Agew AWI Times

Agew AWI  Times Agaw Awi is relatively flat and fertile, whose elevations vary from 1,800 to 3,100 m above sea level, with an average altitude of about 2,300 m.

water features include two crater lakes, Zengena and Tirba, one of the most productive in the Amhara Region. AWI ZONE IS one of the most richest in fertile soil better for living things ! have lots of natural,cultural and historical places including the most descent peoples ......Ethiopian history tells us about each and everything .like this Agew Awi (Amharic: አገው አዊ) is one of 10 Zones in the Am

hara Region of Ethiopia. Agew Awi is named for the Awi sub-group of the Agaw people, some of whom live in this Zone. Agew Awi is bordered on the west by Benishangul-Gumuz Region, on the north by Semien Gondar Zone and on the east by Mirab Gojjam. The administrative centre of Agew Awi is Injibara; other towns include Chagni, and Dangila,Tilili,Addiskidam,Gimjabet,Azena,Jawi,etc

01/06/2026

ሁሉም ካድሬዎችና የካድሬ ቤተሰቦች ከዋዜማው ጀምረው በሁሉም ምርጫ ጣቢያ ታጅበው እየተዟዟሩ ኮረጁውን መልተውታል::

01/06/2026

የዘድሮውን ምርጫ ለዬት የሚያደርገው...ብለው ሊያዝጉን ነው ደግሞ በቃ አንደኛው እና ዋነኛው የምርጫው ውጤት ከምርጫው በፊት መታወቁና ለMock election ምስኪኑን በሚሊሻ እያስገደዱ ማስወጣቱ በመጨረሻም ያለማንም ከልካይ ያለምንም ገደብ በግል ምርጫ ጣቢያዎች ኮርጆዎች መጠቅጠቃቸው ነው::

በመጨረሻም በቅርብ ቀን የመረጣችሁትን ለማገልገል እስከወዲያኛው ....

13/05/2026

ሁሌም የማይገባኝ የፖሊስ ስራ ህግን ማስከበር ወይስ ህግን መጣስ የእውነት ካልተደባደቡና አካል ካላጎደሉ ይገመገማሉ እንዴ???

እባካችሁ እንደሰው አስቡ???

ልብሱን ብለው እንጅ ልብሱን ብታወልቁት ኖሮ

12/05/2026

ይድረስ ለኢቢኤስ (EBS) ቴሌቪዥ

ኢቢኤስ በሀገራችን የሚዲያ ኢንዱስትሪ ውስጥ ትልቅ ስም ያለው ተቋም እንደመሆኑ የጥበብ ሰዎችን ልዩ ተሰጥኦ የማክበር ግዴታ አለበት።

ወንድማችን ነፃነት ወርቅነህ በራሱ ልዩ ቀለምና ተፈጥሯዊ ብቃት የብዙዎችን ልብ የገዛ ድንቅ ሰው ነበር ነፍሱን ይማረውና የእሱ የሥራ አሻራ የራሱ የነፃነት ብቻ ሆኖ ሊኖር ይገባል...

ይሁን እንጂ አሁን ላይ ተቋሙ ነፃነትን ለመተካት በመልክ በቁመትና በአነጋገር እሱን የሚመስል ሰው ፍለጋ ማለቱ የጥበብን ምንነትና የአንድን ሰው ግላዊ ተሰጥኦ ካለመረዳት የሚመጣ ትልቅ ስህተት እየመሰለኝ ነው...

ጥበብ ልክ እንደ ሎሬት ፀጋዬ ግጥሞች ወይም እንደ ስብሃት ገብረእግዚአብሔር ድርሰቶች የማይደገም የግል ማንነት አለው።

የነፃነትንም ስራና አቀራረብ ፎቶ ኮፒ በማድረግ መተካት አይቻልም የሰውን ልጅ አምሳያ መፈለግም ለሟቹ ክብር አይሰጥም ለሚመጣውም አዲስ ተሰጥኦ ዕድል ይነፍጋል።

ህዝቡ ልክ እንደ ነፂ የሚሰራ ሰው ወይም በመልክ የሚመሳሰል ሰው ስያይ የሚሰጠው ግብረ መልስ ለነፃነት ካለው ፍቅር እና ከናፍቆት የመነጨ ስሜት እንጂ የጥበብ ሰውን በሌላ ሰው መተካት እንደሚቻል ማረጋገጫ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባም።

ስለዚህ የEBS የሥራ ኃላፊዎች ፍለጋችሁን ከመልክና ከቁመት ወደ ችሎታና ወደ አዲስ ዕይታ እንድታዞሩ መልዕክቴ ነው።

ለቦታው የሚመጣው አዲስ ሰው በራሱ ማንነትና ልዩ ተሰጥኦ ታሪክ እንዲሰራ እድል ሊሰጠው ይገባል እኛም ማየት የምንፈልገው የነፃነትን ጥላ ሳይሆን እንደ ነፃነት ሁሉ በራሱ ብቃት ወደፊት የምናስታውሰውን አዲስ ብርሃን ነው።

ነፃነትን በስራዎቹ እናከብረዋለን ተቋሙ ግን በራሱ መንገድ የሚመጣ አዲስ ጎበዝ ሰው በመፈለግ ሙያዊነቱን ሊያሳይ ይገባል።
ካልሆነ ግን ለነፃነት ሲባል ፕሮግራሙ በሌላ ፕሮግራም ይተካ ወይም ይዘጋ::
EBS
Friends
Facebook
Ethiopian Broadcasting Corporation

In logic if the mother is not born how can the son will be…ፀሐይን የወለደችው እውነተኛይቱ ሰማይ ድንግል ማርያም ልደታለማርያም ብለን እናባለን::ልደቷ ልደታ...
10/05/2026

In logic if the mother is not born how can the son will be…
ፀሐይን የወለደችው እውነተኛይቱ ሰማይ ድንግል ማርያም ልደታለማርያም ብለን እናባለን::

ልደቷ ልደታችን ነው::

''የሰው ልጅ ህይወት፣ ያውም የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ኃላፊነት በተሰጠው የፀጥታ አካል እጅ ሲቀጠፍ ከማየት በላይ ልብ የሚሰብር ክስተት የለም። በአዲስ አበባ ከተማ የተፈፀመውን አንጀትን...
09/05/2026

''የሰው ልጅ ህይወት፣ ያውም የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ኃላፊነት በተሰጠው የፀጥታ አካል እጅ ሲቀጠፍ ከማየት በላይ ልብ የሚሰብር ክስተት የለም።

በአዲስ አበባ ከተማ የተፈፀመውን አንጀትን የሚበላ የአንድ ዜጋ ግድያ ተከትሎ፣ የከተማው ፖሊስ ተቋም ድርጊቱን በፅኑ ሲያወግዝ፤ "ዲሽታጊና" በሚለው ተወዳጅ ስራው የሚታወቀው ድምፃዊ ታሪኩ ጋንኪሲ ደግሞ ጥላቻን እና ፍርሃትን የሚያወግዝ ጥልቅ የልብ ጩኸቱን አሰምቷል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት፣ ይህ አሳዛኝ ክስተት የተፈጠረው ሚያዚያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 አካባቢ ነው። በዕለቱ ከቀኑ 10፡40 ላይ፣ ረዳት ሳጅን ማቴዎስ ተመቸው የተባለ የፖሊስ አባል አቶ ተገኝ ባልቻ የተባሉትን ግለሰብ በክላሽንኮቭ ጠመንጃ ተኩሶ ህይወታቸው እንዲያልፍ አድርጓል። ፖሊስ ግድያውን የፈፀመውን አባል ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ ጀምሯል።

ከዚህ ዘግናኝ ድርጊት ጀርባ ያለውን መንስኤ ፖሊስ ሲያብራራ፣ በሟች እና በፖሊስ አባሉ መካከል ከዚህ ቀደም የተፈጠረ ቂም እንደነበር ጠቁሟል። ከዚህ በፊት በተፈጠረ ጠብ አቶ ተገኝ በፖሊስ አባሉ ላይ ጉዳት አድርሰው ታስረው በዋስ ወጥተው ነበር። ይሁንና በዕለቱ ሟች በሌላ ወንጀል ተጠርጥረው በፖሊስ ተይዘው ወደ ጣቢያ ሲመጡ፣ ከመኪና ወርደው ወደ ውስጥ አንገባም በማለታቸው በተፈጠረ ግብግብ ይህ አሳዛኝ ግድያ ሊፈፀም ችሏል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ይህንን ድርጊት "ፍፁም ተቀባይነት የሌለው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት" ሲል በፅኑ አውግዞታል። ምንም እንኳን ግለሰቡ ከፖሊስ አባላት ጋር ግርግር መፍጠራቸው ተገቢ ባይሆንም፣ የፖሊስ አባሉ የወሰደው የጭካኔ እርምጃ የፖሊስን ዓላማ የሚፃረር እና ተቋሙን የማይወክል መሆኑን አስረግጦ በመግለፅ፤ ለሟች ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን ተመኝቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የሀገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ እና የሰዎችን ህይወት በከንቱ መጥፋት በቅርበት የሚታዘበው ተወዳጁ ድምፃዊ ታሪኩ ጋንኪሲ (ዲሽታጊና)፣ ሀዘኑን ከመግለፅ ባለፈ ልብን ሰርስሮ የሚገባ የማንቂያ መልዕክት አስተላልፏል። በአሁኑ ወቅት ሰዎችን እርስበርስ እያባላ ያለውን የፍርሃት እና የጥርጣሬ ግድግዳ እንድናፈርስ ጥሪውን አቅርቧል።

"ጎረቤትህ ጠላትህ አይደለም፤ እሱም እንደ አንተ በኑሮ ውድነት የሚቃጠል፣ የሰላም ጥማት ያለው ወንድምህ ነው" በማለት የፃፈው ታሪኩ፣ ችግራችን የዘር ሳይሆን እርስ በእርሳችን እንድንፈራራ የሚያደርገን የፍርሀት ግድግዳ መሆኑን አስምሮበታል። አክሎም "እኛ ስንተማመን ጭቆና በራሱ ይፈርሳል፤ እጅ ለእጅ እንያያዝ፤ ያኔ ፍርሀት ቦታ አይኖረውም" ሲል ጽፏል።

የፖሊስ ጥብቅ የምርመራ ቃል እና የድምፃዊው የመተማመን ጥሪ በአንድ ላይ ሲታዩ፣ እንደ ማህበረሰብ ከጥላቻ እና ከበቀል አዙሪት ወጥተን "የነገውን የመተማመን ቤት አብረን እንገንባ" የሚለውን ጥልቅ መልዕክት የሚያስተጋቡ ናቸው። የሰው ልጅ ህይወት ክቡር ነው፤ ፍትህ ለሟች ቤተሰቦች እንዲሰጥና መሰል አሳዛኝ ድርጊቶች ዳግም እንዳይከሰቱ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል።

ዘ-ሐበሻ

01/05/2026

Ethiopia 🇪🇹 ||ኢትዮጵያ

ህጋዊ ህግወጦች ተራ የሰፈር ዱርዬዎች ከመንግስት እስከ ባለሀብት ትስስር ያለበት ሰንሰለት ይህ ሁሉ ተደምሮ የመንግስት ሰራተኛውን ሰርቶ አደር ምስኪኑን ሰፊውን ህዝብ እያሰቃዬው ይገኛል::

በዚህ ከቀጠለ ኢትዮጵያ የድሆች ሲኦል የመንግስት ሰራተኞች ገሀነብ ትሆናለች:ሆናለችም::

መ ል ካም የሰርቶ አደሮች ...

What kind of k..s this African??
01/05/2026

What kind of k..s this African??

24/04/2026

Address

Injibara

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Agew AWI Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share