birr

6 Seychelles 2,600$ 322,400 birr

7 Libya 2,100 260,400 birr

8 Ethipia 85$ 10,540 birr

ሼር
ሼር

Digital Hakim

25/08/2025

"ከድንገተኛ ሞት የምታድን ቅዱስ ገብርኤል ሆይ በመዓልትም በሌሊትም ተስፋ ስለምናደርግ ጥበቃህ አይለየን!
መልካም ቀን
አሜን !

ሻብያ አዲስ ምሽግ ቁፋሮየኤርትራ ጦር በቡሬ የኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ አዲስ ምሽግ ስራ እያከናወነ መሆኑን የሳተላይት ምስሎች አመልክተዋል። በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ድንበር አዋሳኝ ላይ በም...
22/08/2025

ሻብያ አዲስ ምሽግ ቁፋሮ

የኤርትራ ጦር በቡሬ የኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ አዲስ ምሽግ ስራ እያከናወነ መሆኑን የሳተላይት ምስሎች አመልክተዋል።

በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ድንበር አዋሳኝ ላይ በምትገኘው ቡሬ ግንባር የኤርትራ ጦር እያዘጋጀ ያለው ምሽግ በምስል ከላይ ተያይዟል።

የኤርትራ ጦር ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ተጠግቶ ምሽግ ቁፋሮ ላይ መሠማራቱ ቀጣዩ ጊዜ ምን ይዞ እንደሚመጣ አሳሳቢ ሆኗል።

የቡሬ ድንበር በቀደመው የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ከባድ ውጊያ የተካሄደበት አካባቢ ነው።

😭
20/08/2025

😭

18/08/2025
ፈጣሪ ይመስገን  ተርፌያለሁ 🙏🙏ከባህር መስጠም አደጋ በተዓምር የተረፈው ወጣት !ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ተነስተው የስደት ኑሮው ለመጀመር ያሰበው ወንድም ተካለኝ በየመን ከ150 ...
05/08/2025

ፈጣሪ ይመስገን ተርፌያለሁ 🙏🙏

ከባህር መስጠም አደጋ በተዓምር የተረፈው ወጣት !

ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ተነስተው የስደት ኑሮው ለመጀመር ያሰበው ወንድም ተካለኝ በየመን ከ150 በላይ ኢትዮጵያዊያንን አሳፍራ ጉዞ ላይ እያለች የመሰመጥ አደጋ ከደረሰበት መርከብ በሕይወት ከተረፉት መካካል አንዱ መሆኑን እና በፈጣሪ እርዳታ መትረፉን በራሱ የፌስቡክ ገፅ ያጋራው መልክት ያመለክታል።

ፈጣሪ እንኳን አተረፈህ

via:- አረ የመማይ ልጅ

Address

Step
Injibara
ZION

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jano-Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Jano-Media:

Share