08/08/2026
#ትዝብት ዘእንጅባራ
| እንጅባራ ከተማ በአማራ ክልል ከሚገኙ ከተሞች በሰላሟ፣ በአየር ፀባያዋ፣ በአቀማመጧ እና በእንግዳ ተቀባይነቷ ተወዳጅና ተመራጭ እየሆነች የመጣች ውብ ከተማ ነች።
በመንግሥት እቅድ እና በማህበረሰቡ ተነሳሽነት በተከናወነው የኮሪደር ልማት ሥራ (ከአንድ ኪሎ ሜትር በታች በሆነው) ከተማዋ አዲስ እና ውብ ገጽታን እየተጎናጸፈች ትገኛለች፤ ቀጣይነትም ይኖርዋል በሚል ተስፋ።
የኮሪደር ልማቶች መሠረታዊ ከሆኑት አካላት መካከል ደግሞ አካባቢውን በሌሊት የሚያደምቁ እና ለዕይታ ውብ የሚያደርጉ የመንገድና የህንፃ መብራቶች መሆናቸው ሌሎች ከተሞች ማሳያ ናቸው። ዳሩ ግን፦
"ፅድቁ ቀርቶ በቅጡ..." ሆነብን!
ልማቱ እጅግ የሚመሰገን እና ማህበረሰቡን ያኮራ ቢሆንም፣ በሂደቱ ውስጥ መስተካከል የሚገባቸው ክፍተቶች መኖራቸው አልቀረም።
የሀሳቤ ቁንጮ መነሻ፣ የኮሪደሩ አካል ባይሆንም ከአደባባዩ ወደ ቻግኒ መውጫ ያለው መንታ መንገድ አካፋይ መሀል የተተከሉት የመንገድ መብራቶች ቀንድ ይመስል ተወድረው መብራት ግን ናፍቋቸዋል! እናም አፋጣኝ ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል።
የእንጅባራ ከተማ ከዕለት ወደ ዕለት እያደገች ስትመጣ መሠረተ ልማቶቿም በተመሳሳይ ፍጥነት የተሟሉ ሊሆኑ ይገባል። በመሆኑም የሚመለከተው አካል ይህንን ሕዝብ ያሳተፈ የልማት ሥራ ተንከባክቦ ለመያዝ እና የከተማዋን ውበትና ጸጥታ ሙሉ ለማድረግ፣ የተተከሉትን የመብራት መሶቦች ከባዶ (ከፓውዛ) ተሸካሚነት ወደ አብሪነት እንዲቀየሩ ዘንድ ጥረት ሊያደርግ ይገባል!
#እንጅባራ #የኮሪደርልማት #ልማት #ማህበረሰብ #ከተማችን